es
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Ir al canal en Telegram

EEP Communication

Mostrar más

📈 Análisis del canal de Telegram EEP Communication

El canal EEP Communication (@eepcommuication) en el segmento lingüístico de Amárico es un actor destacado. Actualmente la comunidad reúne a 15 537 suscriptores, ocupando la posición 8 326 en la categoría Tecnologías y Aplicaciones y el puesto 2 176 en la región Etiopía.

📊 Métricas de audiencia y dinámica

Desde su creación el невідомо, el proyecto ha mostrado un crecimiento acelerado, reuniendo a 15 537 suscriptores.

Según los últimos datos del 04 julio, 2026, el canal mantiene una actividad estable. En los últimos 30 días la variación de miembros fue de 26, y en las últimas 24 horas de -7, conservando un alto alcance.

  • Estado de verificación: No verificado
  • Tasa de interacción (ER): El promedio de interacción de la audiencia es 26.64%. Durante las primeras 24 horas tras publicar, el contenido suele obtener 15.41% de reacciones respecto al total de suscriptores.
  • Alcance de las publicaciones: Cada publicación recibe en promedio 4 139 visualizaciones. En el primer día suele acumular 2 395 visualizaciones.
  • Reacciones e interacción: La audiencia responde de forma activa: el promedio de reacciones por publicación es 9.

📝 Descripción y política de contenido

El autor describe el recurso como un espacio para expresar opiniones subjetivas:
EEP Communication

Gracias a la alta frecuencia de actualizaciones (últimos datos recibidos el 05 julio, 2026), el canal mantiene la vigencia y un amplio alcance. La analítica demuestra que la audiencia interactúa activamente con el contenido, lo que lo convierte en un punto de referencia dentro de la categoría Tecnologías y Aplicaciones.

15 537
Suscriptores
-724 horas
-77 días
+2630 días
Archivo de publicaciones

የሥራ ዘርፉ የመጀመሪያውን የሩብ በጀት ዓመት ግምገማ አካሄደ ..….//…… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ትራንስሚሽን ሰብስቴሽን ኦፕሬሽን የሥራ ዘርፍ የ2014 በጀት ዓመት የአንደኛ ሩብ ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማው ውይይት ላለፉት ሁለት ቀናት በአዋሳ ከተማ አካሄደ፡፡ የሥራ ዘርፉን የውጤት ተኮር የሥራ አፈጻጸም ምዘና ስርዓት ትግበራን በተቀናጀ እና በተናበበ መልኩ ለመተግበር ከሪጅን ዳይሬክተሮች እና ከዘርፉ የሥራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን የዘርፍን የቁልፍ አፈጻጸም መለኪያ (KPI) ዕቅድ በጋራ መግባባት ላይ ለመድረስ እንደሆነ የትራንስሚሽን ሰብስቴሽን ኦፕሬሽን ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሐብታሙ ውቤ በውይይቱ ላይ ገልፀዋል፡፡ በሩብ ዓመቱም የKPI አፈጻጸም 98.22 በመቶ የደረሰ ሲሆን ከባለፈው ተመሳሳይ የሩብ በጀት ዓመት ከተመዘገበው የ14.02 በመቶ ብልጫ እንዳለው ተነግሯል፡፡ የግምገማው ዋና ዓላማም በውጤት ተኮር የKPI ምዝና ትግበራ ወቅት የታዩ ጠንካራ ጎኖችን ይበልጥ ለማጠናከር፣ የታዩ ክፍተቶችን በቀጣይ እንዲታረሙ አቅጣጫ የማስቀመጥ፣ የልምድ ልውውጥ እና መልካም ተሞክሮን የማካፍል፣ የተሸለ አፈጻጸም ያመጣውን ሪጀን እውቅና በመስጠት የውድድር ስርዓቱን ይበልጥ የማጠናከር፣ የእርስ በርስ ግንኙነት እንዲጠናከር ምቹ ሁኔታን መፍጠር እና ማከፍፈያ ጣቢያዎች ላይ የመስክ ምልከታ ጉብኝት ማካሄድ እንደሆነ ተጠቁሟል፡፡ ትላንት በተጠናቀቀው እና ለሁለት ቀናት በቆየው ግምገማዊ ውይይት ሪጂኖቹ በቀረቡት ስድስት የKPI መለኪያ ውጤት አንጻር የታየባቸውን ክፍተቶች በግልጽ በመወያያትና በመገማገም የመፍተሄ አቅጣጫዎችን አስቀምጠዋል፡፡ በቀጣይም ድክመቶቹ ተስተካክለው እንዲመጡ የጋረ መግባባት ላይ ተደርሷል፡፡ በሩብ በጀት ዓመቱ የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገበው የደቡብ ምዕራብ ሪጅን እውቅና ተሰጥቷል፡፡ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 03 ቀን 2014 ዓ.ም Facebook (https://www.facebook.com/Ethioelectric) Log in or sign up to view See posts, photos and more on Facebook.

photo_2021-10-13_15-35-39.jpg0.33 KB

photo_2021-10-13_15-35-35.jpg0.33 KB

photo_2021-10-13_15-35-30.jpg0.32 KB

photo_2021-10-13_15-35-24.jpg0.24 KB

photo_2021-10-13_15-35-16.jpg0.24 KB

photo_2021-10-13_15-34-31.jpg0.31 KB

የሱዳን ኤሌክትሪክ ኩባንያ የሥራ ኃላፊዎች አዲስ አበባ ገቡ ..........////.......... በሱዳን ኤሌክትሪክ ኩባንያ (ሱዳን ኤሌክትሪክ ትራንስሚሽን ኮርፖሬሽን) ዋና ሥራ አስፈጻሚ የቴክኒክ አማካሪ የተመራ የልዑካን ቡድን በኢትዮጵያና ሱዳን መካከል በቀጣይ ስለሚኖረው የኃይል ትስስር ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ ኃላፊዎች ጋር ለመደራደር አዲስ አበባ ገብቷል፡፡ በዋና ሥራ አስፈጻሚው የቴክኒክ አማካሪ ሚስተር አህመድ አደም ኡመር የተመራዉና አምስት አባላትን ያካተተው የልዑካን ቡድን ትላንት ምሽት አዲስ አበባ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርስ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የስትራቴጂና ኢንቨስትመንት መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ወንድወሰን ተሾመ አቀባበል ተደርጎለታል፡፡ አቶ ወንድወሰን የልዑካን ቡድኑን በተቀበሉበት ወቅት እንደተናገሩት የልዑካን ቡድኑ አዲስ አበባ የገባው በሁለቱ ሃገራት መካከል የኃይል ትስስሩን ለማጠናከር እየተሰሩ ባሉ ስራዎች ላይ ድርድር ለማድረግ ነው፡፡ ከዚህ በፊት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ ኃላፊዎች በሱዳን ዋና ከተማ ካርቱም በመገኘት ከኩባንያው የሥራ ኃላፊዎች ጋር ድርድር መካሄዱን አስታውሰዋል፡፡ በአዲስ አበባ የሚካሄደው ድርድር ከዚህ በፊት በነበሩ ድርድሮች የተነሱ ጉዳዮች እልባት እንዲያገኙና በቀጣይ ስለሚኖረው የአሰራር ሁኔታ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ነው ብለዋል፡፡ ድርድሩ የሱዳን የኤሌክትሪክ ኩባንያ ከኢትዮጵያ ተጨማሪ 1 ሺህ ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ለመግዛት ባቀረበው ጥያቄ ላይ እንዲሁም ተጨማሪ ኃይል ለማቅረብ መከናወን ባለበት የመስመር ዝርጋታ እና ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታዎች ላይ ትኩረት የሚያደርግ እንደሚሆን ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል፡፡ ድርድሩ ከጥቅምት 1 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ለቀጣዮቹ አምስት ቀናት የሚካሄድ መሆኑን ለማወቅ ተችሏል፡፡ ኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት ለሱዳን 230 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል በመሸጥ ላይ ትገኛለች፡፡ ከሱዳን በተጨማሪም ለጅቡቲ የኤሌክትሪክ ኃይል በመሸጥ ላይ የምትገኝ ሲሆን ለኬንያ የአሌክትሪክ ኃይል ለመሸጥ እቅድ መያዙ ተጠቁሟል። በቀጣይ ከሶማሌ ላንድ፣ ከሶማሊያ፣ ከታንዛኒያ፣ ከኤርትራ፣ ከደቡብ ሱዳን እና ከሌሎች የአፍሪካ ሃገራት ጋር የኤሌክትሪክ ኃይል ትስስር ለመፍጠር የሁለትዮሽ ግንኙነት በማድረግ ላይ የምትገኝ መሆኑን ከዚህ በፊት በተለያየ ጊዜ መዘገባችን ይታወሳል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 01 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content

በተቋሙ የሰንደቅ ዓላማ ቀን ተከበረ -----------------------//////----------------------- የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰንደቅ ዓላማ ቀን በዓልን በዋናው መ/ቤት አክብሯል፡፡ የብሔራዊ ሰንደቅ ዓላማ ቀን በዓል ዘንድሮ ለ14ኛ ጊዜ የሚከበር ሲሆን “በአዲስ ምዕራፍ በተሟላ ሉዓላዊነት ለሰንደቅ ዓላማችን ከፍታ” በሚል መሪ ቃል ዛሬ በመከበር ላይ ይገኛል፡፡ ሰንደቅ ዓላማ የብሔራዊ አንድነት መገለጫ፤ ዜጎች ሀገራዊ ፍቅርና ብሔራዊ ስሜት የሚገልፁበት፤ ታሪካዊ ትስስርና የስነ-ልቦናዊ አንድነት የሚንፀባረቅበት የአንድነትና ህብረት አርማና ምልክት ነው፡፡ የዘንድሮው የሰንደቅ ዓላማ ቀን የውስጥና የውጭ ጠላቶቻችን ብሔራዊ አንድነታችንን እና ሉዓላዊነታችንን እየተፈታተኑ ባሉበት ወቅት መከበሩ ተናበንና ተደራጅተን በተባበረ ክንድ የተጋረጠብንን የህልውና አደጋ ለመመከትና ለመቀልበስ በጋራ በምንቆምበት አጋጣሚ ስለሆነ ልዩ ያደርገዋል፡፡ የሰንደቅ ዓላማ ቀን በዓል በየዓመቱ የጥቅምት ወር መጀመሪያ ሰኞ እንዲከበር መወሰኑ ይታወሳል፡፡ ለብሔራዊ አንድነታችንና ሉአላዊነታችን ያለንን ቁርጠኝነት በሰንደቅ ዓላማችን ፊት ዳግም ቃላችንን እናድሳለን!! ጥቅምት 01 ቀን 2014 ዓ/ም ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et

photo content
+4

የስማርት ሜትር ቆጣሪዎችን በራስ አቅም ለመግጠም ታቅዷል በምዕራብና በሰሜን ሪጅን ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የሚተከሉ የስማርት ሜትር ቆጣሪዎችን በራስ አቅም ለመግጠም እቅድ መያዙን በተቋሙ ትራንስሚሻን ሰብስቴሽን ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት የስማርት ሜትር ፕሮጀክት ቢሮ ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ሃይማኖት ተፈራ አስታወቁ፡፡ በሁሉም ሪጅኖች ከሚገኙ ማከፋፈያ ጣቢያዎች መካከል በ130 ጣቢያዎች ላይ የስማርት ሜትር ቆጣሪ ገጠማ ሥራን ለማከናወን “Siemens Proprietary Limited” ከተሰኘ ኩባንያ ጋር ስምምነት በማድረግ ስራው ሲከናወን እንደነበር ሥራ አሰኪያጇ አስታውሰዋል፡፡ ይሁን እንጅ በሁለቱ ሪጅኖች ላይ ባለው የጸጥታ ችግር ምክንያት ሥራ ተቋራጩ የገጠማ ሥራውን ማከናወን ባለመቻሉ በሪጅኖች የሚተከሉ የቆጣሪ ገጠማ ሥራዎችን በተቋሙ የራስ አቅም ለማከነወን እቅድ ተይዟል ነው ያሉት ኃላፊዋ፡፡ ይህ ሥራ በራስ አቅም እንዲከናወን በተቋሙ ከፍተኛ አመራር በኩል ውሳኔ እንደተሰጠበትም ወ/ሮ ሃይማኖት ተናግረዋል፡፡ እንደ ወ/ሮ ሃይማኖት ገለጻ በሁለቱ ሪጅኖች በሚገኙ 21 ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ 216 የስማርት ሜትር ቆጣሪዎችን ለመግጠም እቅድ ተይዟል፡፡ ለዚህም ስራውን በተገቢው የኮንትራት አስተዳደር መርህ መሰረት ለማከናወን ከስራ ተቋራጩ ለይ በመውሰድ (de-scope በማድረግ) በተቋሙ የራስ አቅም ለመስራት ባለሞያዎችን የማብቃት ስራዎች መከናወናቸውን ተናግረዋል፡፡ ቆጣሪ የመግጠማ ሥራውን ለማከናወን የቅድመ ዝግጅት ስራዎች መጠናቀቃቸውን የጠቆሙት ወ/ሮ ሃይማኖት በአካባቢዎች የሚስተዋለው የጸጥታ ችግር መፍትሄ እንዳገኘ ወደ ስራ እንደሚገባ አስታውቀዋል፡፡ በራስ አቅም ለሚከናወነው ስራም ከ3 ነጥብ 1 ሚሊዮን ብር በላይ እና 43 ሺህ 1 መቶ የአሜሪካ ዶላር ገንዘብ ከውሉ ላይ ተቀናሽ በማድረግ ለዚህ ስራ በጀት መያዝኑ ነው ስራ አስኪያጇ የተናገሩት፡፡ ስራ ተቋራጩ በ109 ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ 9 መቶ 92 የስማርት ሜትር ቆጣሪዎችን መግጠም መቻሉን ወ/ሮ ሃይማኖት ገልፀዋል፡፡ አጠቃላይ የገጠማ ስራውን እስከ ታህሳስ 2013 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅ እቅድ ተይዞ የነበረ ሲሆን የኮሮና ቫይረስ፣ በተለያዩ አካባቢዎች የተስተዋላው የጸጥታ ችግር፣ የሳይቶቸ በመላው ሀገሪቱ ክፍል ተበታትነው መገኘታቸው እንዲሁም በጉምሩክ በኩል አዳዲስ አሰራሮች በየጊዜው መቀያየራቸው በመርሃ ግብሩ መሰረት ላለመከናወኑ በምክንያትነት ተጠቅሰዋል፡፡ የቆጣሪ ገጠማ አጠቃላይ ስራውን (Supply, Installation, Test and Commissioning) ለማከናወን በአለም ባንክ የሚሸፈን ከ25 ነጥብ 28 ሚሊዮን በላይ ብር እና ከ2.17 ሚሊዮን በላይ የአሜሪካ ዶላር በጀት መያዙን ከዚህ በፊት መዘገባችን ይታወሳል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 28 ቀን 2014ዓ.ም

image_2021-10-08_12-12-44.png3.91 KB

ማከፋፈያ ጣቢያው የኦፕሬሽን ስራዬ ላይ ተደጋጋሚ እንቅፋት እየገጠመኝ ነው አለ ………/////……… ከደብረ ማርቆስ ባለ 400 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ወጪ የሆኑት የ33 እና የ15 ኪ ቮልት ማሰራጫ መስመሮች በጣቢያው የዕለት ተዕለት የኦፕሬሽን ስራዎች ላይ እንቅፋት እየፈጠሩ መሆኑን የጣቢያው ኃላፊ አቶ ይገርማል ዓለሙ አስታወቁ፡፡ እንደ ኃላፊው ገለፃ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የማሰራጫ መስመሮች ከጊዜ ወደ ጊዜ የሚያጋጥማቸው ችግር እየጨመረ በመምጣቱ በማከፋፈያ ጣቢያው መቆጣጠሪያዎች (Breakers)፣ ትራንስፎርመር እና የኃይል አገናኝ ሽቦዎች feeder power cable) ላይ ጉዳት እያደረሱ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በተፈራረሙት የሰርቪስ ሌቭል ስምምነት መመሪያ ክፍል ሁለት (1) ላይ እንደተመለከተው መስመሮቹ በሚቋረጡበት ጊዜ የሚደረገው ፍተሻ በብሬከር መሆን የለበትም፡፡ ብልሽቱ የግድ በብሬከር የሚፈተሸ ከሆነም በ24 ሰዓት ውስጥ ከሁለት ጊዜ በላይ እንዲሁም በአንድ ወር ውስጥ ከ25 ጊዜ በላይ እንዳይሞከር በግልፅ የተቀመጠ ቢሆንም ከስምምነቱ ውጭ በቀን እስከ ስምንት ጊዜ ብሬከር የሚሞከርበት ጊዜ እንዳለ አቶ ይገርማል ጠቁመዋል፡፡ ኃላፊው እንደሚሉት ከማከፋፈያ ጣቢያው በአንድ ምሶሶ የሚወጡ ሁለት ባለ 15 ኪሎ ቮልት የማሰራጫ መስመሮች ለሁለቱ ተቋማት አለመግባባት ዋነኛ ምክንያቶች ከመሆናቸው ባለፈ መስመሮቹ በተደጋጋሚ እንዲቋረጡና የጣቢያው የኦፕሬሽን ስራዎች እንዲስተጓጎል ምክንያት ሆኗል፡፡ ዲስትሪክቱ ተጨማሪ ኃይል ለመጫን ሲፈልግ የጭነት ፍላጎቱንና የማሳወቅና የማከፋፈያ ጣቢያውን የኃይል አቅርቦት አቅም የመጠየቅ ግዴታ ያለበት ቢሆንም ይህን ሳያደርግ በራሱ ፈቃድ በፈለገበት ጊዜ ተጨማሪ ኃይል መጫኑ በጣቢው ሥራ ላይ ጫና እየፈጠረ ነው ብለዋል፡፡ ከዚህ በፊት ከ285 አምፔር በላይ ኃይል ጭኖ የማያውቀው መስመር ከጣቢያው ዕውቅና ውጭ በአንድ ቀን ተጨማሪ 40 አምፔር የተጫነበት ጊዜ እንደነበርም አስታውሰዋል፡፡ ችግሩን ለአማራ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት ደብረ ማርቆስ ዲስትሪክት በተደጋጋሚ የማሳወቅ ስራ ቢሰራም እስከአሁን መፍትሄ እንዳልተሰጠው ተናግረዋል፡፡ ዲስትሪክቱ ማሰራጫ መስመሮችን እንዲያስተካክል በተደጋጋሚ ቢገለጽለትም ችግሮችን በወቅቱ ከመፍታት ይልቅ ወደ ጣቢያዉ የሚገፋበት ሁኔታ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መጥቷል ብለዋል የጣቢያው ኃላፊ፡፡ የሰሜን ምዕራብ ሪጅን ትራንስሚሽንና ሰብስቴሽን ኦፕሬሽንና ጥገና ቢሮ ዳይሬክተር አቶ ውበት አቤ እነዚህና ሌሎች ያልጠቀሱ በርካታ ችግሮች መኖራቸውን ገልፀው ከአማራ ክልል ኤሌክትሪክ አገልግሎት የስራ ኃላፊዎች ጋር ለመነጋገርና ችግሩን ለመፍታት ጥረት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 28 ቀን 2014

photo content

photo content

የጣቢያውን ሠራተኞች የመኖሪያ ቤት የሚቀርፍ ግንባታ እየተከናወነ ነው ……..///………. በጊቤ 2ኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የተጀመረው የሠራተኞች የመኖሪያ ቤት ግንባታ ሲጠናቀቅ ያለውን የመኖርያ ቤት ችግር ሙሉ በሙሉ እንደሚቀርፍ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጊቤ 2ኛ የሠራተኞች መኖሪያ ቤት ግንባታ ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ ገለፁ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ብርሃኑ ደበላ እንደገለፁት በሚያዚያ ወር 2013 ዓ.ም የተጀመረው የመኖሪያ ቤት ግንባታ አፈጻጸሙ 18 በመቶ ደርሷል፡፡ ግንባታውን በ18 ወራት ውስጥ ሰርቶ ለማጠናቀቅ የታቀደ ሲሆን በአሁኑ ወቅት የፕሮጀክቱ የዕቃ አቅርቦት፣ የተዳፋት ግንባታ አቃፊ ሥራዎች፣ መሰረት የማውጣትና የኮንክሪት ሥራዎች በመከናወን ላይ ናቸው ብለዋል፡፡ በቀጣይም ቀሪ የቁፋሮ እና የመሰረት ሥራዎችን አጠናቆ ግንባታውን በተቀመጠለት የጊዜ ገደብ ለመጨረስ የሲሚንቶ አቅርቦት ችግር እንዳይሆን ከወዲሁ ለማሟላት ጥረት እየተደረገ መሆኑን አቶ ብርሃኑ ተናግረዋል፡፡ የፕሮጀክቱ ተቋራጭ የሳይት ስራ አስኪጅ አቶ አዲስ ፈንታ በበኩላቸው ፕሮጅክቱ ላይ የአናፂና የግንብ ሥራ ባለሙያና የጉልበት ሰራተኛ እጥረት ችግር ቢኖርም ከተቋሙ ጋር በተገባው ውል መሰረት ግንባታውን ሰርቶ ለማስረከብ እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል፡፡ ፕሮጀክቱ ከመኖሪያ ቤት በተጨማሪ የቢሮ፣ የስፖርት መዝናኛ ማዕከል፣ የክሊኒክ እና የትምህርት ቤት ግንባታም ያካተተ ሲሆን ለግንባታው 380 ነጥብ 6 ሚሊዮን ብር ተመድቦለታል፡፡ የፕሮጀክቱን ግንባታ ዓይናለም ጋሻው እና ሉሲ ኢንጅነሪንግ የተባሉ የሀገር ውስጥ ተቋራጮች እያከናወኑት ሲሆን ፕሮጀክቱ 100 ለሚሆኑ የአካባቢው ወጣቶች ጊዚያዊ የሥራ እድል ፈጥሯል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 27 ቀን 2013

photo content

በበጀት ዓመቱ 28 የቴክኒክ እና የፋይናንስ ኦዲቶችን ለማከናወን እቅድ ተይዟል ……….////……… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተያዘው የበጀት ዓመት 28 ቴክኒካልና የፋይናንስ ኦዲት ምርመራ ለማከናወን አቅዶ እየተሰራ መሆኑን የተቋሙ የውስጥ ኦዲት መምሪያ አስታወቀ፡፡ የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ገ/እግዚአብሔር መዝገበ እንዳስታወቁት የኦዲት ምርመራው በተቋሙ ስር የሚገኙ ሁሉንም የስራ ዘርፎችና መምሪያዎችን ባካተተ መልኩ ይካሄዳል፡፡ የኦዲት ምርመራው በተቋሙ ያለውን የስጋት አስተዳደር፣ የመልካም አስተዳደርና የቁጥጥር ስርዓቱ በመፈተሽ ለሚስተዋሉ ክፍተቶች የማሻሻያ ሀሳብ ለማቅረብ እንዲሁም ተቋሙ በበጀት ዓመቱ ለማከናወን ያቀዳቸውን ተግባራት ከግብ ለማድረስ እንደሚያግዝ ተመላክቷል፡፡ በበጀት ዓመቱ የሂሳብና የቴክኒክ ኦዲት ምርመራ ለማካሔድ የስጋት አባቢዎችን በመለየት፣ ለተቋሙ ያላቸው ፋይዳ እንዲሁም ከዚህ ቀደም የኦዲት ምርመራ ያልተደረገባቸውን ጉዳዮች መነሻ በማድረግ ምርመራ ለማከናወን መታቀዱን ዳይሬክተሩ አስረድተዋል፡፡ የምርመራ ስራዉ የሚሸፍነው ጊዜ እንደ ኦዲት የምርመራ ዓይነቱ የሚለያይ መሆኑን የጠቀሱት ዳይሬክተሩ ከዚህ ቀደም ኦዲት የተደረገ የስራ ዘርፍ የኦዲት ምርመራው የሸፈነው ጊዜ ያበቃበትን መነሻ በማድረግ የኦዲት ሥራው ይከናወናል ብለዋል፡፡ ከዚህ በፊት ኦዲት ያልተደረጉ ፕሮጀክቶችም ፕሮጀክቶቹ ከተጀመሩበት ጊዜ አንስቶ እንዲሁም በኦፕሬሽንና ሌሎች ዘርፎች ላይ የሚከናወነው የኦዲት ምርመራ ስራ የኦዲት ምርመራው እስከሚሰራበት ጊዜ ድረስ ያለውን እንደሚሸፍን ኃላፊው ገልፀዋል፡፡ ከፋይናንስና የቴክኒክ የኦዲት ምርመራ ስራዎች በተጓዳኝ በበጀት ዓመቱ የአመራሩንና እና የሠራተኞችን ተግባራትና አፈፃፀም ከተቋሙ ፖሊሲ፣ ደረጃ፣ የአፈፃፀም ስርዓት እና ተፈፃሚነት ሊኖራቸው ከሚገቡ ህጎች፣ ፕሮግራሞች፣ ደንቦችና መመሪያዎች ጋር የተጣጣመ መሆኑን መመርመርና በሚታዩ ክፍተቶች ላይ የማሻሻያ ሃሳቦችን ለማቅረብ እንደሚሰራም ጠቁመዋል፡፡ እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ በበጀት ዓመቱ በተቋሙ የሚፈጸሙ ግዥዎች የድርጅቱን ጥቅም ባስጠበቀ መልኩ መከናወናቸው ይጠናል፡፡ የተቋሙን የጥናት፤ ዲዛይን፣ የፕሮጀክቶች ግንባታ ክትትልና የቁጥጥር ስራዎችን፣ የኃይል ብክነትን ቅነሳ ፍተሻ፣ የመደበኛና የአስቸኳይ ጥገና ስራዎች በተገቢ ሁኔታ መከናወናቸው፤ የገቢ አሰባሰብ እና የወጪ/የክፍያ አስተዳደር ስርዓቱን የማየት እና ወጪን ለመቀነስ በተቋሙ መከናወን ያለባቸው ስራዎች መከናወናቸውንና እና ያስገኙት ዉጤቶችን የመመርመር ስራዎች በበጀት ዓመቱ ትኩረት የሚደረግባቸው ጉዳዮች መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ በተጠናቀቀው የ2013 በጀት ዓመት በተመረጡ የስራ ክፍሎች እና ፕሮጀክቶች ላይ 35 የኦዲት ምርመራ ሥራዎች መከናወናቸውንና በተለያዩ ጊዚያት ከተደረጉ የኦዲት ሪፖርቶች መካከል የ66ቱ ሪፖርቶች የግኝት መከታተያ መዘጋጀቱን ዳይሬክተሩ አንስተዋል፡፡ በተያዘው በጀት ዓመት ለማከናወን የታቀደውን የኦዲት ስራ በጥራት ለማከናወን የስራ ክፍሉን በሰለጠነና ብቃት ባለው የሰው ኃይል ለማደራጀት እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡ ሁሉም አመራርና ሠራተኛ የኦዲት ምርመራው የሚከናወነው ለተቋሙ ግብ ስኬት መሆኑን ተገንዝቦ ለስራው አስፈላጊ እገዛ እንዲያደርጉ ዳይሬክተሩ ጠይቀዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 26 ቀን 2014 ዓ.ም