ch
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

前往频道在 Telegram

EEP Communication

显示更多

📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览

频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 546 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 351,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 178

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 546 名订阅者。

根据 02 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 27,过去 24 小时变化为 8,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 25.76%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.84% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 005 次浏览,首日通常累积 2 463 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 9

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
EEP Communication

凭借高频更新(最新数据采集于 03 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。

15 546
订阅者
+824 小时
-227
+2730
帖子存档
photo content
+2

የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎችን የሰረቁና የተሰረቀውን የገዙ ግለሰቦች ተያዙ ……..///……. ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎችን ፈተው የሸጡ ግለሰቦች በቁጥ
+4
የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎችን የሰረቁና የተሰረቀውን የገዙ ግለሰቦች ተያዙ ……..///……. ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎችን ፈተው የሸጡ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ፡፡ በደቡብ ጎንደር ዞን የሐሙሲት ከተማ አስተዳደር ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ክፍል ኃላፊ ረዳት ኢንስፔክተር ፈንታሁን ግርማ እንደገለፁት ግለሰቦቹ የምሰሶ ብረቶቹን የፈቱት ከባህር ዳር - ወልዲያ - ኮምቦልቻ ከተዘረጋው የከፍተኛ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር ላይ ነው፡፡ የስርቆት ወንጀሉን እንደፈፀሙ የተጠረጠሩት ስድስቱ ግለሰቦች እንዲሁም ብረቱን የገዙ አራት ግለሰቦች በዳማስ መኪና ጭነው ሲንቀሳቀሱ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን ኃላፊው ገልፀዋል፡፡ በመሆኑም ህብረተሰቡ ይህንን መሰል ወንጀሎችን ከፀጥታ ኃይሉ ጋር በመሆን ሊከላከል እንደሚገባ ረዳት ኢንስፔክተር ፈንታሁን ግርማ ማሳሰባቸው የሐሙሲት ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት የማህበራዊ ትስስር ገጽ ያወጣው ዘገባ አመልክቷል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 19 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content

የቃል ፈተና ጥሪ በሎየር 1ኛ የሥራ መደብ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ግንቦት 08 ቀን 2014 ዓ.ም ማስታወቂያ ወጥቶ ነሐሴ 05 ቀን 2014 ዓ.ም የጽሑፍ ፈተና መሰጠቱ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም የጽሑፍ ፈተና ከወሰዳችሁት ውስጥ የማለፊያ ነጥብ ያመጣችሁ ተወዳዳሪዎች የስም ዝርዝራችሁ ከዚህ በታች በተገለፀው መሠረት ነሐሴ 24 ቀን 2014 ዓ.ም የቃል ፈተና የሚሰጥ ስለሆነ ሜክሲኮ ኬ ኬር ህንፃ በሚገኘው የተቋሙ ዋናው መስሪያ ቤት ሁለተኛ ፎቅ ሰራተኛ ምደባ ቢሮ ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ላይ ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡

photo content
+5

የወልዲያ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ የኤሌክትሮ መካኒካል ሥራ በቀጣዮቹ ሦስት ወራት ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው ……….////………. የወልዲያ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ የሲቪል ስራ 94 በመቶ መድረሱን የፕሮጀክቱ የሲቪል ሥራዎች ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ቴዎድሮስ ከፈለኝ እንደገለፁት የኃይል መቆጣጠሪያ ክፍል መሰታወትና ኮርኒስ መግጠም እንዲሁም ግቢውን ማስተካከልና ጠጠር ከማልበስ በስተቀር አብዛኛው የሲቪል ስራ ተጠናቋል። የስዊችያርድ እና የትራንስፎርመር ማስቀመጫ ቦታዎች ግንባታ ስራ ሙሉ ለሙሉ የተጠናቀቀ ሲሆን ቀሪዎቹን የሲቪል ሥራዎች በአስር ቀናት ውስጥ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑንም ሥራ አስኪያጁ ገልፀዋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ራስ ኃይል ኮንስትራክሽን መምሪያ ተጠባባቂ ዳይሬክተር አቶ ሰለሞን ኃ/ጊዮርጊስ በበኩላቸው የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች ተከላ 27 በመቶ መድረሱን አስታውቀዋል፡፡ የትራንስፎርመር ማስቀመጫ ቦታ መሰረት በመጠናቀቁ ትራንስፎርመር አጓጉዞ ለመትከል የሚያስችል ዝግጅት እየተደረገ ስለመሆኑ ገልፀዋል። ለትራንስፎርመር ማጓጓዝ የሚያስፈልገው ጊዜ ከግምት ውስጥ ሳይገባ ቀሪ የኤሌክትሮ መካኒካል ሥራዎችን ለማጠናቀቅ እስከ ሁለት ወር እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል። አጠቃላይ ሥራውን ለማጠናቀቅ ከሦስት ወር ያልበለጠ ጊዜ አንደሚፈልግ ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል። ማከፋፈያ ጣቢያው ከተጠናቀቀ በኋላ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በኩል ከነባሩ ባለ 66 ኪሎ ቮልት መስመር ጋር የማገናኘት ሥራዎች እንደሚፈልጉና በትኩረት መሰራት እንዳለባቸው ዳይሬክተሩ አሳስበዋል። የወልዲያ ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታው ተጠናቆ አግልግሎት መስጠት ሲጀምር ቀደም ሲል ከነበረው አገልግሎት በተጨማሪ ከአላማጣ ማከፋፈያ ጣቢያ ኃይል ሲያገኙ ለነበሩ የተወሰኑ አካባቢዎች ኃይል መስጠት ያስችላል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 18 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content
+5

የኤሌክትሪክ ችግር እንዲፈታላቸው የላሊበላ ከተማ ነዋሪዎች ጠየቁ ......////....... የኤሌክትሪክ ችግር እንዲፈታላቸውና ማህበራዊ አገልግሎቶች ተሟልተው እንዲሰጡ የላሊበላ ከተማና አካባቢው ነዋሪዎች ጠየቁ። የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ዶ/ር ይልቃል ከፋለ በመሩትና የአሸንድዬ በዓልን ምክንያት በማድረግ በላሊበላ ከተማ በተካሄደው ህዝባዊ ውይይት ላይ ነዋሪዎቹ ከኤሌክትሪክ፣ ከማህበራዊ አገልግሎትና ከቱሪዝም ጋር የተያያዙ ጥያቄዎች አቅርበዋል። ኤሌክትሪክን በተመለከተ ለተነሱት ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን፣ የዋግ ኽምራ ዞንና የላስታ ላሊበላ ከተማና አካባቢው ችግር የመነጨው አካባቢው በህወኃት ቁጥጥር ስር ካለው የአላማጣ ማከፋፈያ ጣቢያ ኤሌክትሪክ ያገኝ የነበረ በመሆኑና ኃይል ወደተጠቀሱት አካባቢዎች ኃይል መልሶ ማገናኘት ባለመቻሉ ነው ብለዋል። ይሁንና ከአላማጣ ኃይል ማገናኘት እስከሚቻል ድረስ አዲስ እየተገነባ ካለው የወልዲያ ማከፋፈያ ጣቢያ ወይም ከጋሸና ማከፋፈያ ጣቢያ ለላሊበላና አካባቢው ኃይል ማገናኘት በሚቻልበት ሁኔታ ላይ ሥራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን ገልፀዋል። እየተሰሩ ያሉት ሥራዎች ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር በቅርበትና በቅንጅት መሰራት ያለበት በመሆኑ ተገቢው ዝግጅት እንዲደረግበት አሳስበዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 17 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content
+9

ኢትዮ ኤሌክትሪክ እግር ኳስ ክለብ ለመጪው የውድድር ዘመን ራሱን በማጠናከር ላይ ነው ..........////.......... ኢትዮ ኤሌክትሪክ የወንዶች እግር ኳስ ክለብ ለመጪው የውድድር ዓመት የኢትዮጵያ ቤትኪንግ ፕሪሚዬር ሊግ ተፎካካሪ ለመሆን እየሰራ እንደሚገኝ የክለቡ ጽ/ቤት አስታውቋል። የኢትዮ ኤሌክትሪክ ስፖርት ክለብ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አሸናፊ እጅጉ እንደገለፁት በ2015 ዓ.ም ለሚካሄደው የኢትዮጵያ ቤትኪንግ ፕሪሚዬር ሊግ ጠንክሮ ለመቅረብ ክለቡ 11 አዳዲስ ተጫዋቾችን ያስፈረመ ሲሆን የ10 ነባር ተጫዋቾችን ውልም አራዝሟል። የፈረሙት ተጫዋቾች ከግብ ጠባቂ ጀምሮ የተከላካይ፥አማካይና አጥቂ ተጫዋቾችን ከግምት ውስጥ ያስገባ መሆኑን የጽ/ቤት ኃላፊው ተናግረዋል። በግብ ጠባቂነት ፍቅሩ ወዴሳን ያስፈረመው ኢትዮ ኤሌክትሪክ በተከላካይ ቦታ የሚጫወቱ እንደ ተስፋዬ በቀለ፥ ኃይሌ ገ/ተንሳይ፥ ጌቱ ኃይለማርያም እና ወንድማገኝ ማዕረግ የመሳሰሉ ተጫዋቾችን ወደ ቡድኑ ቀላቅሏል። በፊት መስመርም ሔኖክ አየለን ያስፈረመ ሲሆን የአማካኝ ቦታ አዳዲስ ተጫዋቾችን ወደ ክለቡ ማምጣቱን አቶ አሸናፊ ተናግረዋል። ከአዲስ ተጫዋቾች ባሻገር የቀድሞ የብሔራዊ ቡድን አንጋፋ ተጫዋች ምንያህል ተሾመን ጨምሮ የ10 ነባር ተጫዋቾችን ውል ማራዘሙን ክለቡ አስታውቋል። የክለቡ የቦርድ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ አለማየሁ መንግስቱ የኢትዮ ኤሌክትሪክ ስፖርት ክለብን ለማዘመንና ይበልጥ ተፎካካሪ ለማድረግ በርካታ የለውጥ ስራዎች እየተከናወኑ መሆኑን ገልፀዋል። የ2015 ዓ.ም የኢትዮጵያ ቤትኪንግ ፕሪሚየር ሊግ መስከረም 20 እንደሚጀመር የሚጠበቅ ሲሆን ኢትዮ ኤሌክትሪክ የመጀመሪያ ጨዋታውን ከባህር ዳር ከነማ አቻው ጋር የሚያደርግ ይሆናል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 17 ቀን 2014 ዓ.ም

ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ
ክፍት የሥራ ቦታ ማስታወቂያ

photo content
+5

AnimatedSticker.tgs0.08 KB

AnimatedSticker.tgs0.14 KB

የማሰልጠኛ ማዕከል እና የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች ለማስጀመር ያለመ ምክክር ተካሔደ ...........////......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በፈረንሳይ ልማት ኤጀንሲ ድጋፍ በቢሾፍቱ ከተማ ሊያስገነባው ያቀደው የማሰልጠኛ ማዕከል ወደ ትግበራ ምዕራፍ እንዲገባ ከኤጀንሲው የሥራ ኃላፊዎች ጋር የምክክር መድረክ አካሒዷል፡፡ በውይይቱ ላይ የተቋሙ የሰው ሀብት ልማት መምሪያ ዳይሬክተር ዶክተር ወንድወሰን ካሳ እንደተናገሩት በፈረንሳይ ልማት ኤጀንሲ የፋይናንስ ድጋፍ የሚከናወነው የሰው ሀይል አቅም ግንባታ ስልጠና በ2015 ዓ.ም የሚጀመር ሲሆን የማሰልጠኛ ማዕከሉም ዲዛይን በመጠናቀቅ ላይ ነው። በተቋሙ ለሚገኙ ባለሙያዎችና የሥራ መሪዎች የአቅም ግንባታና የቴክኒክ ሥልጠና የሚሰጡ አማካሪ ድርጅቶችን ለመቅጠር የማወዳደሪያ መስፈርቶች እየተከናወኑ ስለመሆኑ ዶክተር ወንድወሰን ተናግረዋል፡፡ እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ በቢሾፍቱ ከተማ የሚገነባው የማሰልጠኛ ማዕከል ከሀገር ውስጥ ስልጠናዎች ባሻገር በኤሌክትሪክ ኃይል ልማት ዘርፍ ለጎረቤት ሀገራት ባለሙዎች ሥልጠና በመስጠት የውጭ ምንዛሬ ለማስገኘት ያለመ ነው፡፡ በፈረንሳይ ልማት ኤጀንሲ የታስክ ቡድን መሪ (Task team leader) የሆኑት ሚስተር አንሮይን ቤሎሰልስኪ ለማሰልጠኛ ማዕከሉ ግንባታ እና ለአቅም ግንባታ የሚውል 10 ሚሊዮን ዩሮ ድጋፍ በፈረንሳይ ልማት ኤጀንሲ በኩል መፈቀዱን ገልፀዋል፡፡ ሚስተር አንሮይን እንደገለፁት የአማካሪ ቅጥርና የአቅም ግንባታ ሥልጠናዎች በ2015 ዓ.ም የሚጀመሩ ሲሆን የማሰልጠኛ ማዕከሉ ግንባታ በ2016 በጀት ዓመት እንደሚጀመር አስታውቀዋል፡፡ ይህ የገንዘብ ድጋፍ እስከ አምስት ዓመት እንደሚዘልቅና ከግዥ ስርዓት ጀምሮ አጠቃላይ የፕሮጀክት አፈፃፀም ሂደቱን ኤጀንሲው እንደሚከታተል ሚስተር አንሮይን ተናግረዋል፡፡ ፕሮጀክቱን እውን ለማድረግ ከአጋር አካላት ጋር ቀጣይ ውይይቶች እንደሚካሔዱ በምክክር መድረኩ ላይ ተጠቁሟል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 16 ቀን 2014 ዓ.ም

በኃይል ማመንጫ ጣቢያው የአፈር መናድ መከላከያ ሥራና የመንገድ ጥገና ሥራ እየተከናወነ ነው --------////--- የአዋሽ 2 እና 3 የኃይል ማመንጫ ጣቢያ የተንሸራታች መሬት መከላከያ ግንብና የመንገድ ጥገና ስራዎች በተቀላጠፈ ሁኔታ እየተከናወኑ መሆኑን የትራንስሚሽን ሰብስቴሽን ኮንስትራክሽን የራስ ኃይል ኮንስትራክሽን መምሪያ አስታወቀ፡፡ በመምሪያው የሲቪል ሥራዎች ጥገና ሥራ አስኪያጅ ኢንጂነር ግርማ መንገሻ እንደገለፁት በጣቢያው እየተገነባ ያለው የተንሸታራች መሬት መከላከያ ግንብ ሥራ 90 ሜትር ርዝመትና 10 ሜትር ከፍታ አለው፡፡ እስካሁን በተሰራው ሥራ ሙሉ በሙሉ ቁፋሮው መጠናቀቁና 15 ነጥብ 8 ሜትር ርዝመት ያለውና 7 ነጥብ 9 ሜትር ከፍታ ያለው የግንባታ ሥራ ተከናውኗል። ይህም የፕሮጀክቱን አፈፃፀም 41.5 ከመቶ ያህሉን መጠናቀቁን ሥራ አስኪያጁ ገልፀዋል። የግንባታ ሥራውን በሰባት ወራት ጊዜ ውስጥ አጠናቆ ለማስረከበ ከኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን ጽ/ቤት ኮንትራት የተወሰደ መሆኑን ያወሱት ሥራ አስኪያጁ በተለያዩ ሰው ሰራሽና ተፈጥሯዊ ምክንያቶች በታሰበው ፍጥነት ልክ ግንባታውን ማከናወን እንዳልተቻለ ጠቁመዋል። ግንባታው የሚከናወንበት ቦታ ዐለታማ መሆኑና የተለያዩ ከባድ ማሽነሪዎችን መጠቀም የግድ ሆኖ መገኘቱ ፕሮጀክቱን ፈታኝ አድርጎት እንደነበር ገልፀዋል። ሥራ አስኪያጁ እንደተናገሩት ለግንባታው አጠቃላይ ከ18 ሚለየን ብር በላይ በጀት የተያዘ ቢሆንም በወቅቱ ካለው የግብዓት ዋጋ መናር ጋር ተያይዞ የኮንትራት ማሻሻያ እንደተጠየቀበትና ግንባታውን በአጭር ጊዜ ለማጠናቀቅ በቅንጅት እየተሰራ እንደሚገኝ አስረድተዋል። በተለይም የኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽ ጽ/ቤት እያደረገ ለሚገኘው ቀና ትብብብር ምስጋና ያቀረቡት ኢንጂነር ግርማ ይህ ፕሮጀክት የራስ ኃይል ኮንስትራክሽን ቢሮ በኃይል ማመንጫዎች እያከናወነ ከሚገኘው የጥገና ስራዎች ወስጥ ትልቁ መሆኑን ጠቁመዋል። ከአዲስ አበባ በደቡብ ምስራቅ አቅጣጫ 125 ኪሎ ሜትር ርቀት ለይ የሚገኘኙት የአዋሽ ሁለት እና ሦስት ኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች እያንዳንዳቸው 32 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም አላቸው። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 13 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content
+6

የፕሮጀክቱ ግንባታ 85 በመቶ ተጠናቋል ........////...... የአዘዞ ጭልጋ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያ መስመር እና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ግንባታ 85 በመቶ መድረሱን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአዘዞ ጭልጋ ፕሮጀክት ጽ/ቤት ገለፀ። የፕሮጀክቱ አስተባባሪ አቶ ዳንግብጹ መንገሻ እንደገለፁት በአሁኑ ወቅት የፕሮጀክቱ ወሳኝ ሥራዎች የሚባሉት የኤሌክትሪክ ተሸካሚ ምሰሶ ተከላ፣ የማስተላለፊያ ገመድ ዝርጋታ፣ የማከፋፈያ ጣቢያው የውስጥ አጥር እና የአፈር ምለሳ ሥራዎች በመከናወን ላይ ይገኛሉ። ለመስመር ዝርጋታው ከሚያስፈልጉት 105 የኤሌክትሪክ ተሸካሚ ምሰሶዎች ውስጥ 89 ያህሉ መጠናቀቃቸውን የገለፁት አስተባባሪው በካሳ ክፍያና ተያያዥ ጉዳዮች የዘገዩ የማስተላለፊያ መስመር የመሰረት ግንባታ፣ የምሰሶ ተከላና የዝርጋታ ሥራዎች በቀጣይ የሚሰሩ መሆናቸውን ጠቁመዋል፡፡ ፕሮጀክቱ 43 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር እና አንድ ባለ 230/33 ኪሎ ቮልት አዲስ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታን የሚያጠቃልል ነው፡፡ የአዲስ የማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታ ግንባታ በጭልጋ፣ በነባሩ የአዘዞ ማከፋፈያ ጣቢያ ውስጥ ደግሞ ማስፋፊያ እየተከናወነ ሲሆን የጭልጋ ማከፋፈያ ጣቢያ የመጀመሪያ ሙከራ እየተደረገለት መሆኑንም አስተባባሪው ጠቁመዋል። የአዘዞ ጭልጋ የኤሌክትሪክ ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት በአካባቢው የነበረውን ከፍተኛ የኃይል መዋዠቅና መቆራረጥ ከማስቀረት አልፎ ለአካባቢው የኢንቨስትመንት መስፋፋት በር እንደሚከፍት እና በተደጋጋሚ የሚነሳውን የኃይል አቅርቦት ጥያቄ እንደሚፈታ ተስፋ ተጥሎበታል፡፡ የፕሮጀክቱን ግንባታ ሲኖ ኃይድሮ ኮርፖሬሽን የተባለው የቻይና ኩባኒያ ሲያከናውን በአማካሪነት ደግሞ ኢ.ኤል.ሲ. (ELC) የተባለ የጣሊያን ኩባኒያ እየተሳተፈበት ይገኛል፡፡ ፕሮጀክቱ ከአዲስ አበባ በ780 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ማዕከላዊ ጎንደር ዞን ጭልጋ ወረዳ በአንጓባ ቡላድጌ ቀበሌ ይገኛል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ነሐሴ 13 ቀን 2014 ዓ.ም

photo content
+6

photo content
+7