EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 553 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 395,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 164 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 553 名订阅者。
根据 22 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 5,过去 24 小时变化为 1,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 25.99%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.38% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 043 次浏览,首日通常累积 2 393 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 9。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 23 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 553
订阅者
+124 小时
+47 天
+530 天
帖子存档
15 553
ማህበሩ 5ኛ ጠቅላላ መደበኛ ጉባዔውን ማካሄድ ጀመረ
....///.....
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መሠረታዊ የሠራተኛ ማህበር 5ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔውን በዛሬው እለት በአዳማ ከተማ ማካሄድ ጀምሯል፡፡
በጉባዔው ላይ የሪጅን፣ የኃይል ማመንጫ፣ የዋናው መ/ቤት የዘርፍ ተወካዮች እየተሳተፉ ይገኛል።
በጉባኤው ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የማህበሩ ሊቀመንበር አቶ ዳንኤል ገ/ሚካኤል ማህበሩ ባለፉት ዓመታት የተቋሙ የሥራ አመራርና ቦርድ አባል በመሆን ሕግና ሥርዓቱን ተከትሎ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተቀናጅቶ በመስራት የሠራተኛውን መብትና ዘላቂ ጥቅም ለማስጠበቅ በርካታ ተግባራትን ሲያከናውን ቆይቷል፡፡
በዚህም የአባላትን ቁጥር በማሳደግ በአሰሪና ሠራተኛው መካከል የሚከሰቱ አለመግባባቶች በስምምነት መፍትሔ እንዲሰጣቸው በማድረግ በተቋሙ የኢንዱስትሪ ሰላምን በማስፈን በኩል ከፍተኛ ሚና መወጣቱን ተናግረዋል።
በተቋሙ እየተከናወነ ያለው የመዋቅራዊ ማሻሽያ ሕብረት ስምምነቱን የተከተለና የሠራተኛውን የሥራ ዋስትና ያረጋገጠ እንዲሆንም በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል።
ሆኖም የተጠኑ ጥቅማ ጥቅሞች ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ አለመሆን፣ የደህንነት መጠበቂያ ቁሶች በወቅቱ ተደራሽ አለመሆን፣ የጡረተኞች ነፃ ሕክምና አለመፈቀድ እና የፋይናንስ ውስንነት መኖሩ ያጋጠሙ ተግዳሮቶች እንደነበሩ ገልጸዋል።
ጉባዔው የነበሩ ጠንካራ ጎኖችን በማጎልበትና ክፍተቶችን በማረም የሠራተኛውን ሁሉን አቀፍ ጥቅም የሚያስጠብቅ ውሳኔ እንደሚያሳልፍ እምነታቸው መሆኑን ተናግረዋል።
ማህበሩ ባለፉት አምስት ዓመታት ያከናወናቸው ዋና ዋና ተግባራት እና የኦዲት ሪፖርት ቀርቦ ውይይት እንደሚደረግበትና የማህበሩ ማሻሸያ ደንብ ቀርቦ እንደሚጸድቅም ተገልጿል፡፡
በጉባዔው የተጓደሉ የኦዲት አባላት ምርጫ የሚከናወን ሲሆን የማህበሩ 11ኛ መደበኛ የምክር ቤት ስብሰባውን በነገው ዕለት የሚያካሂድ ይሆናል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሐምሌ 12 ቀን 2017 ዓ.ም
15 553
በበጀት ዓመቱ የታዩ ክፍተቶችን በማረም የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ይሰራል
---////----
በተጠናቀቀው የ2017 በጀት ዓመት የታዩ ክፍተቶችን በማረም የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ እንደሚሰራ የአዳማ 2 የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ገለፀ።
የጣቢያው የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች በ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም እና በ2018 ዕቅድ ላይ ውይይት አድርገዋል፡፡
የጣቢያው የጥገና ክፍል ሥራ አስኪያጅ እና የጣቢያው ተወካይ ኃላፊ አቶ ይታየው ቸሩ በውይይት መድረኩ ላይ እንደገለፁት ጣቢያው የ2017 በጀት ዓመት የኃይል ምርት ዕቅዱን ለማሳካት የኦፕሬሽንና የጥገና ሥራዎችን በቅንጅት ሲሰራ ቆይቷል፡፡
በጣቢያው የተለያዩ የአሰራር ሥርዓቶችን በማሳደግ እንዲሁም ዓመታዊ የትንበያ እና የፍተሻ ጥገና ሥራዎችን በተቀመጠላቸው ጊዜ በማከናወን ዕቅዱን ለማሳካት ጥረት ሲደረግ መቆየቱንም ተናግረዋል፡፡
በራስ ኃይል የጥገና ሥራዎችን ማከናወን መቻል እንዲሁም የእርስ በእርስ የመማማር አቅም እያደገ መምጣት በበጀት ዓመቱ ከታዩ ጠንካራ ጎኖች መካከል እንደሚጠቀሱ በውይይቱ ተመላክቷል፡፡
በጣቢያው ባለሙያዎች የተርባይን ቅየራ ሥራ መከናወኑ፣ የ33 ኪሎ ቮልት መስመር እና ሰርኪዩት ብሬከር እንዲሁም የኮሙዩኒኬሽን ፋይበር መጠገን መቻሉ የበጀት ዓመቱ የጣቢያው ስኬቶች መሆናቸውንም ነው አቶ ይታየው ያብራሩት፡፡
በመለዋወጫ ዕቃዎች እጥረት ምክንያት 6 ተርባይኖች ለወራት መቆማቸው እንዲሁም የተጋነነ ዕቅድ መያዙ ለአፈፃፀሙ ዝቅ ማለት እንደምክንያት በውይይቱ ላይ ተጠቅሷል።
የሥራ ላይ መሳሪያዎች በወቅቱ አለመቅረብ እና የተሸከርካሪ እጥረት መኖር እንዲሁም ወደ ተርባይን የሚያስኬዱ መዳረሻ መንገዶች ጥገና አፈፃፀም ዝቅተኛ መሆን በጣቢያው የጥገና ሥራዎች ላይ ተግዳሮት መፍጠራቸውን ጠቁመዋል፡፡
እንደ አቶ ይታየው ገለፃ በ2017 በጀት ዓመት የታዩ ጠንካራ ጎኖችን በማጎልበትና ክፍተቶችን በማረም በቀጣይ በጀት ዓመት የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ ሁሉም በትብብር ይሰራል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሐምሌ 11 ቀን 2017 ዓ.ም
15 553
ውሳኔ ካገኙ የፍትኃብሔር ክርክሮች ከ562 ሚሊዮን ብር በላይ ማዳን ተችሏል
………///……
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በፌዴራልና በክልል ፍርድ ቤቶች ክርክር ካካሄደባቸው የፍትኃብሔር መዝገቦች 562 ነጥብ 722 ሚሊዮን ብር ማዳን መቻሉን የተቋሙ የሕግ አገልግሎት መምሪያ ገለፀ፡፡
የመምሪያው ተወካይ ዳይሬክተር ወ/ሮ መስከረም በቀለ እንደገለፁት በ2017 በጀት ዓመት በተጀመሩ 188 እና ከ2016 በጀት ዓመት በተላለፉ 144 መዝገቦች ላይ በተለያዩ ፍርድ ቤቶች ክርክር ሲደረግ ቆይቷል፡፡
ክርክር ሲካሄድባቸው ከቆዩት መዝገቦች ውስጥ 68ቱ ውሳኔ ያገኙ ሲሆን 42ቱ ለተቋሙ እንዲሁም 5ቱ ደግሞ በተቋሙ ላይ ተወስነዋል ብለዋል፡፡
ቀሪ መዝገቦች በክትትል ሂደት ላይ የሚገኙ ሲሆን ውሳኔ ከተሰጠባቸው መዝገቦችም ከ562 ነጥብ 72 ሚሊዮን ብር በላይ ማዳን ተችሏል ነው ያሉት፡፡
ከፍትኃብሔር መዝገቦች በተጨማሪ 121 የወንጀል መዝገቦች ላይ ክትትል መደረጉን የጠቆሙት ወ/ሮ መስከረም ከዚህ ውስጥ ውሳኔ ባገኙ ዘጠኝ መዝገብ ተከሳሾች ላይ የገንዘብ እና እስከ ስምንት ዓመት የሚደርስ የፅኑ እስራት ቅጣት መተላለፉንም ተናግረዋል፡፡
መምሪያው ከከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ስርቆት እና ተቋሙ ከመሬት ይዞታ ግብር ነጻ በሚሆንበት ዙሪያ ከፍትኅ ሚኒስቴር ጋር በትብብር ሲሰራ መቆየቱን አስታውሰዋል፡፡
የማህበረሰብ የእኔነት ስሜት በመፍጠር ከከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ስርቆትን ለመከላከል ከቀበሌ መስተዳድሮች ጋር በጋራ ለመስራት ውል መዘጋጀቱንም ጠቁመዋል።
በተጨማሪም ከካሳ ጉዳይ ጋር ተያይዞ በፍ/ቤት ያሉ አስተዳደራዊ ችግሮች እንዲቀረፉ እንዲሁም በካሳ ጉዳይ ክርክሮች ላይ ሐሰተኛ ማስረጃ በሚሰጡ የአስተዳድር አካላት፣ በሐሰት ክስ የተጋነነ ብር በሚያስወስኑ ከሳሾች እንዲሁም ያለህጋዊ መብት ክስ እየመሰረቱ በሚከራከሩ ጠበቆች ላይ የሙስና ወንጀል ምርመራ እንዲከናውን ከኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት አቃቤ ሕግ ቢሮ ጋር በትብብር እየተሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል።
እንደ ተወካይ ዳይሬክተሯ ገለፃ የሥራ ክፍሉን ሥራ ውጤታማነት ለማሳደግ የመዝገብ ክትትሉን አውቶሜሽን ለማድረግ የሚያስችል ሶፍትዌር የማበልፀግ እንዲሁም የወጡ ደንቦች፣ መመሪያዎች፣ የአሰራር ሥርዓት ማኑዋሎች እና ፖሊሲዎችን የማሰባሰብ፣ የማደራጀትና የመፈተሽ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው።
የግብዓት ዕጥረት፣ የተደራጀ የመረጃ አያያዝ እለመኖር እና የካሣ ሕጉ በተቋሙ ካለው የአሠራር ሥርዓት ጋር የተቀራረበ አለመሆን በበጀት ዓመቱ ያጋጠሙ ችግሮች እንደነበሩ አብራርተዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሐምሌ 11 ቀን 2017 ዓ.ም
15 553
ሪጅኑ በበጀት ዓመቱ ውጤታማ ሥራ ማከናወኑን ገለጸ
.....///…..
በ2017 በጀት ዓመት የጥገና እና ኦፕሬሽን ሥራዎችን ጨምሮ በሌሎች ዘርፎች ላይ ውጤታማ ሥራ ማከናወኑን የምስራቅ አንድ ሪጅን አስታወቀ።
የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ወርዲ መሃመድ እንዳስታወቁት በበጀት ዓመቱ በመደበኛና ድንገተኛ ጥገናዎች፣ ማከፋፈያ ጣቢያዎችን በማዘመን እና የሠው ኃይል አቅምን በመገንባት በኩል ውጤታማ ሥራዎች ተሠርተዋል።
ሪጅኑ በስሩ በሚያስተዳድራቸው የማስተላለፊያ መስመሮች እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የአቅም ማሳደግ ሥራዎችን በማከናወን የቅድመ መከላከል ጥገና ማድረጉን ዳይሬክተሩ ገልጸዋል።
በበጀት ዓመቱ የተከናወኑት የአቅም ማሳደግ እና የማዘመን ሥራዎች በሪጅኑ ይፈጠር የነበረውን ተደጋጋሚ የኤሌክትሪክ መቆራረጥ እና የጥገና ድግግሞሽ በመቀነስ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለደምበኞች እንዲደርስ ማስቻሉንም ነው የገለጹት።
እንደ ዳይሬክተሩ ገለጻ በሪጅኑ ያለውን የሠው ኃይል አቅም በመገንባት ፈጣን ምላሽ መስጠት የሚችል ሠራተኛ ለማፍራት በበጀት ዓመቱ የተለያዩ ሥልጠናዎች ተሰጥተዋል፡፡
በበጀት ዓመቱ የመረጃ አመዘጋገብ፣ የሳፕ፣ የመሰረታዊ ኮምፒውተርና እንዲሁም የሥራ ላይ ደህንነት እና ጤና ስልጠናዎች መሰጠታቸውን ጠቅሰዋል።
ዳይሬክሩ አክለውም የተሰጡት ስልጠናዎች የሪጅኑን ሠራተኞች የነበራቸውን እውቀት በማዳበር የተሻለ ፈፃሚ አካል እንዲፈጠር ማስቻላቸውን ገልጸዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሐምሌ 11 ቀን 2017 ዓ.ም
15 553
በጣቢያው አጠገብ የሚገኘው የደረቅ ቆሻሻ ማጠራቀሚያ ለኃይል መቋረጥ ምክንያት እየሆነ ነው
.........///........
በለገጣፎ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ አጠገብ ያለው የደረቅ ቆሻሻ ማከማቻ አዕዋፋት እንዲሰባሰቡና ተደጋጋሚ የኃይል መቋረጥ እንዲከሰት ምክንያት መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ አንድ ሪጅን አስታወቀ፡፡
በሪጂኑ የለገጣፎ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ኃላፊ አቶ ታምራት ፎጊ እንደገለፁት በጣቢያው አቅራቢያ የደረቅ ቆሻሻ ማጠራቀሚያ በመኖሩ ከትንሽ እስከ ትላልቅ አእዋፋት ምግብ ለመፈለግ ወደ ቆሻሻ ቦታው ይሰባሰባሉ።
ይኽም ከከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ጋር በሚያደርጉት ንክኪ ተደጋጋሚ የኃይል መቆራረጥ እንዲያጋጥም ምክንያት ሆኗል ብለዋል።
የደረቅ ቆሻሻ ማጠራቀሚያ ቦታው ከጣቢያው አካባቢ እንዲነሳ ለለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 አስተዳደር በደብዳቤ ጥያቄ ቢቀርብም እስከአሁን ድረስ ተግባራዊ ምላሽ አለመሰጠቱን ኃላፊው ተናግረዋል፡፡
ከኃይል መቋረጥ ባሻገር ይህ የደረቅ ቆሻሻ ማጠራቀሚያው በበጋ ወራት የተለያዩ ተቀጣጣይ ቁሶች የሚከማችበት በመሆኑ በአቅራቢው በሚገኘው የኃይል ማከፋፈያ እና የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ የእሳት አደጋ ስጋት በመደቀኑ የቆሻሻ ማከማቻ ቦታው በአፋጣኝ እንዲነሳ አሳስበዋል፡፡
በአዲስ አበባ ከተማ በለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ የሚገኘው የለገጣፎ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ለኤሌክትሪክ ኃይል ተጠቃሚ ደንበኞች የ24 ሰዓት አገልግሎት በመስጠት ላይ ይገኛል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሐምሌ 11 ቀን 2017 ዓ.ም
15 553
ማመንጫ ጣቢያ የወረዳውን የኢንቨስትመንትና የማህበራዊ ኑሮ ገጽታ ለውጧል
...….///…....
የመልካ ዋከና ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በአዳባ ወረዳ የኢንቨስትመንት እንቅስቃሴን ከማሳደጉም በላይ የበርካታ ሺህ ነዋሪዎችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ኑሮ በእጅጉ ማሻሻሉን የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አስታወቁ።
የአዳባ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ አብዱከሪም ከድር እንደገለፁት የኃይል ማመንጫ ጣቢያው በወረዳው ውስጥ መገኘት አካባቢውን ለኢንቨስትመንት ምቹና ተመራጭ በማድረግ የልማት ዕድገቱን አፋጥኖታል። በዚህም ምክንያት ከወረዳው 22 የገጠር ቀበሌዎች መካከል 14ቱ እንዲሁም 5 ከተሞች የ24 ሰዓት ሙሉ በሙሉ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ተጠቃሚ መሆን ችለዋል ብለዋል::
የኤሌክትሪክ ተጠቃሚነት መስፋፋት የህብረተሰቡን የጤና ሁኔታ በእጅጉ እንዳሻሻለ የጠቀሱት አስተዳዳሪው፣ ቀደም ሲል ነዋሪዎች ለብርሃን ምንጭነት ኩራዝ ይጠቀሙ ስለነበር በትራኮማ በሽታ ይሰቃዩ እንደነበር አስታውሰዋል። የኤሌክትሪክ ኃይል መኖር ይህንን ችግር ሙሉ በሙሉ በመቅረፍ የህብረተሰቡን ጤና ጠብቋል።
በተለይ ሴቶችና እናቶች ምግብ ለማብሰልና እህል ለማስፈጨት ለከፍተኛ ወጪ እና የጤና እክል ይዳረጉ ነበር። ነገር ግን አሁን ላይ የኤሌክትሪክ ኃይልን መጠቀም በመጀመራቸው ኑሯቸውን በቀላልና በዘመናዊ መንገድ መምራት ጀምረዋል ብለዋል።
ከዚህም ባሻገር የኃይል ማመንጫው ከ96 ሺህ በላይ ለሚሆኑ የከተማና የገጠር ነዋሪዎች የንጹህ መጠጥ ውሃ አቅርቦት እንዲረጋገጥ አስችሏል። በኤሌክትሪክ ኃይል በሚሰሩ የውሃ ፓምፖች አማካኝነት በርካታ ቀበሌዎች የጉድጓድ ውሃ ተጠቃሚ ሆነዋል።
የመልካ ዋከና ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ለቀሪ የወረዳው ቀበሌዎች የኤሌክትሪክ አገልግሎትን ለማዳረስ በትጋት እየሰራ መሆኑን የገለጹት አቶ አብዱከሪም፣ ለወረዳው ሁለንተናዊ እድገት እያደረገ ያለውን የማይተካ ሚናም አመስግነዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሐምሌ 11 ቀን 2017 ዓ.ም
15 553
በፈታኝ ሁኔታዎች ውስጥ ስኬታማ ሥራዎችን ላከናወኑ የተቋሙ ሠራተኞች ዕውቅና ሊሰጥ ይገባል
….///….
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልን መልካም ስምና ገፅታ በመጠበቅ በፈታኝ ሁኔታዎች ውስጥ ውጤታማ ሥራዎችን ላከናወኑ አመራሮችና ሠራተኞች ዕውቅና ሊሰጥ እንደሚገባ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አስታወቁ፡፡
ዋና ሥራ አስፈፃሚው ኢንጂነር አሸብር ባልቻ የተቋሙ የ2017 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ በተካሄደበት ወቅት እንዳስታወቁት ኢትዮጵያ ለአፍሪካ የኃይል ልማት ዘርፍ ከፍተኛ ድርሻ እያበረከተች ነው፡፡
የፕሮጀክት ግንባታዎችን በራስ አቅም የማከናወን ብቃት እያደገ መምጣቱን የገለፁት ዋና ሥራ አስፈፃሚው ለቀጣዩ ትውልድ የሚተላለፉ ሜጋ ፕሮጀክቶችን በአግባቡ ማጠናቀቅ እየተቻለ ነውም ብለዋል፡፡
የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ አሁን ለደረሰበት ስኬት የበቃው በተቋሙ አመራሮች እና ሠራተኞች እንዲሁም በመንግሥት እልህ አስጨራሽ ትግል መሆኑን ተናግረዋል፡፡
የሀገር መከላከያ ሠራዊት እና የፌዴራል ፖሊስ ከተቋሙ ጋር በመተባበር ለፕሮጀክቱ የሚያስፈልጉ ዕቃዎችን በአስቸጋሪ ሁኔታ ሲያጓጉዙ እንደነበር የጠቀሱት ኢንጂነር አሸብር የፀጥታ ዘርፎቹ እና የተቋሙ ሠራተኞች ለቀጣዩ ትውልድ የሚሻገር አኩሪ ተግባር ላይ በመሳተፋቸው ሊኮሩ እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡
እንደ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ የ2017 በጀት ዓመት አፈፃፀም በተግዳሮቶች የተሞላ ቢሆንም በመንግሥት እና በተቋሙ የቦርድ አመራር ክትትልና ድጋፍ የላቀ ውጤት ተመዝግቧል፡፡
በፕሮጀክቶች አፈፃፀም ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ የሚያስችሉ የአሰራር ሥርዓቶችን በመዘርጋት ወጪ ቆጣቢ ሥራዎች ሊሰሩ እንደሚገባም ነው ያነሱት፡፡
በበለስ፣ ፊንጫ፣ ህዳሴ እና አይሻ የኃይል ማመንጫዎች እየሰሩ የሚገኙ የተቋሙ ሠራተኞች በብዙ ፈተናዎች ውስጥ ውጤታማ ሥራዎች እያከናወኑ ነው ያሉት ኢንጂነር አሸብር ለዚህም ዕውቅና ሊሰጣቸው ይገባል ብለዋል፡፡
እንደ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ በተቋሙ በሁሉም የሥራ ዘርፎች የላቀ አፈፃፀም ላስመዘገቡ አመራሮች እና ሠራተኞች የማበረታቻ ዕውቅና ይሰጣል፡፡
በኃይል መሠረተ ልማቶች ላይ በሚደርሱ ጉዳቶች ሳቢያ ለጥገና የሚወጣው ወጪ ከፍተኛ እየሆነ መምጣቱን የገለፁት ኢንጂነር አሸብር የተቋሙን ሀብት በእኔነት ስሜት መጠበቅ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡
በቀጣይ ተቋሙ ተግባራዊ እያደረገው በሚገኘው አዲስ መዋቅር የሠራተኛውን አቅም በማጎልበት የእርካታ ደረጃውን ለማሻሻል እንደሚሰራም ነው ዋና ሥራ አስፈፃሚው የጠቆሙት፡፡
በተቋሙ ለሦስት ዓመታት ሲተገበር የቆየው የግሪድ ስትራቴጂ በቀጣዩ በጀት ዓመት እንደሚጠናቀቅ የገለፁት ኢንጂነር አሸብር አዲስ ለሚቀረፀው የስትራቴጂክ ዕቅድ ሁሉም ሠራተኛ ግብዓቶችን በማቅረብ እገዛ እንዲያደርግ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሐምሌ 9 ቀን 2017 ዓ.ም
15 553
የጣቢያውን የሥራ ቅልጥፍና ለማምጣት ያለመ አውደ ጥናት ተካሄደ
....///....
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር የረጲ ከደረቅ ቆሻሻ ኃይል ማመንጫ ጣቢያን የሥራ ቅልጥፍና ለማምጣት የሚያስችል አውደ ጥናት ትናንት አካሄደ፡፡
አውደ ጥናቱ በዋናነት በጣቢያው ላይ የሚያጋጥሙ ችግሮችን በመፍታት የጣቢያውን ኃይል የማምረት ዘላቂነት እና አስተማማኝነት ለማሳደግ ያለመ ነው፡፡
በተቋሙ የኢትዮ-ፓወር አካዳሚ ዳይሬክተር ዶ/ር ወንዶሰን ካሳ አውደ ጥናቱን አስመልክተው ባደረጉት ንግግር ማመንጫ ጣቢያው ኃይል ከማምረት ባሻገር ከቆሻሻ አወጋገድ ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ የብክለት እና የእይታ ጉድለቶችን በመቅረፍ ከተማዋን ለማስዋብ ወሳኝ ሚና እንዳለው አስረድተዋል።
ጣቢያው ለህብረተሰቡ ሰፊ የሥራ ዕድል በመፍጠር ተጨባጭ ጥቅሞችን እየሰጠ የከተማ አካባቢ ችግሮችን እንዴት እንደሚፈታ ለአፍሪካ ጭምር ምሳሌ መሆኑን ገልጸዋል።
በዕለቱም የረጲ ከደረቅ ቆሻሻ ኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ኃይል ከማመንጨት ጎን ለጎን የመዲናዋን ቆሻሻ ተቀብሎ ወደ ጥቅም በመቀየር ፅዱ፣አረንጓዴ እና ለጤና ተስማሚ ከተማ ለማድረግ ስለሚኖረው ፋይዳ እና እያጋጠሙት ስላሉ ተግዳሮቶች የተመለከተ አውደ ጥናት ቀርቧል፡፡
በጥናቱ ከቆሻሻ የኤሌክትሪክ ኃይል ማምረት ለከተማ ቆሻሻ አያያዝ እና ለአየር ንብረት ለውጥ ቅነሳ ያለውን ጥቅም ከአለም አቀፍ መመዘኛዎች ጋር በማነፃፀር በሠፊው ተዳሷል፡፡
በአዲስ አበባ ፅዳት አስተዳደር ሥራ አስኪያጅ የሆኑት አቶ ማስረሻ አስናቀው ባቀረቡት ጥናት ላይ እንዳብረሩት ቆሻሻን ወደ ጥቅም መቀየር የግሪንሀውስ ጋዝ ልቀትን በመቀነስ የአየር ንብረት ለውጥን ለመከላከል ቁልፍ ቴክኖሎጂ ነው።
ይሁን እንጅ በከተማዋ የሚሰበሰበው ቆሻሻ ከፍተኛ እርጥበት ያለው፣ለመቀጣጠል የማይመች እና የተቀላቀለ በመሆኑ በጣቢያው ኃይል የማምረት ሂደት ላይ ችግር እንደሚፈጥር በጥናቱ አመላክተዋል፡፡
በቆሻሻ አሰባሰብ ፣አወጋገድ እና አጠቃቀም ዙሪያ ደጋፊ የህግ ማዕቀፍ አለመዘጋጀቱ እንዲሁም የግንዛቤ እጥረት እና የተሳሳቱ አመለካከቶች መኖራቸውንም ጨምረው ገልፀዋል።
በአውደ ጥናቱ የተለዩ ችግሮችን ለመፍታት የአጭር፣የመካከለኛ እና የረጅም ጊዜ ዕቅዶችን አቅዶ መስራት እንደሚገባ ባለድርሻ አካላቱ በውይይታቸው አንስተዋል፡፡
ማመንጫውን የዋጀ የቆሻሻ አሰባሰብ ሥርዓት በመዘርጋት፣ስለቆሻሻ አስተዳደር የህግ ማዕቀፍ በማዘጋጀት እና የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናዎችን በመስጠት የቆሻሻ ሃብትን ወደ ጥቅም ለመቀየር በጋራ መስራት እንደሚያስፈልግ ተወያዮቹ አስገንዝበዋል፡፡
በአውደ ጥናቱ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጅ ኢንስቲትዩት፣ከውሃና ኢነርጅ ሚንስቴር፣ከአዲስ አበባ ፅዳት አስተዳደር እና ከሌሎች የተውጣጡ ባለድርሻ አካላት ታድመዋል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሐምሌ 9 ቀን 2017 ዓ.ም
15 553
‹‹የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ መጠናቀቅ የማንሰራራት ዘመን ምሳሌ ነው›› ኢንጂነር አሸብር ባልቻ
...///…
በሁሉም ኢትዮጵያዊያን ትብብር እና ተሳትፎ የተገነባው የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት መጠናቀቅ የማንሰራራት ዘመን ማሳያ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ገለፁ፡፡
ተቋሙ በሰው ኃይል ልማት፣ በፋይናንስ፣ በኃይል ማመንጨት፣ በማስተላለፊያ፣ በማመንጫና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የኦፕሬሽን፣ ግንባታና የጥገና እንዲሁም የሪፎርም ሥራዎች አፈፃፀምን ገምግሟል።
የበጀት ዓመቱን አፈፃፀም ያቀረቡት በተቋሙ የትራንስሚሽን ቢዝነስ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አንዱዓለም ሲዓ እንደገለፁት ተቋም የሚቀየረው የሠራተኛውን አቅም በማሳደግ በሚሰሩ ዘርፈ ብዙ ሥራዎች ነው፡፡
በበጀት ዓመቱ በርካታ ስኬቶች መመዝገባቸውን የተናገሩት ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚው በሁሉም ዘርፍ የነበረው አፈፃፀም እንዲሁም የኦፕሬሽን ሥራዎች እና የኃይል ሽያጭ የተሻለ እንደነበር ገልፀዋል።
እንደ ኢንጂነር አንዱዓለም ገለፃ ለዓመታት ሳይከለስ የቆየውን የኤሌክትሪክ ታሪፍ የማሻሻል ሥራን በማከናወን ተቋሙ የተሻለ ገቢ እንዲኖረው ተደርጓል፡፡
በበጀት ዓመቱ በፕሮጀክቶች አፈፃፀም ላይ የነበሩ ችግሮችን በመፍታት በታቀደላቸው ጊዜ ተጠናቀው ወደ አገልግሎት እንዲገቡ ማድረግ መቻሉን ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚው አስረድተዋል።
ፕሮጀክቶቹ ከጅማሬ አንስቶ፣ በትግበራ ሂደት እና በማጠቃለያ ወቅት ያላቸውን አፈፃፀም እንዲሁም አጠቃላይ መረጃዎቻቸውን መመዝገብ የሚያስችል መተግበሪያ ተዘጋጅቶ አገልግሎት ላይ መዋሉን ጠቅሰዋል፡፡
በበጀት ዓመቱ አንድ አጠቃላይ የኃይል መቋረጥ በግሪድ ሥርዓቱ ላይ ማጋጠሙ፣ በግዥ የአሰራር ሥርዓቶች የውሳኔ አሰጣጥ ሂደቶች ላይ ክፍተት መታየቱ፣ የመቆጣጠሪያ ሥርዓቶችን የማዘመንና ወጥነት ያለው ሥራ አለመሰራቱ እና በቴክኖሎጂ የተደገፉ አሠራሮችን በተሟላ ሁኔታ መተግበር አለመቻሉ በበጀት ዓመቱ የታዩ ክፍተቶች መሆናቸው በመድረኩ ተነስቷል፡፡
በውይይቱ ላይ የማጠቃለያ ሀሳብ የሰጡት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደገለፁት በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ላይ የታየውን ትብብር እና በጋራ የመልማት ቁርጠኝነት በሌሎች ፕሮጀክቶች መድገም እንደሚገባ ገልፀዋል፡፡
የፕሮጀክቱ መጠናቀቅ የኢትዮጵያ የማንሰራራት ዘመን ማሳያ መሆኑን ዋና ሥራ አስፈፃሚው ጠቅሰዋል።
የህብረተሰቡን የኃይል ፍላጎት ጥያቄ አስተማማኝ በሆነ መልኩ ለማሟላት የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማቶች ግንባታ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ዋና ሥራ አስፈፃሚው በማረጋገጥ የኃይል አቅርቦትን ተደራሽ ለማድረግ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልገሎት ጋር በጋራ እየተሰራ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
ሙስናን በመዋጋት የተቋሙን መልካም ሥምና ዝና በማስጠበቅ ረገድ ሁሉም የሥራ አመራር እና ሠራተኛ የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣም አሳስበዋል፡፡
በውይይቱ ላይ ከተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች በሚመለከታቸው የዘርፍ ሥራ አስፈፃሚዎች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሐምሌ 8 ቀን 2017 ዓ.ም
15 553
ተቋሙ የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈፃፀም መገምገም ጀመረ
.....///.....
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ አመራሮችና ሠራተኞች የተቋሙን የ2017 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈፃፀም በተቋሙ የስብሰባ አዳራሽ መገምገም ጀምረዋል።
የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ የግምገማ መርሃ-ግብሩን ሲያስጀምሩ እንደተናገሩት በጀት ዓመቱ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት መጠናቀቅ ለዓለም ህዝብ የተበሰረበት ነው።
የግድቡ መጠናቀቅ የሁሉም የተቋሙ የሥራ አመራሮች እና ሠራተኞች እንዲሁም የመንግሥት ቁርጠኝነት የታየበት መሆኑን ተናግረዋል።
እንደ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ በተቋሙ የ12 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም እና ተቋሙን በቀጣይ ማሻሻል በሚቻልባቸው ጉዳዮች ላይ ውይይት ይደረጋል።
በ2018 በጀት ዓመት የበለጠ ውጤት ለማምጣት በሚቻልባቸው የትኩረት አቅጣጫዎች ላይ የጋራ መግባባት ለመፍጠር ሁሉም የበኩሉን ድርሻ እንዲወጣ ጥሪ አቅርበዋል።
በአፈፃፀም ውይይቱ ላይ ሁሉም አመራሮችና ሠራተኞች ለተቋሙ ውጤታማነት ንቁ ተሳትፎ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው ዋና ሥራ አስፈፃሚው አሳስበዋል።
ግምገማው በተቋሙ የስትራቴጂክ ዕቅድ የትኩረት መስኮች በሆኑት የአስተዳደርና የኦፕሬሽን ልህቀት፣ የማይበገርና አስተማማኝ የመሠረተ ልማት ግንባታዎች፣ የፈጠራና የዲጂታል ሽግግር እንዲሁም በሰው ሃብት ልማት ላይ ባለፉት 12 ወራት በተከናወኑ አበይት ተግባራት ላይ ያተኩራል።
በአፈፃፀም ግምገማው ላይ የተቋሙን የ12 ወራት የዕቅድ አፈፃፀም ጠንካራና ደካማ ጎኖች፣ የተገኙ መልካም አጋጣሚዎች እና ያጋጠሙ ችግሮች እንዲሁም በቀጣይ ትኩረት በሚሹ ጉዳዮች ላይ ውይይት ይካሔዳል ተብሎም ይጠበቃል።
የዕቅድ አፈፃፀም ግምገማ ከመጀመሩ አስቀድሞ ተቋሙ በጀት ዓመቱ በህይወት ላጣቸው ሠራተኞች የህሊና ፀሎት ተደርጓል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሐምሌ 8 ቀን 2017 ዓ.ም
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
