ar
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

الذهاب إلى القناة على Telegram

EEP Communication

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام EEP Communication

تُعد قناة EEP Communication (@eepcommuication) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 695 مشتركاً، محتلاً المرتبة 8 017 في فئة التكنولوجيات والتطبيقات والمرتبة 2 152 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 695 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 31 أغسطس, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 142، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 2، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 30.85‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 16.42‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 4 842 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 578 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 10.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
EEP Communication

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 01 سبتمبر, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التكنولوجيات والتطبيقات.

15 695
المشتركون
+224 ساعات
+237 أيام
+14230 أيام
أرشيف المشاركات
photo content
+2

ከፊታችን ለሚጠብቀን ከባድ ሥራ ታጥቀን ልንነሳ ይገባል .......///....... ኢትዮጵያዊያን በሰራነው ገድል ሳይሆን ከፊታችን ለሚጠብቀን ከባድ ሥራ ታጥቀን ልንነሳ እንደሚገባ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አሳስበዋል፡፡ ዶ/ር ዐቢይ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ምርቃት ላይ ባደረጉት ንግግር ከዛሬ በኋላ ዳግም ዓድዋ ጉባ ላይ በመሰራቱ የኢትዮጵያ የልመና፣ የስንፍናና የእንጉርጉሮ ዘመን አብቅቶ እንደ ልኳ የምትመዘንበት ዘመን ከፊታችን መዘርጋቱን ገልፀዋል፡፡  ኢትዮጵያ ተረጅነቷ ቀርቶ ረጂ ትሆናለች ያሉት ዐቢይ አህመድ በኢትዮጵያ የማንሰራራት ዘመን የመጀመሪያው ቀን የተገኙ ወዳጆች ኢትዮጵያ ወዳጅነት ብቻ ሳይሆን ከሀብቷ፣ ከብልጽግናዋ፣ ከተስፋዋ፣ ከእውቀቷ ከልምዷ የምታቋድሳቸው እንደምትሆን አረጋግጠዋል፡፡ "የኢትዮጵያ ብልጽግና የማይሳካ ለሚመስላቸው ለቅርብና ለሩቅ ጠላቶቻችን እኛ ኢትዮጵያዊያን የማይሞት ስም እንጅ የማይሞት አካል የለንም፤ አካላችን ሞቶ የማይሞት ስም ለማስቀረት፤ የማይሞት አሻራ ለማኖር የምንተጋ ህዝቦች ነን" ሲሉም ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተናግረዋል፡፡ ህዳሴ ጥቁሮች እንደምንችልና እንደምናሳካ በጥቁር ዘር ታሪክ የመጀመሪያው ታላቅ ሥራ  ነው ያሉት ዶ/ር ዐቢይ ህዳሴን በንግግር፣ በፎቶና በተንቀሳቃሽ ምስል ብቻ መግለጽ ስለማይቻል የህዳሴን ልክ ለመገንዘብ መላው ኢትዮጵያዊያንና አፍሪካዊውያን ግድቡን በመጎብኘት የተሰራውን ገድል እንድገነዘቡም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ ከእንግዲህ የህዳሴ ፋይል ተዘግቷል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ኢትዮጵያ በሚቀጥሉት አምስትና ስድስት ዓመታት በአጠቃላይ ከ30 ቢሊዮን ዶላር በላይ ሀብት የሚፈስባቸው የአፍሪካን ልጆች ቀና የሚያደርጉ እና የኢትዮጵያን ብልጽግና የሚያሰምሩ የተለያዩ ሜጋ ፕሮጀክቶችን ለመገንባት ዕቅድ እንዳላት አብስረዋል፡፡ የኢትዮጵያ የታሪክ እጥፋት፣ የብልጽግና መሰረት እና የማንሰራራት ዘመን ዛሬ በሁሉም አቅጣጫ መታወጁን በመጠቆም ኢትዮጵያን ለማቅናት ሁሉም በአንድ ልብና በአንድ መንፈስ በጋራ በመቆም የኢትዮጵያን ብልጽግና እውን ማድረግ እንደሚጠበቅበትም አሳስበዋል። የኢትዮጵያ ብልጽግና እውን መሆኑን ኢትዮጵያ ዳግም አደዋን ደጋግማ ለጥቁር ህዝቦች ማሳየቷ አይቀሬ ነው ያሉት ዶ/ር ዐቢይ የጥቁር ህዝቦች ከልመና በመውጣት ለመበልጸግ በአንድ ላይ ሊቆሙ እንደሚገባም ጥሪ አቅርበዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም

ግድቡ ከብሔራዊ ፕሮጀክትነት ባለፈ የፓን አፍሪካ አቅምን በተግባር ያሳየ ነው -ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ….///…. የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ከብሔራዊ ፕሮጀክትነት ባለፈ የፓን አፍሪካ አቅምን በተግባር ያሳየና የአፍሪካ መር መሰረተ ልማት ግንባታ መገለጫ መሆኑን የኬኒያው ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ተናገሩ፡፡ በዛሬው ዕለት የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የምርቃት ሥነ-ሥርዓት ላይ የኬንያው ፕሬዚዳንት ዊሊያም ሩቶ (ዶ/ር)፣ የጂቡቲው ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ኦመር ጊሌህ፤ የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ (ዶ/ር)፣ የደቡብ ሱዳን ፕሬዚዳንት ሳልቫኪር ማየርዴት፣ የባርባዶስ ጠቅላይ ሚኒስትር ሚያ አሞር ሞትሊ፣ የኢስዋቲኒ ጠቅላይ ሚኒስትር ሩሴል ሚሶ ድላሚኒ፣ የአፍሪካ ሕብረት ሊቀመንበር መሀመድ አሊ ዩሱፍ፣ በተባበሩት መንግስታት የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን ዋና ፀሐፊ ክላቨር ጋቴቴ እና ሌሎችም ተገኝተዋል። በምርቃት ሥነሥርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ እንደተናገሩት የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ምርቃት ትልቅ ታሪካዊ አንድምታ ያለው መሆኑን እና አፍሪካ የራሷን እጣ ፈንታ በራሷ የመወሰን አቅም እንዳላት የሚያሳይ ታላቅ ፕሮጀክት ነው፡፡ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የምህንድስና ሥራ ሳይሆን አፍሪካ የራሷን መጻኢ እድል በራሷ መወሰን እንደምትችል የሚያሳይ በመሆኑ የኢትዮጵያ ሕዝብ እና መንግስት ለዚህ ታሪካዊ ስኬት እንኳን ደስ አላችሁ ለማለት እወዳለሁ ብለዋል። አፍሪካውያን የራሳቸውን የብልጽግና መሻት በራሳቸው ማካሳት እንደሚችሉም የሚያመላክት መሆኑን የጠቆሙት ፕሬዝዳንቱ ፕሮጀክቱ የአፍሪካ ቀንድ እና የናይል ተፋሰስ ሀገራት ለጋራ ትብብር ያለንን ቁርጠኝነት በግልጽ እያሳየን መሆኑንም በንግግራቸው አንስተዋል፡፡ ኢትዮጵያ በኢነርጂ ራሷን ለመቻል እና ኢኮኖሚዋን ለመለወጥ እያደረገች ያለውን ጥረትም አድንቀዋል። የደቡብ ሱዳን ፕሬዝዳንት ሳልቫኪር  ማየርዲት በበኩላቸው ግድቡ ሕዝብ በተባበረ ክንድ ምን መስራት እንደሚችል ያሳየ የአንድነትና የመስዋዕትነት ምልክት መሆኑን ገልፀዋል፡፡ የደቡብ ሱዳን ሕዝብና መንግስት ከኢትዮጵያውያን ጋር የጋራ ታሪክ እና ሕልም ያላቸው መሆኑን ጠቅሰው ለግድቡ ግንባታ መጠናቀቅ እንኳን ደስ አላችሁ ብለዋል፡፡ የባርባዶስ ጠቅላይ ሚኒስትር ሚያ አሞር ሞትሊ በበኩላቸው የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የአድዋ ድል ተምሳሌት ሆኖ በኢንጅነሪንግ ጥበብ ዳግም የተገለጠበት መሆኑን ጠቁመዋል፡፡ ግድቡ ኢትዮጵያውያ ለመላው አፍሪካውያን መቻላቸውን ያሳዩበት ፕሮጀክት መሆኑንም አብራርተዋል፡፡ ሌሎችም መሪዎችም የግድቡ ግንባታ መጠናቀቅ ለአፍሪካና ለቀጠናው የሚኖረውን በጎ ሚና በማውሳት የእንኳን ደስ ያላችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

ገደሉን ተሻግረን በሕዳሴ ገድል አትመናል   - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ….///….. የገጠሙንን ፈተናዎችና ችግሮች ተጋፍጠን ገደሉን ተሻግረን የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታን በማጠናቀቅ ገድል አትመናል ሲሉ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ተናገሩ፡፡ ጠቅላይ ሚኒስቴሩ ይህን የተናገሩት የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ምርቃት ላይ ባደረጉት ንግግር ነው፡፡ ሕዳሴ የትላንት ቁጭት ማሰሪያ የመጭው ንጋት ማብሰሪያ እንዲሁም ለመላ ኢትዮጵያውያን ብቻ ሳይሆን ለጥቁር ሕዝቦች ሁሉ ታሪክ ሆኖ የሚኖር ገድል ነው ብለዋል፡፡ ኢትዮጵያ ሕዳሴን የሰራችው የታችኛውን ተፋሰስ ሀገራት ጨምሮ አፍሪካውያንን በኃይል ለማስተሳሰር እንጂ የጎረቤት ሃቅን ለማስቀረትና ለመጉዳት አለመሆኑንም አረጋግጠዋል፡፡ ስለሕዳሴ በመናገር ጊዜ አናባክንም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የሕዳሴን ግድብ የሚስተካከል ለሠላማዊ ዓላማ ብቻ የሚውል የኒኩሌር ኃይል ማመንጫን ጨምሮ የአየር ማረፊያ ግንባታ፣ የማዳበሪያ እና የጋዝ ፋብሪካዎችን ሥራ በቅርቡ እንደምታስጀምርም ተናግረዋል፡፡ የኢትዮጵያ የማንሰራራት ዘመን በሁሉም አቅጣጫ በሕዳሴ መጀመሩንም አብስረዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+1

በግድብ ግንባታ ላይ አበርክቶ የነበራቸው አመራሮች ተሸለሙ፤ …....///…..... በታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ ምርቃት ላይ በግድብ ግንባታው ወቅት በአመራርነት አበርክቶ የነበራቸው አመራሮች በጠቅላይ ሚኒስቴር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የክብር ኒሻን ተሸልመዋል፡፡ የክብር ኒሻን የተሸለሙት  ኢንጂነር ኤፍሬም ወልደኪዳን አማካለኝ  ከህዳር 2004 ዓ.ም ጀምሮ ጥር 14 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ የፕሮጀክቱ ምክትል ሥራ አስኪያጅ፣ ኢንጂነር ከማል አህመድ ሱለይማን ከሚያዚያ 2013 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ የፕሮጀክቱ የኦፕሬሽን ሥራ አስኪያጅ አቶ በላቸው ካሳ ወልዴ በምክትል ሥራ አስኪያጅ ማዕረግ የፕሮጀክቱ ሳይት አስተባባሪ ኢንጂነር ክፍሌ ሆሮ የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ ናቸው፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የዐባይ ልጆችን በአንድ ጥላ ስር የሚያሰባስብ ግዙፍ ፕሮጀክት ነው -ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ …..///…… የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ የታላቁ የኢትዮጵያ
ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የዐባይ ልጆችን በአንድ ጥላ ስር የሚያሰባስብ ግዙፍ ፕሮጀክት ነው -ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ …..///…… የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ፕሬዝዳንት ታዬ አጽቀሥላሴ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ምርቃትን አስመልክቶ ባስተላለፉት የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት ኢትዮጵያውያን ያላቸውን የማደግ መሻት በላባቸው፣ በእንባቸው፣ በደማቸው እና በክብራቸው ያሳኩበት ታላቅ ሀገራዊ ፕሮጀክት ነው ብለዋል። ህዳሴ ግድብ የዐባይ ልጆችን አንድ የሚያደርግ የኢትዮጵያውያን የፅናት ሽልማት ነው ያሉት ፕሬዝዳንቱ ግድቡ የኢትዮጵያ የቀጣይ ጊዜ ታላላቅ ስኬቶች ጅማሮ ነው ሲሉም በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው አስፍረዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የመላ ኢትዮጵያውያን የላብ፣ የደም፣ የእንባ ጠብታ ድምር ውጤት ነው! 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethio
+2
ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የመላ ኢትዮጵያውያን የላብ፣ የደም፣ የእንባ ጠብታ ድምር ውጤት ነው! 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ምርቃት እየተካሄደ ነው ….///…. ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ኃይል ማመንጫ ግድብ ምርቃት ሥነ-ሥርዓት በይፋ እየተከናወነ ይገኛል፡፡ በምርቃት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)፣ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህን ጨምሮ የአሁንና የቀድሞ የፌደራል መንግስት ከፍተኛ ባለሥልጣናት እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡ በተጨማሪም በምርቃት ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የአፍሪካ ህብረት ሊቀመንበር መሀመድ ዓሊ የሱፍ፣ የኬንያው ፕሬዝዳንት ዊሊያም ሩቶ ፣ የሶማሊያው ፕሬዝዳንት ሀሰን ሼክ መሀሙድ፣ የጅቡቲው ፕሬዚዳንት ኢስማኤል ኦማር ጊሌህን ጨምሮ ሌሎችም የሀገራት መሪዎች እና ተወካዮች እንዲሁም የተለያዩ ቀጣናዊ ፣ አህጉራዊና ዓለምአቀፋዊ ተቋማት ኃላፊዎች ተገኝተዋል። የክብር እንግዶቹ የግድቡን የተለያዩ ክፍሎች እና የኃይል ማመንጫ ቤቶቹን ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን ተርባይኖቹንም በይፋ ሥራ አስጀምረዋል። በፕሮጀክቱ ስፍራ የተገነባውን ሀውልትም መርቀዋል። እኛም የምርቃት ሥነ-ሥርዓቱን በመከታተል መረጃዎችን የምናደርሳችሁ ይሆናል፡፡ ላለፉት 14 ዓመታት በግንባታ ላይ የቆየው ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በ13 ተርባይኖች 5 ሺ 150 ሜጋ ዋት ኃይል የማመንጨት አቅም አለው፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

photo content
+8

የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሰለ ግድብ ምርቃት ድባብ በከፊል 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም

ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ የመቻል ትዕምርት ነው ….///…. ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በኢትዮጵያ ልጆች ጥሪት፣ ላብ፣ ዕውቀት እና ደም የተገነባ የመቻል ትዕምርት መሆኑን የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን አገልግሎት ገለፀ፡፡ አገልግሎቱ የግድቡን ምርቃት አስመልክቶ በሰጠው መግለጫ እንደገለፀው የግድቡ ግንባታ ተጠናቆ ለምርቃት መብቃቱ ኢትዮጵያ የተፈጥሮ ሀብቷን በፍትሐዊነት በመጠቀም የታላቁ ግድብ ባለቤት እንጂ የወንዙ ባለቤት ብቻ አለመሆኗን ዐቢይ ማሳያ ነው፡፡ ህዳሴ የኢትዮጵያ የተሰናሰለ ብዝኃነት አቅም የታየበት፣ በየክፍለ ዘመኑ የዓለምን ታሪክና ፖለቲካ የሚቀይር ተምሳሌታዊ ጥረትና ድል ከኢትዮጵያ እንደሚመነጭ ያስመሰከረ ነውም ብሏል፡፡ ኢትዮጵያውያን ህልማቸዉን ከማሳካት የሚያስቆማቸዉ አንዳች ምድራዊ ኃይል እንደሌለ በግድቡ አሳይተዋል ያለው አገልግሎቱ የውኃ ፍትኃዊ አጠቃቀምን “ከህዳሴ ግድብ በፊት እና በኋላ፣ የአፍሪካ ፖለቲካ ከህዳሴ ግድብ በፊት እና በኋላ፣ ዓለምአቀፍ ዲፕሎማሲ ከህዳሴ ግድብ በፊት እና በኋላ” ብሎ መክፈል የሚችል ታላቅ ድል የተመዘገበበት መሆኑንም አብራርቷል፡፡ ህዳሴ የኢትዮጵያን የመልማት አቅም እና የአፍሪካዊያን ራስን የመቻል ብስራት እንዲሁም የታዳሽ ኃይል በማመንጨት በካይ የኃይል ምንጮችን የሚያስቀር በኢትዮጵያውያን የጋራ ጥረት የተሳካ ልዩ ፕሮጀክት መሆኑንም ገልጿል፡፡ ግድቡ የታችኛው ተፋሰስ ሀገራት በትነት ይባክን የነበረዉን ውኃ በመቆጣጠር እና ዓመቱን ሙሉ ከድንገተኛ ጎርፍ የፀዳ የተመጠነ ውኃ እንዲያገኙና ግድቦቻቸዉ በደለል እንዳይሞሉ የሚያደርግ መሆኑንም አመልክቷል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

ስንተባበር እንጠነክራን! በአንድ ልብ አስበን አንድ ቃል ስንናገር እንደመጣለን! በጋራ ስንሰራ ሀገር እንለውጣለን! ይህ ዛሬ በታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ያሳየነው እውነታ ነው። ከነበርንበት አንሰራርተናል። በአንድነት ጸንተን የጀመርነውን ፈጽመናል። የዚህ ታሪክ ሰሪ ትውልድ አካል ከመሆን በላይ የሚያኮራ ምን ነገር ይኖር ይሆን! የግድቡን ግንባታና ይህን ግንባታ በላይነት የመራውን ተቋም በኃላፊነት መምራት በተገኘው ውጤት እጅግ በጣም ደስ ብሎኛል። ስሜቴ በቃላት ከምገልፀው በላይ ነው። ለተቋማችን ሠራተኞች፣ የማኔጅመንት አባላት፣ የሥራ አመራር ቦርድ እና ለመላው ኢተረዮጵያውያን እንኳን ደስ አለን! እንኳን ደስ አላችሁ እላለሁ! አሸብር ባልቻ(ኢንጂነር) የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

የውስጣዊ ፍስሃ፥ ደስታ፣ እንባ–ሲቃ፣ ሳቅ፣ ብርሃን የዘመናት የቁጭት ስሜት፣ የስኬት ተድላ፤ አሁናዊ የሚሰማኝ ስሜት!! በቅድሚያ፥ የሀገሬ ኢትዮጵያ የኔ ትውልድ ዓድዋ፣ የላቀ የታሪክ ምዕራፍ–ታሪክ ቀያሪ  ጉዞ አካል ላደረገኝ  ፈጣሪ ተመስገን! 🙏🏾 የዓመታት ምኞት፥ የዘመናት ፅኑ ሕልም፣ የመጪው ትውልድ ደማቅ ብርሃን እውን ሆኖ በአዲስ ዓመት መባቻ ከላቀ ገፀ-በረከት ጋር አዲስ ዓመቱን ስንቀበል፥ ድርብ ደስታ ነው። እንኳን ደስ አለን፥ እንኳን አደረሰን። ለመላው ኢትዮጵያዊያን እና ትውልደ ኢትዮጵያዊያን ወገኖቼ፥  እንኳን ደስ አለን፥ እንኳን ደስ አላችሁ።  እንኳን በደስታ ሲቃ ለምንቀበለው አዲስ ዓመት አደረሳችሁ። እኛ የዚህ ዘመን ትውልድ፥ ለትውልድ የምናወርሰው መቻልን፣ ብርታትን እና የልማት አርበኝነትን ነው። የተጣመመ ትርክት አቃንተን፥ በዕዳ  የተረከብነውን ለውጠን ወረት እና ምንዳን እናስረክባለን:: እንኳን ደስ አለን! አብርሃም በላይ (ዶ/ር) የመስኖና ቆላማ አካባቢ ሚኒስትር እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ አመራር ቦርድ ሰብሳቢ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ጳጉሜን 4 ቀን 2017 ዓ.ም