EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 553 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 399,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 163 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 553 名订阅者。
根据 20 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 12,过去 24 小时变化为 7,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 26.73%。内容发布后 24 小时内通常能获得 14.92% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 157 次浏览,首日通常累积 2 320 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 10。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 21 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 553
订阅者
+724 小时
+77 天
+1230 天
帖子存档
15 553
+5
ፕሮጀክቱ የግብርና ማቀነባበሪያ ፓርኩን ወደ ሙሉ የማምረት አቅም ያሸጋግረዋል
…….///….…
የገንደ አርባ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ሲጀምር ለቡልቡላ የተቀናጀ የግብርና ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርክ ከ40 ሜጋ ዋት በላይ ኤሌክትሪክ እንደሚያቀርብ የፓርኩ ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ፡፡
ሥራ አስኪያጁ አቶ ገቢታ ኢረጎ እንደገለፁት የማከፋፈያ ጣቢያው መጠናቀቅ የግብርና ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርኩን ወደ ሙሉ የማምረት አቅም ለማሸጋገርና ለኢንቨስትመንት መፋጠን ወሳኝ ሚና ይጫወታል።
ፓርኩ ካረፈበት 271 ሄክታር መሬት ውስጥ 136 ሄክታሩ ለኢንዱስትሪዎች ልማት የሚውል መሆኑን ጠቁመው ይህንኑ ግዙፍ የልማት ቀጠና ለማንቀሳቀስ ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት እንደሚያስፈልገው ነው ያብራሩት።
ተጨማሪ ለማንበብ…
https://www.eep.com.et/?amh-news=ፕሮጀክቱ-የግብርና-ማቀነባበሪያ-ፓርኩን&lang=am
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
መጋቢት 25 ቀን 2018 ዓ.ም
15 553
+3
የኢትዮጵያ የኢነርጂ ፖሊሲ ሊከለስ ነው
........///........
ከ1986 ዓ.ም ጀምሮ በሥራ ላይ የቆየውን የኢነርጂ ፖሊሲ የሚከልስ ረቂቅ ፖሊሲ ለውይይት ቀረበ።
በውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር አቅራቢነት
በተዘጋጀው የረቂቅ ፖሊሲ ውይይት ላይ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ተሳትፈዋል።
ኢትዮጵያ ስትጠቀምበት የቆየችው የኢነርጂ ፖሊሲ አሁን ካለው የሀገሪቱና የዓለም ነባራዊ ሁኔታ ጋር እንዲጣጣም ማድረግ አስፈላጊ በመሆኑ በሥራ ላይ ያለውን ፖሊሲ መከለስ እንዳስፈለገ ተነስቷል።
በረቂቅ ፓሊሲው ላይ ስድስት ዐበይት ጉዳዮች የተካተቱ ሲሆኑ ሙያዊ ድጋፍ በመስጠትና በማማከር የሀገር ውስጥ እና ከሌሎች ሀገራት የተውጣጡ የዘርፉ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።
ተጨማሪ ለማንበብ…
https://www.eep.com.et/?amh-news=የኢትዮጵያ-የኢነርጂ-ፖሊሲ-ሊከለስ-ነው&lang=am
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
መጋቢት 25 ቀን 2018 ዓ.ም
15 553
በሁለቱ ዞኖች ላይ ተቋርጦ የቆየው ኃይል ዳግም ተመልሷል
......///.......
በአባ ባለ 132 ኪሎ ቮልት ተንቀሳቃሽ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ አቅራቢያ አንድ የእንጨት ምሰሶ በመውደቁ ምክንያት ተቋርጦ የቆየው ኤሌክትሪክ ዳግም መመለሱን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የደቡብ ምዕራብ ሪጅን አስታወቀ፡፡
የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ጌታሁን ሲሳይ እንዳስታወቁት ወደ ማከፋፈያ ጣቢያው ኃይል በሚያደርሰው አንድ ገቢ የእንጨት ምሰሶ መስመር ላይ ችግር በመፈጠሩ ምክንያት በዳውሮ እና ኮንታ ዞኖች ኃይል ተቋርጦ ቆይቷል፡፡
ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታም ቀደም ሲል ስድስት የእንጨት ምሰሶዎችን ይጠቀም የነበረውን መስመር በአንድ አዲስ የእንጨት ምሰሶ አማካኝነት በአቅራቢያው ከሚገኝ የኃይል ተሸካሚ ምሰሶ ጋር በማገናኘት ኤሌክትሪክ ማቅረብ መቻሉን ተናግረዋል፡፡
እንደ አቶ ጌታሁን ገለፃ የተበጣጠሱ የኤሌክትሪክ ሽቦዎች እና የተበላሹ የኮንዳክተር ሽቦ ማያያዣዎችን በመቀየር በአካባቢው ሊደርሱ የሚችሉ አደጋዎችን መከላከል ተችሏል፡፡
አሁን ላይ በዞኖቹ ተቋርጦ የቆየውን የኤሌክትሪክ ኃይል ሙሉ በሙሉ መመለስ ተችሏል ያሉት ሥራ አስኪያጁ በጥገና ሥራው ላይ ርብርብ ሲያደርጉ ለነበሩ የጥገና ባለሙያዎች እንዲሁም ችግሩ እስኪፈታ ድረስ በትግዕስት ለጠበቁ ደንበኞች ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
መጋቢት 25 ቀን 2018 ዓ.ም
15 553
🇪🇹 የኢነርጂ ዘርፍ ሪፎርም - ከተቋማዊ ዕዳ ወደ ፋይናንስ ጥንካሬ! 🇪🇹
የሀገራችን የኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት የሆነው የኃይል ዘርፍ፣ ባለፉት ጥቂት ዓመታት ውስጥ ታሪካዊ የሚባል የሪፎርም እና የፋይናንስ ማሻሻያ እርምጃዎችን አከናውኗል። ከተከናወኑት የሪፎርም ሥራዎች መካከል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የነበረበትን ከፍተኛ የዕዳ ጫና በመቀነስ ረገድ የተከናወኑ ሥራዎች ተጠቃሾች ናቸው፡፡
🔍 ከሪፎርሙ በፊት የነበረው ተግዳሮት ምን ነበር?
ከ2010 ዓ.ም በፊት የኃይል ዘርፉ በከፍተኛ የንግድ ብድር ዕዳ የተዘፈቀ ነበር፤ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሂሳብ መዝገብ የዕዳና የካፒታል ጥምርታ (Debt-to-equity ratio) ከፍተኛ ልዩነት እንዳለው የሚያሳይ ነበር። ይህ ዕዳ ተቋሙን ለፋይናንስ ሥጋት ከመዳረግ ባለፈ ብድርም ሆነ የግል የኃይል አምራቾችን (IPPs) ለመሳብ እንቅፋት ሆኖ ቆይቷል።
🇪🇹 🚀 የተወሰዱ ታሪካዊ የማሻሻያ እርምጃዎች፦
1. የሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ (HGER)
ማክሮ ኢኮኖሚውን ለማረጋጋትና የኢነርጂ ዘርፉን የፋይናንስ ዘላቂነት ለማረጋገጥ የተቀረጸ ስልታዊ አጀንዳ ነው።
2. የዕዳና ሀብት አስተዳደር ኮርፖሬሽን (LAMC)
የመንግሥት የልማት ድርጅቶችን ዕዳ "ለመውሰድ" መንግሥት ባቋቋመው የዕዳና ሀብት አስተዳደር ኮርፖሬሽን (LAMC) አማካይነት የተቋሙ የሂሳብ መዝገብ (Balance sheet) መልሶ እንዲስተካከል ተደርጓል።
3. የዕዳ ስረዛና የካፒታል እድገት
በ2016 ዓ.ም ብቻ ወደ 217 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዕዳ ከተቋሙ የሂሳብ መዝገብ እንዲሰረዝ ተደርጓል። ይህም የተቋሙን የተከፈለ ካፒታል ከ319 ቢሊዮን ወደ 589 ቢሊዮን ብር በማሳደግ በሁለት እጥፍ እንዲጨምር አድርጓል።
4. አስደናቂ የዕዳ ቅናሽ
በመንግሥት ጣልቃ ገብነት የተቋሙ አጠቃላይ የፋይናንስ ዕዳ በ2015 ዓ.ም መጨረሻ ከነበረበት 355 ቢሊዮን ብር በ2016 ዓ.ም መጨረሻ ወደ 128 ቢሊዮን ብር ዝቅ እንዲል ተደርጓል።
💡 የዚህ ለውጥ ፋይዳ ምንድነው?
የተቋሙ የፋይናንስ ጤንነት መመለስ ተቋሙ የብድር ተዓማኒነቱን መልሶ እንዲያገኝ አድርጎታል። ከኪሳራ ወደ ትርፋማነት እንዲሸጋገርም አድርጓል፡፡ በዚህም እንደ ዓለም ባንክ ካሉ ተቋማት ጋር እንደ "ASCENT" ባሉ ግዙፍና አዳዲስ ንጹሕ የኃይል ተደራሽነት መርሀ ግብሮች ላይ ለመሳተፍ በር ከፍቶለታል።
የኢትዮጵያን የኃይል ተደራሽነት ለማሳድና የሀገራችንን የኢንዱስትሪ ሽግግር ለማፋጠን ጠንካራና በፋይናንስ የዳበረ የኃይል ተቋም መገንባት አማራጭ የሌለው ጉዳይ ነው!
15 553
+7
በሪጅኑ የጥገና ሥራዎችን በራስ አቅም የማከናወን ልምምድ እያደገ ነው፤
.....///…...
የጥገናና የማስፋፊያ ሥራዎችን በሪጅኑ አቅም የማከናወን ልምምድ ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ መምጣቱን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የምስራቅ 2 ሪጅን ገለጸ።
በሪጅኑ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የኦፕሬሽንና ጥገና ሥራ አስኪያጅ አቶ ወርቁ ሙሉ እንደገለጹት ምስራቅ 2 ሪጅን አምስት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን እንዲሁም 719 ኪሎ ሜትር ርዝመትና 1 ሺህ 643 ከፍተኛ የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ያሉት የማስተላለፊያ መስመሮችን ያስተዳድራል።
በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት በሁሉም ማከፋፈያ ጣቢያዎችና ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ የቅድመ መከላከል፣ ድንገተኛና በዕቅድ ላይ የተመሠረቱ የጥገና የፍተሻ ሥራዎች መከናወናቸውን ገልፀዋል።
ተጨማሪ ለማንበብ…
https://www.eep.com.et/?amh-news=በሪጅኑ-የጥገና-ሥራዎችን-በራስ-አቅም-የ&lang=am
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
መጋቢት 25 ቀን 2018 ዓ.ም
15 553
🌋 ከጥልቁ ምድር የሚገኝ የማይነጥፍ የኃይል በረከት - የከርሰ ምድር እንፋሎት (Geothermal)! 🇪🇹⚡️
ኢትዮጵያ በምስራቅ አፍሪካ ስምጥ ሸለቆ ውስጥ በመገኘቷ ከፍተኛ የከርሰ ምድር እንፋሎት ወይም የጂኦተርማል ኃይል እምቅ አቅም ካላቸው ጥቂት ሀገራት አንዷ ናት። ይህንን በመጠቀም ረገድ እንደ ሀገር የአሉቶ ላንጋኖ የጂኦተርማል ፕሮጀክት እንደ ዓይን ከፋች ፕሮጀክት ተደርጎ የሚወሰድ ቢሆንም በዘርፉ ብዙ መስራት እንዳለብን የሚያሳይ ተደርጎ የሚወሰድ ነው፡፡ በአሉቶ እስከ 70 ሜጋ ዋት ለማመንጨት የማስፋፊያ ፕሮጀክት እየተከናወነ ሲሆን እንደ ቱሉ ሞዬ እና ኮርቤቲ ባለ ሳይቶች የግል አልሚዎች በዘርፉ ለመሰማራት የተለያዩ ሥራዎችን በመስራት ላይ ይገኛሉ፡፡
⚙️ የኃይል አመራረት ሂደቱ እንዴት ነው?
የጂኦተርማል ኃይል አመራረት ሂደት ተፈጥሮንና ቴክኖሎጂን አቀናጅቶ የሚሠራ አስደናቂ ሂደት ነው፡፡ ዋና ዋና ሂደቶቹም፡-
1. ቁፋሮ፦
በመጀመሪያ ጥልቅ የሆኑ ጉድጓዶች (Wells) እስከ ሦስት ሺህ ሜትር ድረስ ወደ መሬት ውስጥ ይቆፈራሉ።
2. የእንፋሎት መውጣት፦
ከመሬት በታች ያለው ከፍተኛ ሙቀት በውስጥ ያለውን ውሃ ወደ ትኩስ እንፋሎት ይቀይረዋል። ይህ ከፍተኛ ግፊት ያለው እንፋሎት በትቦዎች አማካይነት ወደ ላይ ይወጣል።
3. ተርባይን ማሽከርከር፦
ወደ ላይ የወጣው እንፋሎት ግዙፍ ተርባይኖችን በከፍተኛ ፍጥነት ያሽከረክራል።
4. ኤሌክትሪክ ማመንጨት፦
ተርባይኑ ሲሽከረከር ከጄነሬተር ጋር በመገናኘት ሜካኒካዊ ኃይልን ወደ ኤሌክትሪክ ኃይል ይቀይራል።
5. መልሶ መጠቀም፦
ጥቅም ላይ የዋለው እንፋሎት ተመልሶ ወደ ውኃነት እንዲቀየር ተደርጎ ወደ መሬት ውስጥ ተመልሶ በመርፌ (Injection) መልክ ይገባል፤ ይህም ሂደቱ ተደጋጋሚና ቀጣይነት እንዲኖረው ያደርጋል።
🌟 የጂኦተርማል ኃይል ዋና ዋና ጥቅሞች፦
🌋 ከአየር ንብረት ጋር አለመለዋወጡና አስተማማኝነቱ (Reliability)፦
እንደ ውኃ ግድቦች በዝናብ እጥረት፣ ወይም እንደ ፀሐይና ነፋስ በአየር ሁኔታ አይቀያየርም። በቀን 24 ሰዓት፣ በዓመት 365 ቀናት ያለ ማቋረጥ ኃይል ይሰጣል።
🌋 ታዳሽና ንጹሕ ኃይል መሆኑ፦
ምንም ዓይነት ተረፈ ምርት ወይም በካይ ጋዝ ስለማያመነጭ ለአካባቢ ጥበቃና ለ"አረንጓዴ ኢኮኖሚ" ግንባታ ተመራጭ ነው።
🌋 ዘላቂና የማይነጥፍ የኃይል ምንጭ መሆኑ፦
የከርሰ ምድር እንፋሎት ሁልጊዜም ያለ በመሆኑ ለዘመናት አገልግሎት የሚሰጥ ዘላቂ የኃይል ምንጭ ነው።
🌋 አነስተኛ ቦታ የሚፈልግ መሆኑ፦
ከውኃ ግድቦች ወይም ከሶላር ፓርኮች አንጻር ሲታይ በጣም አነስተኛ በሆነ የቆዳ ስፋት ላይ ሰፊ ኃይል ማመንጨት ይቻላል።
ሀገራችን በአሉቶ ላንጋኖ፣ በቱሉ ሞዬ እና በኮርቤቲ አካባቢዎች የጀመረቻቸው የጂኦተርማል ፍለጋና የማልማት ፕሮጀክቶች እውን ሲሆኑ የኃይል አቅርቦታችንን ይበልጥ አስተማማኝ እንደሚያደርጉት ይታመናል።
የኢትዮጵያ ብርሃን ከምድር ጥልቀት እስከ ሰማይ ከፍታ ይበራል!
15 553
+2
የተቋሙ የህጻናት ማቆያና መንከባከቢያ ማዕከል እውቅና ተሰጠው
…….///……..
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለሴት ሠራተኞቹ ምቹ የሥራ አካባቢ ለመፍጠር ያቋቋመው የህጻናት ማቆያና መንከባከቢያ ማዕከል “የሞዴል ማዕከል” እውቅና ማግኘቱን በተቋሙ የሴቶችና ማህበራዊ ጉዳዮች መምሪያ አስታወቁ፡፡
የመምሪያው ዳይሬክተር ወ/ሮ ሌንሴ ኢደኤ እንዳስታወቁት የህጻናት ማቆያና መንከባከቢያ ማዕከሉ በሴቶችና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስቴር እውቅና ከተሰጣቸው ሰባት ሞዴል የህጻናት ማቆያና መንከባከቢያ ማዕከላት መካከል ግንባር ቀደም ሆኗል፡፡
የማዕከሉ ከባቢያዊ ሁኔታ፣ የህጻናት መመገቢያ፣ መኝታና፣ መጫወቻ ክፍሎች ስፋት፣ የመጸዳጃና የመታጠቢያ ክፍሎች ሁኔታ እና የህጻናት ቅበላ መስፈርት እንዲሁም የሞግዚትና የህጻናት ንጽጽር ተቋማቱ የተወዳደሩባቸው መስፈርቶች እንደነበሩ ተናግረዋል፡፡
ተጨማሪ ለማንበብ…
https://www.eep.com.et/?amh-news=የተቋሙ-የህጻናት-ማቆያና-መንከባከቢያ-ማ&lang=am
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
መጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ም
15 553
⚡️ ኢትዮጵያ - የምሥራቅ አፍሪካ የኃይል ማማ (Power Hub)! 🇪🇹
ሀገራችን ኢትዮጵያ በተፈጥሮ የታደለችው የታዳሽ ኃይል ጸጋ እጅግ ግዙፍ መሆኑን ያውቃሉ?
እውነታው ምን ይላል?
📊 ኢትዮጵያ ያላት እምቅ አቅም፦ ከውሃ፣ ከፀሐይ፣ ከነፋስና ከከርሰ ምድር እንፋሎት (Geothermal) ምንጮች እስከ 150 ጊጋ ዋት (GW) ኃይል የማመንጨት አቅም አላት።
🏗 እስካሁን የለማው፦ ካለን አጠቃላይ አቅም ውስጥ እስካሁን ማልማት የቻልነው 9.5 ጊጋ ዋት (GW) ብቻ ነው። ይህ ማለት ካለን ጸጋ ጥቅም ላይ የዋለው 6.33% ብቻ ሲሆን፣ ቀሪው 93.67% ገና ያልተነካና ለልማት የሚጠበቅ መሆኑን ያሳያል።
ይህ አቅም ለሀገራችን ምን ትርጉም አለው?
1. 🏭 የኢንዱስትሪ ሽግግርን ይደግፋል፤
ለአምራች ፋብሪካዎቻችንና ለኢንዱስትሪ ፓርኮች አስተማማኝና ርካሽ ኃይል ለማቅረብ ያስችላል።
2. 💰 የውጭ ምንዛሪ ግኝትን ያሰፋል፤
ለጎረቤት ሀገራት ኃይል በመሸጥ ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ በማግኘት የመሰረተ ልማት ተደራሽነት ለማረጋገጥ ተጨማሪ አቅም ይፈጥርላታል።
3. 🌿 የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታን ያግዛል፤
ከብክለት ነጻ የሆነና የአካባቢ ጥበቃን ያገናዘበ ታዳሽ የኃይል ምንጭ ለመገንባት የተጀመረውን ሀገራዊ እንቅስቃሴ እውን ለመሆን ያግዛል።
4. 💡 ለትውልድ ብርሃን ይሆናል፤
የኤሌክትሪክ አገልግሎት ያልደረሳቸውን የገጠር አካባቢዎች ተጠቃሚ ማድረግ ያስችላል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይህንን እምቅ አቅም በስፋት በማልማት፣ ኢትዮጵያን የአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል ለማድረግ በቁርጠኝነት ይሰራል!
ኢትዮጵያ በታዳሽ ኃይል ትበራለች!
ምስል በአርቴፊሻል ኢንተሌጀንስ የበለፀገ
15 553
+1
ተቋሙ የትራንስፖርትና የነዳጅ አስተዳደሩን በማዘመን ውጤት እያመጣ ነው
………///….….
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተሽከርካሪና የነዳጅ አስተዳደርን ለማዘመንና ብክነትን ለመቀነስ የዘረጋቸው አዳዲስ አሠራሮች ውጤት እያመጡ መሆኑን በተቋሙ የተሽከርካሪ አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ፡፡
የቢሮው ሥራ አስኪያጅ አቶ ዋለ ታምሬ እንደገለፁት ተቋሙ በአሁኑ ወቅት በ27 ዋና ዋና መስመሮች ላይ የትራንስፖርት አገልግሎት እየሰጠ ሲሆን ከነዚህም ውስጥ 26ቱ በራሱ ተሽርካሪዎች የሚሸፈኑ ናቸው፡፡
ከእነዚህ መስመሮች መካከል 16ቱ ሙሉ በሙሉ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች መሆናቸውን ጠቅሰው ይህም በተቋሙ የትራንስፖርትና የነዳጅ አጠቃቀም ሥርዓት ላይ አዲስ ምዕራፍ ከመክፈቱም ባሻገር በዓመት ለነዳጅ ይወጣ የነበረውን ከ18 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ ለማዳን አስችሏል ብለዋል፡፡
ተጨማሪ ለማንበብ…
https://www.eep.com.et/?amh-news=ተቋሙ-የትራንስፖርትና-የነዳጅ-አስተዳደ&lang=am
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
መጋቢት 24 ቀን 2018 ዓ.ም
15 553
የምስራቅ ሪጂን አንድ ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን (ማርች 8) አከበረ
.......///.......
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የምስራቅ ሪጂን አንድ "የሴቶች ድምፅ ለእኩልነትና ለበለፀገች ኢትዮጵያ" በሚል መሪ ቃል ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀንን (ማርች 8) በልዩ ሁኔታ አክብሯል። በበዓሉ አከባበር ላይ የሪጂኑ ዳይሬክተር አቶ ወርዲ መሀመድን ጨምሮ ሌሎች አመራሮችና ሠራተኞች ተገኝተዋል።
አቶ ወርዲ በመርሃ-ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት በሪጂኑ የሚገኙ ሴት አመራሮችና ሠራተኞች ለድርጅቱ ውጤታማነት እያበረከቱት ያለው አስተዋጽኦ ከፍተኛ መሆኑን ገልፀው በቀጣይም የሴቶችን ተሳታፊነትና ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማሳደግ ተቋሙ በትኩረት እንደሚሠራ አረጋግጠዋል።
የዘንድሮው ዓለም አቀፍ የሴቶች ቀን በዓለም አቀፍ ደረጃ ለ115ኛ ጊዜ፣ በሀገራችን ደግሞ ለ50ኛ ጊዜ በልዩ ልዩ ዝግጅቶች ተከብሮ ውሏል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
መጋቢት 23 ቀን 2018 ዓ.ም
15 553
በስርቆት ምክንያት የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ወድቋል
……..///…….
በአማራ ክልል ማዕከላዊ ጎንደር ዞን እንፍራንዝ ከተማ ልዩ ስሙ ሰብሀ ገብርኤል አካባቢ በስርቆት ምክንያት በከፍተኛ የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ላይ ጉዳት መድረሱን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ምዕራብ ሪጅን አስታወቀ።
በሪጅኑ የማስተላለፊያ መስመሮች ጥገና ሥራ አስኪያጅ አቶ በላይነህ ልጅዓለም እንዳስታወቁት በተፈፀመው ስርቆት ምክንያት ከባህርዳር- አዘዞ ቁጥር ሁለት በተዘረጋ አንድ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ላይ ጉዳት ደርሷል፡፡
በዚህም ምክንያት የኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ የብረት ምሰሶው መውደቁን ተናግረዋል።
በአሁኑ ወቅት ከባህርዳር - አዘዞ ቁጥር ሁለት የተዘረጋው መስመር ኃይል ማስተላለፍ ማቋረጡን ሥራ አስኪያጁ ገልፀዋል።
ይሁን እንጂ በባህርዳር - አዘዞ ቁጥር አንድ ባለ 230 ኪሎ ቮልት መስመርን እንደ አማራጭ በመጠቀም በማዕከላዊ እና ሰሜን ጎንደር ዞኖች ስር ለሚገኙ ከተሞች ኤሌክትሪክ እየቀረበ ይገኛል ብለዋል።
እንደ አቶ በላይነህ የወደቀውን የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶ በአፋጣኝ መልሶ በመትከል በአጭር ጊዜ ውስጥ የኃይል አቅርቦቱን ወደነበረበት ለመመለስ የተቀናጀ ጥረት ይደረጋል፡፡
በኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶው ላይ የስርቆት ወንጀል የፈፀሙ አካላትን ተከታትሎ ለህግ ለማቅረብ እየተሰራ እንደሆነ ነው ያብራሩት።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
መጋቢት 23 ቀን 2018 ዓ.ም
15 553
+1
በዳወሮ እና ኮንታ ዞኖች የኤሌክትሪክ ኃይል እቅርቦት ተቋርጧል
......///.......
የጅማ- አባ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ለጊዜው ምክንያቱ ባልታወቀ ምክንያት ከመጋቢት 22 ቀን 2018 ሌሊት 9፡15 ጀምሮ ኃይል ማስተላለፍ ማቋረጡን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የደቡብ ምዕራብ ሪጅን አስታወቀ፡፡
የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ጌታሁን ሲሳይ እንዳስታወቁት የማስተላለፊያ መስመሩ ኃይል ማስተላለፍ ማቋረጡን ተከትሎ በዳውሮና በኮንታ ዞኖች ከትላንት ሌሊት ጀምሮ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ተቋርጧል፡፡
መስመሩ የተቋረጠበትን ምክንያት በመለየት ለችግሩ መፍትሔ ለመስጠት የሪጅኑ የጥገና ባለሙያዎች በመስመሩ ላይ የፍተሻ ሥራዎችን እያከናወኑ እንደሚገኙም ጠቅሰዋል፡፡
የማስተላለፊያ መስመሩ ዳግም ኃይል ማስተላለፍ እስኪጀምር ድረስ ኃይል በተቋረጠባቸው አካባቢዎች የሚገኙ ደንበኞች በትዕግስት እንዲጠብቁ አቶ ጌታሁን ጥሪ አቅርበዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
መጋቢት 23 ቀን 2018 ዓ.ም
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
