uk
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Відкрити в Telegram

EEP Communication

Показати більше

📈 Аналітичний огляд Telegram-каналу EEP Communication

Канал EEP Communication (@eepcommuication) у мовному сегменті Амхарська є активним учасником. На даний момент спільнота об'єднує 15 691 підписників, посідаючи 8 014 місце в категорії Технології та додатки та 2 155 місце у регіоні Ефіопія.

📊 Показники аудиторії та динаміка

З моменту свого створення невідомо, проект продемонстрував стрімке зростання, зібравши аудиторію у 15 691 підписників.

За останніми даними від 29 серпня, 2026, канал демонструє стабільну активність. Хоча за останні 30 днів спостерігається зміна кількості учасників на 137, а за останні 24 години на 5, загальне охоплення залишається високим.

  • Статус верифікації: Не верифікований
  • Рівень залученості (ER): Середній показник залученості аудиторії становить 34.17%. Протягом перших 24 годин після публікації контент зазвичай збирає 17.11% реакцій від загальної кількості підписників.
  • Охоплення публікацій: В середньому кожен допис отримує 5 362 переглядів. Протягом першої доби публікація в середньому набирає 2 685 переглядів.
  • Реакції та взаємодія: Аудиторія активно підтримує контент: середня кількість реакцій на один пост – 11.

📝 Опис та контентна політика

Автор описує ресурс як майданчик для висловлення суб'єктивної думки:
EEP Communication

Завдяки високій частоті оновлень (останні дані отримано 30 серпня, 2026), канал підтримує актуальність та високий рівень охоплення публікацій. Аналітика показує, що аудиторія активно взаємодіє з контентом, що робить його важливою точкою впливу в категорії Технології та додатки.

15 691
Підписники
+524 години
+77 днів
+13730 день
Архів дописів
ወድቀው የነበሩ የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎችን መልሶ የመትከል ሥራ ተጀመረ ......///...... በስርቆት ምክንያት ወድቀው የነበሩትን 17 የአዘዞ-ሸኽዲ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላ
+5
ወድቀው የነበሩ የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎችን መልሶ የመትከል ሥራ ተጀመረ ......///...... በስርቆት ምክንያት ወድቀው የነበሩትን 17 የአዘዞ-ሸኽዲ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር የብረት ምሰሶዎችን ከአንድ ዓመት በኋላ መልሶ የመትከል ሥራ መጀመሩን የሰሜን ምዕራብ ሪጅን አስታወቀ፡፡   በሪጅኑ የማስተላለፊያ መስመሮች ጥገና ሥራ አስኪያጅ አቶ በላይነህ ልጅዓለም እንዳስታወቁት የወደቁትን የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች በአፋጣኝ መልሶ በመትከል በአካባቢው አስተማማኝ የኤሌክትሪክ አቅርቦት እንዲኖር ጥረት እየተደረገ ይገኛል፡፡   በአሁኑ ወቅት የሁለት የኃይል ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎችን መልሶ የመትከል ሥራ መጠናቀቁን ገልፀው የቀሪዎቹን ተከላ ለማከናወን በአካባቢው ያለው ዝናባማ የአየር ሁኔታ እንቅፋት መፍጠሩን ተናግረዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ወድቀው-የነበሩ-የኃይል-ተሸካሚ-የብረት-ም 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም

የተቋሙ ተልዕኮ እና ዓለም አቀፍ ግቦች ......///...... በፈጠራ፣ በቴክኖሎጂ፣ በተሞክሮ፣ በፍትሃዊነት እና በቁርጠኝነት አስተማማኝ እና ዘላቂ የኤሌክትሪክ ኃይል ማቅረብ ተልዕኳችን ነው! ይህ
የተቋሙ ተልዕኮ እና ዓለም አቀፍ ግቦች ......///...... በፈጠራ፣ በቴክኖሎጂ፣ በተሞክሮ፣ በፍትሃዊነት እና በቁርጠኝነት አስተማማኝ እና ዘላቂ የኤሌክትሪክ ኃይል ማቅረብ ተልዕኳችን ነው! ይህንን ተልዕኳችንን ከኮፕ 32 (COP32) ዓለም አቀፍ የአየር ንብረት ግቦች ጋር በማጣጣም የአረንጓዴ ልማት በተግባር እንዲረጋገጥ የበኩላችንን አሻራ እያሳረፍን ነው። 🌱⚡️ #COP32 #EEPMission #ዘላቂኢነርጂ #GreenDevelopment #ClimateAction 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም

የኃይል ሽያጭ እና የቀጣናው ትስስር ......///...... በሕግ በተሰጠን ሥልጣን መሠረት ኃይልን በጅምላ የመሸጥ ኃላፊነታችንን በመጠቀም፣ ለጎረቤት ሀገራት ንፁህ ታዳሽ ኃይል እያቀረብን ነው። ተ
የኃይል ሽያጭ እና የቀጣናው ትስስር ......///...... በሕግ በተሰጠን ሥልጣን መሠረት ኃይልን በጅምላ የመሸጥ ኃላፊነታችንን በመጠቀም፣ ለጎረቤት ሀገራት ንፁህ ታዳሽ ኃይል እያቀረብን ነው። ተቋማችን የተገበራቸውን ተሞክሮዎች በኮፕ 32 (COP 32) ዓለም አቀፍ መድረክ ላይ የሚያስተጋባ ሲሆን በዚህም ኢትዮጵያ የምሥራቅ አፍሪካን አየር ንብረት በመጠበቅ ረገድ ቀዳሚ ሚናዋን እየተወጣች መሆኑን ያረጋግጣል። #COP32 #የኃይልሽያጭ #RegionalIntegration #CleanEnergyEthiopia #EEP 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብ↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 7 ቀን 2018 ዓ.ም

በፕሮጀክት አመራርና አፈጻጸም ላይ መሠረታዊ ለውጥ ማምጣት እንደሚገባ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ አሳሰቡ ......///...... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሚገነባቸው የኃይል መሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች አፈፃፀም ላይ መሠረታዊ ለውጥ ማምጣት እንደሚገባ የተቋሙ ዋና ሥራ አሥፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ አሳሰቡ፡፡ ዋና ሥራ አሥፈጻሚው ይህንን ያሳሰቡት የተቋሙን የኃይል መሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች አፈፃፀም ግምገማ ማጠቃለያ ላይ ባደረጉት ንግግር ነው፡፡ ፕሮጀክቶች የተሻለ የግንባታ አፈፃፀምና የፋይናንስ ቁመና እንዲኖራቸው ለማድረግ የተቋሙ የሥራ አመራር ቦርድና በየደረጃው የሚገኙ የሥራ ኃላፊዎች ክትትልና ድጋፍ እያደረጉ መሆኑን ዋና ሥራ አሥፈጻሚው ገልፀዋል። በበጀት ዓመቱ የተሻሉ ውጤቶች ቢመዘገቡም በአንዳንድ ፕሮጀክቶች ላይ በታዩ ደካማ የአፈፃፀም ክፍተቶች ምክንያት የግንባታ መዘግየቶች መታየታቸውን ኢንጂነር አሸብር ጠቁመዋል። ተቋሙ አብዛኛውን በጀቱን ለፕሮጀክቶች ግንባታ የሚያውል በመሆኑ የፕሮጀክቶች አፈፃፀም መዘግየትና የሚያጋጥሙ ፈተናዎች ለከፍተኛ ወጪና ኪሳራ እየዳረጉት መሆኑን አስገንዝበዋል። በአሁኑ ወቅት አፈፃፀማቸው እየተገመገሙ ያሉ አንዳንድ ፕሮጀክቶች የተጠናከረ ክትትልና ድጋፍ ተደርጎላቸው ቢሆን ኖሮ በታቀደላቸው ጊዜ ተጠናቀው አገልግሎት መስጠት መጀመር እንደነበረባቸውም አስታውሰዋል። በመሆኑም እየተገነቡ በሚገኙ ፕሮጀክቶች የፋይናንስ አጠቃቀም፣ የሥራ ጥራትና ቅልጥፍና የተቋሙ መለያ እንዲሆኑ አመራሩ የጋራ ርዕይ ሰንቆ ለላቀ ውጤት መረባረብ እንዳለበት ዋና ሥራ አሥፈጻሚው አሳስበዋል። በተቋሙ ሥራ አመራር ቦርድ እና በየደረጃው በሚገኙ የሥራ ኃላፊዎች ሊፈቱ የሚገባቸውን ችግሮች በመለየት፣ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በተቀናጀ መልኩ በመሥራት ውጤት ማስመዝገብ እንደሚገባም አብራርተዋል። እንደ ኢንጂነር አሸብር ገለፃ የአመራሩን የፕሮጀክት አስተዳደር አቅም በማሳደግ ከመረጃ አያያዝ፣ ከሪፖርት አቀራረብ እና ከሀብት አጠቃቀም ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመፍታት ተቋሙ ትኩረት ሰጥቶ ይሠራል። በበጀት ዓመቱ ከፕሮጀክት አፈፃፀም ጋር ተያይዞ ያጋጠሙ ችግሮችንና ተግዳሮቶችን ለመቅረፍም በቀጣይ ነባራዊ ሁኔታውን ያገናዘበ ዕቅድ ይዞ መንቀሳቀስ እንደሚገባ ገልፀው አመራሩ ለዚህ ልዩ ትኩረት እንዲሰጥ አሳስበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 6 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+9

በፕሮጀክቶቹ አፈጻጸም ላይ የሚስተዋሉ ችግሮች በአስቸኳይ ሊፈቱ ይገባል .....///..... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች እየገነባቸው የሚገኙ የኃይል መሰረተ ልማት ፕሮጀክ
+9
በፕሮጀክቶቹ አፈጻጸም ላይ የሚስተዋሉ ችግሮች በአስቸኳይ ሊፈቱ ይገባል .....///..... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች እየገነባቸው የሚገኙ የኃይል መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶችን አፈፃፀም እየገመገመ ይገኛል። የፕሮጀክቶቹ አፈፃፀም በተቋሙ የኢንጅነሪንግና ኮንስትራክሽን ቢዝነስ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አሥፈፃሚ ኢንጅነር ውድነህ የማነ፣ በጀነሬሽን ቢዝነስ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አሥፈጻሚ ኢንጅነር ኤፍሬም ወልደ ኪዳን እና በትራንስሚሽን ቢዝነስ ዘርፍ ተወካይ ሥራ አሥፈጻሚ ኢንጅነር ደስታዓለም ኃይሉ በኩል ቀርቧል። ኢንጅነር ደስታዓለም እንደገለፁት በአሁኑ ወቅት የተለያዩ የኪሎ ቮልት መጠን ያላቸው 29 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ እና ማስተላለፊያ መስመሮች በተለያዩ የግንባታ ምዕራፎች ላይ ይገኛሉ። ከእነዚህ ውስጥ ዘጠኙ በጥሩ አፈፃፀም ላይ የሚገኙና በተቀመጠላቸው የጊዜ ገደብ ይጠናቀቃሉ ተብለው የሚጠበቁ መሆናቸውን አብራርተዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=በፕሮጀክቶቹ-አፈጻጸም-ላይ-የሚስተዋሉ-ች&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 6 ቀን 2018 ዓ.ም

ተቋሙ የፕሮጀክቶች አፈጻጸምን እየገመገመ ነው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚያስተዳድራቸውን የኃይል መሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች አፈጻጸም መገምገም ጀምሯል። በኃይሌ ግራንድ ሆቴል እየተካሄደ በሚገኘው የግምገማ መድረክ ላይ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጅነር አሸብር ባልቻን ጨምሮ ሁሉም የማኔጅመንት አባላት፣ የፕሮጀክት ዳይሬክተሮችና ሥራ አስኪያጆች ተገኝተዋል። በበጀት ዓመቱ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን፣ የአይሻና የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫዎችን ጨምሮ በርካታ የማከፋፈያ ጣቢያዎችንና ማስተላለፊያ መስመሮችን አጠናቆ በማስመረቅ ረገድ ትልልቅ ስኬቶች መመዝገባቸው በግምገማው መጀመሪያ ላይ ተገልጿል፡፡ ይህ የግምገማ መድረክ ባለፉት 11 ወራት በፕሮጀክት አፈጻጸም ረገድ የታዩ ጥንካሬዎችንና ያጋጠሙ ተግዳሮቶችን በመለየት ቀጣይ አቅጣጫዎችን ለማስቀመጥ ያለመ ነው። እንደ ተቋም ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው ጊዜ፣ በጀትና የጥራት ደረጃ ለማጠናቀቅ ከሪፖርት ባለፈ በተግባር የተደገፈ የቅርብ ክትትልና ድጋፍ ለማድረግ መሰል መድረኮች አስፈላጊ መሆናቸውም ተብራርቷል። በአሁኑ ወቅት በግንባታ ሂደት ላይ የሚገኙ ሌሎች ፕሮጀክቶች አፈጻጸም በዝርዝር እየቀረበ የሚገኝ ሲሆን እኛም ሂደቱን እየተከታተልን ተጨማሪ መረጃዎችን የምናደርሳችሁ ይሆናል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 6 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+9

#COP32 ከፍተኛ የሆኑ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችን እና ማከፋፈያ ጣቢያዎችን በብቃት መገንባትና ማስተዳደር ኃላፊነታችን ነው! ንፁህ ኃይልን ያለምንም ብክነት ለደንበኞች ለማድረስ የምናደርገው ጥ
#COP32 ከፍተኛ የሆኑ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችን እና ማከፋፈያ ጣቢያዎችን በብቃት መገንባትና ማስተዳደር ኃላፊነታችን ነው! ንፁህ ኃይልን ያለምንም ብክነት ለደንበኞች ለማድረስ የምናደርገው ጥረት የካርቦን አሻራን ለመቀነስ ትልቅ አስተዋጽኦ አለው። #COP32 #የኃይልማስተላለፊያ #EEP #Infrastructure 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 6 ቀን 2018 ዓ.ም

ማከፋፈያ ጣቢያዎችን በራስ አቅም የመጠገን ሥራ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል ......///...... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የደቡብ ምዕራብ ሪጅን በሚገኙ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የሚያጋጥሙ የቴክኒክ
+7
ማከፋፈያ ጣቢያዎችን በራስ አቅም የመጠገን ሥራ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል ......///...... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የደቡብ ምዕራብ ሪጅን በሚገኙ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የሚያጋጥሙ የቴክኒክ ችግሮችን በጣቢያዎቹ የውስጥ አቅም የመፍታት አቅም ከጊዜ ወደ ጊዜ እየተጠናከረ መምጣቱን ሪጅኑ ገለፀ የሪጅኑ ዳይሬክተር ተወካይ አቶ ቢኒያም ታደሰ እንደገለፀት በማከፋፈያ ጣቢያዎች ለሚያጋጥሙ ድንገተኛ ችግሮች ፈጣን ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል ስልታዊ አሠራር ተዘርግቷል። ጣቢያዎቹ የጥገና ሥራዎችን በራሳቸው አቅም ማከናወን እንዲችሉ ለባለሙያዎች ተከታታይ የአቅም ግንባታ ስልጠናዎች የተሰጡ ሲሆን አስፈላጊ የመለዋወጫ ዕቃዎችም እንዲሟሉ መደረጉን ገልፀዋል። በዚህም መሰረት ከሪጅኑ ማዕከል ርቀው በሚገኙ እንደ መቱ፣ ጋምቤላ፣ ሚዛን እና በደሌ ባሉ ማከፋፈያ ጣቢያዎች አብዛኞቹ ድንገተኛ የጥገና ሥራዎች በአሁኑ ወቅት በየጣቢያው ባለሙያዎች እየተከናወኑ መሆኑን አብራርተዋል ። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ማከፋፈያ-ጣቢያዎችን-በራስ-አቅም-የመጠገ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 5 ቀን 2018 ዓ.ም

"የአፍሪካ የታዳሽ የኃይል ማዕከል መሆን!" 🇪🇹✨ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይህንን ታላቅ ራዕይ ሰንቆ በዓለም አቀፉ የኮፕ 32 (COP32) አረንጓዴ መድረክ ላይ የሀገራችንን የማይበገር የታዳ
"የአፍሪካ የታዳሽ የኃይል ማዕከል መሆን!" 🇪🇹✨  የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይህንን ታላቅ ራዕይ ሰንቆ በዓለም አቀፉ የኮፕ 32 (COP32) አረንጓዴ መድረክ ላይ የሀገራችንን የማይበገር የታዳሽ ኃይል ጉዞ ለዓለም ያበስራል። #COP32 #የአፍሪካየኃይልማዕከል #EEP #ታዳሽኃይል

ሪጅኑ አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ የሚያስችሉ ሥራዎችን እያከናወነ ነው ........///....... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የደቡብ ምዕራብ ሪጅን ለደንበኞች አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረ
+9
ሪጅኑ አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ የሚያስችሉ ሥራዎችን እያከናወነ ነው ........///....... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የደቡብ ምዕራብ ሪጅን ለደንበኞች አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ የሚያስችሉ የተለያዩ ሥራዎችን እያከናወነ እንደሆነ የሪጅኑ ዳይሬክተር ተወካይ አቶ ቢኒያም ታደሰ ገልፀዋል ። ተወካዩ እንደተናገሩት በሪጅኑ ከሚገኙ 12 የማከፋፈያ ጣቢያዎች መካከል 10 ተጨማሪ ደንበኞችን የማስተናገድ ሙሉ አቅም ስላላቸው በአሁኑ ወቅት ለሚቀርቡ የኃይል ጥያቄዎች በአግባቡ ምላሽ እየተሰጠ ይገኛል። በአሁኑ ወቅት ከሁሉም የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች በአጠቃላይ ከ134 ሜጋ ዋት በላይ ኃይል ለደንበኞች እየቀረበ መሆኑንም አብራርተዋል። ሪጅኑ በተለያዩ ምክንያቶች እያደገ ለሚሄደው የኃይል ፍላጎት በአስተማማኝ መልኩ ምላሽ ለመስጠት በጣቢያዎቹ ላይ የአቅም ማሳደግ እና የመቆጣጠሪያ ብሬከሮችን የማዘመን ሥራዎችን በትኩረት እያከናወነ ይገኛል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ሪጅኑ-አስተማማኝ-ኃይል-ለማቅረብ-የሚያስ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 4 ቀን 2018 ዓ.ም

ዓለምን ከብክለት የመታደግ ብሔራዊ ኃላፊነት! ብዙ ሀገራት ከከሰልና ከነዳጅ ኃይል ለመላቀቅ በሚታገሉበት በዚህ ዘመን፣ ኢትዮጵያ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አማካኝነት ከካርቦን ነፃ (Zero-Carb
ዓለምን ከብክለት የመታደግ ብሔራዊ ኃላፊነት! ብዙ ሀገራት ከከሰልና ከነዳጅ ኃይል ለመላቀቅ በሚታገሉበት በዚህ ዘመን፣ ኢትዮጵያ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አማካኝነት ከካርቦን ነፃ (Zero-Carbon) የሆነ የኤሌክትሪክ ኃይል በማመንጨት ረገድ ቀዳሚ ናት። ኮፕ 32ን ስናስተናግድ፣ ተቋማችን የዓለምን የአየር ንብረት ሙቀት ለመቀነስ እያበረከተ ያለውን ተጨባጭ አስተዋጽኦ በኩራት እናሳያለን። እኛ የምናመነጨው ኃይል ሀገርን ያበራል፣ አየር ንብረትን ግን አይበክልም! ⚡️ ንፁህ አየር፣ አስተማማኝ ኃይል! #ZeroCarbon #Decarbonization #ClimateAction #COP32Host #EEPGreen 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 3 ቀን 2018 ዓ.ም

ተቋሙ እያከናወናቸው ያሉ የኃይል ተደራሽነት ሥራዎች የማህበረሰቡን ቅሬታ እየፈቱ ነው .......///....... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በደቡብ ምዕራብ ክልል እያከናወናቸው ያሉ የኃይል ማከፋፈ
+7
ተቋሙ እያከናወናቸው ያሉ የኃይል ተደራሽነት ሥራዎች የማህበረሰቡን ቅሬታ እየፈቱ ነው .......///....... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በደቡብ ምዕራብ ክልል እያከናወናቸው ያሉ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ተደራሽነት ሥራዎች ማህበረሰቡ ከኃይል አቅርቦት ጋር በተያያዘ ለሚያነሳቸው ቅሬታዎች ተጨባጭ መፍትሔ እየሰጡ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የደቡብ ምዕራብ ሪጅን አስታወቀ የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ ብርሃኑ ገብሬ እንደገለፁት ሪጅኑ ከማሻ፣ ቦንጋ፣ አባ እና ሚዛን ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኃይል በመቀበል በደቡብ ምዕራብ ክልል ለሚገኙ ስድስት ዞኖች የኤሌክትሪክ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። በአሁኑ ወቅት ከሚዛን ማከፋፈያ ጣቢያ በስተቀር ከሌሎች ጣቢያዎች በቂ የኃይል አቅርቦት እያገኘ በመሆኑ ደንበኞችን በአግባቡ ማገልገል መቻሉን ዳይሬክተሩ ተናግረዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የኃይል-አቅርቦቱ-የፋብሪካው-ማሽኖች-ደህ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 3 ቀን 2018 ዓ.ም

የኃይል አቅርቦቱ የፋብሪካው ማሽኖች ደህንነታቸው ተጠብቆ ምርታማ እንዲሆኑ እያስቻለ ነው …….//…… በሃይንከን ኢትዮጵያ ስር ለሚገኘው ለበደሌ ቢራ ፋብሪካ እየቀረበ ያለው የኤሌክትሪክ ኃይል የፋብሪ
+9
የኃይል አቅርቦቱ የፋብሪካው ማሽኖች ደህንነታቸው ተጠብቆ ምርታማ እንዲሆኑ እያስቻለ ነው …….//…… በሃይንከን ኢትዮጵያ ስር ለሚገኘው ለበደሌ ቢራ ፋብሪካ እየቀረበ ያለው የኤሌክትሪክ ኃይል የፋብሪካው ማሽኖች ደህንነታቸው ተጠብቆ ምርታማ እንዲሆኑ እያስቻለ መሆኑን የፋብሪካው ሥራ አስኪያጅ አቶ ተገኑ ዲባባ ገለፁ። ሥራ አስኪያጁ እንደገለፁት ፋብሪካው ቀጥታ ከበደሌ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው ለብቻው በተዘረጋ በባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመር ኃይል እያገኘ ነው። ይህም ለምርት እንቅስቃሴው የሚያስፈልገውን በቂ ኃይል ሳይቆራረጥ በአግባቡ እንዲያገኝ አስችሎታል። አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት መኖሩ ማሽነሪዎች ደህንነታቸው ተጠብቆ ለረጅም ጊዜ አስፈላጊውን አገልግሎት እንዲሰጡ በማስቻል የፋብሪካው ምርታማነት ከጊዜ ወደጊዜ እንዲጨምር አድርጎታልም ብለዋል ። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የኃይል-አቅርቦቱ-የፋብሪካው-ማሽኖች-ደህ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 3 ቀን 2018 ዓ.ም

ተቋሙ የምስራቅ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪሲቲ ማጠናከሪያ ፕሮጀክትን ለማስጀመር ከአካባቢው መስተዳድሮች ጋር ተወያየ .....///..... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በመላው አገሪቱ የሚያከናውናቸው የኤሌክት
+9
ተቋሙ የምስራቅ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪሲቲ ማጠናከሪያ ፕሮጀክትን ለማስጀመር ከአካባቢው መስተዳድሮች ጋር ተወያየ .....///..... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በመላው አገሪቱ የሚያከናውናቸው የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ግንባታዎች ማህበረሰቡን ባቀፈ መልኩ የሚሰሩ መሆናቸውን አስታወቀ ተቋሙ ይህንን የገለፀው የምስራቅ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪሲቲ ማጠናከሪያ ፕሮጀክትን በቅርቡ ለማስጀመር የሚያስችል የጋራ ውይይት ከአካባቢው የመስተዳድር አካላት ጋር ባካሄደበት ወቅት ነው። ውይይቱ በዋናነት ከይዞታ አሰጣጥ ጋር ተያይዘው የነበሩ የቆዩ ተግዳሮቶችን በመፍታት ግንባታውን በፍጥነት ለማስጀመር በሚያስችሉ የጋራ መፍትሔዎች ላይ ያተኮረ ነው። ተቋሙ ከሐረር ከተማ በቅርብ ርቀት ላይ ለሚገነባው ማከፋፈያ ጣቢያ የሚሆን ቦታ ከአሁን በፊት ተሰጥቶት የነበረ ቢሆንም ወደ ኋላ የተመለሰበትን ምክንያት የአካባቢው የመስተዳድር አካላት ማብራሪያ እንዲሰጡበት በውይይቱ ላይ ጠይቋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ተቋሙ-የምስራቅ-ኢትዮጵያ-ኤሌክትሪሲቲ-ማ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ም

"ያለ ኤሌክትሪክ ኃይል ሃገራዊ ዕድገትን ማረጋገጥ አይታሰብም" አቶ ከሊል ሽፋ .....///..... ያለ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት የሚከናወን የልማት እንቅስቃሴም ሆነ ሃገራዊ ዕድገት
+7
"ያለ ኤሌክትሪክ ኃይል ሃገራዊ ዕድገትን ማረጋገጥ አይታሰብም"  አቶ ከሊል ሽፋ .....///..... ያለ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት የሚከናወን የልማት እንቅስቃሴም ሆነ ሃገራዊ ዕድገት እንደሌለ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተቋማዊ ደህንነትና አስተዳደራዊ ጉዳዮች መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ከሊል ሽፋ ገለፁ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የምሥራቅ አንድ ሪጅን የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ደህንነትን ለማስጠበቅ ከአካባቢው የመስተዳድር፣  የፍትህና ፀጥታ አካላት እና ከማህበረሰቡ ተወካዮች ጋር በድሬዳዋ ከተማ የግንዛቤ ማስጨበጫ ውይይት አካሂዷል። ውይይቱ በከፍተኛ ኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ የሚፈፀሙ ስርቆቶችን እና መሰረተ ልማቶቹ በተገነቡበት ቦታዎች የሚስተዋሉ ህገ-ወጥ ግንባታዎችን እንዴት ማስቆም እንደሚቻል ግንዛቤ ለመፍጠርና የጋራ የመፍትሔ አቅጣጫዎችን ለማስቀመጥ ያለመ ነው። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ያለ-ኤሌክትሪክ-ኃይል-ሃገራዊ-ዕድገትን-ማ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ም

በሪጅኑ ከሚገኙ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች በቂ ኃይል እያገኘን ነው ......///...... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ደቡብ ምዕራብ ሪጅን ሥር ከሚገኙ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ለኅብረተሰቡና ለኢንዱስትሪዎች አገልግሎት የሚውል በቂ ኃይል እየቀረበ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጅማ ሪጅን አስታወቀ:: በአገልግሎቱ የጅማ ሪጅን የማሰራጫ መስመሮች ኦፕሬሽንና ጥገና ክፍል ኃላፊ አቶ ሻምበል አድማሱ እንደገለፁት ሪጅኑ ከወልቂጤ ማከፋፈያ ጣቢያ በአንድ ወጪ መስመር የሚያገኘውን ጨምሮ በአጠቃላይ ከስድስት ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኃይል እየተቀበለ ይገኛል። የጅማ ሪጅን ከእነዚህ ማከፋፈያ ጣቢያዎች የሚነሱ 22 የኤሌክትሪክ ማሰራጫ መስመሮችን በመጠቀም በሪጅኑ ለሚገኙ ደንበኞች በሙሉ የኤሌክትሪክ ኃይል አገልግሎት በማቅረብ ላይ መሆኑን ኃላፊው ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማከፋፈያ ጣቢያዎችን የቁጥጥር ሥርዓት የማዘመን ሥራዎችን በስፋት እያከናወነ ይገኛል። ይህ የማዘመን ሥራ በመስመሮቹ ላይ የሚከሰቱ ብልሽቶችንና መቆራረጦችን በፍጥነት በመለየትና ለመፍታት ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው አቶ ሻምበል አስረድተዋል። ይህ የቴክኖሎጂ ማሻሻያ በተለይም እንደ ሊሙ ለመሳሰሉ ከማከፋፈያ ጣቢያ በረጅም ርቀት ለሚጓዙ የኃይል ማሰራጫ መስመሮች ላይ ብልሽቶች ሲፈጠሩ ችግሩን በቀላሉ ተቆጣጥሮ ለመጠገን ትልቅ እገዛ ያደርጋል ብለዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ እያከናወናቸው ያሉ የአቅም ማሳደግና የማዘመን ሥራዎች በአገልግሎቱ ደንበኞች የሚነሱ ቅሬታዎችን እየቀረፉ እንደሚገኝ የጠቀሱት ኃላፊው ተቋሙ በቀጣይም ይህን በጎ ጅምር አጠናክሮ እንደሚቀጥል እምነታቸውን አቶ ሻምበል ገልፀዋል። ለኅብረተሰቡ አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ ሲባል ሁለቱ ተቋማት በኃይል አቅርቦት ላይ ችግሮች ሲያጋጥሟቸው የሰው ኃይላቸውንና ማሽነሪዎቻቸውን በማስተባበር በጋራና በትጋት እየሠሩ እንደሚገኙ ኃላፊው ተናግረዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+6

ማከፋፈያ ጣቢያዎች ለጅማ ከተማዋና አካባቢው ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መነቃቃት ጉልህ አስተዋፅኦ እያበረከቱ ነው በጅማ ከተማ የሚገኙት ሁለቱ የኤሌክትሪክ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ለከተማዋና ለአካባቢው ሁለንተናዊ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት መነቃቃት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከቱ እንደሚገኙ የጣቢያዎቹ የሥራ ኃላፊዎች ገለፁ። የጅማ ቁጥር አንድ ባለ 132 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ኃላፊ አቶ ናትናኤል ወርቅነህ እንደተናገሩት ጣቢያው ከመስከረም 1980 ዓ.ም ጀምሮ የጅማ ቁጥር ሁለት ማከፉፈያ ጣቢያ አገልግሎት መስጠት እስከጀመረበት እስከ ነሐሴ 2007 ዓ.ም ድረስ ለከተማዋና ለአካባቢው ብቸኛ የኃይል አቅራቢ በመሆን አገልግሏል። ይሁንና የቁጥር ሁለት ማከፋፈያ ጣቢያ ወደ ሥራ ከገባ በኋላ የተወሰኑ የከተማዋ አካባቢዎች ከቁጥር ሁለት እንዲያገኙ በመደረጉ አሁን ላይ ጣቢያው 90 በመቶ የሚሆነውን የከተማዋን የኃይል አቅርቦት እየሸፈነ ይገኛል ብለዋል። ጣቢያው ባለ 20 እና ባለ 16 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያላቸው ሁለት ትራንስፎርመሮች፣ አንድ ባለ 132፣ ዘጠኝ ባለ 15 እና ስድስት ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመሮች አሉት። አሁን ላይ በአራት ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመሮች አማካኝነት ለጅማ ከተማ እስከ 18 ሜጋ ዋት ኃይል እያቀረበ እንደሚገኝ የገለፁት አቶ ናትናኤል በሦስት ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመሮች ደግሞ ለሊሙ ገነትና ለሾቤ ወረዳዎች እንዲሁም ለጅማ ኢንዱስትሪ ፓርክ እስከ 8 ሜጋ ዋት ኃይል በማቅረብ ላይ ይገኛል። ይህም ለአካባቢው ኢኮኖሚ መነቃቃት ትልቅ መሠረት ጥሏል። ቀሪዎቹ አምስት ባለ 15 እና ሦስት ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመሮች ለታለመው የስማርት ሲቲ ፕሮጀክትና ለሌሎች አዳዲስ አገልግሎቶች በመጠባበቂያነት መዘጋጀታቸውንም ኃላፊው አክለዋል። በአሁኑ ወቅት የባለ 20 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመሩ የመጫን አቅሙ በመሙላቱ ተጨማሪ ደንበኞችን ማስተናገድ እንደማይችል ጠቁመው የባለ 16 ሜጋ ቮልት አምፒር ትራንስፎርመሩ ደግሞ ከአቅሙ 55 በመቶ በላይ  የሚሆነው ጥቅም ላይ ውሏል ብለዋል። ከቴክኖሎጂ ማሻሻያ ጋር ተያይዞ ከዘጠኝ ወር በፊት የጣቢያውን የ33 ኪሎ ቮልት የመቆጣጠሪያ ብሬከሮች ወደ ዘመናዊው የጂአይኤስ (GIS) ሥርዓት በመቀየር ከመረጃ አያያዝ እና ከኦፕሬሽን አሰራር ጋር ይስተዋሉ የነበሩ ችግሮችን መቅረፍ ተችሏል። በቀጣይም ለረጅም ዓመታት ያገለገሉትን የሲዊች ያርድ፣ የባዝ ባርና ሌሎች የጣቢያው አካላትን ማሻሻል እንደሚያስፈልግ ኃላፊው አስገንዝበዋል። የጅማ ቁጥር ሁለት ባለ 230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ኃላፊ አቶ ይልማ አበበ በበኩላቸው ጣቢያው እያንዳንዳቸው 63 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያላቸው ሁለት አዉቶ ትራንስፎርመሮች እና የ25 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ያለው አንድ ፖወር ትራንስፎርመር እንዳለው ገልፀዋል። በተጨማሪም አንድ ባለ 230 ጥምር ገቢ፣ አንድ ባለ 230 ጥምር፣ ሁለት ባለ 132 እና አምስት ባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመሮች አሉት። ጣቢያው በአሁኑ ወቅት በባለ 15 ኪሎ ቮልት ወጭ መስመሮቹ ለጅማ ከተማ ማህበረሰብ፣ ለጅማ ዩኒቨርሲቲ፣ ለውሃ አገልግሎት ተቋማት፣ ለአባ ጅፋር ቤተ መንግስት እና ለሰርቦ ከተማ እስከ 18 ሜጋ ዋት ኃይል በማሰራጨት ላይ ይገኛል። እንደ አቶ ይልማ ማብራሪያ የጣቢያው አውቶ ትራንስፎርመሮች እስከ 100 ሜጋ ዋት የመጫን አቅም ቢኖራቸውም የፖወር ትራንስፎርመሩ አቅም አነስተኛ በመሆኑ ያለውን አጠቃላይ አቅም በአግባቡ ጥቅም ላይ ማዋል አልተቻለም። ስለሆነም በአካባቢው በፍጥነት እያደገ ለመጣው የኃይል ጥያቄ ተገቢውን ምላሽ ለመስጠት እና የቁጥር ሁለት አውቶ ትራንስፎርመሮችን ሙሉ አቅም ለመጠቀም የቁጥር አንድ ባለ 20 እና የቁጥር ሁለት ባለ 25 ሜጋ ቮልት አምፔር ትራንስፎርመሮችን አቅም የማሳደግ ሥራ በዕቅድ መያዙን የሥራ ኃላፊዎቹ ጠቁመዋል። ከዚህ ጎን ለጎን የቁጥር ሁለት ማከፋፈያ ጣቢያ የመቆጣጠሪያ ሥርዓትን በጂአይኤስ (GIS) ብሬከር ለማዘመን ዕቅድ ተይዟል። የማከፋፈያ ጣቢያዎቹ በአካባቢው መኖራቸው ስማርት ከተሞች እንዲመሠረቱ፣ የኢንዱስትሪ ኢንቨስትመንት እንዲስፋፋ እና ሰፊ የሥራ ዕድል እንዲፈጠር ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን የገለፁት የሥራ ኃላፊዎቹ በቀጣይም ይበልጥ አስተማማኝና ያልተቋረጠ የኤሌክትሪክ ኃይል ለደንበኞች ለማቅረብ ከአገልግሎቱ ተቋሙ ጋር በቅንጅትና በትብብር እየተሠራ መሆኑን አስታውቀዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ.ም