EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 553 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 399,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 163 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 553 名订阅者。
根据 20 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 12,过去 24 小时变化为 7,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 26.73%。内容发布后 24 小时内通常能获得 14.92% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 157 次浏览,首日通常累积 2 320 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 10。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 21 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 553
订阅者
+724 小时
+77 天
+1230 天
帖子存档
15 553
በተሽከርካሪ አስተዳደር ላይ የሚታዩ ክፍተቶችን የማረም ሥራ እየተሰራ ነው
…….///…….
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በተሽከርካሪ አስተዳደር ላይ የሚታዩ ክፍተቶችን ለማረም ጥብቅ የማስተካከያ እርምጃዎች እየወሰደ መሆኑን በተቋሙ የተሽከርካሪ አስተዳደር ቢሮ አስታወቀ፡፡
የቢሮው ሥራ አስኪያጅ አቶ ዋለ ታምሬ እንደገለፁት ከተሽከርካሪ አስተዳደር ጋር በተያያዘ ተሽከርካሪዎችን ላልተፈቀደላቸው አካላት አሳልፎ መስጠትን ጨምሮ መመሪያን ያለማክበር እና የተቋሙን ተሸከርካሪ እንደ ግል ንብረት ያለመጠበቅ የአያያዝ ጉድለቶች እየተበራከቱ መጥተዋል፡፡
ችግሮቹን ለማረም የአያያዝ ችግር በሚፈጥሩ አሽከርካሪዎች ላይ ከሥራ ማገድን ጨምሮ ሌሎች አስተዳደራዊ እርምጃዎች እየተወሰዱ መሆኑን ነው የገለፁት።
እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ የተሸከርካሪዎችን ደህንነት ይበልጥ ለማረጋገጥ የሰርቪስ ጊዜያቸው ሳያልፍ በወቅቱ እንዲጠገኑ የማስቻል ሥራ የሁሉም ሥራ ኃላፊዎች እና አሽከርካሪዎች ኃላፊነት ሊሆን ይገባል፡፡
ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት አዳዲስ አሰራሮችን ተግባራዊ ማድረግ መጀመሩን የጠቆሙት አቶ ዋለ አዲስ ተሽከርካሪዎች ሲገዙም ሆነ ከፕሮጀክት ሲመለሱ ጥብቅ በሆነ የፍተሻ እና የርክክብ ሂደት ውስጥ እንደሚያልፉ ተናግረዋል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
መጋቢት 23 ቀን 2018 ዓ.ም
15 553
+9
የቴክኒክ ችግር የገጠመውን የበለስ ትራንስፎርመር በሌላ ቀይሮ አገልግሎት ለማስጀመር በርብርብ እየተሰራ ነው
…....///…....
በበለስ 400/132/33 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ ባጋጠመ የቴክኒክ ችግር ምክንያት ለረጅም ጊዜ ተቋርጦ የቆየውን የኃይል አቅርቦት ለመመለስ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የበለስ ኃይል ማንጫ ጣቢያ አስታወቀ፡፡
የጣቢያው ኃላፊ አቶ የወጉ ጌትዬ እንዳስታወቁት በጣቢያው ላይ 400 ኪሎ ቮልትን ወደ 132 ኪሎ ቮልት የሚቀይር 125 ሜጋ ቮልት አምፒር አቅም ባለው ትራንስፎርመር ላይ በተፈጠረ የቴክኒክ ችግር ምክንያት በመቃጠሉ ለኢንዱስትሪዎችና ለአካባቢው ነዋሪዎች የሚደርሰውን አስተማማኝ ኃይል ለዓመታት አስተጓጉሏል፡፡
ተጨማሪ ለማንበብ…
https://www.eep.com.et/?amh-news=የቴክኒክ-ችግር-የገጠመውን-የበለስ-ትራን&lang=am
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
መጋቢት 23 ቀን 2018 ዓ.ም
15 553
+3
የኃይል የማከፋፈያ ጣቢያው አገልግሎት መስጠት ጀመረ
…....///……..
የአርባምንጭ ቁጥር 2 ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የግንባታ ሥራ በተያዘለት የጊዜ ገደብ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የብሔራዊ ኤሌክትሪክ ደቡባዊ ግሪድ ማስፋፊያ ፕሮጀክት ጽ/ቤት አስታወቀ።
የፕሮጀክቱ ተወካይ ሥራ አስኪያጅ አቶ አንዱዓለም መላኩ እንደገለፁት የአርባ ምንጭ 2 ማከፋፈያ ጣቢያ ከወላይታ ሶዶ ቁጥር 2 ባለ 400/230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ ጣቢያ የማስፋፊያ ግንባታ ቀጥሎ አገልግሎት መስጠት የጀመረ የብሔራዊ ኤሌክትሪክ ደቡባዊ ግሪድ ማስፋፊያ ፕሮጀክት አንዱ አካል ነው፡፡
የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው በአርባ ምንጭ ከተማ ሊገነባ ለታሰበው የተቀናጀ የግብርና ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርክ እና በ120 ኪሎ ሜትር ወሰን ውስጥ ለሚገኙ አካባቢዎች አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ ታስቦ መገንባቱን ተናግረዋል፡፡
ተጨማሪ ለማንበብ…
https://www.eep.com.et/?amh-news=የኃይል-የማከፋፈያ-ጣቢያው-አገልግሎት-መ&lang=am
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
መጋቢት 23 ቀን 2018 ዓ.ም
15 553
+9
በአካባቢያዊና ማህበረሰባዊ እንዲሁም በሥራ ላይ ጤናና ደህንነት ጉዳዮች ዙሪያ በተከናወነ ዳሰሳ ጥናት ላይ አውደ ጥናት ተካሄደ
…....///……..
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአካባቢያዊና ማህበረሰባዊ እንዲሁም በሥራ ላይ ጤናና ደህንነት ጉዳዮች ዙሪያ በተከናወነ የዳሰሳ ጥናት ላይ አውደ ጥናት ተካሂዷል።
በአዲስ አበባ ቤስት ዌስተርን ፕላስ ሆቴል በዛሬው ዕለት በተዘጋጀው አውደጥናት ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢትዮ ፓወር አካዳሚ ዳይሬክተር ወንድወሰን ካሳ (ዶ/ር) እንደገለፁት ተቋሙ የሀገርን ልማት የሚያረጋግጡ በርካታ የኃይል መሠረተ ልማት ፕሮጀክቶችን እያከናወነ ይገኛል።
ፕሮጀክቶቹን ሲያከናውን ለማህበረሰባዊ እና አካባቢያዊ ጉዳዮች ትኩረት እንደሚሰጥ የተናገሩት ዳይሬክተሩ ጥናቱ በፕሮጀክቶች ላይ ለሚነሱ ችግሮች ቀድሞ መፍትሔ ለመስጠት በሚሰራው ሥራ ላይ የተቋሙን አቅም ለማጠናከር እንደሚያግዝ ገልፀዋል።
ተጨማሪ ለማንበብ…
https://www.eep.com.et/?amh-news=በአካባቢያዊና-ማህበረሰባዊ-እንዲሁም-በ&lang=am
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
መጋቢት 22 ቀን 2018 ዓ.ም
15 553
+7
የማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታው የሲቪል ሥራ ከ85 በመቶ በላይ ደርሷል
……..///……..
የገንደአርባ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ግንባታን በተያዘለት የጊዜ ገደብ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የፕሮጀክቱ የሲቪል ሥራዎች አስተባባሪ አስታወቁ፡፡
አስተባባሪው አቶ ገረመው ወልደ ማርያም እንደገለፁት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው መገንባት ለቡልቡላ የተቀናጀ የግብርና ምርቶች ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርክ አስተማማኝ ኤሌክትሪክ ለማቅረብ ያስችላል።
ለኢንዱስትሪ ፓርኩ ኃይል ለማቅረብ ከአራት ዓመት በፊት ሥምምነት ቢፈረምም በወቅቱ ከውጭ ምንዛሪ እጥረት ጋር በተያያዘ ግንባታው መዘግየቱን አስታውሰዋል።
ተጨማሪ ለማንበብ…
https://www.eep.com.et/?amh-news=የማከፋፈያ-ጣቢያ-ግንባታው-የሲቪል-ሥራ-ከ85&lang=am
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
መጋቢት 22 ቀን 2018 ዓ.ም
15 553
+3
ተቋማዊ ለውጡን በብቃት መምራት የሚችል አመራር ለመፍጠር እየተሰራ ነው
…….///……
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተጀመረውን ተቋማዊ ለውጥ በአግባቡ መምራት የሚችል የሥራ መሪ ለመፍጠር እየተሰራ መሆኑን የኢትዮ ፓወር አካዳሚ የአመራር ልማት ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ተናኘ መኮንን ገለጹ።
ሥራ አስኪያጇ እንደተናገሩት ተቋማዊ ለውጡን በአግባቡ ተረድቶ መምራት የሚችል አመራር ለመፍጠር የለውጥ ምንነትንና ተያያዥ ጉዳዮችን ማዕከል ያደረጉ ተከታታይ ስልጠናዎች እየተሰጡ ይገኛሉ።
ቀደም ሲል በ14 ዙሮች በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ስልጠና መሰጠቱን ያስታወሱት ወ/ሮ ተናኘ ዛሬን ጨምሮ ለአምስት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ተመሳሳይ የአቅም ግንባታ ሥልጠና መጀመሩን አስታውቀዋል።
ተጨማሪ ለማንበብ…
https://www.eep.com.et/?amh-news=ተቋማዊ-ለውጡን-በብቃት-መምራት-የሚችል-አ&lang=am
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
መጋቢት 21 ቀን 2018 ዓ.ም
15 553
+5
ፕሮጀክቱን ወደ ኦፕሬሽን በማስገባት ሀገራዊ የኃይል ስብጥርን ማስፋት እንደሚገባ ተገለፀ
……..///……..
የአሉቶ ላንጋኖ የእንፋሎት ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን በማጠናቀቅ ለኦፕሬሽን ማብቃት እንደሚገባ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጀነሬሽን ቢዝነስ ዘርፍ አስታወቀ።
በዘርፉ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ኤፍሬም ወልደኪዳን የተመራ የሥራ ኃላፊዎች እና ባለሙያዎች ቡድን በአሉቶ ላንጋኖ የእንፋሎት ጉድጓድ (Wellhead) ፕሮጀክት እና በነባሩ የአሉቶ ጂኦተርማል የኃይል ማመንጫ ጣቢያ ላይ የመስክ ምልከታ አድርጓል።
የመስክ ምልከታው የ5 የእንፋሎት ጉድጓድ ቁፋሮና የነባሩን ጣቢያ የመልሶ ጥገና ሂደት በመገምገም ቀጣይ የሥራ መመሪያዎችን ለማስተላለፍ ያለመ ነው።
ጉብኝቱ ነባር የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችን ውጤታማነት እና ደህንነት ለማሳደግ ዘርፉ የጀመረው ተሃድሶ አካል መሆኑም ተገልጿል።
ተጨማሪ ለማንበብ…
https://www.eep.com.et/?amh-news=ፕሮጀክቱን-ወደ-ኦፕሬሽን-በማስገባት-ሀገ&lang=am
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
መጋቢት 21 ቀን 2018 ዓ.ም
15 553
+6
የጉዞ አበል የአሰራር ሂደትን ወደ ዲጂታል ሥርዓት ለመቀየር እየተሰራ ነው
.........///.......
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በወረቀት እየተሰራ ያለውን የጉዞ አበል የአሰራር ሂደት ወደ ዲጂታል ሥርዓት ለመቀየር እየተሰራ መሆኑን በተቋሙ የፋይናንስ ሥራ አስፈጻሚ አስታወቁ፡፡
ሥራ አስፈጻሚው አቶ አለማየሁ መንግስቱ እንዳስታወቁት ተቋሙ የጉዞ አበልን ጨምሮ የተለያዩ የአሰራር ሂደቶችን ዲጂታላይዝድ ለማድረግ እየሰራ ይገኛል፡፡
በተቋሙ እየተተገበረ ያለውን የጉዞ አበል አሰራር ወደ ዲጂታል ሥርዓት የመቀየሩ ሥራ በሦስት ምዕራፎች ተከፋፍሎ የሚተገበር ሲሆን በመጀመሪያው ምዕራፍ በኮርፖሬት ዘርፎችና በዋና ሥራ አስፈጻሚ ስር ባሉ የሥራ ክፍሎች፣ በሁለተኛው ምዕራፍ በቢዝነስ ዘርፎች እንዲሁም በሦስተኛው ምዕራፍ በኃይል ማመንጫ ጣቢያዎችና በሪጂኖች ላይ ተግባራዊ እንደሚደረግ አስረድተዋል፡፡
ተጨማሪ ለማንበብ…
https://www.eep.com.et/?amh-news=የጉዞ-አበል-የአሰራር-ሂደትን-ወደ-ዲጂታል&lang=am
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
መጋቢት 18 ቀን 2018 ዓ.ም
15 553
+4
የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ተጠግኖ ከሁለት ዓመታት በኋላ ለአገልግሎት ዝግጁ ተደረገ
........///........
የበለስ-ጃዊ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ከሁለት ዓመታት በኋላ ተጠግኖ ዳግም ኤሌክትሪክ ለመስጠት ዝግጁ መደረጉን የሰሜን ምዕራብ ሪጅን አስታወቀ።
በሪጅኑ የማስተላለፊያ መስመሮች ጥገና ሥራ አስኪያጅ አቶ በላይነህ ልጅዓለም እንዳስታወቁት ከሁለት ዓመት በፊት በበለስ ባለ 400/132/ 33 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ ባጋጠመ የትራንስፎርመር ችግር ምክንያት የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ከአገልግሎት ውጪ ሆኖ ቆይቷል፡፡
የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ለረጅም ጊዜ ከአገልግሎት ውጪ ሆኖ በመቆየቱ ምክንያትም በአማራ ክልል አዊ ብሔረሰብ ዞን ጃዊ ከተማ አካባቢ ለከፍተኛ ስርቆትና ውድመት ተዳርጎ እንደነበርም አስረድተዋል።
ተጨማሪ ለማንበብ…
https://www.eep.com.et/?amh-news=የኃይል-ማስተላለፊያ-መስመሩ-ተጠግኖ-ከሁ&lang=am
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
መጋቢት 16 ቀን 2018 ዓ.ም
15 553
+5
በማከፋፈያ ጣቢያው ተጨማሪ የኃይል ትራንስፎርመር ለመትከል ቅድመ ዝግጅት ተጠናቋል
…….///……
ለድሬዳዋ ቁጥር 3 ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ አንድ ተጨማሪ የኃይል ትራንስፎርመር ለመትከል የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መጠናቀቃቸውን የምስራቅ አንድ ሪጅን ገለፀ።
የሪጅኑ ተወካይ ዳይሬክተር አቶ ቴዎድሮስ በየነ እንዳስታወቁት በምስራቅ ኢትዮጵያ ያለውን ከፍተኛ የኤሌክትሪክ ኃይል ፍላጎት ለማርካት ተጨማሪ የኃይል ትራንስፎርመር ለመትከል የሚያስችሉ ሥራዎች ተከናውነዋል።
125 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያለውን የኃይል ትራንስፎርመር የማጓጓዝ ሥራ በቅርቡ እንደሚጀመር የገለፁት አቶ ቴዎድሮስ የተከላ ሥራው በሪጅኑ ባለሙያዎች በራስ አቅም እንደሚከናወን ተናግረዋል።
ተጨማሪ ለማንበብ…
https://www.eep.com.et/?amh-news=በማከፋፈያ-ጣቢያው-ተጨማሪ-የኃይል-ትራን&lang=am
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
መጋቢት 15 ቀን 2018 ዓ.ም
15 553
+3
በጣቢያው እየተከናወነ ያለው የጂ አይ ኤስ ተከላ 90 በመቶ ተጠናቋል
…….///……..
በድሬዳዋ ቁጥር 2 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ እየተከናወነ የሚገኘው የጂ አይ ኤስ (GIS) ተከላ ሥራ 90 በመቶ መጠናቀቁን የምስራቅ አንድ ሪጅን አስታወቀ።
የሪጅኑ ተወካይ ዳይሬክተር አቶ ቴዎድሮስ በየነ እንደገለጹት በአሁኑ ወቅት የተከላ ሥራው ተጠናቆ የኬብል አቅርቦት በመጠባበቅ ላይ ይገኛል።
አስፈላጊው የኬብል አቅርቦት እንደተሟላም በአጭር ጊዜ ውስጥ የዝርጋታ ሥራው ተጠናቆ የጂ አይ ኤስ ሥርዓቱ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምር አስረድተዋል።
በጣቢያው የጂ አይ ኤስ (GIS) ቴክኖሎጂ ተከላ መከናወኑ ማከፋፈያ ጣቢያውን ከማዘመኑ ባለፈ፣ በአደጋ ጊዜ የሚያጋጥሙ ችግሮችን በአፋጣኝ ለመከላከልና አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት ለመፍጠር እንደሚያስችል ተገልጿል።
በተጨማሪም ባለ 15 ኪሎ ቮልት አቅም ያላቸው አዳዲስ አምስት ወጪ መስመሮች መዘርጋታቸውን የገለጹት አቶ ቴዎድሮስ፤ እነዚህ መስመሮች ወደ አገልግሎት ሲገቡ የድሬዳዋንና የአካባቢውን የኃይል አቅርቦት እንደሚያሳድጉት አረጋግጠዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
መጋቢት 15 ቀን 2018 ዓ.ም
15 553
+6
የማህበራዊ ኃላፊነት ሥራው የኃይል መሰረተ ልማት ጥበቃ ሥራዎችን ያጠናክራል- ተቋማቱ
…….///……
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት በጋራ በሶዶ ኮንቨርተር ጣቢያ ዙሪያ ለሚገኙ 12 ቀበሌዎች የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ተደራሽ ለማድረግ የተከናወነው ሥራ የእኔነት ስሜት በመፍጠር የኃይል መሰረተ ልማት ጥበቃ ሥራዎችን እንደሚያጠናክር የወላይታ ሶዶ ኮንቨርተር ጣቢያ ሥራ አስኪያጅ ገለፁ፡፡
ሥራ አስኪያጁ አቶ ሀብታሙ ግርማ እንደገለፁት ጣቢያው ከተሰጠው ሀገራዊና ቀጣናዊ ተልዕኮ በተጨማሪ በአካባቢው የሚገኙ የህብረተሰብ ክፍሎችን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የማህበራዊ ኃላፊነት ሥራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡
ተቋሙ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር በቅንጅት በመስራት በጣቢያው ዙሪያ ለሚገኙ ቀበሌዎች የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽ በማድረግ በማህበረሰቡ ሲነሳ የነበረውን የኃይል አቅርቦት ጥያቄዎች መመለስ መቻሉን አስታውሰዋል፡፡
ተጨማሪ ለማንበብ…
https://www.eep.com.et/?amh-news=የማህበራዊ-ኃላፊነት-ሥራው-የኃይል-መሰረ&lang=am
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
መጋቢት 15 ቀን 2018 ዓ.ም
15 553
+3
እያንዳንዷ ሴት ህልሟን በነፃነት የምትኖርበት ዓለም መፍጠር የጋራ ኃላፈነታችን ነው - ኢንጂነር ምትኩ ንጉሴ
......///......
የደቡብ 1 ሪጅን ሠራተኞች እና አመራሮች 50 ኛውን ዓለም ዓቀፍ የሴቶች ቀን በዓል አከበሩ።
በበዓል አከባበሩ ላይ ኢንጂነር ምትኩ ንጉሴ እንደተናገሩት ማርች 8 በዓለም ዙሪያ ያሉ ሴቶች ስኬት ፅናት እዲሁም ለእኩልነት የሚደረግ ቀጣይ ትግል የሚታወስበት ቀን በመሆኑ ከካላንደር በላይ የሆነ ኹነት ነው።
ተጨማሪ ለማንበብ…
https://www.eep.com.et/?amh-news=እያንዳንዷ-ሴት-ህልሟን-በነፃነት-የምትኖ&lang=am
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
መጋቢት 13 ቀን 2018 ዓ.ም
15 553
ለተከበራችሁ የእስልምና እምነት ተከታዮች በሙሉ፤
እንኳን ለ1447ኛው የኢድ አል-ፈጥር በዓል በሰላም አደረሳችሁ እላለሁ።
ረመዳን የራስን ፍላጎት በመግታት ለላቀ ዓላማ የመገዛት፣ የመረዳዳትና የጽናት ወር ነው። ይህ መንፈስ ደግሞ እኛ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ውስጥ ለምንከተለው “ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” ለሚለው ተልዕኳችን ዋነኛ ስንቅ ነው።
ተቋማችን በታዳሽ የኃይል ምንጮች ላይ የተመሰረቱ ግዙፍ የኃይል ማመንጫዎችን፣ የማከፋፈያ ጣቢያዎችንና የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችን በመገንባት የሀገራችንን የብልጽግና ጉዞ ለማፋጠን ቀን ከሌሊት እየደከመ ይገኛል። ይህ ጉዞ ያለ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ድጋፍ፣ እንዲሁም ያለ ተቋማችን ሠራተኞች ጥረት፣ መስዋዕትነትና ብርቱ ተጋድሎ ሊሳካ የሚችል እንዳልሆነ አምናለሁ፡፡
በመሆኑም ዛሬም እንደ ትናንቱ፣ በብርሃን ጉዟችን ላይ የሚገጥሙንን ፈተናዎች በጋራ በማለፍ፣ ለሀገራችን የኢንዱስትሪና የማኅበራዊ እድገት የጀርባ አጥንት የሆነውን ኃይል ለማቅረብ ሁላችንም በጋራ እንድንተጋ ጥሪዬን አቀርባለሁ። በተመደባችሁበት ፈታኝ የሥራ ሁኔታ እና ቦታ ውስጥ የምትከፍሉት ዋጋ ለሚሊዮኖች ተስፋ የሚሰጥ የሀገር ኩራት እንደሆነ አምናለሁ።
ታላቁ የኢድ አል-ፈጥር በዓል የሠላም፣ የፍቅርና የመተሳሰብ እንዲሁም አንድነታችን ይበልጥ የሚጠነክርበት እንዲሆን ከልብ እመኛለሁ።
ኢድ ሙባረክ!
አሸብር ባልቻ(ኢንጂነር)
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ
15 553
+6
ማከፋፈያ ጣቢያዎቹ ለሐዋሳ ከተማ ዕድገት አስተዋፅኦ እያደረጉ ነው
……..///………
በሐዋሳ ከተማ የሚገኙት ሁለቱ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ለከተማዋ ሁሉን አቀፍ ዕድገት ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያበረከቱ መሆኑን የከተማ አስተዳደሩ አስታወቀ።
በከተማዋ መሬት አስተዳደርና ኢንቨስትመንት መምሪያ የኢንቨስትመንት ዘርፍ ኃላፊ አቶ አበራ አዴላ እንደገለፁት በከተማው ያለው የኃይል አቅርቦት ከጊዜ ወደጊዜ እየተሻሻለ በመምጣቱ ለኢንቨስትመንት ፍሰቱ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እያደረገ ነው።
የኃይል አቅርቦቱ ኢንቨስትመንትን በመሳብ ምርትና ምርታማነትን ለመጨመር ከሚኖረው ሚና ባለፈ ለከተማ ውበት፣ የማህበረሰቡን የአኗኗር ዘይቤ ለመቀየር እና ለሥራ ዕድል ፈጠራ የሚኖረው ድርሻ የጎላ ነው ብለዋል።
ተጨማሪ ለማንበብ…
https://www.eep.com.et/?amh-news=ማከፋፈያ-ጣቢያዎቹ-ለሐዋሳ-ከተማ-ዕድገት&lang=am
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
መጋቢት 9 ቀን 2018 ዓ.ም
15 553
በስርቆት ምክንያት ኃይል የተቋረጠበት መስመር ወደ አገልግሎት ተመልሷል
……..///…….
በስርቆት ምክንያት ኃይል የተቋረጠበት የይርጋለም ቁጥር 2 - ሐዋሳ ቁጥር 2 ባለ 230 ኪሎ ቮልት ጥምር የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ዳግም ወደ አገልግሎት መመለሱን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የደቡብ 1 ሪጅን አስታወቀ፡፡
በሪጂኑ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ኦፕሬሽንና ጥገና ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ሞሲሳ ገልቻ እንደገለፁት በማስተላለፊያ መስመሩ ላይ በተፈፀመበት ስርቆት ምክንያት አንድ የኃይል ማተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶ በመውደቁ ከመጋቢት 2 ቀን 2018 ዓ.ም ምሽት 12 ሰዓት አካባቢ ጀምሮ መስመሩ ኃይል ማስተላለፍ አቋርጧል፡፡
የወደቀውን ባለ 230 ኪሎ ቮልት የብረት ምሰሶ በጊዜያዊነት በባለ 132 ኪሎ ቮልት የብረት ምሰሶ በመተካት ተቋርጦ የነበረው መስመር ዳግም ወደ አገልግሎት መመለስ መቻሉን ተናግረዋል፡፡
በዚህም በመስመሩ መቋረጥ ምክንያት በከፊል ኃይል ሲያገኙ የነበሩ ደንበኞች ሙሉ በሙሉ እንዲያገኙ መደረጉን በመግለጽ ኃይል በከፊል ተቋረጦ በነበረበት ወቅት በትዕግስት ለጠበቁ ደንበኞች ምስጋና አቅርበዋል፡፡
የወደቀውን ምሰሶውን ወደነበረበት በመመለስ ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት የተለያዩ ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑን አቶ ሞሲሳ ገልፀዋል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
መጋቢት 9 ቀን 2018 ዓ.ም
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
