ch
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

前往频道在 Telegram

EEP Communication

显示更多

📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览

频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 540 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 340,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 161

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 540 名订阅者。

根据 28 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 1,过去 24 小时变化为 -4,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 24.98%。内容发布后 24 小时内通常能获得 16.34% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 882 次浏览,首日通常累积 2 539 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 8

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
EEP Communication

凭借高频更新(最新数据采集于 29 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。

15 540
订阅者
-424 小时
-147
+130
帖子存档
ለሃያ አምስት የዳታ ማይኒንግ ድርጅቶች ኃይል በዶላር ሊሸጥ ነው ...........///......... ሃያ አምስት የዳታ ማይኒንግ ድርጅቶች ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር ለመሥራት ጥያቄ ማቅረባቸውንና ከእነዚህ ውስጥ አራቱ ሥራ መጀመራቸውን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የገበያና ቢዝነስ ልማት መምሪያ አስታወቀ። የመምሪያው ዳይሬክተር አቶ ህይወት እሸቱ እንዳስታወቁት የዳታ ማይኒንግ ኩባንያዎቹ በሀገር ውስጥ ኃይል የሚጠቀሙ ቢሆንም የፍጆታ ሂሳባቸውን በዶላር እንዲከፍሉ ከስምምነት ተደርሷል፡፡ የኢንቨስትመንት ፍቃድና ሌሎች አስፈላጊ መስፈርቶችን ካሟሉት ከሃያ አምስቱ ድርጅቶች መካከል አራቱ ከ10 እስከ 100 ሜጋ ዋት ድረስ ኃይል መጠቀም መጀመራቸውን አቶ ህይወት ተናግረዋል፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ በሀገር ውስጥ በውጭ ምንዛሪ ከተከናወነው ሽያጭ አስቀድመው ሥራ ከጀመሩት ከሁለቱ የዳታ ማይኒንግ ድርጅቶች ብቻ ከሁለት ሚሊየን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን ገልፀዋል። የቀሪዎቹ ሁለት ድርጅቶች የፍጆታ ሂሳብ በቀጣዩ ወር መሰብሰብ እንደሚጀምር ነው ያስታወቁት፡፡ አቶ ህይወት እንደገለፁት በዳታ ማይኒንግ ዘርፍ ለመሰማራት ፍቃድ ከወሰዱትና ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር የኃይል ሽያጭ ስምምነት ከተፈራረሙት አስራ ስምንት ድርጅቶች መካከል አምስቱ ግንባታ ሲጀምሩ አስሩ ደግሞ ግንባታ ለመጀመር በሂደት ላይ ናቸው፡፡ ሦስቱ የዳታ ማይኒንግ ድርጅቶች ግን ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ ባለመጀመራቸው በፍጥነት ወደ ሥራ እንዲገቡ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸዋል ብለዋል፡፡ መስፈርቶቹን ካሟሉት የዳታ ማይኒንግ ድርጅቶች መካከል ሌሎች ሶስት ድርጅቶች ከተቋሙ ጋር የኃይል ሽያጭ ስምምነት ለመፈራረም በሂደት ላይ መሆናቸው ታውቋል፡፡ ከዚህ በኋላ የሚቀርብ የዳታ ማይኒንግ ድርጅቶች የኃይል ፍላጎት ጥያቄ የሚስተናገደው አስቀድመው የኃይል ፍላጎት ያቀረቡትን ድርጅቶች ጥያቄ ምላሽ ካገኘ በኋላ የሚኖረውን የኃይል አቅርቦት በመመርመር እንደሚሆን አቶ ህይወት ተናግረዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 13 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

photo content
+1

የፈተና ጥሪ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሾፌር 4ኛ የሥራ መደብ ሠራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ጥር 17 ቀን 2016 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወሳል፡፡ በዚሁ መሰረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለጸው አመልካቾች በሙሉ የካቲት 19 ቀን 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ኮተቤ ብረታ ብረት ፊት ለፊት በሚገኘው የተቋሙ ዋና መ/ቤት የማሰልጠኛ አዳራሽ የጽሁፍ ፈተና የሚሰጥ በመሆኑ ለፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 13 ቀን 2016 ዓ.ም

የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን በታቀደለት ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው ……….///……….. በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን በቀጣዮቹ አራት ዓመታት ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን የፕሮጀክቱ ምክትል ሥራ አስኪያጅ ገለጹ። ምክትል ሥራ አስኪያጁ አቶ አባይነህ ጌትነት እንደተናገሩት የዋና ግድብ፣ የኃይል ማመንጫ ቤቶች (power houses)፣ የውሃ ማስተንፈሻና ሌሎች ተጓዳኝ ሥራዎች በፍጥነት እየተከናወኑ ናቸው። የግድብ ግንባታው 6 ነጥብ 6 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ የአፈር ቁፋሮ በማካሄድ አጠቃላይ ግድቡ ከሚፈልገው 7 ነጥብ 7 ሚሊዮን ሚሊየን ኪዩብ የኮንክሪት ሙሊት ውስጥ 42 በመቶው ማለትም 3 ነጥብ 25 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ የኮንክሪት ሙሊት (RCC) ሥራ መከናወኑን ተናግረዋል። የኃይል ማመንጫው 2 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ ቁፋሮ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ከሚያስፈልገው 160 ሺ ሜትር ኪዩብ ኮንክሪት ሙሊት ውስጥ 52 በመቶው መከናወኑን ምክትል ሥራ አስኪያጁ ጠቁመዋል። አቶ አባይነህ አክለውም በኃይል ማመንጫው ላይ ያለው የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራ በዲዛይንና በቅድመ ዝግጅት ሂደት ላይ መሆኑን ገልጸዋል። 6 ነጥብ 65 ሚሊዮን ሜትር ኪዩብ ቁፉሮ የሚጠይቀው የውሃ ማስተንፈሻ (spill way) ሥራ 90 ከመቶው መጠናቀቁንና 13 በመቶ የሚሆን የአርማታ ሙሊት ሥራ መከናወኑንም አብራርተዋል። በፋይናንስ በተለይም በውጭ ምንዛሬ እጥረት እና ተያያዥ ችግሮች ምክንያት ግንባታው በታቀደለት የጊዜ ገደብ እንዳይጠናቀቅ አድርጎት መቆየቱን ተናግረዋል። እንደ አቶ አባይነህ ገለጻ አሁን ላይ መንግስት ለፕሮጀክቱ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ ከኮንትራክተሩ ጋር በመነጋገር የነበሩበትን ችግሮች በመፍታት የክትትልና ድጋፍ ሥርዓቱን በማጠናከሩ ግንባታው በፍጥነት እየተከናወነ ይገኛል። የቀድሞ ሳሊኒ የአሁኑ ዊ ቢዩልድ የኮይሻ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ማናጀር የሆኑት ሚስተር ዞፒስ በበኩላቸው ከአሁን ቀደም በኢትዮጵያ ከገነቧቸው ግድቦች ልምድ በመውሰድ የኮይሻ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን የሲቪል ስራ በታቀደለት የጊዜ ገደብ ለማጠናቀቅ የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎችን አጠናቀው ወደ ሥራ መግባታቸውን አውስተዋል። ሆኖም በሂደት ባጋጠመው የፋይናንስና የስሚንቶ እጥረት ምክንያት የግንባታ ሂደቱ በታሰበለት ፍጥነት አለመከናወኑን ገልጸዋል። ይሁንና ከመንግስት ጋር በመነጋገርና የገጠሙትን ችግሮች በመፍታት የፕሮጀክቱን የሲቪል ሥራ በተቻለ ፍጥነት በተያዘው መርሃ ግብር ለማከናወን ሌትና ቀን እየሰሩ መሆናቸውን የጠቆሙት ሚስተር ዞፒስ አሁን ላይ አጠቃላይ የፕሮጀክቱ አፈጻጸም 62 በመቶ ላይ መድረሱን ተናግረዋል። የኮይሻ የውኃ ኃይል ማመንጫ ሲጠናቀቅ እያንዳንዳቸው 300 ሜጋ ዋት የሚያመነጩ 6 ተርባይኖች የሚኖሩት ሲሆን በዓመት በአማካይ 6 ሺ 340 ጊጋ ዋት ስዓት ኃይል ያመነጫል ተብሎ ይጠበቃል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 12 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+7

photo content

የሲስተም ማስተካከያ ሥራዎች እየተሰሩ በመሆናቸው አልፎ አልፎ የኃይል መቋረጥ ሊያጋጥም ይችላል ...........///......... በበለስ - ባህርዳር፣ በበለስ - ህዳሴና በገናሌ ዳዋ 3 - ይርጋለም የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ የሲስተም ማስተካከያ ሥራዎች እየተሰሩ መሆናቸውን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ። የዘርፉ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሀብታሙ ውቤ እንደገለፁት በመስመሮቹ ላይ በተደጋጋሚ የሚያጋጥመው የኃይል መቋረጥ ከ5 እስከ 10 በመቶ የሲስተም አለመረጋጋት እንዲፈጠር ምክንያት እየሆነ ነው። ከኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ዩኒቶች ለብሔራዊ ኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል ኃይል ማድረስ ሳይችሉ ሲቀር ሲስተሙ አውቶማቲክ በሆነ መንገድ ራሱን በራሱ ስለሚቆጣጠር የፍሪኩዌንሲ ዝቅ ማለት እንደሚያጋጥም ጠቁመዋል። በዚህ የተነሳ የሲስተም አለመረጋጋትና አልፎ አልፎም የኃይል መቋረጥ እንደሚከሰት ሥራ አስፈፃሚው አብራርተዋል። በመሆኑም የሲስተም አለመረጋጋቱን ለማስተካከል የተጀመሩት ሥራዎች የተወሰኑ ቀናት የሚፈልጉ በመሆናቸው ህብረተሰቡ ችግሩን ተረድቶ በትዕግስት እንዲጠብቅ ጥሪ አቅርበዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 11 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+5

የትራንስፎርመር ቅየራ ሥራው ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት ጀመረ ........///........ የሰኮሩ ማከፋፈያ ጣቢያ የትራንስፎርመር ቅየራ ሥራ ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት መጀመሩን የፕሮጀክቱ ሱፐርቫይዘር ገለፁ፡፡ ሱፐርቫይዘሩ አቶ አሊ ካሚል አንደገለጹት ጣቢያው ካሉት ሁለት ትራንስፎርመሮች በአንዱ ላይ በብልሽት ምክንያት ላለፉት ሦስት ዓመት ከአገልግሎት ውጭ ሆኖ ቆይቷል። የትራንስፎርመር ቅየራው ከአንድ ዓመት በላይ መውሰዱን ያስታወሱት አቶ አሊ አሁን ላይ ሥራው ተጠናቆ ከግሪድ ጋር በማገናኘት አገልግሎት መስጠት መጀመሩን ገልጸዋል። ጣቢያው በአንድ ትራንስፎርመር ብቻ ሲሰራ በነበረበት ጊዜ በሥርጭቱ ላይ ጫና ከመፍጠሩም ባለፈ የማስፋፊያ ሥራ እንዳይከናወን አድርጎ መቆየቱን ተናግረዋል። የትራንስፎርመር ቅየራው ተጠናቆ አገልግሎት መስጠት መጀመሩ በግሪዱ ላይ ያለውን ጫና በመቀነስ የኃይል መቆራረጥ እንዳይኖር እና በማሰራጫ ጣቢያው የማስፋፊያ ሥራ ለማከናውን ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው አቶ አሊ አብራርተዋል። እንደ ሱፐርቫይዘሩ ገለጻ የትራንስፎርመር ቅየራው የሲቪልና ኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራው በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የራስ ኃይል ኮንስትራክሽን መምሪያ ተከናውኗል። ይህም ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ ከማዳን ባለፈ በኃይል ዘርፉ ትልልቅ ፕሮጀክቶችን በራስ አቅም ለመስራት እንደሚቻል ማሳያ መሆኑን አቶ አሊ ተናግረዋል። ትራንስፎርመሩ 400/230 ኪሎ ቮልት የሆነና 250 ሜጋ ቮልት አምፔር አቅም ያለው መሆኑን ቀደም ሲል መዘገባችን ይታወሳል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 11 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

ለአምስቱ ዞኖች የኃይል መቋረጥ ምክንያት ሆኗል .........///........ ከወላይታ ሶዶ ወደ ሳውላና ጂንካ የሚሄደው ባለ 132 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀመረ። የደቡብ ሪጅን 2 የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ምትኩ ታዬ እንዳስታወቁት በደቡብ ክልል ለአምስት ዞኖች ኃይል መቋረጥ ምክንያት የሆነው በስርቆት ምክንያት የወደቀው ታወር በሌላ ተተክቷል። ታወሩን በሌላ የመተካት ሂደት በመጠናቀቁ ዛሬ ከቀኑ 7:15 ጀምሮ አገልግሎት መስጠት መደመሩን ዳይሬክተሩ ገልፀዋል፡፡ ላለፉት አራት ቀናት ኃይል የተቋረጠባቸው ዞኖች ዳግም ኃይል ማግኘታቸውን የገለፁት አቶ ምትኩ ከቀናት በፊት በተፈፀመ ስርቆት ለአንድ ሳምንት በአካባቢው ኃይል መቋረጡን አስታውሰዋል፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 11 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+8

የንፋሰ ኃይል ማመንጫ ጣቢያው ግንባታ 48 በመቶ ደርሷል ……..///………. የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ፕሮጀክት ግንባታ 48 በመቶ መጠናቀቁን የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ ተወካይ አስታወቁ። ተወካዩ አቶ ደረጀ ጣሰው እንዳስታወቁት የፕሮጀከቱ የሲቪልና መካኒካል ሥራዎች በተያዘላቸው ዕቅድ መሰረት እየተከናወኑ ነው። አቶ ደረጀ እንደተናገሩት 40 በመቶ የሚሆኑት የንፋስ ተርባይኖችና ጀነሬተሮች ከወደብ ወደ ፕሮጀክቱ ሳይት ደርሰው ለተከላ ዝግጁ ሆነዋል፡፡ እስካሁን ሁለት የንፋስ ተርባይኖችና ጀነሬተሮቸ መተከላቸውን፣ ለአራት ተርባይኖች ተከላ ቦታ ዝግጁ መደረጉንና የአስራ ሁለት የንፋስ ተርባይኖች መትከያ መሰረት መሞላቱን ገልፀዋል፡፡ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቱ የሲቪል ሥራ 47 በመቶ፤ የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራው ደግሞ 2 ነጥብ 99 በመቶ መጠናቀቁን ተወካዩ ተናግረዋል። አጠቃላይ የመሰረት ሙሌት ሥራ 46 በመቶ መጠናቀቁንና የፕሮጀክቱ ግንባታ አማካይ አፈፃፀም 48 በመቶ መድረሱን አቶ ደረጀ አስታውቀዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 11 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+5

በሁለት ሳምንት ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜ የተፈፀመው ስርቆት ለአምስት ዞኖች የኃይል መቋረጥ ምክንያት ሆኗል .........///........ ከወላይታ ሰዶ ወደ ሳውላና ጂንካ የሚሄደው ባለ 132 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ በሁለት ሳምንት ውስጥ ለሁለተኛ ጊዜ ስርቆት ተፈጽሞበታል፡፡ ትናንት ምሽት 2፡00 ሰዓት አካባቢ ከወላይታ ሶዶ በ91 ኪሎ ሜትር ርቀት አካባቢ በተፈፀመው ሥርቆት በደቡብ ክልል አምስት ዞኖች ኃይል ተቋርጧል፡፡ ከቀናት በፊት በመስመሩ ላይ በተፈፀመ ስርቆት አምስቱ ዞኖች እስካለፈው እሁድ ድረስ ለአንድ ሳምንት ያህል በጭለማ ውስጥ መቆየታቸው ይታወሳል፡፡ ቀደም ሲል በተፈፀመው ስርቆት የተነሳ የገጠመው ችግር በተጠገነ በቀናት ውስጥ በኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶዎች ላይ ስርቆት መፈፀሙ የአካባቢው መስተዳድር ሆነ ህብረተሰቡ ለችግሩ ትኩረት እንዳልሰጡት የሚያሳይ ሆኖ አግኝተነዋል፡፡ በስርቆት ድርጊቱ የተነሳ የሚፈጠረው የኃይል መቋረጥ ህብረተሰቡ ኤሌክትሪክ እንዳያገኝ የሚያደርገው፣ ማህበራዊ እንቅስቃሴውን የሚገዳና ተጽዕኖው ከፍ ያለ በመሆኑ ሁሉም የሚመለከታቸው አካላት ለመሰረተ ልማት ጥበቃው ትኩረት እንዲሰጡት እንጠይቃለን፡፡ ትናንት ምሽት ስርቆት የተፈፀመበት ኣባቢ ጫካና ገደላማ በመሆኑ የጥገና ሥራውን አስቸጋሪ ሊያደርገው ስለሚችል ህብረተሰቡ በትዕግስት እንዲጠብቅ እናሳስባለን፡፡ በዚህ አጋጣሚ ፈታኝ በሆነው የጥገና ሥራ ላይ እየተሳተፋችሁ ያላችሁ የተቋማችን የጥገናና ድጋፍ ሰጪ ሠራተኞችን እናመሰግናለን፡፡ "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 08 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+3

photo content
+9

ተቋማቱ ተቀናጅቶ ለመስራት የሚያስችላቸውን ውይይት አካሄዱ .........///......... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኃይል ልማቱን ይበልጥ ለማሳደግ ያለመ የሁለትዮሽ ውይይት አካሂደዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አሸብር ባልቻ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነትን ለማሳደግ በሁሉም ዘርፎች ጥናትን መሠረት ያደረገ ማሻሻያ እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ሽፈራው ተሊላ በበኩላቸው የኃይል ልማቱን ዘርፍ ይበልጥ ለማዘመን የሀገሪቱን የኢነርጂ ፖሊሲ መርህ ያደረገ የምክክር መድረክ በሁለቱ ተቋማት መካከል ተጠናክሮ ሊቀጥል ይገባል ብለዋል። በውይይቱ የሁለቱ ተቋማትን ቅንጅታዊ አሰራር ለማሻሻል የሚያስችሉ ዝርዝር ጉዳዮች ተዳሰዋል። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና መስሪያ ቤት በተካሔደው ውይይት ላይ የሁለቱ ተቋማት ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተሳታፊ ሆነዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et የካቲት 07 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+6