ch
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

前往频道在 Telegram

EEP Communication

显示更多

📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览

频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 692 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 024,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 156

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 692 名订阅者。

根据 28 八月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 137,过去 24 小时变化为 -5,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 35.24%。内容发布后 24 小时内通常能获得 17.40% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 528 次浏览,首日通常累积 2 730 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 12

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
EEP Communication

凭借高频更新(最新数据采集于 29 八月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。

15 692
订阅者
-524 小时
-17
+13730
帖子存档
ተቋሙ የሠራተኛውን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየሰራ ነው …///… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሠራተኛውን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ በትኩረት እየሰራ እንደሚገኝ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ገለፁ፡፡ ዋና ሥራ አስፈፃሚው ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደተናገሩት የተቋሙ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች በተለያዩ ጊዜያት የጥቅማጥቅም ጥያቄዎችን ሲያቀርቡ የቆዩ ቢሆንም ከተቋሙ የፋይናንስ ቁመና ጋር ተያይዞ በወቅቱ ምላሽ ሳይሰጥ ቆይቷል፡፡ ይሁን እንጂ በተያዘው በጀት ዓመት የተቋሙ የፋይናንስ አቅም እያደገ በመምጣቱና ወደ ትርፋማነት በመሸጋገሩ ምክንያት ሲነሱ ለነበሩ የተለያዩ የጥቅማጥቅም ጥያቄዎች ምላሽ መስጠት መቻሉን ገልፀዋል፡፡ ይህም የሠራተኛውን የኑሮ ሁኔታ ከመደገፍ ባለፈ የተቋሙን ምርታማነትና የፕሮጀክቶችን አፈፃፀም ለማሳደግ ከፍተኛ እገዛ እንደሚያደርግ ጠቅሰዋል፡፡ መንግሥት ለተቋሙ መለወጥና መጠናከር ከፍተኛ ድጋፍ እያደረገ መሆኑን ያብራሩት ኢንጂነር አሸብር ተቋሙ የነበረበትን ከፍተኛ ዕዳ ወደ ካፒታል እንዲቀየርለት ማድረጉን አስታውሰዋል፡፡ የታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት መጠናቀቅ፣ የነባር የኃይል ማመንጫዎች አፈፃፀም መሻሻል እና በሀገር ውስጥ ለሚገኙ የዳታ ማይኒንግ ኩባንያዎች በዶላር የኤሌክትሪክ ኃይል መሸጥ መጀመሩ የተቋሙን የውጭ ምንዛሬ ገቢ በከፍተኛ ሁኔታ እንዳሳደገው አብራርተዋል፡፡ ይህ የገቢ ዕድገት ተቋሙ ለጀመራቸው አዳዲስና ነባር ፕሮጀክቶች የሚያስፈልጉ ግብዓቶችን በራስ አቅም ለመሸፈን ዕድል መፍጠሩንም ተናግረዋል፡፡ የተቋሙ ዕድገትና የሠራተኛው ጥቅም በቀጥታ የተሳሰሩ መሆናቸውን የጠቀሱት ዋና ሥራ አስፈፃሚው እያንዳንዱ የሰው ኃይል በቁርጠኝነት ከሠራ ተቋሙን ይበልጥ ትርፋማ ማድረግ እንደሚችል አስገንዝበዋል፡፡ በመሆኑም እያንዳንዱ ሠራተኛ ጥቅምን ብቻ ከመጠበቅ ይልቅ ለተቋሙ ዕድገትና ውጤታማነት ማበርከት የሚጠበቅበትን ድርሻ በተግባር ማሳየት እንዳለበት አሳስበዋል፡፡ ተቋሙን በዘላቂነት ለማሳደግ በፕሮጀክቶች አፈፃፀም ላይ የሚታዩ መዘግየቶችን ማስወገድ፣ በሥራ አፈፃፀምና በኦፕሬሽን ላይ የሚባክኑ ሀብቶችን መቀነስ እንዲሁም ጠንካራ ስትራቴጂ በመንደፍ በቀጣይ በራስ ገቢ ሌሎች ትልልቅ የኃይል ማመንጫዎችን መገንባት እንደሚገባ አመላክተዋል፡፡ እንደ ኢንጂነር አሸብር ገለፃ የሠራተኞችን ጥቅማጥቅም ማረጋገጥ በሥራ ገበታቸው ላይ ተረጋግተው እንዲሠሩ ስለሚያስችል ለተቋማት ውጤታማነት ያለው ሚና የጎላ ነው፡፡ በአሁኑ ወቅት ተቋሙ የሀገሪቱን የኤሌክትሪክ ተደራሽነት ለማሳደግ ሰፊ የኢንቨስትመንት ሥራዎችን በማከናወን ላይ እንደሚገኝ ገልፀው ሠራተኛውና አመራሩ ይህንን ትልቅ ሀገራዊ ግብ ለማሳካት በቁርጠኝነትና በቅንጅት መሥራት እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+6

photo content
+6

አረንጓዴ የፋይናንስ ምንጭ (Green Financing) ......///..... ከአገር ውስጥና ከውጭ የገንዘብ ምንጮች ጋር የምናደርጋቸው የብድር ውይይቶችና ድርድሮች በሙሉ አረንጓዴ ኢንቨስትመንትን
አረንጓዴ የፋይናንስ ምንጭ (Green Financing) ......///..... ከአገር ውስጥና ከውጭ የገንዘብ ምንጮች ጋር የምናደርጋቸው የብድር ውይይቶችና ድርድሮች በሙሉ አረንጓዴ ኢንቨስትመንትን ማዕከል ያደረጉ ናቸው። በኮፕ 32 (COP 32) የአየር ንብረት ጉባኤ ላይ በምናደርገው ንቁ ተሳትፎም ለታዳሽ ኃይል ግንባታ የሚውሉ ዓለም አቀፍ አረንጓዴ የፋይናንስ አጋርነቶችን (Green Financing) ይበልጥ ለማጠናከር እንሠራለን። 💳🌐 #COP32 #GreenFinance #ClimateAction #RenewableEnergy #EEP "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ.ም

"7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ለኢትዮጵያ የሀገረ መንግሥት ግንባታ ትልቅ ስኬት ነው" ኢንጂነር አሸብር ባልቻ …..///…. 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ለኢትዮጵያ የሀገረ መንግሥት ግንባታና ለቀጣይ መዋቅራዊ ሥራዎች ስኬት ትልቅ መነሳሳትን የፈጠረ ታሪካዊ ምዕራፍ መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ አስታወቁ፡፡ የተቋሙ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች "ከምርጫ ድል ማግስት፤ ጠንካራ መንግሥት" በሚል መሪ ቃል በወቅታዊና ተቋማዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት አካሂደዋል፡፡ በመድረኩ ላይ የመወያያ ሰነድ ያቀረቡት በተቋሙ የኮርፖሬት ፋይናንስና ሀብት አስተዳደር ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ደመረ አሰፋ እንደገለፁት 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ሰላማዊ፣ ፍትሃዊ፣ ነፃና ዲሞክራሲያዊ እንዲሁም የኢትዮጵያ አሸናፊነት የተረጋገጠበት ሆኖ ተጠናቋል፡፡ የምርጫው ስኬት የተገኘው ጊዜ ተወስዶ በተከናወኑ የቅድመ ምርጫ ሥራዎችና በማህበረሰቡ ፅናት መሆኑን ገልፀው በቅድመ ምርጫው ወቅት የታየው ፅናትና ከፍተኛ ርብርብ በድህረ ምርጫ ተግባራት ላይም ሊደገም እንደሚገባ አስረድተዋል። ጠንካራ ሀገረ መንግስት ለመገንባት ሠራተኛው የህዝብን ፍላጎት የሚያሳካ እና ሀገራዊ ትልሞችን አውቆ የሚተገብር  መሆን እንዳለበትም ጠቅሰዋል። በድህረ-ምርጫ ወቅት የተቋማት ዝግጁነት፣ የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትና የመንግሥት ሠራተኛው የሥራ ዲስፕሊን ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች መሆናቸውንም ነው አቶ ደመረ ያነሱት፡፡ የሀገሪቱን ሁለንተናዊ ዕድገት ለማፋጠን በኃይል ልማት ዘርፉ ላይ ያሉትን ሥራዎች በከፍተኛ ቁርጠኝነትና በትጋት ማከናወን እንደሚገባና ለዚህም ሠራተኛው የተሰጠውን ኃላፊነት በአግባቡ በማከናወን ለሀገረ መንግሥት ግንባታ የበኩልን ድርሻ እንዲወጣ አሳስበዋል፡፡ በተቋሙ የኢንጂነሪንግና ኮንስትራክሽን ቢዝነስ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ውድነህ የማነ በበኩላቸው በኢትዮጵያ ለሚስተዋሉ መሠረታዊ ችግሮች ዋናው መንስኤ የሀገረ መንግሥት ግንባታ ሂደቱ ዘላቂና ተቋማዊ አሠራርን ተከትሎ አለመከናወኑ መሆኑን ገልፀዋል። ይህንን ክፍተት በዘላቂነት ለመቅረፍም ገለልተኛና ጠንካራ ተቋማትን መገንባት እንደሚያስፈልግም ነው ያብራሩት፡፡ በአሁኑ ጊዜ በተለያዩ የአፍሪካና የዓለም ሀገራት ከምርጫ ጋር ተያይዞ ከባድ አለመረጋጋትና ውጥረት የሚስተዋል ቢሆንም በኢትዮጵያ ግን ሂደቱ ሰላማዊ በሆነ መንገድ መጠናቀቁ ለቀጣይ መዋቅራዊ ሥራዎች ስኬት ትልቅ መነሳሳት መፍጠሩን አብራርተዋል። በውይይቱ ላይ የማጠቃለያ ሃሳብ የሰጡት የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እንደተናገሩት 7ኛው ሀገራዊ ምርጫ ሕዝቡ ለሀገረ መንግሥት ግንባታ ያለውን ፅኑ የሆነ አቋም ያሳየበት ነው፡፡ በምርጫው ወቅት ከፍተኛ የተለያዩ ጫናዎች የነበሩ ቢሆንም መራጩ ህዝብ ጫናዎቹን ተቋቁሞ ሂደቱን በከፍተኛ ዲሲፕሊን እና ቁርጠኝነት ማካሄዱን ተናግረዋል። ምርጫ በሰላማዊ መንገድ መጠናቀቁ ለኢትዮጵያ ተቋማዊ የሀገረ መንግስት ግንባታና ለቀጣይ መዋቅራዊ ስራዎች ስኬት ትልቅ መነሳሳትን የፈጠረ ታሪካዊ ምዕራፍ መሆኑንም አመላክተዋል፡፡ ይህም ሀገሪቱ በቀጣይ መዋቅራዊ ሥራዎች ላይ በሰላም ለመወያየት እንድትችል ትልቅ ማሳያ መሆኑን ጠቅመዋል፡፡ ለዲጂታላይዜሽን ሥራዎች የተሰጠው ትኩረት ውጤት እያመጣ መሆኑን የገለፁት ኢንጂነር አሸብር ሀገራዊ ምርጫው ላይ የተጀመረው የዲጂታላይዜሽን የአሰራር ሥርዓት የዜጎችን እንግልት ለመቀነስ አስተዋፅኦ ማድረጉን አንስተዋል፡፡ የምንመኛትን ሀገር ለቀጣዩ ትውልድ ለማስተላለፍ በሚደረገው ጉዞ ውስጥ የኢነርጂ ዘርፉ የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ መሆኑን ጠቅሰው አዲስ መንግሥት በይፋ እስከሚመሰረት ድረስ ሁሉም ሠራተኛ የተጣለበትን ሀገራዊ አደራ በመገንዘብ ኃላፊነቱን በአግባቡ መወጣት እንዳለበትም አሳስበዋል። የውይይቱ ተሳታፊዎችም በመድረኩ ላይ የተለያዩ አስተያየቶችና ጥያቄዎችን አቅርበው በሥራ ኃላፊዎቹ ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶባቸዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም

photo content
+9

ሠራተኞች በወቅታዊ እና ተቋማዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት እያካሄዱ ነው ......///...... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች "ከምርጫ ድል ማግስት፤ ጠንካራ መንግሥት" በሚል መሪ
+8
ሠራተኞች በወቅታዊ እና ተቋማዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት እያካሄዱ ነው ......///...... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች "ከምርጫ ድል ማግስት፤ ጠንካራ መንግሥት" በሚል መሪ ሀሳብ በተቋማዊ እና ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በዋና መሥሪያ ቤት ውይይት ማካሄድ ጀምረዋል። የውይይት መድረኩን የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በንግግር የከፈቱት ሲሆን በውይይቱ ላይ ሌሎች ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችና በርካታ ቁጥር ያላቸው የተቋሙ ሠራተኞች እየተሳተፉ ይገኛሉ። የውይይት መድረኩ በዋናነት በ7ኛው ሀገራዊ ጠቅላላ ምርጫ ቅድመ ሂደቶችና በቀጣይ በድህረ ምርጫ በሚከናወኑ ዓበይት ሥራዎች ላይ ትኩረት ያደረገ ነው። በመድረኩ ላይ "ከምርጫ ድል ማግስት፤ ጠንካራ መንግሥት" በሚል በመንግሥት የተዘጋጀው መነሻ ሰነድ በንባብ እየቀረበ ሲሆን በቀጣይም በሰነዱ ዙሪያ ከተሳታፊዎች የተለያዩ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች ተነስተው ሰፊ ውይይት ይደረግባቸዋል ተብሎ ይጠበቃል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም

የተቋረጠውን የኤሌክትሪክ ኃይል ለመመለስ ርብርብ እየተደረገ ነው በሑመራ እና አካባቢው የተቋረጠውን የአሌክትሪክ ኃይል ለመመለስ ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን
+2
የተቋረጠውን የኤሌክትሪክ ኃይል ለመመለስ ርብርብ እየተደረገ ነው በሑመራ እና አካባቢው የተቋረጠውን የአሌክትሪክ ኃይል ለመመለስ ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰሜን ሪጅን አስታወቀ። በሪጅኑ የማስተላለፍያ መስመሮች እና የኦፕቲካል ፋይበር (OPGW) ጥገና ኃላፊ አቶ ህንፃ ኣረጋዊ እንደገለፁት በሸራሮ ከተማ አካባቢ በተከሰተው ከፍተኛ ንፋስ ምክንያት ከሽሬ ወደ ሑመራ እና ወልቃይት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች በተዘረጋው ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ (tower) ላይ በደረሰ ጉዳት የኃይል መቋረጥ አጋጥሟል። በብረት ምሰሶው ላይ በደረሰው ጉዳት ምክንያት በሑመራ እና አከባቢው የኃይል አቅርቦቱ በጊዜያዊነት መቋረጡን ተናግረዋል። ያገጠመውን ችግር በመለየት የተቋረጠውን ኃይል ለመመለስ የሪጅኑ የጥገና ባለሙያዎች ከፍተኛ ርብርብ በማድረግ ላይ እንደሚገኙ ተናግረዋል፡፡ በመሆኑም ኃይል በተቋረጠባቸው አካባቢዎች ያሉ የሕብረተሰባችን ክፍሎች ችግሩ እስኪፈታ ድረስ በትዕግስት እንዲጠብቁና ሌሎች የኃይል አማራጮችን እንዲጠቀሙ አቶ ህንፃ አሳስበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 13 ቀን 2018 ዓ.ም

ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቱን ጎበኙ …..//….. ከፍተኛ የፌዴራልና የክልል የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ለገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ
+9
ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክቱን ጎበኙ …..//….. ከፍተኛ የፌዴራልና የክልል የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች ለገዳ ልዩ የኢኮኖሚ ዞን የኤሌክትሪክ ኃይል ለማቅረብ እየተገነባ የሚገኘውን ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ፕሮጀክት ጎበኙ። በጉብኝቱ ላይ የኦሮሚያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሽመልስ አብዲሳ፣ በሚኒስትር ማዕረግ የጠቅላይ ሚኒስትሩ የማክሮ ኢኮኖሚ አማካሪና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ አመራር ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ አምባሳደር ግርማ ብሩ፣ የብሔራዊ ባንክ ገዥ ኢዮብ ተካልኝ (ዶ/ር)ን ጨምሮ ሌሎችም የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች ተሳትፈዋል። በጉብኝቱ ወቅት ለከፍተኛ የሥራ ኃለፊዎቹ ገለፃ ያደረጉት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢንጅነሪንግና ኮንስትራክሽን ቢዝነስ ዘርፍ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር ውድነህ የማነ እንደተናገሩት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው ግንባታ የመጨረሻው ምዕራፍ ላይ ደርሷል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ከፍተኛ-የመንግሥት-የሥራ-ኃላፊዎች-የኃይ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 13 ቀን 2018 ዓ.ም

ለአየር ንብረት ደህንነት ቅድሚያ መስጠት …..//….. የኤሌክትሪክ ኃይል መሠረተ ልማቶችን ስንገነባ ለአካባቢ ጥበቃና ለአየር ንብረት ደህንነት ሁሌም ቅድሚያ እንሰጣለን! የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል
ለአየር ንብረት ደህንነት ቅድሚያ መስጠት …..//….. የኤሌክትሪክ ኃይል መሠረተ ልማቶችን ስንገነባ ለአካባቢ ጥበቃና ለአየር ንብረት ደህንነት ሁሌም ቅድሚያ እንሰጣለን! የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከኮፕ 32 (COP32) መርሆች ጋር ሙሉ በሙሉ የተገጣጠሙ አረንጓዴ ፕሮጀክቶችን በመቅረጽ ለአካባቢያችን ዘላቂ ጥበቃ እያደረገ ይገኛል። 🌿 #COP32 #ለአየርንብረትደህንነት #EEP #EcoFriendly #GreenProjects 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 13 ቀን 2018 ዓ.ም

ማከፋፊያ ጣቢያው በአካባቢው መኖሩ የከተማዋን ኢኮኖሚ አነቃቅቷል …..//….. የቦንጋ ማከፋፈያ ጣቢያ የከተማዋን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ማነቃቃቱን የቦንጋ ከተማ ከንቲባ ተክለአብ ቡሎ (ዶ/ር
+4
ማከፋፊያ ጣቢያው በአካባቢው መኖሩ የከተማዋን ኢኮኖሚ አነቃቅቷል …..//….. የቦንጋ ማከፋፈያ ጣቢያ የከተማዋን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ዕድገት ማነቃቃቱን የቦንጋ ከተማ ከንቲባ ተክለአብ ቡሎ (ዶ/ር) ተናገሩ፡፡ በከተማዋ የሚገኘው የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ለአካባቢው የኢኮኖሚ መነቃቃት ለኢንቨስትመንት መስፋፋትና ለአገልግሎት ሰጪ ተቋማት መበራከት ከፍተኛ ሚና መጫወቱንም ከንቲባው ገልፀዋል። በከተማው አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት በመኖሩ በተለያዩ ዘርፎች ኢንቨስትመንቶች እንዲስፋፉ ትልቅ መነቃቃት የፈጠረ መሆኑን የገለፁት ከንቲባው በተለይ ደረጃቸውን የጠበቁ ሆቴሎችና የተለያዩ ማህበራዊ አገልግሎት ሰጪ ተቋማት በየአቅጣጫው እንዲበራከቱ እና የማህበራዊ ግንኙነቶች እንዲጠናከሩ ማድረጉንም ተክለአብ አድርጓል (ዶ/ር) አስረድተዋል። ከ10 ዓመታት በፊት በከተማዋ ታሪክ የነበረውን የግል የጤና ተቋማት እጥረት በመጥቀስ በአሁኑ ወቅት የኃይል አቅርቦቱ አስተማማኝ በመሆኑ በርካታ የግል ጤና ጣቢያዎችና ሆስፒታሎች በስፋት እየተገነቡ እንደሚገኙ አስታውቀዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ማከፋፊያ-ጣቢያው-በአካባቢው-መኖሩ-የከተ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 13 ቀን 2018 ዓ.ም

ኦፕሬሽን፣ የጥገና ሥራዎች እና ዘላቂነት ......///...... የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎቻችንን በዘላቂነት ማስተዳደር፣ የኦፕሬሽን እና የጥገና ሥራዎችን በላቀ ቴክኖሎጂ ማከናወን ዋነኛ ተግባራችን ነ
ኦፕሬሽን፣ የጥገና ሥራዎች እና ዘላቂነት ......///...... የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎቻችንን በዘላቂነት ማስተዳደር፣ የኦፕሬሽን እና የጥገና ሥራዎችን በላቀ ቴክኖሎጂ ማከናወን ዋነኛ ተግባራችን ነው። ይህ አሠራራችን በኮፕ 32 (COP 32) የአየር ንብረት ጉባኤ ላይ በስፋት የሚነሳውን "የመሠረተ-ልማት ዘላቂነት" (Infrastructure Sustainability) በተግባር ያረጋገጠ መሆኑን ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ እናሳያለን። #COP32 #ኦፕሬሽንናጥገና #ዘላቂነት #Sustainability #EEP 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ.ም

ተቋሙ የአካባቢውን የኃይል አቅርቦት ችግር ለመፍታት ትኩረት ሰጥቶ ይሰራል- ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ....///..... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በእንጅባራና አካባቢው የሚስተዋለውን የኃይል አቅር
+9
ተቋሙ የአካባቢውን የኃይል አቅርቦት ችግር ለመፍታት ትኩረት ሰጥቶ ይሰራል- ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ....///..... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በእንጅባራና አካባቢው የሚስተዋለውን የኃይል አቅርቦት ችግር በዘላቂነት ለመፍታት ትኩረት ሰጥቶ እንደሚሰራ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ ገለፁ፡፡ ዋና ሥራ አስፈፃሚው የእንጅባራና የዳንግላ ከተሞችን ወክለው ከመጡ የሕዝብ እንደራሴዎች፣ ከንግድ ማኅበራት ምክር ቤትና ከተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች ተወካዮች ጋር በአካባቢው የኃይል አቅርቦት ችግሮችና መፍትሔዎቻቸው ዙሪያ ተወያይተዋል፡፡ በውይይቱ ወቅት የአካባቢው ተወካዮች እንደገለጹት የኃይል አቅርቦት ችግሩ በየጊዜው እየተባባሰ በመምጣቱ ምክንያት ኅብረተሰቡ ለተለያዩ ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውሶች እየተዳረገ ይገኛል። ይህም በአካባቢው በተለያዩ የኢንቨስትመንት ዘርፎች ላይ በተሰማሩ ባለሀብቶችና በነዋሪው የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ ላይ አሉታዊ ተፅዕኖ እያሳደረ መሆኑን ተወካዮቹ አስገንዝበዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ተቋሙ-የአካባቢውን-የኃይል-አቅርቦት-ችግ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 11 ቀን 2018 ዓ.ም

ለአየር ንብረት ደህንነት ቅድሚያ መስጠት ….///…. የኤሌክትሪክ ኃይል መሠረተ ልማቶችን ስንገነባ ለአካባቢ ጥበቃና ለአየር ንብረት ደህንነት ሁሌም ቅድሚያ እንሰጣለን! የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል
ለአየር ንብረት ደህንነት ቅድሚያ መስጠት ….///…. የኤሌክትሪክ ኃይል መሠረተ ልማቶችን ስንገነባ ለአካባቢ ጥበቃና ለአየር ንብረት ደህንነት ሁሌም ቅድሚያ እንሰጣለን! የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከኮፕ 32 (COP32) መርሆች ጋር ሙሉ በሙሉ የተገጣጠሙ አረንጓዴ ፕሮጀክቶችን በመቅረጽ ለአካባቢያችን ዘላቂ ጥበቃ እያደረገ ይገኛል። 🗺🌿 #COP32 #ለአየርንብረትደህንነት #EEP #EcoFriendly #GreenProjects 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 10 ቀን 2018 ዓ.ም

ለአየር ንብረት ደህንነት ቅድሚያ መስጠት ….///…. የኤሌክትሪክ ኃይል መሠረተ ልማቶችን ስንገነባ ለአካባቢ ጥበቃና ለአየር ንብረት ደህንነት ሁሌም ቅድሚያ እንሰጣለን! የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል
ለአየር ንብረት ደህንነት ቅድሚያ መስጠት ….///…. የኤሌክትሪክ ኃይል መሠረተ ልማቶችን ስንገነባ ለአካባቢ ጥበቃና ለአየር ንብረት ደህንነት ሁሌም ቅድሚያ እንሰጣለን! የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከኮፕ 32 (COP32) መርሆች ጋር ሙሉ በሙሉ የተገጣጠሙ አረንጓዴ ፕሮጀክቶችን በመቅረጽ ለአካባቢያችን ዘላቂ ጥበቃ እያደረገ ይገኛል። 🗺🌿 #COP32 #ለአየርንብረትደህንነት #EEP #EcoFriendly #GreenProjects 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 10 ቀን 2018 ዓ.ም

ከተቋሙ ጋር በአቅም ግንባታ ዙሪያ ተባብሮ ለመሥራት ዝግጁ ነኝ፤ ምህረት ደበበ (ዶ/ር) ….///…. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሚያከናውናቸው የኃይል መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች አስተዳደርና በሌሎች
+1
ከተቋሙ ጋር በአቅም ግንባታ ዙሪያ ተባብሮ ለመሥራት ዝግጁ ነኝ፤ ምህረት ደበበ (ዶ/ር) ….///…. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሚያከናውናቸው የኃይል መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች አስተዳደርና በሌሎች የአቅም ግንባታ ጉዳዮች ዙሪያ ከተቋሙ ጋር ተባብረው ለመሥራት ዝግጁ መሆናቸውን የቀድሞው የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አሥፈፃሚ ገለፁ፡፡ የቀድሞው ዋና ሥራ አሥፈፃሚ ምህረት ደበበ (ዶ/ር) እንደገለጹት ተቋሙ የኃይል ተደራሽነትን በማረጋገጥ የአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል ለመሆን በመላ ሀገሪቱ በርካታ የኃይል መሰረተ ልማት ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል፡፡ እነዚህ የመሰረተ ልማት ሥራዎች ዘመኑን የሚመጥኑና ነገን ታሳቢ ያደረጉ እንዲሆኑ የባለሙያዎችን አቅም መገንባት ወሳኝ መሆኑን ያነሱት ዶ/ር ምህረት እርሳቸውም በፕሮጀክት አመራርና አስተዳደር እንዲሁም በተቋማዊ አቅም ግንባታ ዙሪያ ሥልጠናዎችን ለመስጠትና ያላቸውን የካበተ ልምድ ለማካፈል ዝግጁ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡ ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ከተቋሙ-ጋር-በአቅም-ግንባታ-ዙሪያ-ተባብሮ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 10 ቀን 2018 ዓ.ም

የውጤት ማስታወቂያ ......///...... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በጄንደርና ሶሻል አፌየርስ አፌርስ -5ኛ (Gender and Social Affairs Expert V) የስራ መደብ ሠራተኞችን አ
የውጤት ማስታወቂያ ......///...... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በጄንደርና ሶሻል አፌየርስ አፌርስ -5ኛ (Gender and Social Affairs Expert V) የስራ መደብ ሠራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር የካቲት 05 ቀን 2018 ዓ.ም. በአዲስ ዘመን ጋዜጣ የውጭ ማስታወቂያ የወጣ መሆኑ ይታወቃል፡፡ በመሆኑም ከቀረቡት አመልካቾች መካከል ዝቅተኛ መስፈርቱን በማሟላት ያለፉት ተወዳዳሪዎች የጽሁፍ ፈተና ግንቦት 21/2018 ዓ.ም. ወስደው ፈተናውን ያለፉ ተወዳዳሪዎች ግንቦት 26/2018 ዓ.ም. የቃል ፈተና ወስደዋል፡፡ በመሆኑም የተወዳዳሪዎች አጠቃላይ የጽሁፍና የቃል ፈተና ውጤት ዝርዝር ከዚህ በታች የተገለፀ ሲሆን በውጤቱ ላይ ቅሬታ ያላችሁ ተወዳዳሪዎች ውጤቱ ከተገለጸበት ቀን ጀምሮ ባሉት 5 (አምስት) ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ ቅሬታችሁን ማቅረብ የምትችሉ መሆኑን :: 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 9 ቀን 2018 ዓ.ም

የባህርዳር-ወልዲያ-ኮምቦልቻ የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ ፕሮጀክትን ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው የባህርዳር-ወልዲያ-ኮምቦልቻ ባለ 400 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት የተለያዩ
+6
የባህርዳር-ወልዲያ-ኮምቦልቻ የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ ፕሮጀክትን ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው የባህርዳር-ወልዲያ-ኮምቦልቻ ባለ 400 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ፕሮጀክት የተለያዩ ፈታኝ ሁኔታዎችን በፅናት በማለፍ ወደ ማጠናቀቂያው ምዕራፍ መሸጋገሩ ተገልፀ የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ አቶ አሸናፊ ሙሉ ብርሃን እንደገለፁት ከባህርዳር እስከ ወልዲያ ያለውን 296 ኪሎ ሜትር የሚረዝመውን የፕሮጀክት አካል ለማጠናቀቅ በአሁን ወቅት የቀረው 5 ኪሎ ሜትር ብቻ ነው። ፕሮጀክቱ በተያዘው በጀት ዓመት ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ከኃይል ጋር እንዲገናኝ ከፍተኛ ርብርብ እየተደረገ ባለበት በዚህ ወቅት በሰሜን ወሎ ዞን መቄት ወረዳ ልዩ ስሙ አግሪት በተባለ አካባቢ በሰባት የኃይል ተሸካሚ ምሰሶዎች (ታወሮች) እና በ2 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር በሚገመት ኮንዳክተር ላይ ጉዳት አጋጥሟል። ይህ የደረሰው ጉዳት በቀሪ ስራዎች ላይ የራሱን ተፅዕኖ አሳድሯል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=የባህርዳር-ወልዲያ-ኮምቦልቻ-የከፍተኛ-ኃ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 9 ቀን 2018 ዓ.ም

ተቋሙ የኃይል አቅርቦትን ለማስፋት በርካታ ስራዎች እያከናወነ ነው .....///..... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የኃይል አቅርቦት ተደራሽነትን ለማስፋት በርካታ ስራ
ተቋሙ የኃይል አቅርቦትን ለማስፋት በርካታ ስራዎች እያከናወነ ነው .....///..... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች የኃይል አቅርቦት ተደራሽነትን ለማስፋት በርካታ ስራዎችን እያከናወነ መሆኑን አስታወቀ። በተቋሙ የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያ ዳይሬክተር ተወካይ ወ/ሮ ሃይማኖት ገበየሁ እንደተናገሩት ተቋሙ ከደብረ ማርቆስ እስከ ባህር ዳር ባለው ኮሪደር ላይ የተለያዩ የኃይል መሠረተ ልማት ግንባታዎችን እያከናወነ ይገኛል። ከተከናወኑ ተግባራት መካከልም የደጀን - ደብረ ማርቆስ የ230 ኪሎ ቮልት ማከፋፈያ እና ማስተላለፊያ መስመር ግንባታ በቅርቡ ተጠናቆ ወደ ሥራ መግባቱ በዋና ማሳያነት ተጠቃሽ ነው። በዚሁ ኮሪደር ውስጥ እየተገነባ የሚገኘውና አጠቃላይ አፈፃፀሙ ከ55 በመቶ በላይ የደረሰው የቡሬ አግሮ ኢንዱስትሪ ባለ 230 ኪ.ቮ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ሌላኛው ማሳያ መሆኑን ወ/ሮ ሃይማኖት ገልፀዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=ተቋሙ-የኃይል-አቅርቦትን-ለማስፋት-በርካ&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 9 ቀን 2018 ዓ.ም

በማከፋፈያ ጣቢያ የተተከለው የጂአይኤስ (GIS) ቴክኖሎጂ የኦፕሬሽን ሥራዎችን እያቀላጠፈ ነው በበደሌ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በሰኔ 2016 ዓ.ም የተተከለው የጂአይኤስ (GIS
+4
በማከፋፈያ ጣቢያ የተተከለው የጂአይኤስ (GIS) ቴክኖሎጂ የኦፕሬሽን ሥራዎችን እያቀላጠፈ ነው በበደሌ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በሰኔ 2016 ዓ.ም የተተከለው የጂአይኤስ (GIS) መቆጣጠሪያ ብሬከር የኦፕሬሽንና የጥገና ሥራዎችን በማዘመን ረገድ ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን የጣቢያዉ ኃላፊ አቶ ሲሳይ ቀኖ ተናገሩ በቡኖ በደሌ ዞን የሚገኛውና በ1981 ዓ.ም. አገልግሎት መስጠት የጀመረው ይህ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ የኤሌክትሪክ ብልሽትንና አደጋን ሙሉ በሙሉ በሚከላከለው በዚህ ዘመናዊ የጋዝ መቆጣጠሪያ ሥርዓት (GIS) በመታገዙ የአካባቢውን እያደገ የመጣ የኃይል ፍላጎት በአስተማማኝ ሁኔታ ማሟላት መቻሉን  ኃላፊው ተናግረዋል። ጣቢያው ቀደም ሲል በነበረው አንድ ትራንስፎርመር ላይ የአቅም ማሳደግ ሥራዎችን በማከናወን አጠቃላይ የትራንስፎርመር ቁጥሩን ወደ አራት ያሳደገ ሲሆን ይህም ወደ ተለያዩ አካባቢዎች በቂ ኃይል ለማስተላለፍ ሰፊ ዕድል ፈጥሯል ብለዋል። ተጨማሪ ለማንበብ… https://www.eep.com.et/?amh-news=በማከፋፈያ-ጣቢያ-የተተከለው-የጂአይኤስ-gis&lang=am 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክ↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም