ch
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

前往频道在 Telegram

EEP Communication

显示更多

📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览

频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 546 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 351,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 178

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 546 名订阅者。

根据 02 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 27,过去 24 小时变化为 8,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 25.76%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.84% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 005 次浏览,首日通常累积 2 463 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 9

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
EEP Communication

凭借高频更新(最新数据采集于 03 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。

15 546
订阅者
+824 小时
-227
+2730
帖子存档
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1497ኛው የመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ መልካም ምኞቱን ይገልፃል፡፡ በዓሉ የሰላም፣ የጤና እና የፍቅር እንዲሆንላችሁ
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለመላው የእስልምና እምነት ተከታዮች እንኳን ለ1497ኛው የመውሊድ በዓል በሰላም አደረሳችሁ መልካም ምኞቱን ይገልፃል፡፡ በዓሉ የሰላም፣ የጤና እና የፍቅር እንዲሆንላችሁ ይመኛል፡፡ ኢድ ሙባረክ!! የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et

ሙስናና ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከልና በሥነ- ምግባር የታነፀ ሠራተኛና የሥራ መሪ ለመፍጠር እየተሠራ ነው ………///……… የሙያ ሥነ ምግባር እንዲዳብርና የተቋሙ ሀብትን ለታለመለት ዓላማ እንዲውል በማድረግ ሁሉም ኃላፊነቱን በአግባቡ እንዲወጣ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥነ ምግባርና የፀረ ሙስና መከታተያ ክፍል ሥራ አስፈፃሚ ገለፁ፡፡ ሥራ አስፈጻሚው አቶ መርጋ ተረፈ እንደገለጹት ሙስናና ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከልና በሥነ- ምግባር የታነፀ ሠራተኛና የሥራ መሪ ለመፍጠር እየተሠራ ነው፡፡ በሥነ-ምግባር ጥሰትና በብልሹ አሰራር የሚከሰቱ የዲሲፕሊን ችግሮች ላይ ምርመራ በማድረግ ተጠያቂነት እንዲሰፍን እና የአሰራር ጥናት በማድረግ ክፍተት ያለባቸው አሰራሮች እንዲታረሙ የማድረግ ሥራ መጀመሩን ተናግረዋል፡፡ አቶ መርጋ እንዳሉት በሥነ ምግባር የታነፀና ሙስናን የሚፀየፍ ሠራተኛ ለመፍጠር እንዲሁም በተቋሙ ውስጥ የሚፈፀሙ የሙስና እና የብልሹ አሰራሮችን በመጠቆምና በማጋለጥ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች የፀረ-ሙስና ትግሉ አካል እንዲሆኑ ለማድረግ የሚያስችል የአሰራር ስርዓት ተዘርግቷል፡፡ የተቋሙ ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች ኃላፊነታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ፤ ደንቦችና መመሪያዎች በአግባቡ ሥራ ላይ እንዲውሉ፤ የሙስና ወንጀልና ብልሹ አሰራር እንዲያጋልጡና በሚመለከተው አካል እንዲመረመር እንዲሁም በአጥፊዎች ላይ ተገቢው የእርምት እርምጃ እንዲወሰድ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ እንደሚገኝ ገልፀዋል፡፡ በ2014 በጀት ዓመት ለ780 ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች የሥነ - ምግባር ግንባታ ላይ ያተኮረ ሥልጠና መሰጠቱን ያነሱት አቶ መርጋ በ2015 በጀት ዓመት ለ800 የተቋሙ ሠራተኞችና የሥራ ኃላፊዎች ልዩ ልዩ የግንዛቡ መፍጠሪያ ሥልጠናዎች ለመስጠት መታቀዱን አስታውቀዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ ለሙስና ተጋላጭ ናቸው ተብለው በተለዩ የሥራ ክፍሎች ላይ ትኩረት በማድረግ የሙስና መከላከል ሥራ እንደሚሰራም ጠቁመዋል፡፡ በ2014 በጀት ዓመት በፋይናንስ የክፍያ ሥርዓት፤ በፕሮጀክቶች እና ኦፕሬሽን መካከል በሚካሄድ የንብረት ርክክብ፤ በሚወገዱ የተቋሙ ንብረቶች እንዲሁም በውጪ ሥልጠና አመራረጥ ላይ የአሰራር ጥናት በማድረግ ክፍተቶች እንዲታረሙ መደረጉን አቶ መርጋ አስታውሰዋል፡፡ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ለዘርፉ የቀረቡ ጥቆማዎችን መሰረት በማድረግ የተለያየ የዲሲፕሊን ችግር የታየባቸውን አንድ የሥራ ኃላፊና ሰባት ሠራተኞች ከጽሁፍ ማስጠንቀቂያ እስከ ሥራ ማሰናበት የሚደርስ እርምጃ እንዲወሰድ ማድረጉን እና ከድርጅቱ አላግባብ የተወሰደ ከ3 መቶ ሺህ በላይ ለማስመለስ ጉዳዩ በፍርድ ቤት መያዙን ከሥራ ክፍሉ ያገኘነው መረጃ ይጠቁማል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 27 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content

ከሀገር ውስጥ የኃይል አቅርቦትና ከፋይበር ኦፕቲክስ ኪራይ ከ2 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ ተገኝቷል ………////……… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ባለፉት ሁለት ወራት ከሀገር ውስጥ የኃይል አቅርቦትና ከፋይበር ኦፕቲክስ (OPGW) ኪራይ ከ2 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በላይ ሽያጭ ማከናወኑን የማርኬቲንግና ቢዝነስ ልማት መምሪያ አስታወቀ፡፡ በመምሪያው የሽያጭና ደንበኞች አስተዳደር ሥራ አስኪያጅ አቶ ምኒሊክ ጌታሁን እንዳስታወቁት በሐምሌና ነሐሴ ወራት ከሀገር ውስጥ የኃይል ሽያጭ እና ከፋይበር ኦፕቲክስ ኪራይ ከ2 ነጥብ 74 ቢሊዮን ብር በላይ ሽያጭ ተከናውኗል፡፡ ይህም ከዕቅዱ የ1 ነጥብ 5 በመቶ ወይም የ40 ነጥብ 64 ሚሊዮን ብር ብልጫ እንዳለው ለማወቅ ተችሏል፡፡ ከተከናወነው ሽያጭ ውስጥ ከ2 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር በላይ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት፣ ከ158 ነጥብ 85 ሚሊዮን ብር በላይ ለከፍተኛ የኃይል ተጠቃሚ ኢንዱስትሪዎች፣ ከ62 ነጥብ 61 ሚሊዮን ብር በላይ ለኢትዮ - ጅቡቲ ምድር ባቡር የኃይል አቅርቦት የተከናወነ ሽያጭ ነው፡፡ የፋይበር ኦፕቲክስ ለኢትዮ ቴሌኮም፣ ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ እና ዌብስፕሪክስ አይ ቲ ሶሉሽን ለተባሉ ኩባንያዎች በማከራየት ከ18 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ መገኘቱን ሥራ አስኪያጁ ገልፀዋል፡፡ ከሀገር ውስጥ የኃይል ሽያጭ ለማግኘት ከታቀደው መካከል የኢትዮ - ምድር ባቡር ከዕቅዱ የ170 በመቶ እንዲሁም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከዕቅዱ 0 ነጥብ 45 በመቶ ብልጫ ያለው ሲሆን የከፍተኛ ኃይል ተጠቃሚዎች ደግሞ የ7 ነጥብ 37 በመቶ ቅናሽ ማሳየቱን ነው የተገለጸው፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለጻ ባለፉት ሁለት ወራት ለሀገር ውስጥ 2 ነጥብ 1 ቢሊዮን ኪሎ ዋት ሰዓት ኃይል በመሸጥ የዕቅዱን 97 በመቶ ማሳካት ተችሏል፡፡ በዚህ መሰረት ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ከ1 ነጥብ 95 ቢሊዮን ኪሎ ዋት ሰዓት፣ ለከፍተኛ ኢንዱስትሪዎች ከ132 ነጥብ 88 ሚሊዮን ኪሎ ዋት ሰዓት እንዲሁም ለኢትዮ- ጂቡቲ ምድር ባቡር ከ13 ነጥብ 61 ሚሊዮን ኪሎ ዋት ሰዓት በላይ የኤሌክትሪክ ኃይል መሸጡንም አቶ ምኒሊክ አስታውቀዋል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 26 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+1

1.jpg0.15 KB

ማመንጫ ጣቢያው በበጀት ዓመቱ 220 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ለማመንጨት አቅዷል ……..////……. የጢስ አባይ 2 የኃይል ማመንጫ ጣቢያ በተያዘው የ2015 በጀት ዓመት 220 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት ማቀዱን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ገለጹ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ደጀኔ ጉታ እንደገለጹት ዕቅዱን ለማሳካትና የኦፕሬሽን ሥራውን አስተማማኝ ለማድረግ መደበኛና ድንገተኛ የጥገና ሥራዎች በዕቅድ እየተመሩ በመሰራት ላይ ናቸው፡፡ አቶ ደጀኔ እንዳሉት በበጀት ዓመቱ ዕቅድ ላይ ከሠራተኞች እና ከሥራ መሪዎች ጋር ውይይት በማድረግ በዕቅዱ ላይ መግባባት ተፈጥሮ ወደ ሥራ ተገብቷል፡፡ በክረምቱ ወራት የሚፈጠረዉን ከፍተኛ የዉሃ አቅም በመጠቀም ተርባይኖቹ በሙሉ አቅማቸዉ እንዲሰሩ በመደረጉ ያለፉት ሁለት ወራት አፈፃፀምም የበጀት ዓመቱን ዕቅድ ማሳካት እንደሚቻል አመላክቷል ብለዋል፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ ባለፈው ዓመት የጣቢያው ዩኒቶች በራስ ኃይል በመጠገናቸው ተርባይኖቹ በአስተማማኝ ሁኔታና በሙሉ አቅማቸው ኃይል እያመነጩ ነው፡፡ በተያዘው በጀት ዓመት በገበያ ላይ በቀላሉ ሊገኙ የማይችሉ እና ከፍተኛ ወጪ የሚያስወጡ የመለዋወጫ ዕቃዎችን በራስ ኃይል በሌላ የመተካት (የሞዲፊኬሽን) ሥራ በመስራት ተቋሙን ከወጪ ለመታደግ መታቀዱን ተናግረዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ የኤሌክትሮ መካኒካል ክፍሎች በሆኑት የቮልቴጅ መቆጣጠሪያ (ኤግዛይቴሽን ሲስተም)፣ የተርባይን ፍሪኩዌንሲ መቆጣጠሪያ (ገቨርነር ሲስተም) እና ኮንትሮሊንግ ሲስተሙ ላይ የጥገና ሥራዎችን ለመስራት እቅድ መያዙንም ኃላፊው ጠቁመዋል፡፡ የጢስ አባይ ማመንጫ ጣቢያ ባለፈው የበጀት ዓመት 157 ነጥብ 8 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ለማመንጨት አቅዶ 182 ነጥብ 3 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት መቻሉን ከጣቢያው ያገኘነው መረጃ ይጠቁማል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 23 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content

ማመንጫ ጣቢያው በበጀት ዓመቱ 220 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ለማመንጨት አቅዷል ……..////……. የጢስ አባይ 2 የኃይል ማመንጫ ጣቢያ በተያዘው የ2015 በጀት ዓመት 220 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት ማቀዱን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ገለጹ፡፡ ሥራ አስኪያጁ አቶ ደጀኔ ጉታ እንደገለጹት ዕቅዱን ለማሳካትና የኦፕሬሽን ሥራውን አስተማማኝ ለማድረግ መደበኛና ድንገተኛ የጥገና ሥራዎች በዕቅድ እየተመሩ በመሰራት ላይ ናቸው፡፡ አቶ ደጀኔ እንዳሉት በበጀት ዓመቱ ዕቅድ ላይ ከሠራተኞች እና ከሥራ መሪዎች ጋር ውይይት በማድረግ በዕቅዱ ላይ መግባባት ተፈጥሮ ወደ ሥራ ተገብቷል፡፡ በክረምቱ ወራት የሚፈጠረዉን ከፍተኛ የዉሃ አቅም በመጠቀም ተርባይኖቹ በሙሉ አቅማቸዉ እንዲሰሩ በመደረጉ ያለፉት ሁለት ወራት አፈፃፀምም የበጀት ዓመቱን ዕቅድ ማሳካት እንደሚቻል አመላክቷል ብለዋል፡፡ እንደ ሥራ አስኪያጁ ገለፃ ባለፈው ዓመት የጣቢያው ዩኒቶች በራስ ኃይል በመጠገናቸው ተርባይኖቹ በአስተማማኝ ሁኔታና በሙሉ አቅማቸው ኃይል እያመነጩ ነው፡፡ በተያዘው በጀት ዓመት በገበያ ላይ በቀላሉ ሊገኙ የማይችሉ እና ከፍተኛ ወጪ የሚያስወጡ የመለዋወጫ ዕቃዎችን በራስ ኃይል በሌላ የመተካት (የሞዲፊኬሽን) ሥራ በመስራት ተቋሙን ከወጪ ለመታደግ መታቀዱን ተናግረዋል፡፡ በበጀት ዓመቱ የኤሌክትሮ መካኒካል ክፍሎች በሆኑት የቮልቴጅ መቆጣጠሪያ (ኤግዛይቴሽን ሲስተም)፣ የተርባይን ፍሪኩዌንሲ መቆጣጠሪያ (ገቨርነር ሲስተም) እና ኮንትሮሊንግ ሲስተሙ ላይ የጥገና ሥራዎችን ለመስራት እቅድ መያዙንም ኃላፊው ጠቁመዋል፡፡ የጢስ አባይ ማመንጫ ጣቢያ ባለፈው የበጀት ዓመት 157 ነጥብ 8 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ለማመንጨት አቅዶ 182 ነጥብ 3 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት መቻሉን ከጣቢያው ያገኘነው መረጃ ይጠቁማል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 23 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content

በሁለት የመቆፈሪያ ማሽኖች ጥልቅ ጉድጓድ ለመቆፈር በቀን በአማካይ እስከ 10 ሺህ ሊትር ነዳጅ ያስፈልጋል ………////…….. የከርሰ ምድር የእንፋሎት ጥልቅ ጉድጓድ ቁፋሮ ሥራ ለማከናወን ከፍተኛ የነዳጅ አቅርቦት እንደሚያስፈልገው በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአሉቶ ላንጋኖ ጂኦተርማል ፕሮጀክት አስታወቀ፡፡ የፕሮጀክቱ ምክትል ሥራ አስኪያጅ አቶ ልዑል አስፋወሰን እንዳስታወቁት በሁለት የጥልቅ ጉድጓድ መቆፈሪያ ማሽኖች የቁፋሮ ሥራ ለማከናወን በቀን በአማካይ እስከ 10 ኪዩቢክ ሜትር ወይም 10 ሺህ ሊትር ነዳጅ ያስፈልጋል፡፡ የከርሰምድር እንፋሎት ጉድጓዶችን የቁፍሮ ሥራ ሂደት ማቋረጥ የቴክኒክና የፋይናንስ ችግር ሊያስከትልና በሂደትም ብዙ ወጪ ሊያስወጣ ስለሚችል ቁፋሮው በነዳጅ እጥረት መስተጓጎል አይኖርበትም ብለዋል፡፡ በተያያዘ ዜና በአሉቶ 1 ሳይት እየተከናወነ ለሚገኘው የከርሰ ምድር እንፋሎት ልማት እና በቦቤሳ ሳይት እየተካሄደ ለሚገኘው የእንፋሎት ፍለጋ ጉድጓድ ቁፋሮ የተያዘው ጊዜ እስከ ቀጣዩ ዓመት ታህሳስ ወር ቢሆንም ሥራው ከተያዘው ጊዜ አስቀድሞ ሊጠናቀቅ እንደሚችል ተገልጿል፡፡ እንደ ምክትል ሥራ አስኪያጁ ገለፃ በፕሮጀክቱ እስከ ታህሳስ 2015 ድረስ እስከ አራት ተጨማሪ ጥልቅ የእንፋሎት ጉድጓዶችን በመቆፈር የእንፋሎት ምርት መጠኑን ለማሳደግ የሚያስችል ሥራ እየተሰራ ነው፡፡ የጉድጓድ ቁፋሮው ሥራ ከተጠናቀቀ በኋላ እንፋሎቱን ከጉድጓዶች የሚያሰባስብ የቧንቧ ኔትወርክ (Steam Gathering Pipe Line Network) ተዘርግቶ ወደ ኃይል ማመንጨት ሥራ እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡ የቁፋሮውን ሥራ መጠናቀቅ ተከትሎ የጉድጓዶቹን እንፋሎት የማመንጨት አቅም፣ የሙቀት ባህርይ እና ከእንፋሎቱ ጋር የሚወጣውን ፈሳሽ ዓይነት የሚለይ (Geo - Chemistry) ጥናት ከተካሄደ በኋላ ምን ዓይነት ተርባይን በምን ዓይነት ዲዛይን እንደሚያስፈልግ እንደሚወሰን ገልፀዋል፡፡ የአሉቶ የከርሰምድር እንፋሎት ቁፋሮ በላንጋኖ ሳይት እስከ 35 ሜጋ ዋት ለማመንጨት እየተሰራ ሲሆን ቦቤሣ በተባለው ሳይት ደግሞ የከርሰ ምድር እንፋሎት ፍለጋ ቁፋሮ በ 2 የሙከራ ጉድጓዶች የሚከናወን ይሆናል፡፡ የከርሰ ምድር እንፋሎት ኃይል ከታዳሽ የኃይል ምንጮች ጎራ የሚመደብ ሲሆን ኢትዮጵያም በዚህ ዘርፍ ያልተነካ እምቅ ሀብት እንዳላት መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ የፍለጋና የማልማቱ ሥራም በቂ የካፒታል አቅም፣ ቴክኖሎጂና የዓለም አቀፍ ተሞክሮ ሽግግርን ይጠይቃል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 20 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+2

ተቋሙ ከባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችለውን ስምምነት ተፈራረመ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከባህር ዳር ዩኒቨርስቲ ጋር በጋራ ለመስራት የሚያስችል የትብብር ሥምምነት ተፈራረመ፡፡ ስምምነቱን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ፕላኒንግ ሥራ አስፈፃሚ አቶ አንዷለም ሲዓ እና የባህር ዳር ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ፍሬው ተገኝ ተፈራርመዋል፡፡ ስምምነቱ በጥናትና ምርምር፣ በሰው ኃይል አቅም ግንባታ፣ በማማከር ሥራዎችና መሰል ጉዳዮች ላይ ትኩረትን ያደረገ መሆኑን በተቋሙ የሰው ኃይል ስልጠናና ልማት ዳይሬክተር ዶ/ር ወንድወሰን ካሳ ገልፀዋል፡፡ በዘርፉ ላይ የሚካሄዱ ጥናቶችን በጋራ ለመስራት እንደሚያስችል የጠቆሙት ዳይሬክተሩ በተቋሙ የሠው ኃይል አቅም ግንባታ ሥራዎች ላይ ከፍተኛ ሚና የሚጫወት ስምምነት መሆኑን አስረድተዋል፡፡ በኃይል ልማት ዘርፉ የሠለጠኑ ባለሙያዎችን ለማፍራት በሚሰራው ሥራ ላይ የራሱን አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት የተናገሩት ዳይሬክተሩ ስምምነቱ በሠው ኃይል አቅም ግንባታ ሂደት የተቋሙ ሠራተኞች በፓዎር ኢንጅነሪንግ የሦስተኛ ድግሪ ትምህርት እንዲያገኙ ዕድል የሚፈጥር ነው ብለዋል፡፡ በተጨማሪም የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች እና መምህራን በተቋሙ የሥራ ላይ ልምምድ የሚያደርጉበትን ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል፡፡ ስምምነቱ ለቀጣይ አምስት ዓመታት የሚቆይ ሲሆን ተቋሙ የያዘውን የረጅም እና የአጪር ጊዜ ዕቅድ ለማሳካት የሚያግዝ መሆኑን ዶ/ር ወንድወሰን ተናግረዋል፡፡ ተቋሙ ከዚህ በፊት ከጅማ ዩኒቨርሲቲ ጋር በጋራ መስራት የሚያስችለውን የትብብር ስምምነት መፈራረሙ የሚታወስ ነው፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 20 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content
+1

አሦሳ የኤሌክትሪክ ኃይል አገኘች በቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል አሶሳ ከተማ ከአራት ቀን በኋላ የኤሌክተሪክ ኃይል አገች፡፡ በከተማዋ በታወር ብረት ስርቆት ምክንያት ለአራት ቀናት ሙሉ በሙሉ ተቋርጦ የነበረው የኤሌክትሪክ ኃይል በተደረገው ጊዚያዊ ጥገና ከመስከረም 16 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ኃይል አንድታገኝ መደረጉን አቶ ተስፋዬ መንግስቱ የትራንስሚሽን መስመር ጥገና ቴክኒካል ሰፖርት ሥራ አስኪያጅ ገልፀዋል፡፡ የኃይል መቋረጥ የተከሰተው ከመንዲዳ አሶሳ በሚሄደው 132 ኬ.ቪ የትራንስሚሽን መስመር ከፍተኛ የኃይል ተሸካሚ መስመር በተደረገ ስርቆት ታወሮች መውደቅ ምክናንያት ነው፡፡ የወደቀውን ታወር በእንጨት በመቀየር የተቋማችን የምዕራብ ሪጅን ትራንስሚሽን ባለሙያዎች እና የኢትዮጵያ ኤሌክትክ አገልግሎት አሶሳ ቅርንጫፍ ባለሙያዎች ጋር በተደረገ ከፍተኛ ርብርብ ጥገናው መከናወኑን ሥራአስኪያጁ አሳውቀዋል፡፡ እንደ ስራ አስኪያጁ ገለፃ በክልሉ የሚፈፀም ተደጋጋሚ የመሰረተ ልማት ስርቆት ክልሉን ለተደጋጋሚ የኃይል መቋረጥ ዳርጎታል፡፡ ህብተሰቡ በመሰረተ ልማቶች ላይ የሚፈፀሙ ስርቆቶች የሚያደርሱትን ጫና ግንዛቤ ውስጥ በማስገባት ወንጀለኞችን ተከታትሎ ማጋለጥ እንዳለበት እና ክልሉም ወንጀለኞች ላይ ተገቢውን እርምጃ ሊወስድ እንደሚገባ የገለፁት አቶ ተስፋዬ የመሰረተ ልማት ስርቆት የሚፈጥረው ጫና በመረዳት የታወር ምሶሶዎችን ደህንነት ትኩረት ሰጥቶ እንዲያስጠብቅ አሳስበዋል፡፡ በጥገናው ወቅት የቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ስራ አስፈፃሚ አቶ ካሳሁን ከበደ ላደረጉት ከፍተኛ ድጋፍ የኢትዮጵያ አሌክትሪክ ኃይል ልባዊ ምስጋና ያቀርባል፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 17 ቀን 2015 ዓ.ም

photo content

photo content

photo content

photo content

photo content
+6