EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 546 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 351,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 178 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 546 名订阅者。
根据 02 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 27,过去 24 小时变化为 8,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 25.76%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.84% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 005 次浏览,首日通常累积 2 463 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 9。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 03 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 546
订阅者
+824 小时
-227 天
+2730 天
帖子存档
15 546
የፕሮጀክት አፈፃፀምን ለማሻሽል በተዘጋጀው የሥራ መምሪያ ረቂቅ ሰነድ ላይ ውይይት ተካሔደ
………/////………
ግንባታዎችን በተደራጀ መልኩ በማከናወን ውጤታማ የፕሮጀክት አፈፃፀም ለማስመዝገብ የሚያስችል የሥራ መምሪያ ረቂቅ ሰነድ ተዘጋጀ፡፡
የኃይል ማከፋፈያዎች እና ማስተላለፊያ መስመሮች ግንባታ ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት ለራስ ኃይል መምሪያ ባዘጋጀው የስራ መምሪያ ረቂቅ ሰነድ ላይ ከመምሪያው ሠራተኞች እና የሥራ ኃላፊዎች ጋር ውይይት አካሂዷል፡፡
የዘርፉ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ክብሮም ካህሳይ የረቂቅ ሰነዱን ይዘትና ዓላማ ለውይይት ሲያቀርቡ እንደተናገሩት ረቂቅ ሰነዱ ከሠራተኛ እና ከሥራ መሪዎች ምን እንደሚጠበቅና የሥራ መዘርዝሮችን በግልጽ አሳቀምጧል፡፡
ከዚህ ቀደም የተሰሩ ሥራዎች ቢኖሩም ያልተደራጁና ወጥ ባልሆነ መልኩ በመከናወናቸው የሚጠበቀውን ውጤት ማስመዝገብ አለመቻሉን ሥራ አስፈፃሚው ገልፀዋል፡፡
አዲስ የተዘጋጀውን የሥራ መመሪያ ረቂቅ ሰነድ በአግባቡ በመተግበር በኃይል ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ግንባታ ዘርፍ በኢትዮጵያ ብሎም በአፍሪካ ተወዳዳሪ አቅም መፍጠር እንደሚጠበቅ ሥራ አስፈፃሚው አሳስበዋል፡፡
በአዲሱ የአሰራር ሥርዓት የራስ ኃይል መምሪያ የራሱ የግዥ እና የንብረት ክፍል የሚኖረው ሲሆን ይህም በግዥ ሥርዓት መጓተት የተነሳ ይከሰት የነበረውን የፕሮጀክቶች አፈፃፀም ችግር እንደሚቀርፍ አስታውቀዋል፡፡
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሰው ኃይል ሥራ አስፈፃሚ አቶ አታላይ አበበ በበኩላቸው የግዥና የንብረት አስተዳደር አደረጃጀቶች በራስ ኃይል መምሪያ እንደ አዲስ መደራጀቱ ለአሰራር አመቺ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
አደረጃጀቱን ተከትሎ የሙስና እና ብልሹ አሰራሮችን ለመከላከል ጠንካራ የክትትልና ቁጥጥር ሥርዓት መዘርጋት አስፈላጊ ነው ብለዋል፡፡
እንደ ሥራ አስፈፃሚው ገለፃ ከሠራተኞችና ከሥራ መሪዎች የተነሱ ገንቢ ሀሳቦችን እንደ ግብዐት በመውሰድ ረቂቅ የሥራ መመሪያው ተግባራዊ ይደረጋል፡፡
የተቋሙ መሰረታዊ የሠራተኛ ማህበር ዋና ፀሐፊ አቶ ኃይሉ ወልዴ በቀጣይ የሚተገበሩ የጥቅማ ጥቅም ማዕቀፎች የሥራ አፈፃፀምን መሰረት የሚያደርጉ በመሆኑ ሠራተኞች በተቀመጠላቸው የሥራ መመሪያ ሰነድ መሠረት ውጤታማ ስራ ሊያከናወኑ እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡
የስብሰባው ተሳታፊዎች በተሸከርካሪና የግንባታ ማሽኖች፣ በፋይናንስ እና መረጃ አያያዝ ዙሪያ ጥያቄዎች አቅርበው በዘርፉ ኃላፊዎች ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 13 ቀን 2015 ዓ.ም
15 546
የአይሻ 2 ከንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ለአካባቢው ማህበረሰብ የሥራ ዕድል ፈጥሯል
………///………
በሶማሌ ክልል ሲቲ ዞን አይሻ ወረዳ እየተገባ የሚገኘው የአይሻ ሁለት የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ለአካባቢው ማህበረሰብ የሥራ ዕድል መፍጠሩን የፕሮጀክት ጽ/ቤት አስታወቀ።
የፕሮጀክቱ ምክትል አስተባባሪና የሳይት ሥራ አስኪያጅ አቶ ሙሉቀን ተሰማ እንደተናገሩት በአካባቢው በግንባታ ዘርፍ ላይ የተሰማሩ ንዑስ ሥራ ተቋራጮች በመኖራቸው የውሃ መስመር ዝርጋታ እና የሠራተኞች ቋሚ የመኖሪያ ቤት ግንባታ ሥራዎችን በመስጠት የሥራ ዕድል ተፈጥሮላቸዋል።
የግንባታ ሥራው ዶንግፋንግ ኤሌክትሪክ በተባለ የቻይና ኩባንያ እየተከናወነ መሆኑን የጠቆሙት ሥራ አስኪያጁ ለፕሮጀክቱ ሥራ የሚያስፈልገው የሰው ኃይል በወረዳው በተደራጀው የሠራተኞች ኤጀንሲ በኩል ሲቀርብ እንደነበር አውስተዋል።
ለግንባታው አስፈላጊ የሆኑ እንደ ገረጋንቲ፣ አሸዋ፣ ጠጠር፣ ማሽነሪዎችና ተሽከርካሪዎችን ለማቅረብ ደግሞ የግንባታ ግብዓት አቅራቢዎች እንዲኖሩ የማድረግ ሥራ በመሰራቱ በጥቅሉ ከ400 በላይ ለሆኑ ዜጎች ቋሚና ጊዜያዊ የሥራ ዕድሎች ተፈጥሯል ብለዋል።
የአካባቢው ተወላጆች በፕሮጀክቱ የተለያዩ የሥራ ዘርፎች ላይ ተሳታፊ እንዲሆኑ መደረጉ በቂ ልምድና አቅም እንዲያገኙ ያስቻለ መሆኑንና በቀጣይ በሚመጡ መሠል ፕሮጀክቶች ላይ ተሳታፊ የሚሆኑበትን ዕድል የፈጠረ መሆኑን ጠቅሰዋል።
ፕሮጀክቱ ይዞት ከመጣው የሥራ ዕድል ፈጠራ በተጨማሪ ማህበረሰቡ ፕሮጀክቱ የኔ ነው የሚል ስሜት እንዲፈጥር አድርጎታል ያሉት አቶ ሙሉቀን ፕሮጀክቱ አሁን ለደረሰበት ደረጃ እንዲደርስ ከወረዳ እስከ ክልል ያሉ አመራሮች ላበረከቱትን አስተዋፅኦ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
የአይሻ ወረዳ ከምስራቅ አፍሪካ ከፍተኛ እምቅ የንፋስ ኃይል ከሚገኘባቸው አካባቢዎች አንዱ ሲሆን በቀጣይም አይሻ አንድ እና ሦስት የሚል ስያሜ የተሰጣቸው ሁለት ፕሮጀክቶችን ለመተግበር የአዋጭነት ጥናቶች ተጠናቀዋል።
በአካባቢው ላይ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ መገንባቱ ለሀገሪቱ ልማት መፋጠን ከሚኖረው አዎንታዊ ሚና በተጨማሪ ኢንዱስትሪዎችን ለመሳብና የሥራ አጥ ቁጥርን በመቀነስ ለክልሉ ልማት መፋጠን ከፍተኛ አስተዋጽኦ ይጫወታል ተብሎ ይታመናል።
120 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያለው የአይሻ ሁለት የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት በኢትዮጵያ መንግስትና ከቻይና ኤግዚም ባንክ በተገኘ 270 ሚሊየን ዩሮ እየተገነባ የሚገኝ ፕሮጀክት ነው።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 13 ቀን 2015 ዓ.ም
15 546
ከፕሮጀክቱ እስካሁን 20 ሜጋ ዋት የከርሰምድር እንፋሎት ኃይል ተገኝቷል
……..////…….
ከአሉቶ ላንጋኖ ጥልቅ የከርሰ ምድር እንፋሎት ቁፋሮ ፕሮጀክት እስካሁን 20 ሜጋ ዋት የሚደርስ የእንፋሎት ኃይል መገኘቱን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የአሉቶ ጂኦተርማል ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ፡፡
ሥራ አስኪያጁ አቶ መሣይ ፍቃዱ እንደገለፁት እስካሁን ቁፋሯቸው ከተጠናቀቀና የምርት ፍተሻ ከተደረገላቸው አምስት ጥልቅ ጉድጓዶች መካከል በአራቱ 20 ሜጋ ዋት የእንፋሎት ኃይል ተገኝቷል፡፡
የጉድጓዶቹ ጥልቀት ከ 2700 እስከ 3000 ሜትር እንደሚደርስ የጠቀሱት ሥራ አስኪያጁ የ6ኛ እና የ7ኛ ጉድጓድ ቁፋሮ ስራም እየተከናወነ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ስራውም በዘመናዊ ቴክኖሎጂ የታገዘና የከርሰምድሩን የእንፋሎት መጠን ጥራትና ተደራሽነትን ከማረጋግጥ አኳያ እየተካሄደ ይገኛል፡፡
እንደ ሥራአስኪያጁ ገለፃ የ6ኛው ጉድጓድ ቁፋሮ 1300 ሜትር ጥልቀት ላይ ከደረሰ በኋላ የተቆፈረውን ጉድጓድ በሲሚንቶ የማሸግ (casing) ሥራ ላይ አነስተኛ ቴክኒካዊ ችግር በማጋጠሙ ሥራው ለጊዜው የቆመ ሲሆን የ7ኛው ጉድጓድ ቁፋሮ ግን በጥሩ ሁኔታ እየተካሄደ ይገኛል፡፡
ይሁንና ችግር ያጋጠመውን ጉድጓድ የቁፋሮ ሥራ ለማስቀጠል የሚያስችል የእቃ መለዋወጫ ሳይቱ ጋ ሲደርስ አስፈላጊው የጥገና ስራ ተደርጎለት የቁፋሮ ስራው የሚቅጥል መሆኑን ገልጸዋል፡፡
በአሉቶ 1 የከርሰ ምድር እንፋሎት ቁፋሮ ፕሮጀክት እስካሁን ከተገኘው 20 ሜጋ ዋት የእንፋሎት ኃይል በተጨማሪ 15 ሜጋ ዋት እንፋሎት ለማግኘት የሚያስችሉ ከ 2 እስከ 4 የሚሆኑ ጥልቅ ጉድጓዶች መቆፈር እንደሚያስፈልግ ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡
የጉድጓዶቹ ቁፋሮ ሥራ እንደተጠናቀቀ ወደ ኃይል ማመንጫ ፋሲሊቲ ግንባታ ፕሮጀክት እንደሚሸጋገርም ጠቁመዋል፡፡
ፕሮጀክቱ የሚጠቀማቸው ማሽኖች ነዳጅ በከፍተኛ መጠን የሚፈለጉ መሆናቸውና መለዋወጫ መሳሪያዎቹም ከውጪ ሀገር የሚገቡ መሆናቸው በቁፋሮ ሂደቱ ያጋጠሙ ዋና ዋና ተግዳሮቶች መሆናቸውን ሥራ አስኪያጁ ጠቅሰዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 13 ቀን 2015 ዓ.ም
15 546
የአይ ኤፍ አር ኤስ አሰራሮችን ሠራተኛው እንዲተዋወቃቸውና እንዲተገብራቸው እየተደረገ ነው
……..////……..
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እየተገበረው ባለው የአለም አቀፍ የፋይናንስ ሪፖርት አዘገጃጀትና አቀራረብ ሥርዓት ላይ የሚመጡ አዳዲስ አሰራሮችን ሠራተኛው እንዲተዋወቃቸውና እንዲተገብራቸው እየተደረገ መሆኑን በተቋሙ የንብረት ክለሳና አይ ኤፍ አር ኤስ ፕሮግራም መምሪያ ዳይሬክተር ገለፁ፡፡
ዳይሬክተሩ አቶ ይርጉ ኃይሉ እንደተናገሩት ከ41 ዓለም አቀፍ የሂሳብ አያያዝ መመዘኛ ደረጃዎች እና አይ ኤፍ አር ኤስ ካሉት 17 መመዘኛዎች መካከል በተቋሙ ተመርጠው እየተተገበሩ ባሉ 28 መመዘኛዎች ላይ ትኩረቱን ያደረገ ሥልጠና ለፋይንስ ባለሙያዎች ተሰጥቷል፡፡
የአይ ኤፍ አር ኤስ አሰራር ስርዓት በየጊዜው እየተሻሻለ የሚሄድ መሆኑን የጠቆሙት ዳይሬክተሩ የሚኖሩ ለውጦችን ለማሳወቅ እና ሠራተኞች ከአሠራሩ ጋር የሚሄድ ዕውቅት እንድጨብጡ ለማድረግ ሥልጠና አስፈላጊ መሆኑን አስታውቀዋል፡፡
ከመስከረም 5 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ በተለያዩ የሥራ ክፍሎች ለሚገኙ 115 የፋይናንስ ባለሙያዎች በሁለት ዙር 115 ለሚሆኑ ሠራተኞች ሥልጠና መሰጠቱንም ጠቁመዋል፡፡
ሠራተኞች ከሥልጠናው ያገኙትን ዕውቀት እንደ ሥራቸው ባህርይ በተግባር ላይ በማዋል ድርጅቱን ተወዳዳሪ ለማድረግ በትኩረት መስራት እንዳለባቸውም አሳስበዋል፡፡
የአይ ኤፍ አር ኤስ ፕሮጀክት ሥራ አስኪያጅ አቶ ሕሊና ገዛኸኝ በበኩላቸው አይ ኤፍ አር ኤስ እያደገ የሚሄድ እንጂ ያለቀለት የቆመ ስታንዳርድ ባለመሆኑ ቀጣይነት ያለው ትምህርትና ሥልጠና ያስፈልጋል ብለዋል፡፡
የሥልጠናው ተሳታፊዎች በበኩላቸው ሥልጠናው በሥራቸው ላይ እያጋጠሙ ያሉ ችግሮችን በመፍታት በኩል ከፍተኛ ፋይዳ እንዳለው ተናግረው ከርዕሰ ጉዳዩ ስፋት አንጻር ለሥልጠናው የተሠጠው ጊዜ አጭር በመሆኑ በቀጣይ ሰፊ ጊዜ ተይዞለት እንዲሰጥ ጠይቀዋል፡፡
ሥልጠናው ፕራይስ ወተር ሀውስ ኮፐርስ አሶሼትስ አፍሪካ ሊሚትድ በተሰኘ ዓለም አቀፍ ተቋም እንደተሰጠ ከዚህ ቀደም መዘገባችን ይታወሳል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 12 ቀን 2015 ዓ.ም
15 546
የኃይል ዘርፉን በጥናት ለማገዝ የሚያስችል የትብብር ስምምነት ተፈረመ
…….....///..........
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና ጅማ ዩኒቨርስቲ በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸው የትብብር ሥምምነት ተፈራረሙ፡፡
የትብብር ስምምነቱን የፈረሙት በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ፕላኒንግ ሥራ አስፈፃሚ አቶ አንዷለም ሲዓ እና በጅማ ዩኒቨርስቲ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር ረዳት ፕሮፌሰር ኤፍሬም ዋቅጅራ ናቸዉ።
የትብብር ስምምነቱ በኃይል ዘርፉ የሚታዩ ተግዳሮቶችን በጥናት ለይቶ መፍትሔ ለማስቀመጥ ፣ የቴክኖሎጂ ሽግግሮች እንዲኖሩ ለማድረግ ፣ በድኅረ ምረቃ የትምህርት ዘርፎችና በአጫጭር ሥልጠናዎች የሠራተኞችን አቅም ለማጎልበት ያለመ ነው፡፡
ስምምነቱ በምርምር ፣ በሰው ኃይል አቅም ግንባታና በማማከር ተግባራት ላይ ትኩረት የሚያደርግ ሲሆን ወደፊትም ከሌሎች ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑ ታውቋል።
ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር የሚካሄዱ ስምምነቶች ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ እንደሚኖራቸው በፊርማ ሥነ ሥርዓቱ ላይ ተገልጿል፡፡
በዋናነት በተቋሙ ስትራቴጂካዊ ዕቅድ ላይ በተቀመጠው አግባብ የስትራቴጂክ አጋርነት በመፍጠር የተቋሙን ተልዕኮ ለማሳካት ተጨማሪ አቅም ይፈጥራሉ ተብለዋል።
የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች የሥራ ላይ ልምምድ የሚያደርጉበትንና መምህራን በሴክተሩ ላይ ተግባራዊ ተሞክሮ የሚያገኙበትን ምቹ ሁኔታ በመፍጠር በኃይል ዘርፍ የተሻለ የአቅም ግንባታ ሂደት እንዲፈጠር እንደሚያስችል ታምኖበታል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 12 ቀን 2015 ዓ.ም
15 546
ጣቢያው በበጀት ዓመቱ ከአምናው የተሻለ ኃይል ለማምረት እየሰራው ነው አለ
………///……..
የአዳማ አንድ ንፋስ ኃይል ማመንጫ በ2015 በጀት ዓመት 137 ነጥብ 9 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል ለማመንጨት እየሰራ መሆኑን አስታወቀ።
የጣቢያው ኃላፊ ወ/ሮ ዓይናለም ወልደሚካኤል እንደገለፁት ጣቢያው በብልሽት የቆሙ የንፋስ ተርባይኖችን በወቅቱ በመጠገንና ወደ ሥራ በማስገባት የተሻለ ኃይል ለማምረት ተዘጋጅቷል።
ከኃይል ማምረት ጎን ለጎን የቅድመ መከላከል፣ የፍተሻ እና የጥገና ሥራዎችን በወቅቱ ለማከናወን መታቀዱንም ገልፀዋል።
በብልሽት ምክንያት የማይሰሩ የተርባይን መቆጣጠሪያ (አይጂቢቲ) እና የሲስተም ካርዶችን እንዲሁም ሞተሮችን በጣቢያው ወርክሾፕ በመጠገን የውጭ ምንዛሬ ለማስቀረት እንደሚሰራም ወ/ሮ አይናለም አስታውቀዋል።
እንደ ወ/ሮ ዓይናለም ገለፃ የሥራ ላይ ደህንነትን ለማስጠበቅ የሚያስችል አደረጃጀትና አሠራር ተግባራዊ በማድረግ ከአደጋ የፀዳ የሥራ ከባቢ ለመፍጠር የሚያስችል እንቅስቃሴ ተጀምሯል።
ለሥራ የሚያገለግሉ እንደ ስካዳ ያሉ የተለያዩ ሶፍትዌሮችን የማሻሻል እና የማዘመን ሥራዎች እንደሚሰራና የጣቢያውን ሠራተኞች የክህሎትና የዕውቀት አቅም ለመገንባትም ትኩረት መሰጠቱንም ኃላፊዋ ተናግረዋል።
የአዳማ አንድ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ባሳለፍነው በጀት ዓመት 133 ነጥብ 75 ጊጋ ዋት ሰዓት ማመንጨቱ ይታወሳል።
በአዳማ ከተማ አቅራቢያ የተገነባው የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያው በኢትዮጵያ የመጀመሪያው የንፋስ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ነው።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 11 ቀን 2015 ዓ.ም
15 546
በለገጣፎ-ደብረብርሃን-ኮምቦልቻ ባለ 230 ኪ.ቮ ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ የተከናወነው ጥገና ተጠናቀቀ
............////..........
በብልሽት ምክንያት ከአንድ ሳምንት በላይ ተቋርጦ የቆየው የለገጣፎ-ደብረብርሃን-ኮምቦልቻ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር በአስቸኳይ ተጠግኖ አገልግሎት እንዲሰጥ መደረጉን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያ ኦፕሬሽን ዘርፍ ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት አስታወቀ።
በጽ/ቤቱ የኃይል ማስተላለፊያዎች የቴክኒክ ድጋፍ ሥራ አስኪያጅ አቶ ተስፋዬ መንግስቱ እንደገለፁት ባለ 230 ኪሎ ቮልት መስመር ላይ ብልሽት በማጋጠሙ ምክንያት ባለ 132 ኪ.ቮ ሁለተኛ መስመርን በመጠቀም ለማህበረሰቡና ለፋብሪካዎች ኃይል ሲቀርብ ነበር።
ይሁንና ባለ 132 ኪሎ ቮልት መስመሩ በአማራጭ አገልግሎት እየሰጠ ቢቆይም ካለው ከፍተኛ የኃይል ፍላጎት አንፃር የኃይል መቆራረጥ ያጋጥም እንደነበር ጠቅሰዋል።
የባለ 230 ኪሎ ቮልት ዋናው መስመር ወደ አገልግሎት በመመለሱ የኃይል መቆራረጥ ችግሩን ሙሉ በሙሉ ይፈታዋል ብለዋል።
ችግሩ እንዳጋጠመ የጥገና ባለሙያዎችን በማደራጀት ወደ ሥራ የተገባ ሲሆን በአጠረ ጊዜ የፍተሻ እና የሰርኪዩት ቅያሪዎችን በማከናወን ወደ አገልግሎት እንዲመለስ መደረጉን ነው ሥራ አስኪያጁ የተናገሩት።
መስመሩ በጦርነቱ ምክንያት ከፋተኛ ጉዳት የደረሰበት በመሆኑ በቀጣይም ተከታታይ የፍተሻ እና የጥገና ሥራዎች እንደሚከናወኑለት አቶ ተስፋዬ አስታውቀዋል።
እንደኃላፊው ገለፃ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሩ ደብረብርሃን ከተማን ጨምሮ ለሰሜን ምስራቅ አማራ እና ለአፋር ክልል የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት ከፍተኛ ጠቀሜታ አለው።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 10 ቀን 2015 ዓ.ም
15 546
ንፋስ እና ስርቆት ለኃይል ተሸካሚ ምሶሶዎቹ መውደቅ ምክንያት ሆነዋል
........./////............
ከቃሊቲ -ገላን ማከፋፈያ ጣቢያ እና ከገላን ቃሊቲና ኢንዶዴ የባቡር ማከፋፈያ ጣቢያ ድረስ የተዘረጉ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ አራት ምሶሶዎች ኢንዶዴ በሚባል ቦታ ላይ በዝርፊያና በንፋስ የተነሳ ወደቁ።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያ ኦፕሬሽን የአዲስ አበባ ሪጅን የማስተላለፊያ መስመሮች ሥራ አስኪያጅ አቶ ከበደ ፉፋ እንደገለጹት የምሰሶዎቹ የተለያዩ አካላት ላይ ስርቆት ተፈጽሞባቸው ነበር።
በአካባቢው ተስተውሎ የነበረው ከፍተኛ ንፋስ ከስርቆቱ ጋር ተዳምሮ ለምሰሶዎቹ መውደቅ ምክንያት መሆኑን ተናግረዋል።
ከገላን ማከፋፈያ ጣቢያ የተዘረጋው መስመር በገላን ከተማ ለሚገኘው ለየሱ የብረት ፋብሪካ እና በኢንዶዴ ለሚገኘው የኢትዮ ጂቡቲ ምድር ባቡር የማከፋፈያ ጣቢያ እንዲሁም ለቃሊቲ ማከፋፈያ ጣቢያ ኃይል ሲያስተላልፍ እንደነበር ሥራ አስኪያጁ ገልፀዋል።
ይሁን እንጅ መስመሮቹ ኃይል ማስተላለፍ ካቋረጡ ከመስከረም 7ቀን 2015 ዓ/ም ጀምሮ ለየሱ የብረት ፋብሪካና ለኢንዶዴ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ከዚህ በፊት ተሰርተው በነበሩ አማራጭ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች አማካኝነት ኃይል ማቅረብ መቻሉን ጠቁመዋል፡፡
በዚህም የየሱ የብረት ፋብሪካ ከገላን ማከፋፈያ ጣቢያ እንዲሁም የኢንዶዴ ማከፋፈያ ጣቢያ ደግሞ ከቃሊቲ ማከፋፈያ ጣቢያ በቀጥታ ኃይል እንዲያገኙ ተደርጓል ብለዋል፡፡
የጥገና ሥራዉ ተከናዉኖ መስመሮቹ ኃይል ማስተላለፍ እስኪጀምሩ ድረስ ፋብሪካው እና የኢንዶዴ ማከፋፈያ ጣቢያ በዚሁ መልኩ ኃይል እያገኙ እንደሚቆዩ ሥራ አስኪያጁ አመልክተዋል፡፡
ኢንዶዴ የባቡር ማከፋፈያ ጣቢያ ከቃሊቲ ማከፋፈያ ጣቢያ በቀጥታ ኃይል እንዲያገኝ በመደረጉ በቃሊቲ ማከፋፈያ ጣቢያ ላይ መጨናነቅ ሊፈጠር እንደሚችል ጠቁመዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት በአካባቢው የአርሶ አደሮች አዝመራ በመኖሩና ቦታው ረግረጋማ በመሆኑ ተንቀሳቅሶ የጥገና ሥራውን ለማከናወን አስቸጋሪ ስለሆነ መሬቱ ሲደርቅና አዝመራው ሲነሳ ጥገናውን ለማከናወን መታሰቡን ገልጸዋል፡፡
በመስመሮቹ መቋረጥ የተነሳ በአሁኑ ወቅት የኤሌክትሪክ ኃይል የተቋረጠባቸው አካባቢዎች እንደሌሉም ሥራ አስኪያጁ አስታውቀዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 10 ቀን 2015 ዓ.ም
15 546
የጢስ አባይ 1ኛ ኃይል ማመንጫ ጣቢያን መልሶ ሥራ ለማስጀመር የሚያስችሉ ሥራዎች ሊጀመሩ ነው
…….////………
የጢስ አባይ 1ኛ ኃይል ማመንጫ ጣቢያን መልሶ ሥራ ለማስጀመር የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች መጀመራቸውን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ገለጹ፡፡
ሥራ አስኪያጁ አቶ ደጀኔ ጉታ እንደገለጹት የጣቢያውን የሰዉ ኃይል በማስተባበር እና ባለፈው ዓመት በጢስ አባይ 2ኛ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ የጥገና ሥራ የተገኘውን ልምድና እውቀት በማስተባበር ጣቢያውን መልሶ ሥራ ለማስጀመር ርብርብ ይደረጋል፡፡
በጢስ አባይ 2ኛ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ከስምንት ዓመታት በላይ ቆሞ የነበረን አንድ ዩኒት በራስ አቅም በመጠገን ባለፈው ዓመት ወደ ሥራ እንዲገባ መደረጉ ይታወሳል፡፡
በጥገና ሥራዉ ላይ የተሳተፉ ሠራተኞች ከፍተኛ ዕዉቀት እና ልምድ እንዲያገኙ ዕድል መፈጠሩን ያስታወሱት ሥራ አስኪያጁ ይኽም ተጨማሪ ኃይል እንዲገኝ አስተዋጽኦ ከማድረግ ባለፈ በሠራተኞች እና የሥራ መሪዎች ላይ ከፍተኛ የሆነ የይቻላል መንፈስን ፈጥሯል ብለዋል፡፡
የጢስ አባይ 1ኛ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ከ2002 ዓ.ም ጀምሮ አገልግሎት መስጠት ያቆመ ሲሆን እያንዳንዳቸው አራት ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያላቸው ሦስት ዩኒቶች አሉት፡፡
በአማራ ክልል ባህር ዳር አካባቢ የሚገኘው የጢስ አባይ 2ኛ ማመንጫ ጣቢያ እያንዳንዳቸው 36 ሜጋ ዋት የማመንጨት አቅም ያላቸው ሁለት ተርባይኖች አሉት፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 09 ቀን 2015 ዓ.ም
15 546
ፕሮጀክቱን ከብሔራዊ የኃይል መቆጣጣሪያ ማዕከል ጋር ማገናኘት ተችሏል
……….////……….
የአይሻ ሁለት የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክትን ከብሔራዊ የኃይል ቋት ጋር የማገናኘት ሥራ በስኬት መከናወኑን የፕሮጀክቱ ምክትል አስተባባሪና የሳይት ሥራ አስኪያጅ ገለፁ፡፡
ሥራ አስኪያጁ አቶ ሙሉቀን ተሰማ እንደተናገሩት 40 ሜጋ የኤሌክትሪክ ኃይል የሚያመነጩ 16 የንፋስ ተርባይኖችን የመፈተሸና የመሞከር ሥራ ተጠናቆ ከብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል ጋር የማገናኘት ሥራ ተሰርቷል፡፡
በቀጣይ ደግሞ 40 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል የሚያመነጩ የንፋስ ተርባይኖችን የመፈተሸና የመሞከር ሥራ በማጠናቀቅ ጣቢያው 80 ሜጋ ዋት ኃይል እንዲያመነጭ ለማድረግ ጥረት እየተደረገ ነው ብለዋል፡፡
ይህም ሀገሪቱ ከንፋስ ኃይል የምታገኘውን ኃይል እንደሚያሳድገው ሥራ አስኪያጁ ገልፀዋል፡፡
የፕሮጀክቱ አብዛኛው ሥራ በመጠናቀቅ ላይ መሆኑንና አጠቃላይ አፈፃፀሙ 80 በመቶ መድረሱን ሥራ አስኪያጁ አስታውቀዋል፡፡
እንደ ሳይት ሥራ አስኪያጁ ገለፃ በጣቢያው ሊገነቡ ከታሰቡት 48 የንፋስ ተርባይኖች ውስጥ 32 ያህሉ ተተክለው ተጠናቀዋል፡፡
ቀሪዎቹን 16 ተርባይኖች ለመትከል መሰረት የማውጣት ሥራ ቢጠናቀቅም በፋይናንስ ችግር ምክንያት ተርባይኖችን ወደ ሀገር ውስጥ ማስገባት እንዳልተቻለ የጠቆሙት ሥራ አስኪያጁ ችግሩ የተፈጠረው ግንባታውን እያከናወነ የሚገኘው ኩባንያ ለዕቃ አምራቾችና አቅራቢዎች በወቅቱ ክፍያ ባለመፈፀሙ በተፈጠረ ክፍተት እንደሆነ ጠቅሰዋል፡፡
በመሆኑም የተፈበረኩት ዕቃዎች ተጓጉዘው ወደ ሀገር ውስጥ ሲገቡ የሲቪል ሥራው ስለተጠናቀቀ የመገጣጠም ሥራ ይጀመራል ብለዋል፡፡
የሠራተኛ መኖሪያ ቤት ግንባታ አብዛኛው የሲቪል ሥራ መጠናቀቁን የጠቀሱት ሥራ አስኪያጁ የጣሪያ ክዳንና ሌሎች ቀሪ የማጠናቀቂያ ሥራዎችን ለማከናወን ከውጭ የሚገቡ ዕቃዎች እየተጠበቁ መሆኑን ተናግረዋል፡፡
ፕሮጀክቱ ያጋጠመውን የፋይናንስ ችግር ለመፍታት የተቋሙ ሥራ አመራርና ቦርድ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ውይይት እያደረገ በመሆኑ በቅርቡ መፍትሔ ያገኛል ተብሎ እንደሚጠበቅ ጠቁመዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 09 ቀን 2015 ዓ.ም
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
