ፍኖተ ብርሃን ዘ ቅድስት አርሴማ
前往频道在 Telegram
ይህ በግራር ደ/አባይ ቅድስት አርሴማ ቤ/ክ ፍኖተ ብርሀን ሰንበት ት/ቤት የተዘጋጀ :- ለምዕመናን : ትምህርትን , ዝማሬዎችን , ኪናዊ ዝግጅቶችን, የቤተ ክርስቲያንን ወቅታዊ ዜናዎችንና በአላትን(ንግስ, ልዮ ልዮ የሰርክ ጉባኤያት ..ወዘተ) በምን መልኩ እንደተከበሩ ለምዕመናን ተዘጋጅቶ የሚተላለፍበት ገፅ ነው።
显示更多637
订阅者
无数据24 小时
-37 天
-1230 天
帖子存档
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ እንኳን #ለዘመነ_አስተምሕሮ_ሦስተኛ_ሳምንት ለዕለተ ምኵራብ መታሰቢያ እሑድ እግዚአብሔር አምላክ በሰላም በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #የዚህ_ሳምንት_መዝሙር፦ ሃሌ ሉያ በ፭ "#አምላክ_ፍጹም_በህላዌሁ ዘሀሎ እምቅድመ ይትፈጠር ዓለም ዘበመንግሥቱ ይኴንን ዓለም ሰማየ ገብረ ለስብሐቲሁ ዓለም ፈጠረ ወምድረ ሣረረ ወገሠፀ ባሕረ ወገሠፃሙ ለኵሉ ፍጥረት እለ ውስተ ደይን ያዕርፉ ባቲ አብ ቀደሳ ለሰንበት ቅረቡ ኀቤሁ ለአምላከ ጽድቅ ማኅደር ለንጹሐን ከመ ትንሥኡ አክሊለ ስብሐት ዘአስተዳለወ ለእለ ያፈቅርዎ ፀንዑ በጸጋ በስን ወበሃይማኖት ወረሱ አክሊለ ስምዕ በእምነቶሙ እለ እምዓለም አሥመርዎ ለእግዚኦሙ መምህረ ቅዱሳን አክላለ ሰማዕት ሠያሜ ካህናት"። ትርጉም፦ ቅድመ ዓለም በመንግሥቱ የነበረ፣ #በአናናሩ_ፍጹም_አምላክ የሆነ ዓለምን ይገዛል፣ ለክብሩ ሰማይን አደረገ፣ ሰማይንና ምድርን ፈጠረ፣ ባሕርን ገሠፀ ፍጥረትን ሁሉ ገሠፃቸው በመከራ ውስጥ ያሉ ያርፉበት ዘንድ አብ ሰንበትን ቀደሳት ለሚወዱት ያዘጋጀውን በንጹሐን ማደሪያ ያከብር አክሊልን ትቀዳጁ ዘንድ ወደ እውነት አምላክ ቅረቡ በዓለም ላሉ የቅዱሳን መምህራቸው፣ የሰማዕታት አክሊላቸው፣ የካህናት ክብራቸው የሆነው ጌታቸውን ደስ ያሰኙት ዘንድ በሃይማኖት፣ በጸጋና በልጅነት ጽኑ፣ በእምነታቸውም የምስክርነትን አክሊል ወረሱ። #ሊቅ_ቅዱስ_ያሬድ_በድጓው_ላይ።
፫ #ምኵራብ
❤ ሦስተኛው የዘመነ አስተምሕሮ ሳምንት "ምኵራብ" የሚባል ሲኾን ይህም ከኅዳር ፳–፳፮ ያሉትን ሰባት ቀናት የሚያካትት ሳምንት ነው፡፡ በዚህ ሳምንት ጌታችን፣ አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በምኵራበ አይሁድ ሕዝቡን እየሰበሰበ ማስተማሩ፤ ባሕርና ነፋሳትን መገሠፁ፤ አጋንንትን ከሰዎች ማውጣቱ ይነገራል፡፡
በዕለቱ (እሑድ) የሚቀርበው መዝሙር፡- "አምላክ ፍጹም በህላዌሁ ዘሀሎ እምቅድመ ይትፈጠር ዓለም ….፤ ዓለም ከመፈጠሩ አስቀድሞ የነበረው አምላክ (እግዚአብሔር) በህልውናው (አነዋወሩ) ፍጹም ነው …." የሚለው ሲኾን፣ ምስባኩም፡- "ቅረቡ ኀቤሁ ወያበርህ ለክሙ ወኢይትኀፈር ገጽክሙ ዝንቱ ነዳይ ጸርሐ ወእግዚአብሔር ሰምዖ፤ ወደ እርሱ ቅረቡ፤ ያበራላችሁማል፡፡ ፊታችሁም አያፍርም፡፡ ይህ ችግረኛ ጮኸ፤ እግዚአብሔርም ሰማው፤" የሚል ነው (መዝ ፴፫፥፭-፮)፡፡ ወንጌሉም ከማቴዎስ ፰፥፳፫ እስከ መጨረሻው ድረስ ነው፡፡ ቅዳሴውም ቅዳሴ እግዚእ ነው፡፡
❤ የዕለቱ ወንጌል ጌታችን አምላካችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በመርከብ ውስጥ ሳለ መርከቢቱ እስክትናወጥ ድረስ ታላቅ ማዕበል መነሣቱን፤ ቅዱሳን ሐዋርያት "ጌታ ሆይ እንዳንጠፋ አድነን?" እያሉ በመተማጸኑት ጊዜ ጌታችን ነፋሱንና ባሕሩን በመገሠፅ ጸጥታን፣ ሰላምን፣ መረጋጋትን ማስፈኑን የሚናገረው ክፍል ነው፡፡ በባሕሩ ዓለም ውስጥ የምትገኘው ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ሰዎች በፈቃደ ሥጋቸው ተሸንፈው ባመጡት ጥላቻ፣ ኑፋቄ፣ ክህደት፣ ፍቅረ ንዋይ፣ በአጠቃላይ በልዩ ልዩ የኀጢአት ማዕበልና ሞገድ እየተናወጠች ናት፡፡ ይህን ማዕበልና ሞገድ ጸጥ በማድረግ ፍቅርን፣ አንድነትን፣ ሰላምንና ጽድቅን ማስፈን የሚቻለውን መድኀኒታችን ክርስቶስን እንደ ቅዱሳን ሐዋርያት በአንድነት ኾነን "ጌታ ሆይ እንዳንጠፋ አድነን?›› እያልን እንማጸነው፡፡ የሰላሙ ዳኛ፣ የሰላሙ መሪ፣ የሰላሙ ጌታ፣ የሰላሙ ንጉሥ፣ የሰላሙ ባለቤት እርሱ ጌታችን አምላካችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰላምን፣ መረጋጋትን፣ ፍቅርን፣ አንድነትን ካወጀ በቤተ ክርስቲያናችን ፍቅር፣ አንድነት ሰላም ይሰፍናልና፡፡
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "ቅረብ ኀቤሁ ወያበርህ ለክሙ። ወኢይትኀፈር ገጽክሙ። ዝንቱ ነዳይ ጸርሐ ወእግዚአብሔር ስምዖ"። መዝ 33፥5-6 የሚነበቡት መልዕክታት ዕብ 12፥25-ፍ.ም፣ ያዕ 3፥4-13 እና የሐዋ ሥራ 21፥27-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 8፥22-ፍ.ም። የሚቀደሰው ቅዳሴ እግዚእነ ነው። መልካም ዕለተ ሰንበትና የነቢያት (የገና) የጾም ጊዜ። ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #ኅዳር ፳ (20) ቀን።
❤ እንኳን #በወንጌላዊ_ቅዱስ__ማርቆስ እጅ ጵጵስና ለተሾመው ለእስክንድርያ ሁለተኛ ሊቀ ጳጳስ #ለቅዱስ_አባት_ለአባ_አንያኖስ_ለዕረፍት በዓልና ለሠራዊት አለቃ ለከበረ #ለሰማዕት_ቅዱስ_ቴዎድሮስ ቤተ ክርስቲያኑ ለከበረችበት በዓል በሰላም አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #ሊቀ_ጳጳስ_ቅዱስ_አንያኖስ፦ የዚህም ቅዱስ ወላጆቹ አረማውያን ናቸዉ እርሱም ጫማ ሰፊ ነበር ቅዱስ ወንጌላዊ ማርቆስ ወደ እስክንድርያ አገር መጀመርያ በገባ ጊዜ እግሩን ተደናቅፎ ጫማው ተቆረጠ እንዲሰፋለትም ወደ ጫማ ሰፊ አንያኖስ ዘንድ ሔደና ጫማውን ሰጠው መስፋትም በጀመረ ጊዜ መስፊያው ጣቱን ወጋው በዮናኒም ቋንቋ "አቴኦስ" አለ ትርጓሜውም አንድ እግዚአብሔር ማለት ነው። ቅዱስ ማርቆስም የእግዚአብሔርን ስም ሲጠራ በሰማ ጊዜ ደስ ብሎት የክብር ባለቤት ኢየሱስ ክርስቶስን አመሰገነው።
❤ ከዚህም በኋላ አፈር አንሥቶ በምራቁ ጭቃ አድርጎ በአንያኖስ ጣት ላይ አደረገውና በዚያን ጊዜ አዳነው አንያኖስም ከዚህ ድንቅ ምልክት የተነሣ አደነቀ ቅዱስ ማርቆስንም ወደ ቤቱ ወሰደው ስለ ሥራው ስለ አምልኮቱም የመጣውም ከወዴየት ቦታ እንደሆነ ጠየቀው። ቅዱስ ማርቆስም ከብሉያትና ከሐዲሳት መጻሕፍት የአንድ እግዚአብሔርን ህልውና ስለ ዓለም ሁሉ ድኅነት የወልደ እግዚአብሔር ሰው መሆን መከራ መስቀልንም ተቀብሎ ስለመሞቱ ስለ ትንሣኤውና ስለዕርገቱ ዳግመኛም ለፍርድ ስለ መምጣቱ ይነግረው ጀመረ። የአንያኖስ ልቡ ብሩህ ሁኖለት በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አምኖ ከቤተሰብ ሁሉ ጋር ተጠምቀ። የመንፈስ ቅዱስም ጸጋ በላያቸ ወረደ አዘውትሮ በመጠመድ የሐዋርያ ቅዱስ ማርቆስን ትምህርት የሚሰማ ሆነ የቤተ ክርስቲያንንም ትምህርት ሕጓንና ሥርዓቷንም ተማረ።
❤ ቅዱስ ማርቆስም ወደ ሌሎች አገሮች ሒዶ ለማስተማር በፈለገ ጊዜ እጆቹን በአንያኖስ ላይ ጭኖ በግብጽ አገር ለወገኖቹ ወንጌልን ይሰብክ ዘንድ ሊቀ ጵጵስና ሾመው እርሱም ብዙዎችን አስተምሮ አጠመቃቸው በቀናች ሃይማኖትም አጸናቸው ቤቱንም ቤተ ክርስቲያን አደረጋት እርሷም በስተምራብ ከእስክድርያ ከተማ ውጭ ያለች ዛሬ የሰማዕት ቅዱስ ሰርጊስ ቤተ ክርስቲያን ሁና የታወቀች ናት።
❤ ይህ የተመሰገነ አባት አንያኖስም በወንጌላዊ ቅዱስ ማርቆስ ወንበር ዐሥራ ሁለት ዓመት አገልግሎ በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ አባ አንያኖስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ ትኑር አሜን። ምንጭ፦ የኅዳር 20 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "እስመ መምህረ ሕግ ይሁብ በረከተ። ወየሐውር እምኀይል ውስተ ኃይል። ወያስተርኢ አምላከ አማልክት በጽዮን"። መዝ 83፥6-7። የሚነበቡት መልዕክታት ቲቶ 1፥5-12፣ 1ኛ ጴጥ 5፥1-8 እና የሐዋ ሥራ 20፥20-31። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 10፥1-22። የሚቀደሰው ቅዳሴ የእመቤታችን የማርያም ቅዳሴ ነው። መልካም የቅዱስ አንያኖስ የዕረፍት በዓልና የነቢያት (የገና) ጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #ኅዳር ፲፱ (19) ቀን።
❤ እንኳን #ከዐሥራ_ሁለቱ_ሐዋርያት አንዱ ለሆነው #ለሐዋርያው_ቅዱስ_በርቴሎሜዎስ እልዋህ በሚባል አገር አስተምሮ ብዙዎችን እግዚአብሔር ወደማወቅ ለመለሰበት ለመታሰቢያ በዓሉና #ለቅዱስ_ቴዎፍሎስ_ከሚስቱ_ቅድስት_ጰጥሪቃ ከአምስት ወር ልጁም #ከቅዱስ_ደማሊስ ጋር #ሰማዕትነት_ለተቀበሉበት_ለዕረፍታቸው በዓልና ሩጻፋ በሚባል አገር #ለሰማዕት_ቅዱስ_ሰርጊስ ቤተ ክርስቲያን ለከበረችበት በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #ቅዱስ_ቴዎፍሎስ_ሚስቱ_ቅድስት_ጰጥሪቃ የአምስት ወር ልጁ #ቅዱስ_ደማሊስ፦ ይህ ቅዱስ እግዚአብሔርን በመፍራትና በአማረ አምልኮ ያደገ ነው ሰዎች ሒደው ቅዱስ ቴዎፍሎስ ክርስቲያን መሆኑን ለመኰንኑ ለአንቲጳጦስ ነገሩሩት መኰንኑም በዜውስ ጣዖት ቤት ሳለ ወደርሱ ያመጡት ዘንድ አዘዘ። ቅዱሱንም በአቀረቡት ጊዜ "አንተ ከወዴት ነህ? ሃይማኖትህስ ምንድን ነው?" አለው። እርሱም "የክብር ባለቤት ጌታዬ ኢየሱስን ክርስቶስ የማምን ክርስቲያን ነኝ" አለ መኰንኑም "በክፉ አሟሟት እንዳትሞት ለአማልክተሰ ሠዋ" አለው ቅዱሱም "ክብር ይግባውና ከጌታዬ ከኢየሱስ በቀር ለረከሱ አማልክት አልሠዋም" አለው።
❤ መኰንኑም የሆድ ዕቃው እስቲታይ ሰቅለው ይሠነጥቁት ዘንድ አዘዘ እርሱ ግን በጌታችን ኃይል ስለጠበቀ ምንም ምን አልደረሰበትም ሁለተኛም እሳትን አንድደው ከውስጡ እንዲጨምሩት አዘዘ ቅዱሱም በእሳት መካከል በጸለየ ጊዜ እሳቱ ተበተነ ምንም ምን ሳይነካው ከእሳት ውስጥ ወጣ። መኰንኑም ይህን አይቶ በረኃብ እንዲሞት አሥረው አጽንተው ይጠብቁት ዘንድ አዘዘ ከስምንት ቀንም በኋላ ሚስቱ ጰጥሪቃ ሕፃኗን ተሸክማ መጣች ምስክርም ሁኖ በክርስቶስ ስም ይሞት ዘንድ አጽናቸው።
❤ መኰንኑም ለቅዱስ ቴዎፍሎስ ምግብ የሰጠው እንዳለ ብሎ ሊመረምር ሔደ የእሥር ቤቱንም ደጅ በከፈተ ጊዜ ጣፋጭ የዕጣን መዓዛ ተቀበለው ቅዱስ ቴዎፍሎስንም በተነጠፈ መቀመጫ ላይ ተቀምጦ ሦስት መላእክት ማርና ወተት ሲመግቡት አገኘው በአየውም ጊዜ ደንግጦ ወደኋላው ተመለሰ። በማግሥቱም ቅዱስ ቴዎፍሎስን ወደ አደባባይ እንዲአመጡት አዘዘ እርሱም ሚስቱ ተከታትለው መጣ መኰንኑም "ዲዮስ ለሚባል አምላክ ሠዋ" አለው። ቅዱሱም "እኔ ዓለምን ሁሉ ለያዘ ለእውነተኛው አምላክ ለጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ በቀር ለሌላ አልሠዋም" አለ።
❤ በዚያንም ጊዜ ለአንበሳ እንዲጥሉት መኰንኑ አዘዘ አንበሳውም ሩጦ እግሮቹን ሳመ ከዚያም በኋላ በእግዚአብሔር ፈቃድ አቈሰለው ተጋድሎውን በዚህ ፈጽሞ ነፍሱን ሰጠ ቅድስት ሚስቱ ጰጥሪቃም ሥጋውን አንሥታ ከሣጥን ጨመረች መኰንኑም እርሷንም ወደ አደባባይ አምጥተው ለአንበሳ እንዲሰጧት አዘዘ ሕፃኑም አንበሳውን በአየው ጊዜ ሣቀ የአምስት ወርም ልጅ ሲሆን "አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ አምናለሁ" ብሎ በአንበሳ አፍ ከእናቱ ጋር ተበላ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በእሊህ ሰማዕታት በጸሎታቸው ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #የሰማዕቱ_ቅዱስ_ሰርጊስ_ቤተ_ክርስቲያን_የከበረችበት፦ ይህም ቅዱስ ሰርጊስ በሩጻፋ አገር በሰማዕትነት በአረፈ ጊዜ ምእመናን ሥጋውን ወስደው ገንዘው በእርሱ ዘንድ አኖሩት በፊቱም መብራቶችን አኖሩ የመከራውም ዘመን እስቲያልፍ በእነርሱ ዘንድ ተሠውሮ ኖረ። ከዚያም በኋላ ያማረች ቤተ ክርስቲያንን አነፁለት ዐሥራ አምስት ኤጲስቆጶሳትንም ሰብስበው አከበሩዋት በዚች ቀን ኅዳር 19 ቀን ሥጋውንም በውስጧ አኖሩ ከእርሱም ድንቅ ተአምር ተገለጠ በእምነት ከእርሱ ለሚወስዱ ሁሉ በሽተኞችን የሚፈውሳቸው ሽታው እጅግ ጣፋች የሆነ የሽቱ ቅባት ከሥጋው የሚፈስ ሆኗልና። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳን ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ትድረሰን ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ "#ሰላም_እብል_ሐዋርያ_መስተጋድለ። በተወርዎ ባሕር ዕሙቅ እንዘ ሠቀ ጸጒር ጥብሉለ። #በርተሎሜዎስ ገዳመ አመ ምስሌሆሙ ዔለ። በማየ ጸሎቱ ጽምዐ ነጋድያን አጥለለ። ወአንሥአ ዓዲ ዘሞቱ አግማለ"። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የኅዳር 19።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "ጽልአ በአመፃ ይጸልዑኒ። ዕቀባ ለነፍስየ ወአድኅና። ወኢትኀፈር እስመ ኪያከ ተወከልኩ"። መዝ 24፥19-20። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 15፥17-26።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_ቅዳሴ_ምስባክ፦ "ሕጉ ለእግዚአብሔር ንጹሕ ወይመይጣ ለነፍስ። ስምዑ ለእግዚአብሔር እሙን ወያጠብብ ሕፃናተ። ኵነኔሁ ለእግዚአብሔር ርቱዕ ወያስተፌሥሕ ልበ"። መዝ 18፥7-8። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ቆሮ 12፥28-ፍ.ም፣ ይሁ 1፥20-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 4፥29-36። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 10፥1-16። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ነው። መልካም በዓልና ጾም ጊዜና በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #ኅዳር ፲፱ (19) ቀን።
❤ እንኳን #ለኢትዮጵያዊው_ጻድቅ_ለዓለም_ብርሃን ለሆኑት እመቤታችን ዕጣን እየሰጠቻቸው #ከሃያ_አራቱ_ካህናተ_ሰማይ_ጋር_የሥላሴን_መንበር ላጠኑት #ለአቡነ_ዮሴፍ_ዘእንጂፋት_ለልደታቸው በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላም አደረሰን።
✝ ✝ ✝
❤ #አባ_ዮሴፍ_ዘእንጂፋት፦ አባታቸው ንጉሡ ዐፄ ዳዊት እናታቸው ዳግም ሞገሳ ይባላሉ፡፡ ትውልድ ሀገራቸው ወሎ መቄት እንጂፋ ነው፡፡ አባታችን አባ ዮሴፍ ኅዳር 19 ቀን ሲወለዱ በርካታ ሙታን ተነሥተዋል፡፡ ይህም ቅዱስ ያዩትና የሰሙት እስቲያደንቁት ድረስ በአባቱ ቤት ሳለ የዚህን ዓለም ጥበብ ሁሉ ተማረ የቤተ ክርስቲያንንም መጻሕፍት ተረጐመ ከዚህም በኋላ ዲቁና ሾሙት።
❤ የነፍሱንም ድኅነት እግዚአብሔር በወደደ ጊዜ ብርሃናዊ መልአኩን ቅዱስ ሚካኤልን ላከለትና "ዮሴፍ ሆይ ይህን ኃላፊውን ዓለም ትወድዋለህን አስጸያፊ አይደለምን በውስጡም ያለ ሁሉ" አለው። ከዚያችም ጊዜ ጀምሮ እርሱ የመረጠውን መንገድ ይመራው ዘንድ እግዚአብሔር እየለመነ ጾምና ጸሎትን ጀመረ።
❤ ከወለቃ አውራጃም ስሙ አባ ዘካርያስ የሚባል ነበረ እርሱም ለዮሴፍ ዘመዱ የሆነ በጭልታም ዮሴፍን ወስዶ የምንኵስና ልብስ አለበሰው። ወደትግራይ ምድርም ወስደውና በዚያ ተግባረ እድ ለምንኵስና ሥራ የሚገባ ጽሕፈትን ስፌትን ተማረ።
❤ ከዚህም በኋላ ወደ በረሀ ዱር ገብተው የእንጨት ፍሬ እየበሉ ከዝኆኖች ከአንበሶችና ከዘንዶዎች እየተፈተኑ በየአይነቱ በሆነ ተጋድሎ በመድከም ኖሩ። በጽድቃቸውም ኃይል ብዙ ተአምራትን አደረጉ አባ ናትናኤልም የጋለ ምንቸት በመሐል እጁ ይዞ በመነኰሳቱ ፊት ዞረ። አባ ዮሴፍም የሚያበስሉበት ማሰሮ በተሰበረ ጊዜ ወጡ ሳይፈስ አገናኝቶ እንደ ቀድሞው አደረገው። ገብረ ኄርም ሕዝባዊ ሲሆን በሞተ ጊዜ ሊአጠምቁት ሲሉ "ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ኤጲስቆጶስነት ሹሞኛልና እኔ በእጄ አጠምቃችኋለሁ" አላቸው። እሊህም ቅዱሳን የትሩፋታቸውንና የጽድቃቸውን የአማረ ሥራቸውን አሳዩ።
❤ ከዚህም በኋላ አባ ዮሴፍን ወደ ጳጳስ ወሰዱትና ቅስና ተሾመ። አባ ዘካርያስም በዐረፈ ጊዜ አባ ዮሴፍ ወደ ሌላ ገዳም ሒዶ ሳይቀመጥ ቁሞ አርባ መዓልትም አርባ ሌሊት ጾመ። ከድካም ጽናትም በወደቀ ጊዜ ቅዱስ ሚካኤል አነሣው። ሁለተኛም ከገደል አፋፍ እጁን ዘርግቶ ሳይሰበስብ አርባ ቀን አርባ ሌሊት ቆመ። ሰይጣንም መጥቶ ወደ ቆላ ወረወረው የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልም ተቀብሎ ወደ መቆሚያው መለሰው። ደግሞም ከደንጊያ ወሻ ውስጥ ገብቶ አርባ ቀን አርባ ሌሊት ያለ መብልና ያለ መጠጥ ኖረ። ሰይጣናትም ወደርሱ እየመጡ በየራሳቸው ምትሐት በማሳየት ያስፈራሩት ነበር መላእክትም ያበረቱትና ያጸኑታል። ናላው በአፍንጫው እስቲፈስ ድረስ በየእልፍ እልፍ እየሰገደ ኖረ።
❤ ከዚያም የትራይን አውራጃዎች ሁሉ ዞረ። ወደ ሰሜንም ምድር ተሻግሮ ከቅዱስ ያሬድ መቃብር ገባ በደጃፉም ላይ ተቀርጾ አግኝቶ አንቀጸ ብርሃን ተማረ። ሲመለስም ሽፍቶች አግኝተውት በደንጊያ ወገሩት በበትርም ደበደቡት በጦርም ወግተው ጥለውት ሔዱ። አምላክን የወለደች እመቤታችንም ቅድስት ድንግል ማርያም ወደርሱ መጥታ አዳነችው። አንዲት ቀንም የሴት በድን አግኝቶ በላይዋ ባማተበ ጊዜ ተነሣች።
❤ ወደ ኢየሩሳሌምም ሦስት ጊዜ ሒዶ ከከበሩ ቦታዎች ተባርኳል ወደ አባቶቻችን ሐዋርያት መቃብም እስከ አገረ ባርቶስና ሕንደኬ ደረሰ። ውኃው ከመላበት ወንዝም በሚደርስ ጊዜ በላዩ አማትቦ እንደ የብስ በእግሩ እየረገጠ ይሻገረዋል። አንበሶችና ነብሮች ይከተሉታል ምግብ በአጡ ጊዜ ድንጊያውን ባርኮ ሥጋ አድርጎ ይሰጣቸዋል።
❤ ከዚህ በኋላም ወደ አባታችን ተክለ ሃይማኖት ገዳም ደብረ ሊባኖስ ሔደ። ከአባ ተወልደ መድኅንም እጅ አሰሰኬማ ተቀበለ። አባ ተወልደ መድኅንም ሊፈትነው ወዶ ሰባት የጽድ ቅርንጫፍ ሰብሮ ትከለው ብሎ ሰጠው በተከላቸውም ጊዜ ወዲያውኑ በቅለው አደጉ እስከ ዛሬም አሉ። ብዙዎችም ወደርሱ መጥተው በእርሱ እጅ መነኰሱ እግዚአብሔር አብና አምላክን በወለደች በእመቤታችን ድንግል ማርያም ስም በአነፃቸው አብያተ ክርስቲያን በአንድነት ኖሩ።
❤ በአንዲት ዕለትም እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ዕጣንን ሰጠችውና ከሃያ አራቱ ካህናተ ሰማይ ጋራ የአሸናፊ የእግዚአብሔርን መንበር አጠነ። ብዙ ጊዜም ወደርሱ ሐዋርያት እየመጡ ይባርኩታል። በአንዲት ዕለትም ነብር ከእናቱ እጅ ሕፃንን ነጥቆ ወሰደ በአባ ዮሴፍም ስም በአማጸነችው ጊዜ በሦስተኛው ቀን መለሰላት።
❤ ለልጆቹም ገንዘብም ሆነ የእንስሳ ጥሪት እንዳያደርጉ ሥጋ እንዳይበሉ የወይን ጠጅ እንዳይጠጡ ትሕትናን ቅንነትን እንዲማሩ ከንቱ ነገር ቧልትን እንዳይናገሩ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ እንዳይስቁ ይህ ሁሉና የመሳሰለውን ሥርዓትን ሠራላቸው።
❤ ከዚህም በኋላም ሩጫውን በፈጸመ ጊዜ ግንቦት19 ቀን በሰላም በፍቅር ዐረፈ ደብረ ታቦር ብሎ በሰየማት ቤተ ክርስቲያንም ተቀበረ ከእርሱም ቊጥር የሌላቸው ድንቆች ተአምራት ተገለጡ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ዮሴፍ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑረሰ ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የግንቦት 19 ስንክሳር።
ነቢያት እንደሰበኩ ነገረቻት።
❤ ሁለተኛም ስለ ከበረ ስሙ መከራ በመቀበል ለሚደክሙ ሰማያዊ ሀብት የዘላለም መንግሥትን እግዚአብሔር ስለ ሚሰጣቸው አስረዳቻት። አጥራስስም የዮናን ትምርቷን ሰምታ እጅግ ደስ አላት በሕያው እግዚአብሔር ልጅ በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም አመነች።
❤ እሊህ ደናግልም ሌሊትና ቀን በተጋድሎ ተጠምደው በአንድነት ተቀመጡ የአጥራስስም አባቷ ይህን አያውቅም ከሌሊቶችም በአንዲቱ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን አዩት እናቱን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምንም አዩአት። እመቤታችንም ወደ ልጅዋ እግዚአብሔር እንደ ቁርባን አቀረበቻቸውና እርሱም ባረካቸው።
❤ ከዚህም በኋላ ንጉሥ ወደ ጦርነት ሒዶ በተመለሰ ጊዜ ወደ ልጁ አጥራስስ ገብቶ "ልጄ ሆይ ወደ መሞሸሪያሽ ከመግባትሽ በፊት ለአምላክ አጵሎን ዕጣን ታሳርጊ ዘንድ ነዪ" አላት። አጥራስስ ድንግልም "አባቴ ሆይ ነፍስህና ሥጋህ በእጁ ውስጥ የሆነ የፈጠረህን በሰማይ ያለ አምላክን ትተህ ነፍስ የሌላቸው የረከሱ ጣዖታትን ለምን ታመልካለህ" ብላ መለሰችለት። ንጉሥም እንዲህ ያለ ነገር ከቶ ያልሰማውን ከልጁ አፍ በሰማ ጊዜ አደነቀ በልጁ ላይ ምን እንደደረሰ ልቧንም ማን እንደለወጠው ጠየቀ የፍላጽፍሮን ልጅ ድንግል ዮና የልጁን ልብ እንደ ለወጠች ነገሩት።
❤ ንጉሡም በእሳት ያቃጥሏቸው ዘንድ አዘዘ በወርቅና በብር በተጌጠ የግምጃ ልብሶችን እንደ ተሸለሙ አወጧቸው እነርሱ የነገሥታት ልጆች ስለሆኑ አላራቆቿቸውም ታላላቆችና ታናናሾች ሁሉም ሰዎች ስለ እሳቸው እያዘኑና እያለቀሱ ወጡ ነፍሳቸውንም እንዳያጠፉ ለንገሥ ይታዘዙ ዘንድ ለመኗቸው እነርሱ ግን ከበጎ ምክራቸው አልተመለሱም።
❤ በዚያንም ጊዜ ጉድጓድ ቆፈሩላቸውና በውስጡ እሳትን አነደዱ ነበልባሉም እጅግ ከፍ ከፍ አለ ያን ጊዜ አንዷ ከሁለተኛዋ ጋር እጅ ለእጅ ተያይዘው ወደ እሳት ውስጥ ተወረወሩ ፊታቸውንም ወደ ምሥራቅ መልሰው በመቆም ረጅም ጸሎትን ጸለዩ ከዚህም በኋላ ነፍሳቸውን በእግዚአብሔር እጅ ሰጡ እሳቱም እንደውኃ የቀዘቀዘ ሆነ ምእመናንም ሥጋቸውን አነሡ ተጠጋግተውም ልብሳቸውንም ቢሆን ወይም የራሳቸውን ጠጉር እሳት ምንም ምን ሳይነካቸው አገኟቸው ። የመከራውም ወራት እስቲፈጸም በታላቅ ክብር በአማረ ቦታ አኖርዋቸው ከዚህም በኋላ ቤተ ክርስቲያን ሠርተውላቸው ሥጋቸውን በውስጥዋ አኖሩ ከእርሳቸውም ታላላቅ የሆኑ ድንቆች ተአምራት ተገለጡ ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳን ደናግላን ሰማዕታት አጥራስስና ዮና ጸሎት ይማረን በረከታቸው ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የኅዳር 18 ስንክሳር።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "አልቦ ነገር ወአልቦ ነቢብ ዘኢተሰምዐ ቃሎሙ። ውስተ ኵሉ ምድር ወፅአ ነገሮሙ። ወእስከ አፅናፈ ዓለም በጽሐ ነቢቦሙ"። መዝ 18፥3-4 ወይም መዝ 145፥8-9። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 10፥1-11።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_የቅዳሴ_ምስባክ፦ "እግዚአብሔር ያፈቅሮሙ ለጻድቃን። እግዚአብሔር የዐቅቦሙ ለፈላስያን። ወይትዌክፎሙ ለዕቤራት ወለእጓለ ማውታ"። መዝ 145፥8-8። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ፊል 1፥12-19፣ 1ኛ ጴጥ 3፥10-18 እና የሐዋ ሥራ 16፥14-25። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 10፥16-ፍ.ም። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱሳን ሐዋርያት ነው። መልካም የሐዋርያው የቅዱስ ፊሊጶስ የዕረፍትና የነቢያት (የገና) ጾም ጊዜ በዓል ለሁላችንም ይሁንልን።
ተአምኆ ቅዱሳን ወግጻዌ (የቅዱሳን ሰላምታ) Teamho Kidusan Wegtsawe (Yekidusa Selamta) Saints Of The Orthodox Tewahedo Church.:
❤ "በስመ አብ ወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #ኅዳር ፲፰ (18) ቀን።
❤ እንኳን #ከዐሥራ_ሁለቱ_ሐዋርያት አንዱ ለሆነው #ለሐዋርያው_ቅዱስ_ፊልጶስ_ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓል፣ #ከሮሜ_አገር በንጉሥ እንድርያኖስ እጅ ሰማዕትነት ለተቀበሉ #ለቅዱስ_ኤላውትሮስና_ለእናቱ_ቅድስት_እንትያ ለዕረፍትና #ለቅዱሳን_ደናግል_አጥራስስና_ዮና ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍታቸው በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማ በዚች ቀን ከሚታሰበው፦ ከየዋህ #ከቅዱስ_አትናቴዎስ ከዕረፍቱ መታሰቢያ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
❤ #ሐዋርያ_ቅዱስ_ፊሊጶስ፦ ቁጥሩ ከ12ቱ ሐዋርያት ውስጥ ነው በማቴ 10፥3 ላይ እንደተጠቀሰው ከ12ቱ ሐዋርያት ውስጥ በ5ኛ ደረጃ ተጠቅሷል፡፡ ከገሊላ የተገኘ የቤተ ሳይዳ ሰው ሲሆን የግሪክ ሰዎችን ወደ ጌታችን ያቀረባቸው እርሱ ነው፡፡ ዮሐ12፥20-22፡፡ቅዱስ ፊሊጶስ ሐዋርያው ቅዱስ ናትናኤልን "የናዝሬቱን ኢየሱስን አግኝተነዋል መጥተህ እይ…" በማለት ወስዶ ከጌታችን ጋር አገናኝቶታል፡፡ ዮሐ 1፡44-52፡፡ በኋላም ጌታችንን "አብን አሳየንና ይበቃናል" ብሎ የጠየቀውም ይኸው ሐዋርያ ፊሊጶስ ነው፡፡ ይህም ጥያቄው ለእኛ ለሁላችን መሠረታዊውን የክርስትና እውቀት እንድናገኝ ረድቶናል፡፡ ጌታችንም"እኔን ያየ አብን አይቷል፣ እኔ በአብ እንዳለሁ አብም በእኔ እንዳለ እመኑኝ" በማለት ነው መልስ የሰጠው፡፡ ዮሐ14፥8-14፡፡
❤ ሐዋርያው ቅዱስ ፊሊጶስ ወንጌልን ዞሮ በማስተማር ብዙዎች ጣዖት ማምለካቸውን ትተው በክርስቶስ እንዲያምኑ አድርጓል፡፡ ከጌታችን ዕርገት በኋላ ሐዋርያው ፍርግያ፣ ሰማርያና ጋዛ በሚባሉ አገሮች ወንጌልን ሰብኮ ብዙዎችን አሳምኖ አጥምቆአል፡፡ ሐዋርያው በመጨረሻ ወደ ታናሽዋ እስያ ሄዶ በሄራፖሊስ ከተማ ሲያስተምር ብዙዎችን በማሳመኑ ክፉዎች ይዘው አሠቃዩት፡፡ ከብዙ ሥቃይም በኋላ ጣዖት አምላኪዎች ኅዳር 18 ቊልቁል ሰቅለውት ሰማዕትነቱን ፈጽሞ የድል አክሊልን ተቀዳጅቷል፡፡ ክፉዎችም በግፍ ከገደሉት በኋላ ሥጋውን በእሳት ሊያቃጥሉት በወደዱ ጊዜ የታዘዘ መልአክ የሐዋርያውን ቅዱስ ሥጋ ከእጃቸው ነጥቆ ወሰደባቸውና ሰወረው፡፡ ይህንንም ድንቅ ተአምር በተመለከቱ ጊዜ ሁሉም በአንድ ድምፅ "ከቅዱስ ፊልጶስ አምላክ በቀር ሌላ አምላክ የለም"ብለው፡ጮኹ፡፡
❤ አሠቀይተው ስለገደሉትም ተጸጽተው እጅግ አዘኑ፡፡ ክብር ይግባውና በጌታችን ካመኑ በኋላ የሐዋርያው የቅዱስ ፊሊጶስን ቅዱስ ሥጋውን ይሰጣቸው ዘንድ በጸሎት ለመኑ፡፡ ሰውን የሚወድ ቸር ይቅር ባይ ጌታችንም የቅዱስ ፊሊጶስን ቅዱስ ሥጋውን መልሶ ሰጣቸውና እጅግ ተደሰቱ፡፡ ከሐዋርያውም ቅዱስ ሥጋ ብዙ ድንቅ ድንቅ የሆኑ ተአምራት ተፈጸሙላቸው፡፡ የሐዋርያውም መካነ መቃብሩ እስካሁንም ድረስ በዚህች ከተማ ይገኛል፡፡ ምንጭ፦ መጽሐፍ ቅዱስና ስንክሳር የኅዳር 18።
✝ ✝ ✝
❤ #ቅዱስ_ኤላውትሮስና_እናቱ_ቅድስት_እንትያ፦
ይህም ቅዱስ እግዚአብሔርን ከሚፈራ አንቂጦስ ከሚባል ኤጲስቆጶስ ዘንድ አደገ ዐሥራ ሰባት ዓመትም በሆነው ጊዜ ዲቁና ተሾመ ደግሞ በዐሥራ ስምንት ዐመቱ ቅስና ተሾመ ከዚህም በኋላ በሃያ ዓመቱ አላሪቆስ ለሚባል አገር ጵጵስና ተሾመ።
❤ በዚያንም ወራት ንጉሥ እንድርያኖስ ወደ ሮሜ አገር መጣ ስለ ኤላውትሮስም ሰምቶ ወደርሱ ያመጣው ዘንድ ፊልቅስን አዘዘው ፊልቅስም በሔደ ጊዜ ቅዱሱን በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የእግዚአብሔርን ቃል ሲያስተምር አገኘው። ፊልቅስም ትምርቱን በሰማ ጊዜ አመነና በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ተጠመቀ።
❤ ቅዱስ ኤላውትሮስንም ወደ ንጉሥ እንድርያኖስ በአደረሱት ጊዜ "ለአማልክት ሠዋ አንተ ነጻነት ያለህ ስትሆን ለተሰቀለ ሰው ለምን ትገዛለህ" አለው ። ኤላውትሮስም "ነጻነትማ ሰማይና ምድርን በፈጠረ በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል ነው" ንጉሡም መንኰራኩር ካለው የእሳት ማንደጃ ውስጥ ጨምረው እንዲአቃጥሉት አዘዘ በጨመሩትም ጊዜ እሳቱ ጠፋ መንኩራኩሩም ተቆራረጠ። ንጉሡም አይቶ አደነቀ የሚያደርገውንም አጥቶ ከወህኒ ቤት ጨመረው ርግብም ከገነት መብልን አምጥታለት በልቶ ጠገበ ። ቆሊሪቆስ የሚባለውም መኰንን አይቶ በቅዱስ ኤላውትሮስ አምላክ አምኖ በሰማዕትነት ሞተ የሰማዕትነት አክሊልንም ተቀበለ።
❤ ከዚህም በኋላ ፈረሶችን አምጥተው በሠረገላ ላይ እንዲጠምዷቸው ቅዱስ ኤላውትሮስንም ከሠረገላው በታች አሥረው ሕዋሳቱ እስኪሰነጣጠቅ ፈረሶችን እንዲአስሮጡአቸው እንድርያኖስ አዘዘ። በዚያንም ጊዜ የእግዚአብሔር መልአክ ወረደ ከማሠሪያውም ፈትቶ ወደ ከፍተኛ ተራራ ወሰደው በዚያም እግዚአብሔርን እያመሰገነ ከአራዊት ጋር ተቀመጠ ።
❤ እንድርያኖስም አራዊትን ያድኑ ዘንድ ወታደሮቹን በአዘዘ ጊዜ በዚያ ተራራ ውስጥ ቅዱስ ኤላውትሮስን አግኝተው ከዚያ ወደ ንጉሥ እንድርያኖስ ወሰዱት። ንጉሡም ለአንበሳ እንዲሰጥ አዘዘ አንበሶችም የፊቱን ላብ ጠረጉለትና እግሮቹን ሳሙ ከዚህም በኋላ ተመልሰው ከአረማውያን መቶ ሃምሳ ሰው ገደሉ እንድርያኖስም አይቶ ቁጣን ተመላ ሁለት ወታደሮችን ከእንትያ እናቱ ጋር በጦር እንዲወጉት አዘዘ እርሷንም ብዙ ከአሠቃይዋት በኋላ የልጅዋን አንገት እንዳቀፈች ከእርሱ ጋር ወጓት ነፍሳቸውንም ኅዳር 18 ቀን በእግዚአብሔር እጅ ሰጡ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳን ሰማዕታት በቅዱስ ኤላውትሮስና በእናቱ ቅድስት እንትያ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
✝ ✝ ✝
❤ #ቅዱሳት_ደናግል_ሰማዕታት_አጥራስስና_ዮና፦ አጥራስስ ግን ጣዖታትን ለሚያመልክ ንጉሥ እንድርያኖስ ልጁ ናት እርሱም ከሰው ወገን ማንም እንዳያያት አዳራሽ ሠርቶ ለብቻዋ አኖራት እርሷ ግን ስለዚህ ዓለም ኃላፊነት የምታስብ ሆነች አውነተኛውንና የቀናውን መንገድ ይመራት ዘንድ በቀንና በሌሊት እግዚአብሔርን ትለምነው ነበር። "ወደ ፍላጽፍሮን ልጅ ወደ ድንግሊቱ ዮና ላኪ እርሷም የእግዚአብሔርን መንገድ ትመራሻለች" የሚላትን ራእይ አየች ከእንቅልፏም ስትነቃ በልቧ ደስ አላት ወደ ዮና ድንግልም ላከች እርሷም ፈጥና መጣች ለዮናም ሰላምታ ሰጠቻትና ከእግርዋ በታች ሰገደችላት የእግዚአብሔርንም ሃይማኖት ታሰተምራትና ትገልጥላት ዘንድ ለመነቻት።
❤ ድንግል ዮናም የእግዚአብሔር ልጅ ሰው የሆነበትን ምክንያት እግዚአብሔር አዳምን ከፈጠረበት ጊዜ በመጀመር ልትነግራት ጀመረች አዳም እንደበደለና ከተድላ ገነት እንደ ወጣ በኖኅም ዘመን የጥፋት ውኃ መጥቶ ኃጢአተኞችን ሁሉ እንደደመሰሰ የእግዚአብሔርን ሕግ የጠበቁ ስምነት ሰዎች ብቻ እንደ ቀሩ ከዚህም በኋላ ዳግመኛ ሰዎች በምድር ላይ በበዙ ጊዜ እንደበደሉና ጣዖትን እንዳመለኩ እግዚአብሔርም ለአብርሃም እንደተገለጠለትና መርጦ ወዳጅ እንዳደረገው ከእርሱም ጋር ቃል ኪዳንን እንዳጸና እስራኤልንም ከግብጽ አገር እንዳወጣቸው የሰውንም ወገን ጠላት ሰይጣንን ከማምለክ ለእርሱም ከመገዛት ያድነው ዘንድ የእግዚአብሔር ልጅ መምጣቱንና ከእመቤታችን ከቅድስት ድንግል ማርያም ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነሥቶ ሰው መሆኑን
የአጫብር ዜማ ጥናት እንዲቀጥል የኢትዮጽያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ውሳኔ አስተላለፈ
ለወራት የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት እግድ አስተላልፎበት የነበረው የአጫበር ስም የሚደረጉ የተለያዩ ችግሮችን እንጂ በተፈቀደላቸው ባለ ሙያዎች የሚሰጥ ሥልጠናን ስለማይመለከት የትምህርትና ማሰልጠኛ መምሪያ ከሚመለከታቸውን ባለ ድርሻ አካላት ጋር ውይይት በማድረግ የአጫብር ዜማን ማስጠናት እንዲቀጥል ውሳኔ አስተላልፏል።
የአጫብር ዜማ ጥናቱ ሲቀጥል መጋቤ ሃይማኖት ዲበኵሉ ኅየሰ ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ፣ ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ ክፍልናከአዲስ አበባ ሰ/ት/ቤቶች አንድነት ጋር ተናበው እንዲሰሩ ተብሏል።
የአጫብር ዜማን በተመለከተ በሊቃውንት ተጠንቶ እስኪተገበር ድረስ ሁሉም ሰንበት ትምህርት ቤት የአጫበር ዝማሬን እንዲያቆሙ ተወስኖ እንደነበር ይታወሳል ።
❤ መድኃኔዓለም አምላካችን ለአቡነ ባዕለ ማርያም ይህን ቃል ኪዳን ከሰጣቸው በኋላ "እንደ ነቢያት ነቢይ እንደ ሐዋርያት ሐዋርያ እንደ ሰማዕታት ሰማዕት እንደ ጻድቃን ጻድቅ፤ እንደ ካህናት ካህን ነህ፤" አላቸው ክብርና ጸጋን አጐናጸፋቸው አምስት ጊዜ ባረካቸው አምስት ጊዜ እፍ አለባቸው መንፈስ ቅዱስንም አሳደረባቸው እመቤታችን ድንግል ማርያም እና ዘጠኙ ሊቃነ መላእክት አንድ አንድ አክሊል ሰጧቸው ጌታችንም ዐሥር አክሊላትን አቀዳጅቷቸው "በዛሬው ዕለት ወደ እኔ ትመጣለህ" ብሏቸው ወደ ሰማይ ዐረገ።
❤ ጻድቁ አቡነ ባዕለ ማርያምም "ለአብ ምስጋና ይገባል፣ ለወልድ ምስጋና ይገባል፣ ለመንፈስ ቅዱስም ምስጋና ይገባል፣ አምላክን ለወለደች ለእመቤታችን ድንግል ማርያምም ምስጋና ይገባል፣ በክቡር ደሙ ለተቀደሰው ለመስቀለ ክርስቶስም ምስጋና ይገባል"። ብለው ካመሰገኑ በኋላ በዚሁ ዕለት ኅዳር ፲፯ ቀን ዐረፉ ቅድስት እናታችን ወለተ ጴጥሮስም የታሰሩበት ሰንሰለት የማይፈታ ጽኑ ስለ ነበረ እንዳለ ቀብራቸው ወደ ጎንደር ተመልሳ ሄደች። ከአባታችን ከአቡነ ባዕለ ማርያም እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን፤ በጸሎታቸውም ይማረን!። ምንጭ፦ ከገድለ ቅድስት ወለተ ጴጥሮስ መግቢያ ላይ የተወሰደ።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #ኅዳር ፲፯ (17) ቀን።
❤ እንኳን ለኢትዮጵያዊው ጻድቅ ዐሥር አክሊል ጸጋ ለተሰጣቸው፣ ብዙ ቃል ኪዳን ለተገባላቸው፣ ቅድስት ወለተ ጴጥሮስ በበረሃ በተጣለች ጊዜ በዛ ተገናኝተው ላጽናኗት፣ በጨረሻም በዐረፉ ጊዜ እርሷ ለቀበረቻቸው ለታላቁ አባት #ለአቡነ_ባዕለ_ማርያም ለዕረፍት በዐል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #አቡነ_ባዕለ_ማርያም፦ የምድረ ጀባይ ደብረ ቅዱሳን አቡነ ባዕለ ማርያም ወቅድስት ወለተ ጴጥሮስ አንድነት ገዳም ያለበት ቦታ ጥንቱን መላው አገው ምድር የጉሙዝ ቦታ ነበር። የሀገሩ ንጉሥ ጀባይ ይባል ነበር። ግብሩ አረማዊ ነው፡፡ ስለዚህ ገዳሙ ያለበት በረሃ "ምድረ ጀባይ" ተባለ ትርጕሙም "የሥቃይ ቦታ ማለት ነው በረሃው ልዩ ልዩ አራዊት ይገኙበታል በየጊዜው የነገሡ ከሓድያን በሃይማኖታቸው የጸኑ ሕዝበ ክርስቲያንን እጅ እግራቸውን በሰንሰለት እያሰሩ የሚጥሉበት በረሃ ነበር፡፡
❤ ታስረው የወደቁትን ክርስቲያኖች አራዊት ሰባብረው እየበሏቸውና ሰደድ እሳት እያቃጠላቸው ይሞቱ ነበር የሥቃይ ቦታ የተባለውም ስለዚህ ነው በቊጥር የማይታወቁ ብዙ ሕዝበ ክርስቲያን በሰማዕትነት ስለ ሞቱበትና እንደ ሰማይ ከዋክብት የበዙ ቅዱሳን ስለ ተሰወሩበት ገዳሙ ያለበት በረሃ በበረሃውያን አበው ዘንድ "ደብረ ቅዱሳን" እየተባለ ይጠራል ከፊሉ እስረኛ ሲሞት ከፊሉ እየተሰወረ እስከ ዐሥራ አምስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ደረሰ፡፡
❤ በዚህ ጊዜ ቅዱስ አባታችን አባ ባዕለ ማርያም ወንጌልን እያስተማሩ ሳለ እስከ ሕዝባቸው ድረስ ተገደው እጅ እግራቸውን በሰንሰለት ታስረው በዚህ በረሃ ተጣሉ ከእርሳቸው ጋር እንሞታለን ያሉ ምእመናንን እንደ እርሳቸው በሰንሰለት አስረው በዚሁ በረሃ ወረወሯቸው ከተወረወሩት ምእመናን መካከል አራዊት የበሏቸው አሉ ከበረሃ የሚነሣው ሰደድ እሳት ያቃጠላቸውም አሉ፣ የጻድቃን ዐላማቸው ሰውነታቸውን ከምድራዊ ቅጣት፣ ከእሳትና ከአራዊት መጠበቅ ሳይሆን ነፍሳቸውን ከሰማያዊ ቅጣት መጠበቅ ነውና በሰማዩ ንጉሥ በእግዚአብሔር ፊት ከዘለዐለማዊ ቅጣት ነጻ ይሆኑ ዘንድ ወደው፣ ፈቅደው ለምድራውያን ነገሥታት የሚደርስባቸውን ቅጣት ተቀበሉ። በአራዊት የተበሉት "የባሪያዎችህን በድኖች ለሰማይ ወፎች መብል አደረጉ፤ የጻድቃንህንም ሥጋ ለምድር አራዊት" ብሎ ቅዱስ ዳዊት የዘመረላቸው ናቸው መዝ ፸፰፥፪ በእሳት የተጠበሱትም እንደ አባ መርትያኖስ "ከሰማዩ እሳት የምድሩ ይሻለናል፤" የሚሉ ናቸው። ብዙ ምእመናን በተቃጠሉበት በዚያ የመከራ ወቅት ቅዱስ አባታችን አቡነ ባዕለ ማርያምን ግን እግዚአብሔር ከእሳቱም ከአራዊትም ሠወራቸው ተሠውረው እየጸለዩ እስከ ዐሥራ ስድስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ደረሱ።
❤ በዚህ ጊዜ ዐፄ ሱስንዮስ ቅድስት እናታችን ወለተ ጴጥሮስን ከበረሃው እንዲጥሏት አዘዘ ወታደሮችም አምጥተው "ገርበል" በሚባል በረሃ ጣሏት። ገርበል የተባለው ቦታ ዛሬ አፋፍ ኢየሱስ የሚባለው ነው ቅድስት እናታችን ወለተ ጴጥሮስን ከመሬት ሳትደርስ ቅዱስ ሚካኤል በአየር ላይ በሁለቱ ክንፎቹ ተቀብሎ ወደ ብሔረ ሕያዋን አሳይቶ መልሶ አምጥቶ ዋልድባ አደረሳት፡፡ ሀብተ ምንኵስናን፣ ሥርዐተ አበውን፣ ዜና አበውን፣ ነገረ አበውን፣ ሕንጻ መነኰሳትን አስተምሯት መልሶ ከተጣለችበት ገርበል ከሚባለው በረሃ ከለምለም ሣር ላይ አኖራት። በማግስቱም ወታደሮች ገብተው ቢያዩዋት እንደ ፀሐይ እያበራች ቆማ ስትጸልይ አገኟት። ለንጉሥ ሱስንዮስ እንዳልሞተች ሲነግሩት "እንዲያሠቃያት ጀባይ ለሚባል የጉሙዝ ንጉሥ ሰጥታችኋት ተመለሱ" ብሎ ላከ ወታደሮችም እንደ ታዘዙት አደረጉ።
❤ የጉሙዙ ንጉሥም ተቀብሎ፣ ወደ ምደረ ጀባይ በረሃ አውርዶ፣ እጅ እግሯን አስሮ ከትክል ድንጋይ ላይ አስቀመጣት በላይዋ ላይ ቤት ሠርቶ ሣር ከምሮ በእሳት አቃጠላት። ቅድስት እናታችን ወለተ ጴጥሮስም ጸሎተ ዳንኤልን፣ ጸሎተ ሠለስቱ ደቂቅን ስትጸልይ በእግዚአብሔር ኀይል እሳቱ እንደ በረዶ ቀዘቀዘላት በልዩ ልዩ ጸዋትወ መከራ የጉሙዝ ንጉሥ እያሠቃያት ከቆመች ሳትቀመጥ፣ እጇን ከዘረጋች ሳታጥፍ ሦስት ዐመት ስትጸልይ ኖረች።
❤ በዚህ ጊዜ አቡነ ባዕለ ማርያም ከተሰወሩበት ቦታ እንደ አጥቢያ ፀሐይ ወገግ ብለው ተገለጡላት የታሰሩበት ሰንሰለት ከሰውነታቸው ተጣብቆ በብዙ ድካም ውስጥ የቆዩ ቢሆኑም ፊታቸው እንደ አጥቢያ ፀሐይ ሲያበራ የቤተ መንግሥት ማለፊያ መብልና መጠጥ ሲመገቡ የኖሩ እንጂ ታስረው በምድረ በዳ የተጣሉና ድንጋይ ተተንተርሰው፣ ጤዛ ልሰው ዳዋ ለብሰው የሚኖሩ አይመስሉም ነበር።
❤ ቅድስት እናታችን ወለተ ጴጥሮስም ባየቻቸው ጊዜ ምትሐት አሳይቶ ሰይጣን እንዳይፈታተናት ወደ እግዚአብሔር አመለከተች። ያንጊዜ ጻድቁ አቡነ ባዕለ ማርያም ስሟን ሳያውቁ፣ ግብሯን ሳይጠይቁ በመንፈስ ቅዱስ ተገልጾላቸው "የክርስቶስ ወታደር ወለተ ጴጥሮስ ሆይ!" ብለው በስሟ ጠሯት ክብርት እናታችን ወለተ ጴጥሮስም የእግዚአብሔር ሰው መሆናቸውን በዚህ ዐወቀች ዐይኖቿን ወደ ሰማይ ቀና አድርጋ "ከሰው ተለይቼ በምድረ በዳ ብቸኛ እንዳልሆን ኀጥእት ባሪያህን ሳትረሳ ሰው ላክህልኝን?" ብላ እግዚአብሔርን አመሰገነች።
❤ ወደ አባታችን አቡነ ባዕለ ማርያም ጠጋ ብላም አነጋገረቻቸው እርሳቸውም በብዙ ኅብረ ትንቢት ወደፊት የሚገጥማትን መከራና ሥቃይ ነገሯት። ለጥቂት ጊዜ አጽናንተዋት ለሰባት ቀናት ያህል ታመሙ ኅዳር ፲፯ (17) (ዐሥራ ሰባት) ቀን ጌታችን መድኃኔዓለም ኢየሱስ ክርስቶስ ቅዱሳን ኪሩቤልና ሱራፌል መንበሩን እንደ ተሸከሙ፣ በአንድነቱ በሦስትነቱ ተገልጾ እናቱ ድንግል ማርያምን፣ እልፍ አእላፋት መላእክትንና ሊቃነ መላእክትን አስከትሎ መጥቶ እንዲህ የሚል ቃል ኪዳን ሰጣቸው፤ ወዳጄ ባዕለ ማርያም ሆይ ከድካም ወደ ዕረፍት፣ ከኀሣር ወደ ክብር፣ ከሞት ወደ ሕይወት ላሸጋግርህ ወደ አንተ መጣሁ። አንተም ይህን ቃል ኪዳን ትቀበልና ወደ እኔ ትመጣ ዘንድ ተዘጋጅ። ስምህን የጠራ፣ ዝክርህን የዘከረ፣ ቤተ ክርስቲያንህን የተሳለመ፣ ደዌ ሥጋ ደዌ ነፍስ አያድርበትም እኔ ከክፉ ነገር ሁሉ አድነዋለሁ፣ ቤተ ክርስቲያንህን የሠራውን፣ ያሠራውን በሀብት፤ በገንዘብ፣ በጕልበት፣ በሐሳብ የረዳውንና ያገዘውን ሁሉ ከሓድያን ነገሥታት መከራ ባጸነብህ ጊዜ አንተን እንደ ሰወርኩህ ከመከራ ሥጋ ከመከራ ነፍስ እሰውረዋለሁ። ቢቻል በየወሩ በ፲፯ ቀን ባይቻል በየዓመቱ ኅዳር ፲፯ ቀን ዝክር አዘጋጅቶ የሞትህን መታሰቢያ የዘከረውን፣ ዝክርህን የቀመሰውን አንተ ከገባህበት መንግሥተ ሰማያት አስገባዋለሁ።
❤ በስምህ ከፈለቀው ጠበል የተጠመቀውን ሁሉ የቡዳ መንፈስ፣ ድግምት፣ ዛር ዐይነ ጥላ፣ ሾተላይ፣ ልቡሳነ ሥጋ ረቂቃን አጋንንት እንዲወጡለት አደርጋለሁ፣
የታሰርክበትን ሰንሰለት አይቶ፣ መከራህን አስቦ፣ በልቡ አዝኖ፣ እንባውን አፍስሶ "አምላከ አቡነ ባዕለ ማርያም ይቅር በለኝ" ብሎ ቢማፀን ከልጅነቱ ጀምሮ እስከዚያች ቀን የሠራውን ኀጢአት ይቅር ብዬ እንደ ዐርባ ቀን ሕፃን አደርገውና በሰንሰለቱ ቀለበት ልክ ክብር አድለዋለ፣
ገዳምህን የረገጠውን፣ መቃብርህ ካለበት ቤተ ክርስቲያንና ዝክርህ ከበሰለበት ምድጃ እምነት አንሥቶ የተቀባውን፤ በልቡ ሳይጠራጠር አንተን አምኖ መልካም ነገር ያደረገውን ሁሉ እስከ ሃያ አምስት ትውልድ እምርልሃለሁ።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #ኅዳር ፲፯ (17) ቀን።
❤ እንኳን #ለዓለም_ሁሉ_መምህር ለቊስጥንጥንያው ሊቀ ጳጳስ #ለቅዱስ_ዮሐንስ_አፈ_ወርቅ_ለሥጋው_ለፈለሰበት በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከቡሩክ #አብርሃምና_ከሚስቱ_ሐሪክ_ከወጺፍ_ጻድቃን ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
✝ ✝ ✝
❤ #የቅዱስ_ዮሐንስ_አፈ_ወርቅ_የሥጋው_ፍልሰት፦ ይህም እንዲህ ነው መበለቲቱን ቦታዋን በግፍ ነጥቃታለችና እርሱም እንድትመስላት ቢያዛት ስለአልሰማችው ስለ መበለቲቱ ቦታ ቅዱስ ዮሐንስ ንግሥት አውዶክስያን በአወገዛት ጊዜ በእርሱ ላይ ተቆጣች ሰይጣንም በልቧ አደረና ስለ ክፉ ሥራቸውና ስለ በደላቸው አውግዞ የለያቸውን ኤጲስቆጶሳት በእርሱ ላይ ሰበሰበች። እርሱንም ስለ መሰደዱ ከእርሷ ጋር ተስማምተው አድራኮስ ወደምትባል ደሴት አጋዘችው በዚያም ጥቂት ዓመታት ኑሮ ወደ መንበረ ሢመቱ ተመለሰ።
❤ ከዚህም በኋላ ዳግመኛ መናፍቃን የሆነ ኤጲስ ቆጶሳትን ሰበሰበችና ወደ አርማንያ አጋዙት ከዚያም በረሀ ወደሆነ ሩቅ አገር ሰደዱትና በዚያ ዐረፈ። የአርቃዴዎስም ልጅ ታናሹ ቴዎዶስዮስ በነገሠ ጊዜ መልክተኞችን ልኮ የቅዱስ ዮሐንስን ሥጋ ብዙ በመዘመርና በማመስገን በታላቅ ክብር ወደ ቊስጥንጥንያ አፍልሶ አስመጣው ይህም ከዕረፍቱ በኋላበሠላሳ አምስት ዓመት ነው።
❤ በሌላ በቅብጢ መጽሐፍ በግንቦት ወር ሃያ ሁለት ቀን እንደ ደረሰ ይነገራል በሮሜውያን መጽሐፍ ግን በየካቲት ወር ሃያ ሁለት ቀን ተባለ የዕንቊ ፈርጾች ባሉት የዕብነ በረድ ሳጥን ውስጥ አድርገው ወደ ቤተ መቅደስ አስገቡት ከሥጋውም ታላላቅ የሆነ ድንቆች ተአምራት ተገለጡ።
❤ ሁለተኛም የእስክንድርያ ግጻዌና የአገረ ቅብጥ ኤጲስቆጶስ አባ ዮሐንስ የጻፈው ግጻዌ የመለካውያንም ግጻዌ በዚች በኅዳር ዐሥራ ሰባት ቀን ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ እንዳረፈባት ተባበሩ። ሁለተኛም ደግሞ የመለካውያን ግጻዌ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ዐይሉል በሚባል ወር በዐሥራ አራት እንዳረፈ ይናገራል ይህም በመድኃኒታችን በመስቀል በዓል መስከረም ዐሥራ ሰባት ቀን ነው። ስለዚህም ራሱን ለማሰሰቻል ወደ ኅዳር ዐሥራ ሰባት ቀን ለወጡት።
❤ የቀደሙ መጻሕፍት ግን ዕረፍቱን ግንቦት ዐሥራ ሁለት ቀን እንደሆነ ያወሳሉ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ ቅዱስ በከበረ አባት በዮሐንስ አወ ወርቅ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦የኅዳር 17 ስንክሳር።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #የዕለቱ_የማኅሌት_ምስባክ፦ "እስመ መምህረ ሕግ ይሁብ በረከተ። ወየሐውር እምኀይል ውስተ ኃይል። ወያስተርኢ አምላከ አማልክት በጽዮን"። መዝ 83፥6-7። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 10፥1-22።
✝ ✝ ✝
❤ #የዕለቱ_ምስባክ፦ "እግዚአብሔር ያፈቅሮሙ ለጻድቃን። እግዚአብሔር የዐቅቦሙ ለፈላስያን። ወይትዌከፎሙ ለዕቤራት ወለእጓለ ማውታ"። መዝ 145፥8-9። የሚነበቡት መልዕክታት ፊሊ 1፥12-19፣ 1ኛ ጴጥ 2፥10-18 እና የሐዋ ሥራ 16፥14-25 የሚነበበው ወንጌል ማቴ10፥16- ፍ.ም። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ቅዳሴ ነው። መልካም የቅድስት ወለተ ጴጥሮስና የአቡነ ሲኖዳ የዕረፍታቸው በዓልና የነቢያት (የገና) ጾም ጊዜና ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ #ኅዳር ፲፯ (17) ቀን።
❤ እንኳን #ለኢትዮጵያዊቷ_ሰማዕት_ወጻድቅ ለሆነችው በጣና ባሕር ላይ ቆማ ስትጸልይ ልብሷ ለገዳሙ ያበራ ለነበረችው ለታላቋ እናት #ለቅድስት_ወለተ_ጴጥሮስ ለዕረፍት በዓልና ለኢትዮጵያዊው ጻድቅ ዐፅማቸውን የተሸከች በቅሎም ለወለደችና ለመካኖች ልዩ ቃል ኪዳን ለተሰጣቸው ለታላቁ አባት #ለአቡነ_ሲኖዳ ለዕረፍታቸው በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #ሰማዕት_ወጻድቅ_ቅድስት_ወለተ_ጴጥሮስ፦ የትውልድ ሀገሯ ጎንደር ደዋሮና ፈጠጋር ነው፡፡ አባቷ ቅዱስ ባሕር ሰገድ እናቷ ቅድስት ክርስቶስ ዕበያ ይባላሉ፡፡ በሕግ በሥርዓት በሊቀ ጳጳሱ ትእዛዝ የንጉሥ ሱስንዮስን የአማካሪዎች አለቃ የሆነውን መልክአ ክርስቶስን አግብታ ሦስት ልጆችን ወልዳለች፡፡ ባሏም ታላቅና እጅግ ባለጸጋ ነበርና ከልጆቿ ጋር በተድላ በደስታ መኖር እንደ ጀመረች "አቤቱ ፈጣሪዬ ሆይ እነዚህ ሦስት ልጆቼ አንተን የማያስደስቱ ከሆነ በሞት ውሰዳቸው" ብላ ከጸለየች በኋላ እንደፍላጎቷ ሦስቱም ልጆቿ በሞት ተወስደውላታል፡፡
❤ ባለቤቷም እጅግ እየወደዳት እርሷ ግን"ይህ ዓለም እንደ ጤዛ ያልፋል" ብላ ከሞላ ሀብቷ ከሞቀ ቤቷ ተለይታ ወጥታ በመመነን ጣና ገባች በዚያም በተጋድሎ ስትኖር ባሏ ሄዶ አበምኔቱን "ለምን ገዳም አስገባሃት?" ብሎ ከሰሳቸውና ከገዳሙ አስወጣት፡፡ እርሷ ግን ተደብቃ አክሱም ሄዳ ደብረ በንኰል ገዳም ገባች፡፡ ተመልሳም መጥታ በጣና ባሕር ላይ ቆማ መጸለይ ጀመረች፡፡
❤ በዘመኗም የነበረው ገዢ ጨካኝና ለጣዖት የሚሰግድ ስለነበር በትልቅ ገደል ወርውረው እንዲጥሏት አደረጋት፡፡ ነገር ግን መልአኩ ቅዱስ ሚካኤል ከእግዚአብሔር ተልኮ መጥቶ በክንፉ ተቀብሏት ወስዶ ብሔረ ብፁዓንን አሳይቶ መልሶ አምጥቶ ዋልድባ አደረሳት፡፡
❤ ቅድስት እናታችን ወደ ጉምዝ አገርም ተሰዳ ሳለ በነደደ እሳት ውስጥ ቢጨምሯት እሳቱ ምንም ሳያቃጥላት ወጥታለች፡፡ ተመልሳም በጣና ባሕር ላይ ቆማ ስትጸልይ ልብሷ ለገዳሙ ያበራ ነበር፡፡ ባሏም እምነቱን ቀይሮ ከካቶሊኮች ጋር ስለተዛመደ ቅድስት እናታችን ካቶሊኮችንና ባሏን አጥብቃ ስለተቃወመች በገመድ አስረዋት በጎንደር ከተማ ጎዳና ላይ ጎትተው አሠቃይተዋታል፡፡
❤ ቅድስት ወለተ ጴጥሮስ ሰባት ገዳማትን ያቀናች ሲሆን ከ700 በላይ በሚሆኑ ወንዶች መነኰሳትና ሴቶች መነኰሳይት ላይ እመ ምኔት ሆና ተሹማ አገልግላለች፡፡ ከመነነችበትም ጊዜ ጀምሮ ምግቧም የመረረ ቅጠል፣ ኮሶና አመድ ነበር፡፡
❤ ቅድስት እናታችን ታላቁን የሬማ መድኃኔዓለምን ቤተ ክርስቲያን ሠርታ ሙታንን እያስነሣች፣ ድውያንን እየፈወሰች በታላቅ ተጋድሎ እያገለገለች ሳለ ኅዳር 17 ቀን በታላቅ ክብር ዐርፋለች፡፡ ጌታችንም ድንቅ የሆነ ቃልኪዳን ገብቶላታል፡፡ በዕረፍቷም ጊዜ የብርሃን ምሰሶ ከምድር እስከ ሰማይ ተተክሎ ታይቷል፡፡
❤ የእናታችን የቅድስት ወለተ ጴጥሮስ መላ ዕድሜዋ ሃምሳ ዓመት ነው። ከመመነኗ አስቀድሞ ሃያ አራት ዓመት ከመነነች በኋላ ሃያ ስድስት ዓመት ኖራለች። ከእናታችን ከቅድስት ወለተ ጴጥሮስ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎቷም ይማረን!። ምንጭ፦ ገድለ ወለተ ጴጥሮስና መዝገበ ቅዱሳን።
✝️ ✝️ ✝️
❤ #አቡነ_ሲኖዳ፦ ሲኖዳ ማለት "ታማኝ" ማለት ነው፡፡ ትውልድ አገራቸው ጎጃም ሲሆኑ የሸዋ ባላባት ልጅ ናቸው፡፡ በጎጃም ደብረ ዲማህ አጠገብ ደብረ ፅሞና በተባለው ቦታ ይኖሩ የነበሩ ሰዎች ያመልኩት የነበረውን ትልቅ ዘንዶ አቡነ ሲኖዳ በመስቀል ባርከው ከሁለት ሰንጥቀውታል፡፡ ሰዎቹንም አስተምረው አሳምነው አጥምቀው የእመቤታችንን ቤተ ክርስቲያን ሠርተውላቸዋል፡፡ ጻድቁ የሊቀ ሰማዕታት የቅዱስ ጊዮርጊስ ዓይነት ገድል አላቸው፡፡ ለዘንዶ ምግብ እንዲትሆን ግብር ሆና የተሰጠችውን ሴት ልጅ ከጫካ አግኝተው ዘንዶውን በመስቀላቸው አማትበው ገድለው ልጅቷን አድነዋታል፡፡
❤ በዘመናቸው ነግሦ የነበረው "ሕዝበ ናኝ" የተባለው ንጉሥ በሰዎች ወሬ "ንግሥናዬ ለሌላ ይሰጣል ትላለህሳ" በማለት ጻድቁን እጅና እግራቸውን አስሮ ካሠቃያቸው በኋላ እጃቸውን አስቆረጣቸው፡፡ ነገር ግን ለአቡነ ሲኖዳ እመ ብርሃን የብርሃን እጅ ተከለችላቸው፡፡ በጌቴሴማኒ ያለችው ሉቃስ የሳላትና ስርጉት የተባለችው የእመቤታችን ሥዕል በየጊዜው እየተገለጠች ታነጋግራቸው ነበር፡፡ ንጉሡ በስደትና በግዞት ብዙ እያሠቃያቸው ሳለ መልአክ መጥቶ ዕለተ ዕረፍታቸውን ነግሯቸው እሳቸውም ደቀ መዛሙርቶቻቸውን ጠርተው ከተሰናበቷቸው በኋላ ነው ንጉሡ በኅዳር 17 ቀን አንገታቸውን ያሰየፋቸው፡፡ ከአንገታቸው ውኃ፣ ደምና ወተት ፈሷል፡፡
❤ ጻድቁ በሐይቅ ደሴት የተቀበሩ ቢሆንም ቀድሞ በሚያገለግሉበት በድፍን ምስራቅ ጎጃም ድርቅና ርኃብ ስለሆነ በደብረ ፅሞና ገዳም ይኖሩ የነበሩት አባ መቃርስ ዐፅማቸውን አፍልሰው በማምጣት በደብረ ዲማህ አጠገብ በስማቸው በተሰራው በደብረ ፅሞና ቤተ ክርስቲያን በክብር ሲያሳርፉት ወዲያው ዝናብ ጥሎ ድርቁም ጠፍቷል፡፡ ዐፅማቸውን ተሸክማ ያመጣችው በቅሎም ወልዳለች፡፡ ኢትዮጵያዊው ጻድቅ አቡነ ሲኖዳ ለማይወልዱ መካኖች እጅግ ልዩ ቃልኪዳን ነው የተሰጣቸው፡፡ መቃብራቸውን
እየዞሩ እምነታቸውን እየተቀቡ ገድላቸውን እየታሹ የማይወልዱ መካኖች የሉም፡፡ ከሩቅም ሆነው በስማቸው ተስለው እምነታቸውን ተቀብተው የሚወልዱ በጣም ብዙዎች ናቸው፣ እንኳንስ ሰው ይቅርና ዐፅማቸውን የተሸከች በቅሎም ወልዳለችና!።
❤ የጻድቁ ሌላኛው በስማቸው የተሰየመውና እጅግ ተአምረኛው ታቦታቸው ዛሬም አቡነ ሲኖዳ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ከአ.አ 180 ኪ.ሜ ርቆ ከጣርማ በር አልፎ ሞላሌ ከተማ ውስጥ ይገኛል፡፡ በሰሜን ሸዋ በሚገኘው በዚህ ቤተ ክርስቲያናቸው ውስጥ በዘመናችንም በጣም በርካታ ተአምራት ይደረጋሉ፡፡ ለጻድቁ የተሰጠችውን የስዕለት በግ ጅብ ቤተ ክርስቲያኑ ውስጥ ገብቶ ሊበላ ሲል ቀንዱን ነክሶ ደርቆ ሞቶ ሲገኝ በጉ ግን ምንም አልሆነም፡፡ አቃቢቷም እንዲሁ ከትልቁ ተራራ ሥር በትልቅ ቅል ውኃ ቀድተው ሲመለሱ ገመዱ ተበጥሶ ቅሉ ከነውኃው ከትልቁ ገደል ገብቶ ድንጋይ ላይ ቢያርፍም ቅሉ ሳይሆን ድንጋዩ ነው የተሰበረው፡፡ የአካባቢው ነዋሪም "በጉ ጅብ ገደለ፣ ቅሉ ድንጋይ ሰበረ" እያሉ ጻድቁን ያወድሷቸዋል፡፡ ከአባታች ከአቡነ ሲኖዳ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸውም ይማረን!። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳን ከሚለው መጽሐፍ።
242513398
Arsema Solomon
Abysinya
🔴የመኪና አደጋ ለደረሰባት እህታችን በዚ አካውንት አስገቡልን ነገ ረቡዕ 17/03/18 ማታ 12:00 ባለው ብር ይኬዳል።
