ch
Feedback
HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

前往频道在 Telegram

❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239

显示更多
2 276
订阅者
+524 小时
+117
+3430
帖子存档
«ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ፣ የእግዚአብሔር ልጅ ሆይ፣ ልቤን በመገኘትህ ሙላው። ባዶ አድርገህ አትተወኝ፤ ይልቅስ በመንፈስህ በውስጤ ኑር። ክፉና ርኩስ መንፈስን ሁሉ ከእኔ አርቅልኝ፤ ለዘላለም ያንተ ሆኜ
«ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ፣ የእግዚአብሔር ልጅ ሆይ፣ ልቤን በመገኘትህ ሙላው። ባዶ አድርገህ አትተወኝ፤ ይልቅስ በመንፈስህ በውስጤ ኑር። ክፉና ርኩስ መንፈስን ሁሉ ከእኔ አርቅልኝ፤ ለዘላለም ያንተ ሆኜ እንድኖር በጸጋህ አትመኝ። አሜን።»

«አባቶቻችን ስለ አስትሮሎጂና ኮከብ ቆጠራ የነገሩን!» » ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፦ ከዋክብት አልፈጠሩንም፣ ድርጊቶቻችንንም አይመሩም… ይህን ማለት እግዚአብሔርን ፍትሕ አያደርግም ብሎ እንደ መክሰስ ነው፤ ምክንያቱም እርሱ የሚሸልመን ወይም የሚቀጣን እንደ ሆሮስኮፓችን (የኮከብ ትንበያችን) ሳይሆን እንደ ሥራችን ነው። የቀደመችው ቤተክርስቲያን ቀኖና (የሐዋርያት ሥርዐት) ክርስቲያኖች በኮከብ ቆጠራ እንዳይጠመዱ ወይም ኮከብ ቆጣሪዎችን እንዳያማክሩ ይከለክላል። » ቅዱስ አውግስጢኖስ ዘሂፖ (354–430 ዓ.ም.) ወደ ክርስትና ከመመለሱ በፊት አብዛኛውን የወጣትነት ዘመኑን በኮከብ ቆጠራ አሳልፏል። ኮከብ ቆጣሪዎችን አማክር ነበር፤ አንተ እውነተኛው አምላክ ግን እነዚህ ነገሮች ሐሰት መሆናቸውን አሳየኸኝ። በኮከብ ቆጠራ ማመን ማለት በፈጣሪው ፈንታ በተፈጠሩ ነገሮች ላይ እምነትን መጣል ነው። ያደረገው ነገር በይፋ ንስሐ ገብቷል፣ (በሐዋርያት ሥራ 19:19 እንደተገለጸው) ሌሎችም የኮከብ ቆጠራ መጻሕፍትን እንዲያቃጥሉ አበረታትቷል፣ አጋንንት አእምሮን በባርነት ለመግዛት ኮከብ ቆጠራን እንደሚጠቀሙ አስጠንቅቋል። » ቅዱስ ጎርጎርዮስ ነባቤ መለኮት (ዘእንዚናዙ) ኮከብ ቆጠራን በእጣ ፈንታዊ አስተሳሰቡ ምክንያት ነቅፎታል፦ ከዋክብት ሊያበሩ ይችላሉ፣ ነገር ግን አይገዙንም። ነጻነታችንን ለሰማይ ተረቶች አሳልፈን አንስጥ። ትምህርቱ፦ በዞዲያክ (በከዋክብት) እጣ ፈንታ ማመን የሰውን ነጻ ፈቃድና በውስጡ ያለውን የእግዚአብሔርን መልክ ይክዳል። ክርስቲያኖች የተጠሩት ለመንፈሳዊ ነጻነት እንጂ፣ ለኮከብ ባርነት አይደለም። » ኢሳይያስ 47:13-14 ኮከብ ቆጣሪዎችህ፣ ትንቢት የሚናገሩት ከዋክብት ተመልካቾችህ... ይቅረቡ። እነሆ እነርሱ እንደ ገለባ ናቸው፤ እሳትም ያቃጥላቸዋል። » ዘዳግም 18:10-12 በመካከላችሁ... ምዋርተኛ ወይም ምልክቶችን ተርጓሚ... ማንም አይገኝ። እነዚህን ነገሮች የሚያደርግ ማንኛውም ሰው በጌታ ዘንድ አስጸያፊ ነው። » የሐዋርያት ሥራ 19:19 አዲስ ያመኑት ሰዎች የአስማትና የኮከብ ቆጠራ መጻሕፍቶቻቸውን በይፋ አቃጠሉ — ይህም በክርስቶስ ማመን ማንኛውንም ድብቅ የጥንቆላ ሥራ መተው እንደሚያስፈልግ ያሳያል። ታላቁ ቅዱስ ባስልዮስ፦ የከዋክብትን አካሄድ መመልከትና የእግዚአብሔርን ትእዛዛት ችላ ማለት ምክንያታዊ ያልሆነች ነፍስ ምልክት ነው። #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

«የዕለቱን ወንጌል እናንብብ!» (የሉቃስ ወንጌል ምዕራፍ 16፡19-31) «ቀይ ልብስና ቀጭን የተልባ እግር የለበሰ አንድ ባለ ጠጋ ሰው ነበረ፥ ዕለት ዕለትም እየተመቸው በደስታ ይኖር ነበር። አልዓዛርም የሚባል አንድ ድሀ በቍስል ተወርሶ በደጁ ተኝቶ ነበር፥ ከባለ ጠጋውም ማዕድ ከሚወድቀው ፍርፋሪ ሊጠግብ ይመኝ ነበር፤ ውሾች እንኳ መጥተው ቍስሎቹን ይልሱ ነበር። ድሀውም ሞተ፥ መላእክትም ወደ አብርሃም እቅፍ ወሰዱት፤ ባለ ጠጋው ደግሞ ሞተና ተቀበረ። በሲኦልም በሥቃይ ሳለ አሻቅቦ አብርሃምን በሩቅ አየ አልዓዛርንም በእቅፉ። እርሱም እየጮኸ። አብርሃም አባት ሆይ፥ ማረኝ፥ በዚህ ነበልባል እሣቀያለሁና የጣቱን ጫፍ በውኃ ነክሮ መላሴን እንዲያበርድልኝ አልዓዛርን ስደድልኝ አለ። አብርሃም ግን። ልጄ ሆይ፥ አንተ በሕይወትህ ሳለህ መልካም እንደ ተቀበልህ አስብ አልዓዛርም እንዲሁ ክፉ፤ አሁን ግን እርሱ በዚህ ይጽናናል አንተም ትሣቀያለህ። ከዚህም ሁሉ ጋር ከዚህ ወደ እናንተ ሊያልፉ የሚፈልጉ እንዳይችሉ፥ ወዲያ ያሉ ደግሞ ወደ እኛ እንዳይሻገሩ በእኛና በእናንተ መካከል ታላቅ ገደል ተደርጎአል አለ። እርሱም። እንኪያስ፥ አባት ሆይ፥ ወደ አባቴ ቤት እንድትሰደው እለምንሃለሁ፤ አምስት ወንድሞች አሉኝና፤ እነርሱ ደግሞ ወደዚህ ሥቃይ ስፍራ እንዳይመጡ ይመስክርላቸው አለ። አብርሃም ግን። ሙሴና ነቢያት አሉአቸው፤ እነርሱን ይስሙ አለው። እርሱም። አይደለም፥ አብርሃም አባት ሆይ፥ ነገር ግን ከሙታን አንዱ ቢሄድላቸው ንስሐ ይገባሉ አለ። ሙሴንና ነቢያትንም የማይሰሙ ከሆነ፥ ከሙታንም እንኳ አንድ ቢነሣ አያምኑም አለው።» #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

ሰኔ ፳፯ /27/ አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሰኔ ሃያ ሰባት በዚች ቀን ከተመረጡ አርድእት ውስጥ ሐዋርያው ሐናንያ አረፈ። ይህንንም ቅዱስ ሐዋርያት በደማስቆ ከተማ ኤጲስቆ
ሰኔ ፳፯ /27/
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሰኔ ሃያ ሰባት በዚች ቀን ከተመረጡ አርድእት ውስጥ ሐዋርያው ሐናንያ አረፈ። ይህንንም ቅዱስ ሐዋርያት በደማስቆ ከተማ ኤጲስቆጶስነት ሾሙት ። በውስጧም ሕይወት ሰጭ የወንጌልን ትምህርት አስተማረ ዳግመኛም በቤተ ገብርኤል ውስጥ ሰብኮ ክብር ይግባውና የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ሆነች የቀናች ሃይማኖት ብዙዎቹን መለሳቸው የክርስትና ጥምቀትንም አጠመቃቸው እውነተኛውንም የሃይማኖት ብርሃን አበራላቸው። ይህም ሐናንያ ሐዋርያው ጳውሎስን ይቅር ባይ ጌታችን በቸርነቱ ከክህደቱ በጠራውና ምርጥ ዕቃ በአደረገው ጊዜ ያጠመቀው ነው እጁንም በራሱ ላይና በዐይኖቹ ላይ ጭኖ ያዳነው እርሱ ነው። ጌታችንም በእጆቹ ታላላቅ ድንቆችንና ተአምራቶችን አደረገ በስብከቱም ብዙዎች አሕዛብ አመኑ ከአይሁድም ብዙዎቹን ክብር ይግባውና ክርስቶስን ወደ ማመን መለሳቸው። ከዚህም በኋላ ዐመፀኛው መኰንን ሉክያኖስ ይዞ ታላቅና አስጨናቂ ሥቃይን አሠቃየው ጐኖቹንም ሠንጥቆ በእሳት መብራቶች አቃጠለው ። ከዚህም በኋላ ከከተማው አውጥተው በደንጊያ እንዲወግሩት አዘዘ በዚያም ክብር ይግባውና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ እጅ ነፍሱን ሰጠ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑርለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

ይኼንን ምልክት ካያችሁ ውስጣችን የዝሙት መንፈስ አድፍጧልና ንቁበት!! ያልተረዳናቸው የእርግማን መንፈስ ፈተናዎች!! የበግ ለምድ ከለበሱት እባካችሁ ተጠበቁ!! https://youtu.be/GNExg1wu96w

» አባ አጋቶን:- አንድ ሰው በፊቴ ኃጢአት ቢሠራ፣ ማንም እንዳያየው ልብሴን እሸፍንለት ነበር። የተቆጣ ሰው፣ ሙታንን እንኳ ቢያስነሳ በእግዚአብሔር ዘንድ የተወደደ አይደለም። » አባ ይስሐቅ ሶርያዊ
» አባ አጋቶን:- አንድ ሰው በፊቴ ኃጢአት ቢሠራ፣ ማንም እንዳያየው ልብሴን እሸፍንለት ነበር። የተቆጣ ሰው፣ ሙታንን እንኳ ቢያስነሳ በእግዚአብሔር ዘንድ የተወደደ አይደለም። » አባ ይስሐቅ ሶርያዊ፡- ኃጢአቱን የሚያውቅ ሰው ሙታንን ከሚያስነሳ ይበልጣል። ወደ ጸሎት ስትቀርብ፣ የሚገባህ ይመስል በትዕቢት አትቅረብ። ይልቁንም በንጉሥ ፊት እንደቆመ ለማኝ ሁን። » አማ ሲንቅሌቲካ ዘእስክንድርያ (የበረሃ እናት)፦ በበረሃ እየኖሩ እንደ ከተማ ሰዎች የሚሆኑ ብዙዎች ናቸው። ጊዜያቸውን እያባከኑ ነው። በሕዝብ መካከል ሆኖ እንደ በረሃ ሰው መሆን ይሻላል። ወደ እግዚአብሔር ለሚጓዙ ሰዎች መጀመሪያ ላይ ተጋድሎና ብዙ ድካም አለ። ከዚያ በኋላ ግን ሊገለጽ የማይችል ደስታ አለ። » አባ ጳውሞን (ፖመን)፦ አፍህን በልብህ ያለውን እንዲናገር አስተምረው። ጢስ ንቦችን እንደሚያባርር፣ ከንቱ ወሬም የእግዚአብሔርን ህልውና (መገኘት) ያባርራል። ‘በቃልህ ትጸድቃለህ፤ በቃልህም ትኮነናለህ’ የሚለውን ጽሑፍ የሚያስታውስ ሰው ዝምታን ይመርጥ ነበር። » አባ አርሳንዮስ፦ ስለተናገርኩኝ ብዙ ጊዜ ተጸጽቻለሁ፤ ዝም ስላልኩኝ ግን በፍጹም ተጸጽቼ አላውቅም። ለዓለም ካልሞትክ፣ ለእግዚአብሔር መኖር አትችልም። #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

«የዕለቱን ወንጌል እናንብብ!» (የማቴዎስ ወንጌል 13፡36-44) «በዚያን ጊዜ ሕዝቡን ትቶ ወደ ቤት ገባ። ደቀ መዛሙርቱም ወደ እርሱ ቀርበው። የእርሻውን እንክርዳድ ምሳሌ ተርጕምልን አሉት። እርሱ
«የዕለቱን ወንጌል እናንብብ!» (የማቴዎስ ወንጌል 13፡36-44) «በዚያን ጊዜ ሕዝቡን ትቶ ወደ ቤት ገባ። ደቀ መዛሙርቱም ወደ እርሱ ቀርበው። የእርሻውን እንክርዳድ ምሳሌ ተርጕምልን አሉት። እርሱም መልሶ እንዲህ አላቸው። መልካምን ዘር የዘራው የሰው ልጅ ነው፤ እርሻውም ዓለም ነው፤ መልካሙም ዘር የመንግሥት ልጆች ናቸው፤ እንክርዳዱም የክፉው ልጆች ናቸው፥ የዘራውም ጠላት ዲያብሎስ ነው፤ መከሩም የዓለም መጨረሻ ነው፥ አጫጆችም መላእክት ናቸው። እንግዲህ እንክርዳድ ተለቅሞ በእሳት እንደሚቃጠል፥ በዓለም መጨረሻ እንዲሁ ይሆናል። የሰው ልጅ መላእክቱን ይልካል፥ ከመንግሥቱም እንቅፋትን ሁሉ ዓመፃንም የሚያደርጉትን ይለቅማሉ፥ ወደ እቶነ እሳትም ይጥሉአቸዋል፤ በዚያ ልቅሶና ጥርስ ማፋጨት ይሆናል። በዚያን ጊዜ ጻድቃን በአባታቸው መንግሥት እንደ ፀሐይ ይበራሉ። የሚሰማ ጆሮ ያለው ይስማ።» #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

ካህናትን እጅጉን ዘማዊና ሴሰኛ የሚያደርጉ ክፉ መናፍስቶችና ያስከተሉት ጉዳት!! ባልና ምስት በቤታቸው መጸለያቸው ግድ የሚሆነው ለዚህ ነው!! #ጸሎት #ስግደት https://youtu.be/-xA6BhYmeEE

«ቅዱሳን አባቶቻችን ስለ ስግደት ያስተማሩን!» => በእምነት የሚደረግ አንድ ስግደት ከዲያብሎስ ጋር ከሚደረግ አንድ ሺሕ የቃላት ክርክር የበለጠ ኃይል አለው። – ቅዱስ ሲሉዋን ዘአቶስ (A single prostration done with faith is more powerful than a thousand words of argument against the devil. – St. Silouan the Athonite) => አረጋዊ ፓይሲዮስ፦ ከልብ የተደረገ አንድ ስግደት ክፍሉን በመላእክት ይሞላዋል። (One heartfelt prostration fills a room with angels.) => ቅዱስ አትናቴዎስ፦ የሰገደ ሰው አክሊል ደፍቶ ይነሣል። (The bowed man rises crowned) => ቅዱስ ሴራፊም ዘሳሮቭ፦ ስግደት ፈቃድን ያጠነክራል፤ ልብን ደግሞ ያለሰልሳል። (Prostrations harden the will and soften the heart) => ቅዱስ ዮሐንስ ዘሰዋስው፦ አጋንንት ለሳምንታት ከሚጾም ሰው ይልቅ መሬት ላይ ሆኖ ከሚያለቅስ ሰው ይፈራሉ። (The demons fear the one who weeps on the ground more than one who fasts for weeks.)

«የዕለቱን ወንጌል አንብቡት!» የዮሐንስ ወንጌል 14፡18-27 «ወላጆች እንደ ሌላቸው ልጆች አልተዋችሁም፤ ወደ እናንተ እመጣለሁ። ገና ጥቂት ዘመን አለ ከዚህም በኋላ ዓለም አያየኝም፤ እናንተ ግን
«የዕለቱን ወንጌል አንብቡት!» የዮሐንስ ወንጌል 14፡18-27 «ወላጆች እንደ ሌላቸው ልጆች አልተዋችሁም፤ ወደ እናንተ እመጣለሁ። ገና ጥቂት ዘመን አለ ከዚህም በኋላ ዓለም አያየኝም፤ እናንተ ግን ታዩኛላችሁ፤ እኔ ሕያው ነኝና እናንተ ደግሞ ሕያዋን ትሆናላችሁ። እኔ በአባቴ እንዳለሁ እናንተም በእኔ እንዳላችሁ እኔም በእናንተ እንዳለሁ በዚያን ቀን ታውቃላችሁ። ትእዛዜ በእርሱ ዘንድ ያለችው የሚጠብቃትም የሚወደኝ እርሱ ነው፤ የሚወደኝንም አባቴ ይወደዋል እኔም እወደዋለሁ ራሴንም እገልጥለታለሁ። የአስቆሮቱ ያይደለ ይሁዳ። ጌታ ሆይ፥ ለዓለም ሳይሆን ራስህን ለእኛ ልትገልጥ ያለህ እንዴት ነው? አለው። ኢየሱስም መለሰ አለውም። የሚወደኝ ቢኖር ቃሌን ይጠብቃል፤ አባቴም ይወደዋል ወደ እርሱም እንመጣለን በእርሱም ዘንድ መኖሪያ እናደርጋለን። የማይወደኝ ቃሌን አይጠብቅም፤ የምትሰሙትም ቃል የላከኝ የአብ ነው እንጂ የእኔ አይደለም። ከእናንተ ዘንድ ስኖር ይህን ነግሬአችኋለሁ፤ አብ በስሜ የሚልከው ግን መንፈስ ቅዱስ የሆነው አጽናኝ እርሱ ሁሉን ያስተምራችኋል እኔም የነገርኋችሁን ሁሉ ያሳስባችኋል። ሰላምን እተውላችኋለሁ፥ ሰላሜን እሰጣችኋለሁ፤ እኔ የምሰጣችሁ ዓለም እንደሚሰጥ አይደለም። ልባችሁ አይታወክ አይፍራም።» #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

ሰኔ ፳፭ /25/
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሰኔ ሃያ አምስት በዚች ቀን ከሰባ ሁለቱ አርድእት አንዱ የፀራቢው ዮሴፍ ልጅ ሐዋርያው ይሁዳ በሰማዕትነት ሞተ። ይህም ሐዋርያ በብዙ አገሮች ሰበከ ወደ አንዲት ደሴትም ገብቶ በውስጧም ሰበከ ሰዎቿንም በጌታ አሳመናቸው ቤተ ክርስቲያንም ሠራላቸው በቀናች ሃይማኖትም አጸናቸው። ከዚያም ወደ ሮሃ ሀገር ሒዶ የሮሃ ንጉሥ አውጋንዮስን ከደዌው ፈወሰው የክርስትና ጥምቀትንም አጠመቀው ከዚያም ደግሞ ሐራፒ ወደሚባል አገር ሒዶ በውስጧ ሰበከ ከሰዎቿ ብዙዎቹን አጠመቃቸው ቤተ ክርስቲያንም ሠራላቸው። የዚያችም አገር ገዥ ይዞ ጽኑዕ ሥቃይ አሠቃየው ችንካር ያለው ጫማ በእግሮቹ ውስጥ አድርጎ አንድ ምዕራፍ ያህል አስሮጠው ከዚህም በኋላ ሰቅሎ በፍላፃ ነደፈው ክብርይግባውና በጌታችን እጅ ነፍሱን ሰጠ። ከመከራውም አስቀድሞ ለምእመናን መልእክትን ጽፎ ላከ እርሷም ከሐዋርያት መልእክቶች ሰባተኛ የሆነች ምሥጢርን የተመላች ናት በእርሷም ብዙዎች አረማውያንን ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ወደ ማመን አስገባቸው። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑርለዘላለሙ አሜን። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

ክፋትን ከሰዎች የሚማሩ የዘመናችን መናፍስቶችና ያደረሱብን ጉዳቶች!! እግዚአብሔር ሀብትና ገንዘብ ያልሰጠን ስለሚወደን ነው! ዘርፈ ከበደ ምን እያለችን ነው? https://youtu.be/MNJaIskMnpo

Repost from Dn Eyuel Habtamu
ይህ የብዙ ወጣቶች ጥያቄ ነው ። እግዚአብሔር ከረዳን ዛሬ ማታ 3 : 00 ላይ እንገናኝ ! ማንም እንዳይቀር ... ለ ሰው share እናድርግ !
ይህ የብዙ ወጣቶች ጥያቄ ነው ። እግዚአብሔር ከረዳን ዛሬ ማታ 3 : 00 ላይ እንገናኝ ! ማንም እንዳይቀር ... ለ ሰው share እናድርግ !

=> ታላቁ ቅዱስ እንጦንዮስ፦ ሰዎች የሚያብዱበት ዘመን ይመጣል፤ አንተ እንደነሱ ካልሆንክ ‘አብዷል’ ይሉሃል። ከሰው ማበረታቻን አትፈልግ—እግዚአብሔርን ፈልግ። => "ራስን በሚያከብሩ ከንቱ ቃላት ልብህ ከፍ አይበል። ሰይጣን የወደቀው በጥላቻ ሳይሆን በራሱ ኩራት ነውና።" => ቅዱስ ፓይሲዮስ ዘአቶስ፦ “ዮጋ መንፈሳዊ መርዝ ነው... ስፖርት ሳይሆን መንፈሳዊ ክህደት ነው። የሰውን ማንነት የሚያሳብጡ ዘመናዊ ንግግሮችም እንዲሁ አደገኛ ናቸው።” => ቅዱስ ፖርፊሪዮስ፦ “የሰው ቃላት ሰላም ሊሰጡ አይችሉም። ሰላም የሚሰጠው ክርስቶስ ብቻ ነው፤ ቃላቱም መለኮታዊ ስለሆኑ ኃይል አላቸው።”

ሰኔ ፳፬ /24/ በዚች ቀን አባ ሙሴ ጸሊም በሰማዕትነት ሞተ። ሰዎች ከገድሉ የተነሣ ይህን ቅዱስ ያደንቁታል እርሱ አስቀድሞ መንግሥተ ሰማያትን ገፍቷት ነበረና እርሱ በሥጋው ጠንካራ በሥራውም ኃይለኛ
ሰኔ ፳፬ /24/
በዚች ቀን አባ ሙሴ ጸሊም በሰማዕትነት ሞተ። ሰዎች ከገድሉ የተነሣ ይህን ቅዱስ ያደንቁታል እርሱ አስቀድሞ መንግሥተ ሰማያትን ገፍቷት ነበረና እርሱ በሥጋው ጠንካራ በሥራውም ኃይለኛ ነበር ይበላና ይጠጣ ይቀማና ያመነዝር ነበር ይገድልም ነበር። እርሱም ፀሐይን ለሚያመልኩ ሰዎች አገልጋይ ነበረ ብዙ ጊዜም ወደ ፀሐይ እያንጋጠጠ ፀሐይ ሆይ አንተ አምላክ ከሆንክ አነጋግረኝ ይል ነበር ደግሞም በልቡ የማላውቅህ ሆይ ራስህን አሳውቀኝ ይል ነበር። ከዚህም በኋላ በአስቄጥስ ገዳም ያሉ መነኰሳት እግዚአብሔርን ያዩታልም እያሉ ሲነጋገሩ ሰምቶ ወደ አስቄጥስ ገዳም ሔደ። በዚያም አባመቃርስ ተቀብሎ ሃይማኖትን አስተማረውና አጥምቆ አመነኮሰው እንዲህም አለው ታግሠህ የማስተምርህን ከጠበቅህ እግዚአብሔርን ታየዋለህ። ከዚህም በኋላ ብዙ ተጋደለ።በአንዲትም ዕለት አባ ሙሴ ከአረጋውያን ጋራ ወደ አባ መቃርስ ሔደ አባ መቃርስም ከመካከላቸው አንዱ ሰማዕት እንደሚሆን ነገራቸው አባ ሙሴም ምናልባት እኔ እሆናለሁ በሰይፍ የገደለ በሰይፍ ይገደል ዘንድ አለው የሚል ጽሑፍ አለና ብሎ መለሰ። ወዲያውም የበርበር ሰዎች መጡ። ከዚህም በኋላ አባ ሙሴም ከእርሱ ጋራ ያሉትን መነኰሳት ሽሹ አላቸው አንተስ ሲሉት በሰይፍ የገደለ በሰይፍ ይገደላል እነሆ ያቺን ቀን ስጠብቃት ነበር አላቸው። ወዲያውኑም የበርበር ሰዎች ገብተው በሰይፍ ገደሉት መሸሽ ስለ አልፈለጉ ከእርሱ ጋራ ሰባት መነኰሳትም ተገደሉ። ወስብሐት ለእግዚአብሔር ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239

ወጣ ገባ እያሉ የሚያስቸግሩንን መናፍስቶች ለመቆጣጠር ይኼንን እናድርግ!! ውስጣችን ያደፈጠን መንፈስ እንዲጋለጥ ለማድረግ ይኼን አስተውሉ! ብጹዕ አቡነ ጴጥሮስ https://youtu.be/rQYvb_mT0V4

» አባ ጲሜን እንዲህ አለ፦ "በጸሎት ጊዜ ሰይጣን መቶ ኃጢአቶችህን ቢያስታውስህ፣ አንተ ደግሞ ክርስቶስን መቶ አንድ ጊዜ አስበው።" » ቅዱስ ቴዎፋን ገዳማዊው፦ "በጸሎት ጊዜ የሚመጣ ውስዋሴና ፈተና፣ ቅጥሯ እንደገና በሚገነባበት ወቅት ጠላት ከተማን እንደሚያጠቃው ነው። ይህም ነፍስህ እየተጠናከረች መምጣቷን ያሳያል። ጠላት የሚገባው በዝንጋኤ ነው። አእምሮህ ሲባዝን፣ ቀስ ብለህ ሰብስበህ ወደ ጸሎትህ ተመለስ፤ ይህ ራሱ የመንፈሳዊ ጥንካሬ ጅማሬ ነው።" » ቅዱስ ኤቫግሪየስ:- "አእምሮ በተፈጥሮው ወደ እግዚአብሔር ይሳባል፤ አጋንንት ግን ልክ ጣፋጭ መዓዛን እንደሚከቡ ዝንቦች፣ ትዝታዎችንና ውስዋሴዎችን ይጠቀማሉ።" » ታላቁ ቅዱስ እንጦንዮስ፦ "ጸሎት ስትጀምር ለፈተና ተዘጋጅ። ከትህትና ጋር የተባበረ ጸሎት ግን አጋንንትን ያቃጥላል።" » ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፦ "ሰይጣን በጸሎት ሰዓት በአእምሮህ ላይ የተለያዩ ሐሳቦችን ለመዝራት ከጎንህ ይቆማል፤ አንተ ግን በትህትና ከጸናህ አፍሮ ይሸሻል።"

«በትህትናና በፍቅር ስንጸልይ እግዚአብሔር በታላቅ ኃይል ይሠራል፤ አጋንንት እንኳን ይሸሻሉ። ይህም በእኛ ምክንያት ሳይሆን በእኛ ውስጥ ባለው በክርስቶስ ምክንያት ነው።» «When we pray wit
«በትህትናና በፍቅር ስንጸልይ እግዚአብሔር በታላቅ ኃይል ይሠራል፤ አጋንንት እንኳን ይሸሻሉ። ይህም በእኛ ምክንያት ሳይሆን በእኛ ውስጥ ባለው በክርስቶስ ምክንያት ነው።» «When we pray with humility and love, God works with great power; even demons flee. And this is not because of us, but because of Christ who dwells in us.» ቅዱስ ፓይሲዮስ አቶሳዊው

የቅድስት ቤተክርስቲያን ሀዘኗ የሚያበቃው መቼ ይሆን! ጌታ ሆይ እባክህን ይቅር በለን በእውነት! በሮቤ ወረዳ የገደብሳ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ካህን በአሰቃቂ ሁኔታ ተገደሉ፡፡ በምሥ
የቅድስት ቤተክርስቲያን ሀዘኗ የሚያበቃው መቼ ይሆን! ጌታ ሆይ እባክህን ይቅር በለን በእውነት! በሮቤ ወረዳ የገደብሳ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ካህን በአሰቃቂ ሁኔታ ተገደሉ፡፡ በምሥራቅ አርሲ ሮቤ ወረዳ ቤተ ክህነት የገደብሳ ደብረ ሰላም መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን አገልጋይ የሆኑት ካህን ቀሲስ ተስፋዬ ረታ ሰኔ 21 ቀን 2017 ዓ.ም ከምሽቱ 1፡30 አካባቢ በታጣቂ ኃይሎች በአሰቃቂ ሁኔታ መገደላቸው ተገልጿል። ለማኅበረ ቅዱሳን ሚዲያ በደረሰን መረጃ ባለቤታቸው በተመሳሳይ ሁኔታ መገደላቸው የተገለጸ ሲሆን አካባቢው ካህኑ የተወለዱበት እና ከዲቁና ጀምሮ በአሁኑ ወቅትም በቤተ ክርስቲያኑ በቅስና ማእረግ እያገለገሉ ነበር ተብሏል፡፡ የካህኑ የቀብር ሥነ ሥርዓት በትናንትናው ዕለት ሰኔ 22 ቀን 2017 ዓ.ም ከቀኑ 5፡00 ሰዓት በሮቤ ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን መፈጸሙን የደረሰን መረጃ ያመላክታል፡፡ በአሁኑ ሰዓት በወረዳው እየተባባሰ የሚገኘውን አፈና እና ግድያን በመፍራት እና በመስጋት በአካባቢው የሚኖሩ ምእመናን ከተማውን ለቀው እየተሰደዱ መሆኑ ታውቋል፡፡ MKTV እንደዘገበው! ቀሲስ ተስፋዬ ረታ የሰባት ልጆች አባት ሲሆኑ ልጆቻቸውም ምንም አይነት ሥራ መሥራት የማይችሉ እና ሕጻናት በመሆናቸው ለመጠለያ ይሆናቸው ዘንድ የወረዳው አስተዳደር 200 ካሬ ሜትር መስጠቱን የተናገሩት መረጃ ሰጪያችን የሚመለከታቸው አካላት በሙሉ በጋራ ሆነው አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ሲሉ ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡ ጣቢያችን ጉዳዩ ከተከሰተበት ሰዓት አንስቶ ስለጉዳዩ ተጨማሪ መረጃዎችን ለመሰብሰብ የወረዳው የፀጥታ ኃይል ኀላፊን ለማግኘት በተደጋጋሚ በእጅ ስልካቸው ላይ ብንደውልም መልስ ማግኘት ሳንችል ቀርተናል፡፡ ዩትዩብ:- https://www.youtube.com/@haileG2239

በመልአከ መንክራት ግርማ ወንድሙ እና በቀሲስ ሄኖክ ወ/ማርያም! #_በካናዳ_በካልጋሪ_ከተማ! ሸር በማድረግ መልእክቱን አዳርሱ! ተወዳጆች ሆይ በ July 11, 12, እና 13 አርብ ቅዳሜ እና እሑዱ
በመልአከ መንክራት ግርማ ወንድሙ እና በቀሲስ ሄኖክ ወ/ማርያም! #_በካናዳ_በካልጋሪ_ከተማ! ሸር በማድረግ መልእክቱን አዳርሱ! ተወዳጆች ሆይ በ July 11, 12, እና 13 አርብ ቅዳሜ እና እሑዱ በቶሮንቶ ያለኝን ጉባኤ ካበቃሁ በኋላ፤ ለሁለት ሳምንታት July 18, 19, እና 20 አርብ ቅዳሜ እና እሑድ፤ እንዲሁም በሳምንቱ July 25, 26, 27, አርብ ቅዳሜ እና እሑዱ ከመልአከ መንክራት መምህር ግርማ ወንዱሙ ጋር በአንድ ላይ ታላቅ መንፈሳዊ ጉባኤ ይኖረናል። በተለይ ውጭ ሀገር ያላችሁ እሳቸው እና እኔን በአንድ ላይ እንድናገለግላችሁ ጉጉት እና ፍላጎት ያላችሁ ብዙዎች ናችሁ። የእኛም የእናንተም ሐሳብ በእግዚአብሔር ቸርነት፣ በድንግል ማርያም ጸሎት ተሳክቶ፣ በአንድ ላይ ልናገለግላችሁ ዝግጁ ነን። ወለላይቱ እመቤት እቅፍ ድግፍ አድራጋ በሰላም ሁላችንንም በእለተ ቀኑ ታገናኘን! "ሥራቸውም አንድ ስለነበር .. በአንድ ላይ ሠሩ" የሐዋ. ሥራ 18፥3 ሴኔ 23-10-17 ዓ.ም #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@Estifanos2239