HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
前往频道在 Telegram
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239
显示更多2 269
订阅者
+224 小时
+97 天
+2130 天
帖子存档
ፍታችሁንና ጸጉራችሁን በቁስል የሚመታ ውስጣችን ያደፈጠ የአጋንንት ሴራና ተንኮል!! በውቤታችንና በመልካችን የሚቀናው የዓይነጥላ መንፈስ ጉዳቶች!! #ጸሎት https://youtu.be/A3tNcZrc7ls
መጋቢት ፲፬ /14/
በዚችም ቀን ደግሞ ቅዱስ ቶማስ ሐዋርያ ሰባት ዓመት ያህል የጋኔን ግንኙነት በአስቸገራት በአንዲት ሴት ላይ ተአምራትን አደረገ።
ሐዋርያ ቶማስንም በአየችው ጊዜ የክርስቶስ ሐዋርያው ሆይ እጅግ ከሚያሠቃየኝ ጠላት አድነኝ ብላ ወደርሱ ጮኸች እርሱም በምን ምክንያት አገኘሽ አላት እርሷም ከመታጠቢያ ከውሽባ ቤት ስወጣ እንደ ሰው ድው ድው እያደረገ በመታወክ መጣ ድምጡም ሰላላና ቀጪን ነው በሴትና በወንድ ሥራ ሁሉ ነይ እርስበርሳችን አንድ እንሁን አለኝ በተኛሁም ጊዜ በሌሊት መጥቶ ከእኔ ጋራ አንድ ሆነ ብሸሽም አይተወኝም መጥቶ ያሠቃየኛል እንጂ።
እኔም ከጸሎትህ የተነሣ አጋንንት እንደሚንቀጠቀጡ አውቃለሁና ጸልይልኝ አድነኝም አለችው። ሐዋርያ ቶማስም ሰምቶ ጸለየ ጋኔኑንም ከእርሷ እንዲወጣ አዘዘው ያንጊዜም በእሳትና በጢስ አምሳል ከሴቲቱ ላይ ወጥቶ ተበተነ።
ከዚህ በኋላ በክርስቶስ መስቀል በላይዋ አማተበ ሥጋውንና ደሙንም አቀበላት ወደ ዘመዶቿም አሰናበታት። ልዩ የሆነች በረከቱም በሁላችን የክርስቲያን ወገኖች ላይ ትደር ለዘላለሙ አሜን።
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ምንጭ:- መጽሐፈ ስንክሳር
=> በዚህ ኅብስት ውስጥ የተሰወረ ኃይል አለ፤ በዚህ ጽዋ ውስጥ የሚነድ መንፈስ አለ። ኅብስቱን ብሉ፤ እሳቱንም ጠጡ። እሳቱንና መንፈሱን በውስጣችሁ አሳድሩ። እሳቱ የኃጢአታችሁን እሾህ ያቃጥላል፤ መንፈሱ ደግሞ የጠወለገች ነፍሳችሁን ያለመልማል። ሞት የሰውን ልጅ ሊያጠፋ ሲመጣ፣ በደጃፉ (በአፉና በልቡ) ላይ የክርስቶስን ደም ምልክት ካየ ይርቃል፤ ማጥፋትም አይችልም። (ቅዱስ ኤፍሬም ሶሪያዊ)
=> ከዚህ ቅዱስ ማዕድ (ከቁርባን) ተቀብለን ስንወጣ፣ እንደ አንበሳ እሳት እንደሚተነፍሱ ሆነን መውጣት ይገባናል። ሰይጣን እኛን ሲያየን ሊቋቋመን የማይችል እሳት መስለን ልንታየው ይገባል። ምክንያቱም የክርስቶስን ደም የተቀበለች አንደበት እንደ መንፈሳዊ ሰይፍ ስለት አላት፤ ሰይጣንም የንጉሡን ደም በአፋችን ላይ ሲያይ ይርዳል፤ ይሸሻልም። (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)
እባካችሁ ውድ ቤተሰቦቼ እንቁረብ የክርስቶስን ሥጋና ደም እንቀበል። እንቀደስ እንባረክ!
ይኼንን ቪዲዮ አይታችሁ አሳባችሁን አካፍሉን! https://youtu.be/I63SaRgf-S4?si=5yKZ6niXnmS9Ja1p
"ለፕሮተስታንት ወንድሞች የተሳሳተ አመለካከት የተሰጠ መልስ!"
=> የተሳሳተ አመለካከት፦ "ኦርቶዶክሳውያን ለድንግል ማርያም ይሰግዳሉ፣ ይህ ደግሞ አምልኮ ነው፤ አምልኮ ደግሞ ለእግዚአብሔር ብቻ ነው የሚገባው።"
=> ኦርቶዶክሳዊ ምላሽ፦ ኦርቶዶክሳዊት ቤተ ክርስቲያን ለድንግል ማርያም የምትሰጠው ክብር "የጸጋ ስግደት" (Veneration/Hyperdulia) እንጂ "የባሕርይ ስግደት" (Worship/Latria) አይደለም። አምልኮ ለሥላሴ ብቻ ነው። እኛ የምንሰግድላት የእግዚአብሔር እናት ስለሆነችና እግዚአብሔር ስላከበራት ነው።
=> መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃ፦ ራሷ ድንግል ማርያም በመንፈስ ቅዱስ ተሞልታ "እነሆም፥ ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ሁሉ ብፅዕት ይሉኛል" ብላለች (ሉቃስ ፩፥፵፰)። ትውልድ ሁሉ እንዲያከብራት እግዚአብሔር ወዶአል። መላእክትም አክብረዋታል (ሉቃስ ፩፥፳፰)።
=> የተሳሳተ አመለካከት፦ "ማቴዎስ ፩፥፳፭ ላይ 'የበኩር ልጅዋንም እስክትወልድ ድረስ አላወቃትም' ይላል፤ 'እስከ' ካለ ከወለደች በኋላ አውቋታል (ግንኙነት አድርገዋል) ማለት ነው።"
=> ኦርቶዶክሳዊ ምላሽ፦ በመጽሐፍ ቅዱስ "እስከ" የሚለው ቃል ድርጊቱ ከዚያ በኋላ ተፈጽሟል የሚል ትርጉም ሁልጊዜ አይሰጥም።
=> መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃ፦ ፪ኛ ሳሙኤል ፮፥፳፫፦ "የሳኦል ልጅ ሜልኮል እስክትሞት ድረስ ልጅ አልወለደችም" ይላል። ታዲያ ከሞተች በኋላ ወለደች ማለት ነው? አይደለም። ማቴዎስ ፳፰፥፳፦ "እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ እኔ ከእናንተ ጋር ነኝ" ይላል። ታዲያ ዓለም ሲያልፍ ጌታ ይተወናል ማለት ነው? አይደለም። ስለዚህ ዮሴፍ ድንግል ማርያምን "እስክትወልድ አላወቃትም" ማለቱ፣ ጌታ በተአምር መወለዱን ለማረጋገጥ እንጂ ከልደቱ በኋላ ግንኙነት ማድረጋቸውን አይገልጽም።
=> የተሳሳተ አመለካከት፦ "መጽሐፍ ቅዱስ የኢየሱስ ወንድሞች ይላል (ማቴ ፲፫፥፶፭)፤ ስለዚህ ድንግል ማርያም ሌሎች ልጆች ነበሯት።"
=> ኦርቶዶክሳዊ ምላሽ፦ በመጽሐፍ ቅዱስ "ወንድም" የሚለው ቃል ለቅርብ ዘመድ፣ ለወንድም ልጅ ወይም ለክርስቶስ ተከታዮች ይሠራበታል። ጌታችን በመስቀል ላይ ሆኖ እናቱን ለሐዋርያው ዮሐንስ አደራ የሰጠው (ዮሐ ፲፱፥፳፮-፳፯) ሌላ ልጅ ስላልነበራት ነው። ሌላ ልጅ ቢኖራት ኖሮ ለባዕድ ሰው አደራ አይሰጥም ነበር።
=> መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃ፦ አብርሃም ሎጥን "ወንድሜ ነህ" ብሎታል (ዘፍ ፲፫፥፰)፤ ግን ሎጥ የአብርሃም የወንድሙ ልጅ እንጂ የሥጋ ወንድሙ አልነበረም። የጌታ "ወንድሞች" የተባሉት የዮሴፍ ልጆች ወይም የድንግል ማርያም እህት (የማርያም ቀለዮጳ) ልጆች እንደሆኑ ታሪክና መጽሐፍ ቅዱስ ያስረዳሉ።
=> የተሳሳተ አመለካከት፦ "መካከለኛው አንድ ክርስቶስ ብቻ ከሆነ (፩ኛ ጢሞ ፪፥፭) ድንግል ማርያም እንዴት ታማልዳለች?"
=> ኦርቶዶክሳዊ ምላሽ፦ በ"ቤዛዊ መካከለኛ" እና በ"ልመና አማላጅ" መካከል ያለውን ልዩነት መረዳት ያስፈልጋል። ክርስቶስ ቤዛዊ መካከለኛ (Mediator of Redemption) ነው፤ በደሙ የገዛን እርሱ ብቻ ነው። ቅድስት ድንግል ማርያም ግን በጸሎትና በልመና የምታማልድ ባለሟል ናት።
=> መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃ፦ በቃና ዘገሊላ ሰርግ ቤት (ዮሐንስ ፪) ላይ ጌታ ገና "ጊዜዬ አልደረሰም" እያለ በእናቱ አማላጅነት (ልመና) ውኃውን ወደ ወይን ለውጧል። ይህም የእርሷ ልመና በልጇ ዘንድ ምን ያህል ተሰሚነት እንዳለው ያሳያል። ቅዱስ ጳውሎስም "እርስ በርሳችሁ ጸልዩ" (ያዕ ፭፥፲፮) ካለ፣ ከቅዱሳን ሁሉ የምትበልጠው እናቱ መጸለይዋ እንዴት ስህተት ይሆናል?
=> የተሳሳተ አመለካከት፦ "ማርያም ጌታን ለማምጣት እንደ ኤንቨሎፕ ወይም እንደ መኪና (ትራንስፖርት) አገልግላ አልፋለች፤ ስለዚህ አሁን ልዩ ክብር አይገባትም።"
=> ኦርቶዶክሳዊ ምላሽ፦ ይህ አመለካከት የጌታን ሰው መሆን (ምስጢረ ሥጋዌን) መካድ ነው። ጌታ ከሥጋዋ ሥጋን፣ ከነፍሷ ነፍስን ነስቶ ነው ሰው የሆነው። እርሷ የባሕርይ እናቱ ናት እንጂ ተራ መያዣ አይደለችም። መጽሐፍ ቅዱሳዊ ማስረጃ፦ ኤልሳቤጥ በመንፈስ ቅዱስ ተሞልታ "የጌታዬ እናት ወደ እኔ ትመጣ ዘንድ እንዴት ይሆንልኛል?" በማለት ድንግል ማርያምን አክብራታለች (ሉቃስ ፩፥፵፫)። ድንግል ማርያም "ኤንቨሎፕ" ብትሆን ኖሮ "የጌታዬ እናት" አትባልም ነበር።
ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ድንግል ማርያምን የምታከብረው ስለ ራሷ ብላ ሳይሆን ስለ ልጇ ብላ ነው። እርሷን ማክበር ልጇን ማክበር ነው፤ እርሷን መናቅ ደግሞ ጌታ ከሰው የመወለዱን ምስጢር ማቃለል ነው። "የጻድቅ ሰው ጸሎት በሥራዋ እጅግ ኃይል ታደርጋለች" (ያዕቆብ ፭፥፲፮) ከተባለ፣ ከሰው ልጆች ሁሉ በላይ ቅድስት የሆነችው የእግዚአብሔር እናት ጸሎትማ እንዴት ይበልጥ ኃይል አይኖረውም!
ወንድሞቻችን "ክርስቶስ እየሰማ ለምን በቅዱሳን በኩል ትሄዳላችሁ?" ይላሉ።
- ምክንያት ፩፦ እግዚአብሔር ራሱ እንዲህ ስለወደደ። ለምሳሌ አቢሜሌክን ይቅር ማለት ሲችል "ወደ አብርሃም ሂድ እርሱ ይጸልይልሃል" አለው (ዘፍ ፳፥፯)። የኢዮብን ባልንጀሮች "ወደ ባሪያዬ ወደ ኢዮብ ሂዱ... እርሱ ይጸልይላችኋል" አላቸው (ኢዮብ ፵፪፥፰)።
- ምክንያት ፪፦ ትሕትናን ለመለማመድ። እኛ ኃጢአተኞች ስለሆንን "ጌታ ሆይ በንጹሐን ወዳጆችህ ጸሎት ማረኝ" ማለት በአምላክ ፊት መወደድን ያመጣል።
- ምክንያት ፫፦ የቤተ ክርስቲያንን አንድነት ለማሳየት። በሰማይ ያሉትና በምድር ያሉት ቅዱሳን በክርስቶስ ፍቅር አንድ ናቸው።
ማጠቃለያ፦ ክርስቶስ የመዳን መንገድና የሕይወት ባለቤት ነው። ቅዱሳን ደግሞ የዚያ መንገድ ምስክሮችና አብረውን የሚጸልዩ ወንድሞቻችን ናቸው። ክርስቶስን "አማላጅ" ብቻ አድርጎ ማቅረብ አምላክነቱን ዝቅ ማድረግ ሲሆን፤ "ቅዱሳን አያማልዱም" ማለት ደግሞ እግዚአብሔር ለወዳጆቹ የሰጠውን ቃል ኪዳን መካድ ነው። ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ግን ክርስቶስን እንደ ባሕርይ አምላክ ታመልካለች፤ ቅዱሳንን ደግሞ እንደ ባለሟል ታከብራለች።
ከቅርብ ሰው የተላከ የመተት መንፈስ ካለባችሁ ይኼንን ምልክት ታያላችሁ!! መስገድ ስትጀምሩ ጆሯችሁ ይከፈታል ሕሊናችሁ የነቃ ይሆናል!! #መተት #አጋንንት https://youtu.be/YDByEoh-tos
የመምህር ቀጣይ አገልግሎት የፊታችን እሁድ! በተደጋጋሚ ለጠየቃችሁኝ ቤተሰቦቼ ይኼው የመምህር አገልግሎት ሙሉ መረጃና አድራሻው። #ሸር አድርጉ ለሁሉም።
አዲስ ቪዲዮ ይኼው! ይድረስ ለማንያዘዋል ወንድማችን!
https://youtu.be/9XP7Y5qbUbk?si=ZdjxAAFBsVZUWswc
እጸልያለሁ እሰግዳለሁ ነገር ግን መናፍስት አይጋለጡም ምልክት አጣሁ ለምትሉ!! ለጸሎት እንግዳ የሆነው ትውልድና መከራው!! https://youtu.be/43l2mjBtodQ
“ሚስት ለባልዋ፣ ባልም ለሚስቱ ካልተገዙ የዝሙት ጋኔን በቤቱ መካከል ይሰፍራል። መከልከል ክፋትን እንጂ ቅድስናን አያመጣም። ባል ለዝሙት ቢጋለጥ ሚስት በእግዚአብሔር ፊት ተጠያቂ ትሆናለች።” - ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
“ኃጢአትህን ደብቀህ በያዝካት መጠን ሰይጣን በአንተ ላይ ጉልበት ያገኛል። ምስጢርህን ለካህን ስትናገር ግን የጠላት ሰንሰለት ይበጠሳል። የተሰወረ ቁስል አይድንምና ቍስልህን ለሐኪሙ (ለካህኑ) አሳይ።” - ቅዱስ ኒፎን
“ሥጋ እንደ አህያ ነው፤ አብዝተህ ከቀለብከው ይረግጥሃል (በፍትወት ይወጋሃል)። ሥጋህን በጾምና በድካም ካላሳለልከው በፍትወት እሳት ያቃጥልሃል።” - ታላቁ ቅዱስ እንጦንስ
ከቤት ጸልዮ ስግዶ መውጣት ይኼንን ያስቀራልና እባካችሁ ቤተሰቦቼ ተጠንቀቁ!! አውደ ነገሥትና የጥንቆላ መጽሐፍትን የሚያነቡ ግብረ ሰዶማዊያን! ወላጆች እባካችሁን ልጆቻችሁን አደራ ጠብቁ!! https://youtu.be/OWhMV-omWlI?si=h2rsGUQ_VrgJmSnH
የስልጣንና የዝና መተት ትውልዱን ያከሸፈና የገደለ ይኼንን ጉድ ተመልከቱ!! ቤተመቅደስ በጫማ የገባው ካህን አሳዛኝ ተግባርና የእናቶች ለቅሶ! #ስግደት #ጸሎት https://youtu.be/5fbbsCWDfFc?si=CZr5roaZEaJgbqE7
እሸቱ መለሰ የመምህር ግርማን አገልግሎት መቃወም ለምን ፈለገ?? የመምህር ተስፋዬ መልስ ለኮሜዲያን እሸቱ የተሳሳተ ትምህርት!! #ኮሜዲያን #እሸቱመለሰ #ጸሎት https://youtu.be/xteYU05s0Lc
ከድንገተኛ አደጋና ከመናፍስት ፈተና ለመዳን ይኼንን አሁኑኑ አድርጉ!! ሰይጣን እንድወጣላችሁ ብቻ ሳይሆን ይኼንን ለማግኘት ጸልዩ!! https://youtu.be/9Q6tC0WekyQ
Repost from መልአከ ሕይወት ቀሲስ ሄኖክ ተፈራ መንፈሳዊ ቻናል
የተወደዳችሁ የእግዚአብሔር ልጆች የቅዱሳን ወዳጆች ዛሬ መጋቢት 4 አርብ ከምሽቱ 1:00 ሰዓት ጀምሮ በቴሌግራም የቀጥታ ስርጭት አገልግሎት ይካሄዳል።
በመሆኑም ከስር ባለው ሊንክ በመግባት አገልግሎቱን ይካፈሉ።
https://t.me/kesishenokLive
"እመን እንጂ አትፍራ"
† መልአከ ሕይወት ቀሲስ ሄኖክ ተፈራ።
=> በራሳችን ላይ ያለው ጠጉር እንደ ባዘቶ ነጥቷል፣ የሕይወት አዝመራ መሰብሰቢያው ጊዜ ተቃርቧል፣ የሞት ማጭድም በፍጥነት በእኛ ላይ ተስሏል። ነገር ግን በእንቅልፍ እና በእዚህ ዓለም ሕይወት ውስጥ ባለ በከንቱ ዕብሪት ተይዘን፣ አስፈሪው አጫጅ ድንገት መጥቶ ቆርጦ እንዳይጥለን እፈራለሁ። ወጣቱ “እኔ እኮ ገና አላረጀሁም” ይለኛል። እኔም ይህ እመልሳለሁ:- እንዳትሞኝ ተጠንቀቅ። የሞት ቀጠሮ በምታሳልፈው የዕድሜ ርዝማኔ አይቆረጥም። ወይም ደግሞ ኃይላቸው ገና ብርቱ የሆኑትን ጎልማሶች አፍሮ አይተዋቸውም። ሞት የሚበረታው ጉልበታቸው በደከመ በእነዚያ አረጋውያን ላይ ብቻ እንዳይመስልህ ተጠንቀቅ።
ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ
(To those who delay their baptism, 46.)
አልቆርብ ብላችሁ የምታስቸግሩ ሰዎች ይኼንን አሁኑኑ አዳምጡ!! መምህር ግርማ ጠንቋይና ደብተራን እያጋለጡ ጠንቋይ ተብለው የተሰደቡ!! https://youtu.be/I6DMZKJmc2U?si=vVHF_YN3iPJ85yOr
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
