HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
前往频道在 Telegram
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239
显示更多2 277
订阅者
-124 小时
+107 天
+3530 天
帖子存档
«የንጽሕና ምልክቶች»
◈ አባ ጁስቲን "የንጽሕና ምልክቱ፦ ከተደሰቱት ጋር መደሰት፣ ከዛኑት ጋር ማዘን፣ ከታመሙት ጋር መታመም ከኃጥአንም ጋር የኃጢአትን አስጨናቂነት እያሰቡ መጸጸት፤ ከተነሳሕያን ጋር መደሰት፣ መከራ ከሚቀበሉት ጋር አብሮ መሳተፍ፣ ማንንም ሰው አለመንቀፍ እንዲሁም በራስ ንጹሕ አእምሮ ኹሉንም ሰው መልካምና ቅዱስ አድርጎ ማየት ነው።" ይላሉ። Fr Justin Popovich, Faith and Life in Christ። እኝህ አባት የገለጹትን ሐሳብ ጠቅለል አድርገን ስንመለከተው የንጽሕና ምልክቱ አፍቅሮተ ሰብእ መኾኑን የሚያስረዳ ነው። ከላይ የተዘረዘሩትን ኹሉ ልናደርግ የምንችለው እውነተኛ ፍቅር ሲኖረን ነው። ስለ ሰዎች ያለን አስተሳሰብ ቤተ ክርስቲያናዊ ካልኾነ በቀር በእውነት ሰዎችን ከመውደድ ይልቅ ክፉ ክፉ የምንለውን ነገር ብቻ እየመረጥን እጅጉን ልንጠላቸው እንችላለን። በጥላቻው ውስጥ ከኾን ደግሞ የልቡና ንጽሕናችንን አጥተናል ማለት ነው። የልብ ንጽሕና ኹል ጊዜም ቢኾን ከፍቅር ጋር የተያያዘ ነውና። የእውነት ሰዎችን ስናፈቅር እግዚአብሔርን መውደዳችን በዚያ ይታወቃል። ኹል ጊዜም ቢኾን ወደ ጥላቻ የሚወስዱንን ነገሮች ትተን ወደ ፍቅር የሚወስዱንን ነገሮች ብንመርጥ ጥቅሙ ለእኛው ነው።
◈ ወዳጆች ሆይ! ንጹሕ ሐሳብን ገንዘብ ማድረግ የምትሻ ከኾነ ማንንም ቢኾን ካንተ የተሻለ መልካም በጎ እንደ ኾነ አድርገህ መቀበል ይገባሃል። ሌሎችን ካንተ እንደሚሻሉ አድርገህ ስታምን፡ ኹል ጊዜ ራስህን የእውነት ዝቅ ማድረግ ትጀምራለህ፥ ማስመሰል ያይደለ እውነተኛ ትሕትናን በሕይወትህ እየተለማመድካት ትኖራለህ። ትሕትና ደግሞ ንጹሕ ሕሊናን ይፈጥርልሃል። ስለዚህ በንግግር ብቻ ሳይኾን በእውነት ኹል ጊዜም "እኔን ኃጢአተኛውን ማረኝ" እያልክ ደረትህን እየደቃህ ከልብህ ስለ ራስህ ኃጢአት የምታለቅስ ትኾናለህ። በማንም ሰው ላይ የበላይነት ስሜት አይሰማህም፤ በዚህም ምክንያት ካልተገቡ ትችቶችና ነቀፋዎች ኹሉ ትርቃለህ። ነፍስህ በንጽሕና እየተመላች ስትሄድ ኹሉንም መልካምና ቅዱስ አድርገህ ማሰብ ትጀምራለህ። ወዳንተ የሚመጣውን ኹሉ በፍቅርና በአክብሮት ተቀብለህ በፍቅር ታስተናግዳለህ። ይቅር ባይነት የሕይወትህ መርሕ ይኾናል። የሚበድሉህን እንኳን ጌታን መስለህ በመከራ ውስጥም ኾነህ ይቅር ትላቸዋለህ። ስለ ሌሎች ክፉ እንዲወራና እንዲነገር የማትወድ፣ ስድብና ጥላቻ የማይስማሙ፣ ሐሜትን የምትጸየፍ፣ ሌሎችን ማስነወር የማትፈቅድ ትኾናለህ። የአንተ ዓላማ ኹል ጊዜ ክርስቲያን ኾኖ፣ ክርስቶስንም መስሎ መኖርን ማዕከል ያደረገ ይኾናልና።
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
«መዳን የምንችለው እንዴት ነው?»
"በኦርቶዶክሳዊነት መጽናት፣ እርስ በእርሳችን የአረዳድ አንድነታችንን ስንጠብቅ፣ ግብዘነት የሌለው ፍቅር ሲኖረን፣ የነፍስንና የሥጋን ንጽሕና ስንጠብቅ፣ ክፉና ንጹሕ ያልኾኑ ሐሳቦችን ስናስወግድ፣ በትንሹ ስንበላና ስንጠጣ፣ ከኹሉ በላይ ራሳችንን በትሕትና ስናስጌጥ፣ እንግዳ መቀበልን ቸል ካላልን፣ ከግጭት ስንርቅ፣ በምድራዊ ሕይወት ለማንኛውም ነገር ክብርንና ከፍታን ካልሰጠን ነገር ግን በምትኩ ከእግዚአብሔር ዘንድ ሽልማትንና የሰማያዊ መልካም ነገሮች ደስታን እናገኛለን።" እንዲል። (St. Sergius of Radonezh, Life, 32)
ቴኦፋን "ድኅነትን ማግኘት ከፈለክ፤ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የምታስተምረውን በሙሉ ተማር፣ በልቡናህም ጠብቀው፤ ከቤተ ክርስቲያን ምሥጢራትም ሰማያዊውን ኃይል ተቀበል፤ ክርስቶስ ባዘዘው የትእዛዝ መንገድ ሂድ፣ ይህን ካደረግህ ያለ ጥርጥር ሰማያዊቷን መግሥትም ታገኛለህ ትድንማለህ። ... ማንም ሰው ከዚህ መንገድ ያጎደለ ቢኖር አይድንም።" ይላል።
(St. Theophan the Recluse, Five Teachings on the Path to Salvation, 3)
አባ እንጦንስ አንድ መነኩሴ ለመዳን ግድ ምን ላድርግ? አላቸው። አባ እንጦንስም፦ በራስህ ጽድቅ አትመካ፣ ስላለፈውም አትጨነቅ፣ ምላስህንና ሆድህን ግታ" አለው። (Ancient Patericon, 1.2)። አንድ ወንድም አባ መቃርዮስን 'እንዴት ነው መዳን የምችለው? አላቸው። አባ መቃርስም "እንደ ሞተ ሰው ኹን፤ ከሰዎች የሚመጣብህን ስድብም ኾነ ክብርን አታስብ፣ እንዲህ ካደረግህ ትድናለህ" አሉት። (Ancient Patericon, 10.45)።
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
ግማሽ ሰው ግማሽ ሰይጣን ሆነው የሚኖሩ ተደጋጋሚ ኃጢአትን እንዴት እናቁም መንፈሳዊ ተጋድሎ || የዝሙት ኃጢአት እና ፈተናው በማለዳ ንቁ 2024
https://youtu.be/SI7JcNeCNkE
የማህጸን መተትና ከባዱ ፈተና የመናፍቁ አሳሳቹ መንፈስና ሀሰተኛው ኢየሱስ አፋዊ ሳይሆን የልብ ትሕትና ያስፈልገናል | በልክና በመጠን የመኖር ጥበብ
https://youtu.be/KBCAmdTYgjY
«ኦርቶዶክሳዊ ኑሮ»
◈ ሁል ጊዜም በተወሰነ ሰዓት የመንቃት ልምድ ይኑርህ። ምክንያተኝነትን ከአንተ አስወግድ። ከሰባት ሰዓት በላይ የእንቅልፍ ጊዜ አይኑርህ። ከእንቅልፍህም በነቃህ ጊዜ የተሰቀለውን ጌታችንን በመስቀል ላይ እንዳለ አድርገህ አስብ። ራስህን በብርድልስ ሙቀት አታታል። ከመኝታህ አፈፍ ብለህ ተነሣ። ለጸሎት ስትዘጋጅ ወገብህ የታጠቀ መብራትህ የበራ ይኹን። የጸሎት ልብስህን ልበስ። ይህ ጊዜ የዝግጅት ጊዜ ነው። በሠራዊት ጌታ በልዑል እግዚአብሔር ፊት ልትቆም መኾንህን አስብ። ሁል ጊዜም አእምሮህ የአባትህን የአዳምን የእናትህን የሔዋንን ውድቀት ያስታውስ። አምላክህን የሚያስብ በጎ ሕሊና እንዲኖርህ አባትህ አዳም ተጠልፎ በወደቀበት የሥጋ ሐሳብ፣ የሥጋ ኃጢአት ተጠልፈህ እንዳትወድቅ ፈጣሪህን ለምነው። በፊቱ የምትቆምበትን ጸጋ ብርታት እንዲሰጥህ ለምነው።
◈... በሕመምህ ጊዜ መጀመሪያ በእግዚአብሔር ታመን፥ አዘውትረህ የጌታ ሥቃይ ይታሰብህ። ሥቃይህንና ሕመምህን ያሥታግስልህ ዘንድ የምታውቀውን ጸሎት ያለማቋረጥ ጸልይ። በሕይወት ዘመንህ ሰላማዊና የተረጋጋ ሕይወት እንዲኖርህ ከፈለግህ ሕይወትህን ሊታመን ለሚችለውና አደራውን ለመጠበቅ ለሚቻለው ለእግዚአብሔር አስረክብ። ራስህን ለእግዚአብሔር አሳልፈህ መስጠት ካልቻልክ ፍጹም የኾነ መረጋጋትን አገኛለሁ ብለህ እንዳታስብ። ፍቅር የሚገባውን አምላክህን ውደደውና በፍቅር ኑር። (ታደለ ፈንታው (ዲ/ን)፣ መክሊት፣ 2004 ዓ.ም፣ ገጽ 90-99)።
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
እናት ልጇን እንድትጠላ፣ ልጅ እናቱን እንዲጠላ የሚያደርግ ዓይነጥላ || የምስጥር መተትና ምልክቶቹ | በሕልም ጸጉር ሲቆረጥብን ማየት | በማለዳ ንቁ 2024
https://youtu.be/ve9LPvcOCMI
እናት ልጇን እንድትጠላ፣ ልጅ እናቱን እንዲጠላ የሚያደርግ ዓይነጥላ || የምስጥር መተትና ምልክቶቹ | በሕልም ጸጉር ሲቆረጥብን ማየት | በማለዳ ንቁ 2024
https://youtu.be/ve9LPvcOCMI
«መጸጸት ራስን መመርመር»
◈ ራስህን በምትመረምርበት ጊዜ ኃጢአትህንና ድክመቶችህን ለእግዚአብሔር ትገልጥላቸዋለህ፤ ድክመቶችህን የምትገልጣቸው ከእሱ ኃይል ለማግኘት ነው፤ በኃጢአትህ የምትጸጸተው ደግሞ ከእግዚአብሔር ይቅርታን ለማግኘት ነው፤ ነብዩ ዳዊት እንዳለው በተሰበረ ልብ ሆነህ ስትጸልይ ኃጢአትህንና ድካምህን ገስጸቸው። "በሂሶጵ እርጨኝ እነጻማለሁ እጠበኝ ከበረዶም ይልቅ ነጭ እሆናለሁ" መዝ 51፥7
◈ ከዚህ በኋላ ራስህን ከዚህ ሁኔታ ታወጣና ወደ ንስሐ አባትህ ሄደህ ንስሐ ትገባለህ፤ ካህኑም የንስሐ ጸሎት ይደግሙልሃል፤ ሥጋ ወደሙን እንድትቀበል ይፈቅድልሃል።
◈ በዚህ ጊዜ ሆነህ ከራስህ ጋር ስትወያይ ኃጢአትን መተው እንዳለብህ ከውስጥህ ተቀብለህ ደስ ብሎህ ትወስናለህ፤ ወድ ኋላ ተመልሰህ ስህተቶችህን ለማየት ራስህን መከልከል የለብህም፤ እንዲሁም ራስህን ለመውቀስና ላለመግሰጽ ብዙ ምክንያቶች በመደርደር አትከላክል፤ በዚህ ጊዜ ወደፊትም ከኃጢአት መራቅ እንዳለብህ ዕቅድ ማውጣት አለብህ፤ ለውሳኔህ ታማኝ ሁነህ ለመቀጠልም ቃል ግባ፤ ለወደፊት በንጽህና ለመኖር ስትወስን ዝርዝር ውስጥ ገብተህ መዋኘት የለብህም፤ ድክመቶችህ ለማስወገድ ቅድሚያ ስጥ።
◈ እግዚአብሔር እንዲባርክህ እና ብርታቱ እንዲሰጥህ የተቀደሰ ውሳኔህን ለእግዚአብሔር ንገረው፤ የምመክርህ ይህ ዕቅድ መሃላ አይደለም፤ ብዙ ሰዎች በእግዚአብሔር ፊት ቃል ገብተው ነገር ግን መፈጸም አልቻሉም፤ ቃላቸውን ባለመፈጸማቸው ቃልብባልገባ ኖሮ እመኝ ነበር ብለው ይጸጸታሉ፤ ሁሉም ነገር መንፈሳዊ ከመሆን መፈለግ አይበልጥም፤ አንተ ፍላጎትህ ትገልጻለህ ብሎም ትወስናለና፤ እግዚአብሔር ደግሞ እንድትፈጽመው ኃይል ይሰጥሃል፤ ያለ እግዚአብሔር ከቶውንም ምንም ማድረግ አትችልም። "ያለ እኔ ምንም ልታደርጉ አትችሉምና በእኔ የሚኖር እኔም በእርሱ፣ እርሱ ብዙ ፍሬ ያፈራልና" ዮሐ15፥5
◈ እግዚአብሔር ኃይል ሰጥቶህ በንስሐ እና በንጹህ ልብ እንድትኖር በጸሎት መለመን ያስፈልጋል። በዚህ ራስህ ጋር በምትመክርበት ጊዜ ሰይጣን ሁሉንም ኃይሉ ተጠቅሞ ይቃወምሃል፤ ለዚህም ሁለት ምክንያቶች አሉት፦
፩. ራስህን በመረመርክ ጊዜ ድክመቶችህን አውቀህ እንደምትጸጸትና ከእርሱ እጅ እንደምታመልጥ ስለሚያቅ ይፈራል።
፪. እግዚአብሔር ከአንተ ጋር እንደሚሆን መንፈሳዊ ኃይልም እንደምታገኝና ድል እንደምታደርገው ስለሚያውቅ ይፈራል፤ ስለሆነም ሰይጣን ሰዎች ራሳቸውን እንዳያዩ ሁለት መንገዶችን በመጠቀም ይሰራል።
1ኛ. ራሳችንን ለማየት እንዳንቀመጥ የሚያደርግበት መንገድ በግድ ወይን በቤተሰብ ጉዳዮች እንድንጠመድ በማድረግ ነው፤ እነዚህ ወደራስህ እንዳትመለስ ያደርጉሃል በበዓል፣ ልደት ቀን፣ ወዘተ....
2ኛ. ራሳችን ለመመርመር ጊዜ ከሰጠን በኋላ ራሳችንን ለመመርመር ጊዜ መስጠታችን ጥቅም እንዳይኖረው በማድረግ ነው፤ ራሳችንን እየወቅስን እንዳንጸጸት የተለያዩ ትዝታዎችና ስሜቶች ውስጥ ሆነን እንድናሳልፍ ያደርገናል፤ እንዳናዝንና እንዳንጸጸት ኃጢአቱ ለምን እንደሰራነው በቂ የሚመስሉ ምክንያቶችን እንድንደረድር ያደርገናል። ራሱን በግልጽ የሚመረምር ሰው ደስተኛ ነው፤ ኃጢአቱብ በጌታ ፊት የሚናዘዝ እና የሚያለቅስ ሰው ደስተኛ ነው፤ ራስን መውቀስ ወደ መጸጸትና ወደ ትህትና ሕይወት ይመራል። ስለዚህ እንደ አባ እንጦንስ አባባል "እኛ ኃጢአታችን ስናስታውስ እግዚአብሔር ይረሰዋል፤ እኛ ኃጢአታችን ስንረሳ እግዚአብሔር ያስታውሰዋልና"
◈ ንጉስ ዳዊት ኃጢአቱ በዘነጋ ጊዜ በናታን እንደተነገረው አንተ ሌላ ናታን እስኪ መጣ መጠበቅ የለብህም፤ ከራስህ ጋር ተቀምጠህ መወያየት ይኖርብሃል፤ ያኔ ለይቅርታ ብቁ ትሆናለህ።
✍️"የሚሰማኝ ግን በእርጋታ ይቀመጣል ከመከራም ሥጋት ያርፋል" (ምሳ 1፥33)
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
ለመዳንና ለመፈወስ የትኛውን ጸሎት ልጸልይ? || ለመዋቢያና ጸጉር ለመሰራት ጊዜ አለን || የእምነይ ኃይል ከሕይወታችን ሲጠፋ || በማለዳ ንቁ 2024 😭🙄🙏🙄 https://youtu.be/qrBRnMuD8gs
«ከግልሙትና መውጣት ይቻላል»
◈ አባ ሰራፕዮን በአንድ የግብፃውያን መንደር መካከል ሲያልፍ አንዲት ጋለሞታ አየ። እርሱም "በዚህ ምሽት ጠብቂኝ፣ ሌሊቱን ካንቺ ጋር አሳልፋለሁ" ብሏት ሄደ። ጋለሞታዋም ራሷንም አልጋዋንም አዘጋጀች። ሲመሽ አባ ሰራፕዮን መጣና "አልጋውን አዘጋጀሽውን?" ሲል ጠየቃት። "አዎ አባ" ስትል መለሰች። በሩን ግጥም አድርጎ ከዘጋው በኋላ "ጥቂት ጠብቂኝ፣ በሕጋችን መሠረት ቀድመን መጸለይ አለብንና፣ መጀመሪያ ያንን ልፈጽም" አላት። ከዚያም ዳዊት መድገም ጀመረ። ከእያንዳንዱ መዝሙር በኋላ ለዚያች ሴት ይጸልይላት ነበር። ይህን ከመሰለው ሕይወት አውጥቶ እግዚአብሔር ነፍሷን ያድን ዘንድ አጥብቆ ለመነው። እግዚአብሔርም ሰማው። ያቺ ሴት እየተንቀጠቀጠች ከአባ ሰራፕዮን አጠገብ ቆመችና መጸለይ ጀመረች። መዝሙረ ዳዊትን ሲጨርስ ያቺ ሴት መሬት ላይ በግንባሯ ተደፋች። ከዚህ በኋላ ደግሞ የሐዋርያው የቅዱስ ጳውሎስን መልእክታት ማንበብ ቀጠለ።
◈ ጸሎቱን ሲፈጽም ያቺ ሴት ልቡናዋ በፀፀት ተመልቶ ይህ ታላቅ ሰው ወደ ርሷ የመጣው ነፍሷን ለማዳን እንጂ ኃጢአት ለመሥራት አለመኾኑን ተረዳች። ከዚያም እግሩ ሥር ተደፍታ "አባ እባክህን እግዚአብሔርን ላስደስተው ወደምችልበት ቦታ ውሰደኝ" አለችው። እርሱም ወደ ሴቶች ገዳም ወሰዳትና ለእመ ምኔቷ "ይህቺን እኅት ተቀበዪኝ፣ ነገር ግን ምንም ዓይነት ቀንበር አትጫኚባት። የፈለገችውንም ስጫት፣ እንደምትፈልገውም ትጓዝም ዘንድ ተያት" አላት። ከጥቂት ቀናት በኋላ ያቺ ሴት "እኔ በደለኛ ነኝና በየኹለት ቀኑ ነው መመገብ የምፈልገው" አለች። ከጥቂት ቀናት በኋላ ደግሞ "እኔ ብዙ ኃጢአት ሠርቻለሁና በየአራት ቀኑ ነው የምመገበው" አለች። በዚህ ኹኔታ ጥቂት እንደ ቆየች ደግሞ ወደ እመ ምኔቷ ሄዳ በኃጢአቴ ጌታን አሳዝኜዋለሁና እኔን ለብቻዬን በበኣት አስቀምጠሽ ዝጊብኝ፣ ጥቂት ዳቦና የምሠራውን ሥራ በመስኮት በኲል ስጪኝ አለቻት። እመ ምኔቷም እንዳለችው አደረገችላት። ያቺም ሴት እስከ ዕለተ ዕረፍቷ ዝጉሐዊት ባሕታዊት ኾና ኖረች።" እንዲል። (ዳንኤል ክብረት (ዲ/ን፣ አርተር)፣ በበረሓው ጉያ ውስጥ፣ 2004 ዓ.ም፣ ገጽ 75-76)።
◈ ከማንኛውም ክፉ ልማድ ከኾነብን ኃጢአት ለመውጣት የቅዱሳንን ጸሎት ከልባችን ኾነን ሳናቋርጥ እንጠይቅ። እግዚአብሔር ስለ ወዳጆቹ ጸሎት ብሎ ከተላመድነው ክፉ የሕይወት መርሕ ያስወጣናልና። ይህ ኹል ጊዜ በአንዴ ብቻ የሚኾን አለመኾኑንም ልብ በሉ። አንዳንዴ የብዙ ጊዜ ያልተቋረጠ ትጋታችንን ሊፈልግ ይችላል፣ አንዳንዴ ወዲያውኑ ልቡናችን ሊከፈት ይችላል። የልቡናችንን ቅንነት ሲያይ እግዚአብሔር መልአኩን ወደ ቤታችን በሰው አምሳልም ቢኾን ልኮ ከየተያዝንበት ክፉ ወጥመድ ሊያስወጣን ይችላል። እግዚአብሔር በአንዳች መንገድ ውስጣችንን እንዲነካው ተስፋ ሳንቈርጥ ልንጸልይ ይገባል። ከልብ በልቅሶ የኾነ ጸሎት የለመድነውን ክፋት ማስወገድ ይችላልና።
◈ በታሪኩ ላይ እንደተመለከትነው ልክ እንደ አባ ሰራፕዮን ለብዙዎቻችን የሚጸልዩ ቅዱሳን መኖራቸውን በማሰብ ልንጽናና ይገባናል። በምንም ዓይነት የኃጢአት ሕይወት ውስጥ ያለን ብንኾንም ልባችንን መለስ ካደረግን እግዚአብሔር ሊቀበለን ፈቃደኛ እንደ ኾነ ልብ ማለት ይገባል። በግልሙትና ውስጥ የነበረችው ሴት የቀደመ ነገሯን ትታ እግዚአብሔርን ማግኘት ወዲያውኑ መፈለጓን እናስተውል። ወንድም እኅቶቼ ሆይ! በእርግጥ እኛ ብዙ ዕድሎች እንዳሉንና በአግባቡ እንዳልተጠቀምንባቸው አስተውሉ! ነቅተንና ተግተን በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ጸሎት ብንሳተፍ የእውነት መለወጥ እንችላለን። በየዕለቱ የሚነበብልንን የቅዱሳንን ተጋድሎና ሕይወት የያዘውን ስንክሳር ከልብ ብንሰማ ተጣብቀን የተያዝንበት ኃጢአት ምን ያህል መርዝ እንደ ኾነ ልብ እንላለን።
◈ እግዚአብሔር በተለያየ መንገድ የሚያሰማንን ድምፁን እንስማው ከውስጣችንም ለመለወጥ እናስብ። ጥሩ ክርስቲያን መኾን የማይቻል እንደ ኾነ አድርገንም አጽር ቅጽር አንሥራ፤ ይልቅስ "ኃይልን በሚሰጠን በክርስቶስ ኹሉን እንችላለን" እያልን በመንፈሳዊ ኃይል እንመላ። በየደቂቃውና በየሰዓቱ ኹሌም "እኔን ኃጢአተኛውን ማረኝ" እያልን በልቡናችን ውስጥ ያልተቋረጠ ጸሎት እንጸልይ። እግዚአብሔር ከክፉ መንገዶቻችን ይመልሰን። በርቱ!
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
"ተስፋ መቁረጥና ስንፍና"
◈ ተስፋ መቁረጥና ስንፍና እጅግ ክፉዎች ናቸውና ከእነዚህ እንራቅ “ክፋታቸውስ እንደምን ያለ ነው?” ያልከኝ እንደ ኾነም እንዲህ ብዬ እመልስልሃለሁ፤ ተስፋ መቁረጥ የወደቀው ሰው እንደ ገና እንዲነሣ አይፈቅድለትም፤ ስንፍናም የቆመው ሰው እንዲወድቅ ያደርጓል፤ ስንፍና ገንዘብ ያደረግናቸውን መልካም ነገሮች ከማሳጣቱም በላይ ሊመጡ ካሉ ክፉ ነገሮች እንዳንጠበቅ ያደርገናል፤ ስንፍና ከሰማያትም ቢኾን ይጥለናል፤ ቀቢጸ ተስፋም ወደ ክፋት ዐዘቅት እንድንሰጥም ያደርገናል፤ በእውነት በቀቢጸ ተስፋ ካልተያዝን ከጽኑ ክፋት መመለስ ይቻለናል፡፡
◈ እነዚህ ኹለቱ ምን ያህል ኃይል እንዳላቸው ይበልጥ ታውቅ ትረዳ ዘንድ ምሳሌ ጠቅሼ ልንገርህን? መልካም! ዲያብሎስ መጀመሪያ ላይ መልካም ነበር፤ ከስንፍናና ከቀቢጸ ተስፋ የተነሣ ግን እንደ ገና የማይነሣ ኾኖ ወደ ክፋት ወደቀ፤ ዲያብሎስ ጥንቱ መልካም እንደ ነበረ ሲናገር መጽሐፍ ቅዱስ እንዲህ ያለውን አድምጥ
✍️“ሰይጣን እንደ መብረቅ ከሰማይ ሲወድቅ አየሁ” ሉቃ 10፥18
◈ መብረቅ የሚለው አገላለጽ ዲያብሎስ ከመውደቁ በፊት ምን ያህል ብሩህ ሕይወት እንደ ነበረውና በምን ያህል ቅጽበት እንደ ወደቀ የሚያመለክት ነው፡፡
◈ ቅዱስ ጳውሎስ ደግሞ ተሳዳቢ፣ አሳዳጅና ነውርን የማያውቅ ሰው ነበር፤ ነገር ግን ቀናተኛ ስለ ነበርና ተስፋ ስላልቆረጠ ተነሥቶ መላእክትን የሚተካከል ኾነ፤ ይሁዳ ሐዋርያ ነበር፤ ነገር ግን በስንፍና ምክንያት ጌታውን አሳልፎ ሰጠ፤ ፈያታዊ ዘየማን ደግሞ እንደዚያ እጅግ ክፉ የነበረ ሰው ቢኾንም ቅሉ ተስፋ ስላልቆረጠ ኹሉንም ቀድሞ ገነት ገባ፤ ፈሪሳዊው ሰው ራሱን ከፍ ከፍ ያደርግ ስለ ነበር ከምግባር ማማ ላይ ወደቀ፤ ቀራጩ ግን ተስፋ ስላልቈረጠ ከፈሪሳዊውም በልጦ ወደ ምግባር ሰገነት ወጣ፤ ስለዚህ ይህን ዐውቀን ዘወትር ከስንፍናና ተስፋ ከመቁረጥ እንራቅ!
🙏 ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
ካልተሾምሁ ሲኖዶስ እከፍላለሁ የምትሉ የእኛዎቹ ሰምታችኋል! ፕትርክናን እምቢኝ አሉ 🥰🥰🥰
ዘንድሮ ከምስራቅ ኦርቶዶክስ አብያተክርስቲያናት አባቶች እየተሰማ ያለው ዜና በአግራሞት አፋችንን እያስከፈተ መቀጠሉን ቀጥሏል። ብጹዕ አቡነ ኒኮሎዝ ይባላሉ የፕሎፕዲቭ ሊቀ ጳጳስ ናቸው።
ሊቀ ጳጳሱ የቡልጋሪያ ኦርቶዶክስ የፓትሪያሪክ ዕረፍትን ተከትሎ ለቀጣይ ፓትሪያሊክነት በእጩነት ቢቀርቡም እርሳቸው ግን #እምቢኝ ብለዋል።
ከፕትርክናው እጩነትም ራሳቸውን አግልለዋል!!!
የእኛዎቹስ 😭😭😭
ጸሎትና ስግደትን ለአምልኮት ጊዜ መስጠትን እምቢ ያልነው እኛው እራሳችን ነን || ቸልተኝነት በአኗኗራችን ውስጥ | መምህር ኢዮብ ይመኑ | ግርማ ወንድሙ 😭😰🙄
https://youtu.be/2vtp5Oc-mH4
ሰይጣን መንፈሳዊነታችንን ሲለማመድና አብሮን ሲጠመቅ || የአረማዊ ደብተራዎችን ጉድ ተመልከቱ | መምህር ተስፋዬ ያጋለጠው መረጃ በማለዳ ንቁ 2024 😭😰🙄😭
https://youtu.be/chydElAz248
በአንተ ከጥፋት እድናለሁና በአምላኬም ቅጥሩን እዘልላለሁ። የአምላኬ መንገድ ፍጹም ነው፥ የእግዚአብሔር ቃል የነጠረ ነው፥ በእርሱ ለሚታመኑት ሁሉ ጋሻ ነው። ከእግዚአብሔር በቀር አምላክ ማን ነው? ከአምላካችን በቀር አምላክ ማን ነው? ኃይልን የሚያስታጥቀኝ መንገዴንም የሚያቃና። (መዝሙረ ዳዊት 18:29, 30, 32)
አምላኬ፥ ከታናሽነቴ ጀምረህ አስተማርኸኝ፤ እስከ ዛሬም ተአምራትህን እነግራለሁ። እስካረጅም እስክሸመግልም ድረስ፥ ለሚመጣ ትውልድም ሁሉ ክንድህን ኃይልህንም ጽድቅህንም እስክነግር ድረስ፥ አቤቱ፥ አትተወኝ። (መዝሙረ ዳዊት 71:17, 18)
አቤቱ፥ እርዳታው ከአንተ ዘንድ የሆነለት፥ በልቡም የላይኛውን መንገድ የሚያስብ ሰው ምስጉን ነው። በልቅሶ ሸለቆ ውስጥ በወሰነው ስፍራ የሕግ መምህር በረከትን ይሰጣልና። ከኃይል ወደ ኃይል ይሄዳሉ፤ የአማልክት አምላክ በጽዮን ይታያል። (መዝሙረ ዳዊት 84:5, 7)
በመከራ መካከል እንኳ ብሄድ፥ አንተ ሕያው ታደርገኛለህ፤ በጠላቶቼ ቍጣ ላይ እጆቼን ትዘረጋለህ፥ ቀኝህም ታድነኛለች። (መዝሙረ ዳዊት 138:7)
እምነታችሁም በእግዚአብሔር ኃይል እንጂ በሰው ጥበብ እንዳይሆን፥ ቃሌም ስብከቴም መንፈስንና ኃይልን በመግለጥ ነበረ እንጂ፥ በሚያባብል በጥበብ ቃል አልነበረም። (1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 2:4, 5)
ንቁ፥ በሃይማኖት ቁሙ፥ ጎልምሱ ጠንክሩ። (1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 16:13)
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
(የዮሐንስ ወንጌል 15፡1-27)
እውነተኛ የወይን ግንድ እኔ ነኝ፤ ገበሬውም አባቴ ነው። ፍሬ የማያፈራውን በእኔ ያለውን ቅርንጫፍ ሁሉ ያስወግደዋል፤ ፍሬ የሚያፈራውንም ሁሉ አብዝቶ እንዲያፈራ ያጠራዋል። እናንተ ስለ ነገርኋችሁ ቃል አሁን ንጹሐን ናችሁ፤ በእኔ ኑሩ እኔም በእናንተ። ቅርንጫፍ በወይኑ ግንድ ባይኖር ከራሱ ፍሬ ሊያፈራ እንዳይቻለው፥ እንዲሁ እናንተ ደግሞ በእኔ ባትኖሩ አትችሉም። እኔ የወይን ግንድ ነኝ እናንተም ቅርንጫፎች ናችሁ። ያለ እኔ ምንም ልታደርጉ አትችሉምና በእኔ የሚኖር እኔም በእርሱ፥ እርሱ ብዙ ፍሬ ያፈራል። በእኔ የማይኖር ቢሆን እንደ ቅርንጫፍ ወደ ውጭ ይጣላል ይደርቅማል፤ እነርሱንም ሰብስበው ወደ እሳት ይጥሉአቸዋል፥ ያቃጥሉአቸውማል። በእኔ ብትኖሩ ቃሎቼም በእናንተ ቢኖሩ የምትወዱትን ሁሉ ለምኑ ይሆንላችሁማል። ብዙ ፍሬ ብታፈሩና ደቀ መዛሙርቴ ብትሆኑ በዚህ አባቴ ይከበራል። አብ እንደ ወደደኝ እኔ ደግሞ ወደድኋችሁ፤ በፍቅሬ ኑሩ። እኔ የአባቴን ትእዛዝ እንደ ጠበቅሁ በፍቅሩም እንደምኖር፥ ትእዛዜን ብትጠብቁ በፍቅሬ ትኖራላችሁ። ደስታዬም በእናንተ እንዲሆን ደስታችሁም እንዲፈጸም ይህን ነግሬአችኋለሁ።
እኔ እንደ ወደድኋችሁ እርስ በርሳችሁ ትዋደዱ ዘንድ ትእዛዜ ይህች ናት። ነፍሱን ስለ ወዳጆቹ ከመስጠት ይልቅ ከዚህ የሚበልጥ ፍቅር ለማንም የለውም። እኔ ያዘዝኋችሁን ሁሉ ብታደርጉ እናንተ ወዳጆቼ ናችሁ። ከእንግዲህ ወዲህ ባሮች አልላችሁም፤ ባርያ ጌታው የሚያደርገውን አያውቅምና፤ ወዳጆች ግን ብያችኋለሁ፥ ከአባቴ የሰማሁትን ሁሉ ለእናንተ አስታውቄአችኋለሁና። እኔ መረጥኋችሁ እንጂ እናንተ አልመረጣችሁኝም፤ አብም በስሜ የምትለምኑትን ሁሉ እንዲሰጣችሁ፥ ልትሄዱና ፍሬ ልታፈሩ ፍሬአችሁም ሊኖር ሾምኋችሁ። እርስ በርሳችሁ እንድትዋደዱ ይህን አዛችኋለሁ። ዓለም ቢጠላችሁ ከእናንተ በፊት እኔን እንደ ጠላኝ እወቁ። ከዓለምስ ብትሆኑ ዓለም የራሱ የሆነውን ይወድ ነበር፤ ነገር ግን እኔ ከዓለም መረጥኋችሁ እንጂ ከዓለም ስለ አይደላችሁ ስለዚህ ዓለም ይጠላችኋል። ባርያ ከጌታው አይበልጥም ብዬ የነገርኋችሁን ቃል አስቡ። እኔን አሳደውኝ እንደ ሆኑ እናንተን ደግሞ ያሳድዱአችኋል፤ ቃሌን ጠብቀው እንደ ሆኑ ቃላችሁን ደግሞ ይጠብቃሉ። ዳሩ ግን የላከኝን አያውቁምና ይህን ሁሉ ሰለ ስሜ ያደርጉባችኋል። እኔ መጥቼ ባልነገርኋቸውስ ኃጢአት ባልሆነባቸውም ነበር፤ አሁን ግን ለኃጢአታቸው ምክንያት የላቸውም።
እኔን የሚጠላ አባቴን ደግሞ ይጠላል። ሌላ ሰው ያላደረገውን ሥራ በመካከላቸው ባላደረግሁ፥ ኃጢአት ባልሆነባቸውም ነበር፤ አሁን ግን እኔንም አባቴንም አይተውማል ጠልተውማል። ነገር ግን በሕጋቸው። በከንቱ ጠሉኝ ተብሎ የተጻፈው ቃል ይፈጸም ዘንድ ነው። ዳሩ ግን እኔ ከአብ ዘንድ የምልክላችሁ አጽናኝ እርሱም ከአብ የሚወጣ የእውነት መንፈስ በመጣ ጊዜ፥ እርሱ ስለ እኔ ይመሰክራል፤ እናንተም ደግሞ ከመጀመሪያ ከእኔ ጋር ኖራችኋልና ትመሰክራላችሁ።
#Subscribe #Like #Share
👇👇👇👇
www.youtube.com/@haileG2239
www.youtube.com/@pagumentube
