ch
Feedback
HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ

前往频道在 Telegram

❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239

显示更多
2 279
订阅者
无数据24 小时
+57
+3230
帖子存档
በትዳራችን፣ በሥራችን፣ በትምህርታችን መተት ሲመተትብን የምናያቸው ምልክቶች 3ቱ የአባቶቻችን በረከቶች የፕሮቴስታንቶች ጉድ ተመልከቱ #ethiopiaj https://youtu.be/uKo-c82ptkw

«ጠባቧ መንገድ» "በተጨባጭ እውነታ ሰፊውንና ልቅ የኾነውን መንገድ ይዘን ሳለ ጠባቡንና የቀጠነውን መንገድ እየተከተልን እንደ ኾነ በማሰብ እንዳንታለል በራሳችን ላይ ቅርብ ትኲረት እናድርግ። ቀጥሎ የሰፈረው ነገር ጠባብ መንገድ ማለት ምን እንደ ኾነ ያሳይሃል፦ ሆድን ማጎስቆል (ስስትን መግደል)፣ ትጋሃ ሌሊት (ሌሊቱን ሙሉ መቆም)፣ ጥቂት ውኃ መጠጣት፣ ቍራሽ ዳብ መብላት (ከፊለ ኅብስት)፣ በተዋርዶ ድርቅ መንጻት፣ መናቅ፣ ፌዝን መቀበል፣ መሰደብ፣ የገዛ ፈቃድን ቆርጦ መጣል፣ በሚያስቆጣ ነገር መታገሥ፣ ባለ ማጉረምረም ንቀትን መታገሥ፣ ስድቦችን ቸል ማለት፣ ያልተገባ ጠባይን ጸንቶ መታገሥ፤ ሲታሙ አለመቆጣት፣ ሲዋረዱ አለመቆጣት፣ ሲነቀፉ ትሑት መኾን ነው። የገለጽናቸውን ጎዳናዎች የሚከተሉ ብፁዓን ናቸው፣ መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና። ማቴ 5፡3-13።" እንዲል ዮሐንስ ዘሰዋስው። በዚህ አባት ጽሑፍ ውስጥ አንደኛ ራሳችንን መመርመር እንዳለብን ተገልጿል። ልቅ በኾነው ሰፊ መንገድ በተባለው የዓለማዊነት መንገድ ላይ መኾን አለመኾናችንን በትኩረት እንድናስተውል ምክረ ሐሳብ ቀርቧል። ኹል ጊዜም ቢኾን ትክክለኛ ወደ ኾነው መንገድ ለመግባት አስቀድሞ የቆምንበትን መንገድ እና በዚያ መንገድ እንድንጓዝ ያደረገንን ውስጣዊ ፍላጎት መረዳት ያስፈልጋል። ምን ያህልስ ጊዜ ልቅ በኾነው የኃጢአት መንገድ ተጉዘን ይኾን? ምን ያህልስ የዚያ መንገድ ጣዕም በውስጣችን ቀርቶ ይኾን? እንዴትስ ከዚያ መንገድ መውጣት እንችላለን። እያልን በእርጋታ ለራሳችን ጥያቄ እያቀረብን ራሳችንን እንመርምር። ኹለተኛው መሠረታዊ ነገር ጠባብ መንገድ ማለት ምን ማለት እንደ ኾነ የተገለጸበት ነው። ጥቂት መመገብን ከመለማመድ ጀምሮ ማንኛውንም ክፉ የተባሉ ነገሮችን የሚያደርጉብንን መታገሥ ተገቢ መኾኑን ያስረዳል። መንገዱን ጠባብ ያሰኘውም፥ የተገለጹትን ነገሮች ለመተግበር እጅግ የሚከብዱ ስለ ኾነ ነው። ጽድቁንና መንግሥቱን እያሰብን የምንኖር ከኾነ ግን ከባድ ሊኾኑ አይችሉም። ጠባቡ መንገድ ጣዕመ መንግሥተ እግዚአብሔርን እያሰቡ ኃጢአትን መጥላትን ማዕከል ያደረገ ነውና። የሚንቁንን፣ የሚሰድቡንን፣ የሚያሙንን መታገሥ ለብዙዎቻችን አስቸጋሪ ነው። በእውነትም የሚጠሉንን ላለመጥላት እየታገልንን ኹሌ ራሳችንን ትዕግሥትን ብናለማምድ እግዚአብሔር ይረዳናል። ትዕግሥት በእኛ ጥረት ብቻ ሳይኾን ከእግዚአብሔርም ጸጋ ኾኖ የሚሰጥም ነገር ነውና። እኛ ከልባችን ክፉን በትዕግሥት ስንቀበል እግዚአብሔር ጽናቱን ይሰጠናል። የጠባቡ መንገድ መድረሻው መንግሥተ እግዚአብሔር መኾኑን በሕሊናችን ውስጥ አስቀምጠን፥ መንግሥቱን እያሰብን እንኑር። አንድ ሯጭ ትኲረቱን በሙሉ የሚያደርገው ቀድመውት ያሉ ተወዳዳሪዎች ላይ እንደ ኾነ ኹሉ እኛም ትኲረታችንን ወደ መንግሥተ እግዚአብሔር አቅጣጫ ካደረግን በእኛ ላይ የሚደረጉ ክፉ ነገሮችን ኹሉ ሳናያቸው ማለፍ እንችላለን። #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

እልከኛው አይነጥላ እኛን፣ ባለትዳሮችን፣ እጮኛሞችን አብዝቶ የሚፈትነን መንፈስ የባለትዳሮች የመናፍስት ፈተና እልከኛው የአይነጥላ መንፈስ #ንቁ 😭🙏 https://youtu.be/l9_Yfeq74_4

"ሐጹረ ጸሎት" ◈ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ አቤቱ ራሳቸውን ከሚወዱ ለገንዘብ ከሚስገበገቡ ትምክህተኞች፤ ትዕብተኞችና፤ ተሳዳቢዋች ለወላጆቻቸው ከማይታዘዙ ውለታቢሶች ፍቅር አንድነት ከሌላቸው ሰዎች
"ሐጹረ ጸሎት" ◈ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ አቤቱ ራሳቸውን ከሚወዱ ለገንዘብ ከሚስገበገቡ ትምክህተኞች፤ ትዕብተኞችና፤ ተሳዳቢዋች ለወላጆቻቸው ከማይታዘዙ ውለታቢሶች ፍቅር አንድነት ከሌላቸው ሰዎች የማህበር አንድነት እንዳልተባበር በሐጹረ መስቀልህ እጠረኝ። ◈ አቤቱ እለምንሃለሁ እማልድሃለሁም ከሰው ጋር ስምምነት የሌላቸው ሰው ሆነው ሰውን ከገንዘብ ጋር ለመዋጥ የሚፈልጉ ስም የሚያጠፉ ታርክን የምያጎድፉ የመልካምና የበጎ ነገር ጠላቶች ከሆኑ ራሳቸውን የማይቆጣጠሩ ጨካኞች ጥንቃቄ የጎደላቸው በትዕቢት የተሞሉ እግዚአብሔርን ከመውደድ ይልቅ ሥጋዊ ደስታን የምወዱ ሃይማኖት ያላቸው እየመሰሉ እግዚአብሔርን ክደው ሌላውን የሚያስክዱ ከሐዲዎች ደመ መለኮትን በብርሃን ጽዋ ተቀብሎ በብርሃን መነሳንስ ረጭቶ ዓለምን በቀደሳት ስለ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ዑራኤል ብለህ ወደኔ ወደ አገልጋይህ እንዳይቀርቡ በኃያል ክንድህ አርቅልኝ በቸርነትህም ሐጹር ክበበኝ አሜን። እያላችሁ ጸልዩ 🙏 #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

«ክብረ ክህነት በትውልድ መሃል ይረክስ ዘንድ እየተተጋ ነው!» ካህናት ከቅዱሳን መላእክት አገልግሎት በላይ ለከበረው አገልግሎት የተጠሩ የእግዚአብሔር አይኖች ናቸው። የእግዚአብሔር ምህረትን እና ቸርነት የሚመላለስባቸው ከትውልድ መሃል የተመረጡ ናቸው። ያለክህነት እና ካህናት ምስጢራት መፈጸም አይቻልም። በአጭሩ ያለክህነት እና ካህናት ቤተክርስቲያንንም ጭምር ማሰብ አይቻልም። በትረ ክህነት የጨበጡ እጆች አጋንንትን እየቀጡ ኀጢአትን የሚያቀልጡ ናቸው፡፡ በዓለም ኖረው ዓለምን የሚያክሙ ሀኪሞች ጭምር ናቸው። ዳሩ ግን በስመ ካህናት የተገለጡት እነርሱ እየታመሙ ጤነኛዎችን የሚያመረቅዙ ሆኑ እንጅ። እውነተኛ ካህናት ህዝብ እና አህዛብን ወደ እግዚአብሔር እና ወደ መንግስቱ ያቀርባሉ፤ የመንፈስ ልጆቻቸውን በርህራሄ ይጠብቃሉ፡፡ በለመለመ መስክ፣ በጠራ ውኃ በንጽሁ የዕረፍት ስፍራ ያሠማራሉ፡፡ የኤልያስ መንፈስ በኤልሳዕ እንደሰራ ፣የሙሴ ጸጋ በኢያሱ እንደጸና ዛሬም የሐዋርያት መንፈስ በሀዲስ ኪዳን ካህናት ላይ ይሰራ ዘንድ የታመነ ጸጋ ነው። በአንብሮተ እድ፣ በንፍሐት እፍታ መንፈስ ቅዱስ የጸጋዎች ሁሉ ቁንጮን ለሰው ልጆች እያቀበለ ርህራሄውን በክህነት ጸጋ ተመልክተናል። ይህን ጊዜ በምድርም በሰማይም ያስሩ ይፈቱ ዘንድ ስልጣንን ይጨብጣሉ። የአምላክ ሥጋና ደምን በመሰዊው ላይ ያቀርባሉ። ነገር ግን ይህ የክህነት ጸጋ በትውልድ መሃል እንዲረክስ ቆብ ያጠለቁት ሐሳውያን በትጋት እየሰሩ ነው። እረኞ ነን ያሉት ጭካኔያቸው ከተኩላ በላይ ገልጠው ክህነት እና ካህናትን አምርረው እንዲጠሉ እየተደረጉ ነው። በአጭሩ የቅድስት ቤተክርስቲያን አይተኬ የአገልግሎት ጸጋ ተሸርሽሮ እንዲነቀል ቀሚስ ባደረጉ ቆብ ባጠለቁ የስም እንጅ የግብር ካህነት በነጠፈባቸው ሰዎች በትጋት እየተሰራ ነው። ይህ ዘመን ግዙፍ የእግዚአብሔር ቸርነት ካልታከለበት የሚመጣው ነገር እጅግኑ ያስፈራል። መሰረት መናድ ላይ ከቤተክህነትም ከቤተመንግስትም በምሬት እየተሰራ ይገኛል። ክህነትን የሚያረክስ ትውልድ ተፈጥሮ፣ ካህናትን የሚያቀል እና የሚመዝን ዘመን ተገልጦ ቤተክርስትያን የኃሊት እንድትፈተን በሮች እየተፈተኑ ነው። እግዚአብሔር ምህረቱን ያድልልን! ያሳዝናል! #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

እግዚአብሔር የእኛን መዳን እንጂ ጥፋት የማይወድ መኾኑን ልብ ማለት ይገባናል። በመጽሐፍ ቅዱስ "የእስራኤል ቤት ሆይ! ስለዚህ እንደ መንገዱ በየሰው ኹሉ እፈርድባቸዋለሁ፥ ይላል ጌታ እግዚአብሔር፤ ንስሓ ግቡ፤ ኃጢአትም ዕንቅፋት እንዳይኾንባችሁ ከኃጢአታችሁ ኹሉ ተመለሱ። የበደላችሁትን በደል ኹሉ ከእናንተ ጣሉ፤ አዲስ ልብና አዲስ መንፈስንም ለእናንተ አድርጉ፤ የእስራኤል ቤት ሆይ! ስለ ምን ትሞታላችሁ? የምዋቹን ሞት አልፈቅድምና ይላል ጌታ እግዚአብሔር፤ ስለዚህ በንስሓ ተመለሱና በሕይወት ኑሩ" ይላል። (ሕዝ 18፥30-32) እንግዲህ ይህ የእግዚአብሔር ፈቃድ ነው። እኛ ራሳችንን እንድናጠፋ እርሱ ፈጽሞ አይፈልግም፤ በምንም ዓይነት ችግር ውስጥ ብንኾን በንስሐ ወደ እርሱ እንድንመጣ ጌታ እግዚአብሔር ይፈልጋል። እንግዲያስ ለዚህ በፍቅር ለተመላው የእግዚአብሔር ጥሪ መልሳችን ራስን በማጥፋት መፍትሔ አትሰጠኝም ማለት ሊኾን ይገባዋልን? እርሱ ወደ እኔ ኑ ካለን ስለ ምን ከእርሱ መራቅን ትክክል አድርገን ወደ መጥፎ ውሳኔ እንገባለን! እግዚአብሔር ሲኦልን እንኳን የፈጠረው ስለ ርኅራኄው ሲል መኾኑን ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ያስረዳል። ይኸውም፦"... እግዚአብሔር ኃጢአተኞች ወደ ሲኦል እንዲጣሉ በማሰብ ከዚህ በፊት የነበሩትን ኃጥአን ባይቀጣ ኖሮ ብዙዎች ወደ ሲኦል በገቡ ነበር። በዚህ አስፈሪ ቅጣት ነፍሳችን ብትነሣሣም አንዳንዶች ግን እንዲህ ዓይነት ነገር የለም በማለት ለመበደል ተዘጋጅተዋል። እናም ቅጣቱ ባይታወጅና ባያስፈራ ኖሮ ምን የማንበድለው በደል ይኖራል? ... ለመንግሥተ ሰማይ ከተገባልን ቃል ኪዳን ባልተናነሰ መልኩ የሲኦል አስፈሪነት እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን እንክብካቤ የሚያሳይ ነው። ... ይህንን የጨካኝነት ጉዳይ ነው ብለን አናስብ። ይልቁንም የኀዘኔታና የምሕረት፣ እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን ፍቅርና ትኲረት አርገን እንጂ። በዮናስ ዘመን የነነዌ ጥፋት አስፈሪ ባይኾን ኖሮ ያ ጥፋት አይቀየርም ነበር። የነነዌ ሕዝብ "ነነዌ ትገለበጣለች" ዮና 3፥4 የሚለውን የነቢዩን ማስጠንቀቂያ ባይሰማ ኖሮ ወደ እግዚአብሔር አይቆምም ነበር።" #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

ይህ ዘመን ለቤተክርስቲያን ምቹ ጊዜ ነው ...ብጹዕ አቡነ ሩፋኤል *** 😭 ይህ ዘመን ለቅድስት ቤተክርስቲያን በአራቱም ማዕዘን የመከራ ዶፍ የሚዘንብባት ምቹነት ርቆ የጸናበት የሰማዕትነት እና የስ
ይህ ዘመን ለቤተክርስቲያን ምቹ ጊዜ ነው ...ብጹዕ አቡነ ሩፋኤል *** 😭 ይህ ዘመን ለቅድስት ቤተክርስቲያን በአራቱም ማዕዘን የመከራ ዶፍ የሚዘንብባት ምቹነት ርቆ የጸናበት የሰማዕትነት እና የስደት ዘመኗ ነው። ቅድስት ቤተክርስትያን አሁን ላይ ራሄላዊ ሆናለች። ሄሮድስ የገነነባት የኢየሩሳሌም እናቶችን መስላለች። መኖኮሳት በበዓታቸው የሚረሸኑበት ዘመን የቤተክርስቲያን ምቹ ዘመን ነው ከተባለ ይህን ምቹነት ከረሻኙ ወገን ላሉ ሰልፈኞች ብቻ ነው። 😭 የእረኝነት መንበር እንደ አሜባ ተፈጥሮ ተበጣጥሶ ባለአስኬማ የሆኑ ኖላውያን በዘር ኩሬ ውስጥ ወድቀው የሚንቦራጨቁበት ዘመን የቤተክርስቲያን ምቹ ዘመን ነው ከተባለ እግዚኦታ ይገባናል። የመቅደስ መቃጠል፣ የምዕመናንን ስደት እና ሞት፣ የክብረ ክህነት ሹፈት የበዛበት ይህ ዘመን የቤተክርስቲያን ምቹ ዘመን ነው ከተባለ ቤተክርስቲያን በዘመኗ ምቹ ዘመን አላየችም ማለት ነው። በጵጵስና ስም ደምወዝ እየበሉ፣ ቀሚስ እያጠለቁ፣ አስኬማ እየደፉ፣ በትረ ሙሴ እየጨበጡ ለቄሳራውያን የሚያደላ የስብከት ከንፈር ለያዙ ሰዎች ይህ ዘመን ለቤተክርስቲያን ሳይሆን ለእነርሱ ምቹ ነው። 😭 ሟች የበዛበት ዘመን ለገዳይ እንጅ ለምስኪኖች ምቹ አይደለም። ርሃብ እና ስደት በጸናበት ትውልድ ለአሳዳጅ እና ለሚያገሳው እንጅ ለተጎሳቃዮች ምቹ አይደለም። ግፍ የጸናበትን ዘመን ማውገዝ ቢያቅት እንኳን ዝም ማለት ማንን ጎዳ። ኤሬ ወገን እንዴት ነው ነገሩ ... ይማረን! እግዚአብሔር ይቅር ይበለን፣ ይማረን በእውመት!!! #Subscribe #Like #Share 👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

«የሰይፈ መለኮት ጸሎት» ቁጥር 25 ላይ ያለው ቃል እና ትርጉሙ "ቀንዶቹ ሰባት አይኖቹም ሰባት" (የዮሐንስ ራዕይ 13.1) ያለ ቃል ሲሆን አባቶቻችን እንዲህ ይተረጉሙታል። ሰይፈ መለኮት ቁጥር 25፦ "የጌታችን ቀንዶቹ ሰባት፤ ዓይኖቹም ሰባት፤ እራሶቹ አስር፤ የሆኑ ለመስዋዕት የቀረበ ወይም የተዘጋጄ እርሱ ኢየሱስ ክርስቶስ ነው ይላል።" ቀንዶቹ ሰባት ማለቱ ፦ የሰባቱ ሊቃነ መላእክት ምሳሌ ሲሆን ቀንድ መዋጊያ ስለሆነ መላእክት ለእግዚአብሔር አገልጋይ ተላላኪም ስለሆኑ በቀንድ ይመሰላሉ። ዓይኖቹ ሰባት ማለቱ፦ አንድም የሰባቱ አብያተ ክርስቲያን ምሳሌ እነዚህም ፦ የኤፌሶን ቤተክርስቲያን፣ የሰምርኔስ ቤተክርስቲያን፣ የጴርጋሞንም ቤተ ክርስቲያን፣ የትያጥሮን ቤተ ክርስቲያን፣ የሰርዲስ ቤተ ክርስቲያን፣ የፊልድልፍያ ቤተ ክርስቲያን፣ የሎዶቅያ ቤተ ክርስቲያን ናቸው። በዮሐንስ ራዕይ ከምዕራፍ 2 እስከ 3 ድረስ ታገኙታላችሁ እና በደንብ አንብቡት። እራሶቹ አስር የተባለውም፦ አንድም የአስርቱ ትህዛዛት ምሳሌ ስሆን 👏(የዮሐንስ ራዕይ 13.1) እንዲህ ይላል አንድም አውሬ ከባሕር ሲወጣ አየሁ አሥር ቀንዶችና ሰባት ራሶች ነበሩት በቀንዶቹም ላይ ዐሥር ዘውዶች በራሶቹም ላይ የስድብ ስም ነበረ ይላል። አስር ቀንዶች፦ የአስሩ ነገስታት ምሳሌ ሲሆን፤ ሰባቱ እራሶች ፦ ሰባቱ ሀገራት ሲሆኑ በቀንዶቹም ላይ አስር ዘውዶች ማለቱ፦ መንግስታቸው ገና ያልፀናች አስሩ ነገስታት ናቸው። እንዲሁም ስለ አስሩ ቀንዶች ስለ ሰባቱ እራሶችና በቀንዶቹ ላይ ስላሉት ዘውዶች በዮሐንስ ራዕይ ምዕራፍ 17.9 ጀምራችሁ ብታዩት እንዲህ ይላል "ጥበብ ያለው አእምሮ በዚህ ነው ሰባቱ ራሶች ሴቲቱ የተቀመጠችባቸው ሰባት ተራራዎች ናቸው። ሰባት ነገሥታት ደግሞ ናቸው ዐምስቱ ወድቀዋል አንዱም አለ የቀረውም ገና አልመጣም ሲመጣም ጥቂት ጊዜ ሊቆይ ይገበዋል። የነበረውና የሌለውም አውሬ ራሱ ደግሞ ስምንተኛው ነው ከሰባቱም አንዱ ነው ወደ ጥፋትም ይኼዳል። ያየሀቸውም አስሩ ቀንዶች ገና መንግሥትን ያልተቀበሉ አስር ነገሥታት ናቸው ዳሩ ግን ከአውሬው ጋራ ላንድ ሰዓት እንደ ነገሥታት ሥልጣንን ይቀበላሉ። ስባቱ ሀገራት ተራራ በሚለው ከላይ ተጠቅሷል፤ ሀገርና ተራራ አንድ ስለሆነ አንድ ሀገር በተራራው ሊጠራ ይችላል ተራራውም በአንድ ሀገር ሊጠራ ይችላል። ባጠቃላይ የጌታችን መላእክት የምንጠቀምባቸው የሚራዱን ሲሆነ፣ ቤተ ክርስቲያን የምንጠቀምበት ስጋና ደሙን እንቀበልበት መላእክት የሚራዱን አስሩ ትዕዛዛት ደግሞ የምንጠብቃቸው የምንገሰፅባቸው መንግስቱን የምንወርስባቸው ናቸው፤ የአውሬው ደግሞ ትንቢት ነው። #በርቱ! 👉@haile_gebriel_tube_bot 👉@hailegebriel202

የእረኝነታቸውን ብኩርናቸውን በምስር ያልሸጡ አባት.. *** አሸርጋጅ አጎብዳጅ በበዛበት በእዚህ በእሾህ ዘመን ያለአንዳች አባት ያልተወን ቅድስት ሥላሴ የተመሰገነ ይሁን። እረኛ ያልነው አካል አስብቶ
የእረኝነታቸውን ብኩርናቸውን በምስር ያልሸጡ አባት.. *** አሸርጋጅ አጎብዳጅ በበዛበት በእዚህ በእሾህ ዘመን ያለአንዳች አባት ያልተወን ቅድስት ሥላሴ የተመሰገነ ይሁን። እረኛ ያልነው አካል አስብቶ ለአራጅ የሚሰጥ ሻጫ አጋፋሪ ሆኖ በተገለጠበት በእዚህ ትውልድ እንደ አብርሐም አባትነትን ያልናቀ እረኛ መኖሩ ተመስገን ያስብላል። ብጹዕ አቡነ አብርሐም በረከትዎ ትድረሰን !!! 😭 በእውነት በጣም ከልበ አዝኛለሁ፣ እግዚአብሔር አሁንም ሀገራችንን ሰላም ያድርግልን። እንዲህ አይነት አባቶችን ማየት ያሳዝናልም፣ ያሳፍራልም። 😰😰 #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

የሰላቢ መንፈስ እንዳለባችሁ ማወቂያ መንገዶቹና መፍትሔዎቹ || 3ቱ የመዳን መንገዶች | ዲያብሎስ ሁለም እኛን ለመጣል ይታገላል | መምህር ኢዮብ ይመኑ 🙏😰 https://youtu.be/qAMzbgkFGb0

🙏 ገብረ መንፈስ ቅዱስ ሆይ የብርሃኑ ጸዳል እጅግ በሚያበራ ዓምደ ብርሃን ለተቀረፀ ስም አጠራርህ ሰላም እላለሁ። ክቡሩ አባት ሆይ፤ በኃጢያት ድጥ ላይ ለመውደቅ የሚፍገመግሙትን በኃይል ክንድህ ፈጥ
🙏 ገብረ መንፈስ ቅዱስ ሆይ የብርሃኑ ጸዳል እጅግ በሚያበራ ዓምደ ብርሃን ለተቀረፀ ስም አጠራርህ ሰላም እላለሁ። ክቡሩ አባት ሆይ፤ በኃጢያት ድጥ ላይ ለመውደቅ የሚፍገመግሙትን በኃይል ክንድህ ፈጥነህ የምትደግፍ ነህና በዓለም ላይ መልካም ዝናን ለአተረፈው ስም አጠራርህ ኢትዮጵያ ታመሰግናለች፤ ግብፅም ትዘምራለች። (መልክዐ ገብረመንፈስቅዱስ፤ ለዝክረ ስምከ) ጻድቁ አባታችን አቡነ ገብረመንፈስ ቅዱስ ሆይ ስምህን እየጠራን ዝክር ላደረግን፣ ፀበልህን ለጠጣን፣ እምነትህን ለተቀባን፣ በተቀደሰዉ የመታሰቢያህ ቅዱስ ቦታህ በመገኘት ለተማጸንህና ለጸለይን ሁሉ ፈዉስንና ምሕረትን ስጠን፡፡ ከሰለጠነብን ጽኑ የሥጋ ይሁን የነፍስ ደዌ እንድንድን፣ ስለኃጥያታችን ፀፀትና መመለስን፣ ስለ እዉነት በእውነት እንድንቆም፤ የእግዚአብሔርን ፍቅር አዉቀን ትእዛዛቱን የምንፈጽምበት ጽናት ብርታት እንድናገኝ ስምህን እየጠራን እንማጸንሃለን። ታማልደን ዘንድ ቅዱስ ፈቃድህ ይሁንልን፡፡               🙏   አሜን   🙏 #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

አገልጋዮች ሲተኙ ትልቅ ማዕበል አለባቸው በሁለት ወንድሞቹ ተደፍሮ ከእንስሳት ጋር ወሲብ ይፈጽም የነበረ ሰው ታርክ መምህር ግርማ ወንድሙ 🙄😂😰🙄 https://youtu.be/mOUgN0g6Kjk?si=vxS1SBbGxb4ZJCX0

«የመንፈሶች መተያየት» አብዛኛውን ጊዜ በሕይወታችን ውስጥ ከሚታዩ ነብፈሳዊ ብዥታዎች መካከል በዋናነት የሚጠቀሰው፤ አንዳንዴ መጥፎ መንፈስ ዞር ሲል ማየት ማቻላችን ነው። በዚህ ጊዜ «ሰይጣን ነው መሰለኝ በዚህ በኩል አለፈ» እንላለን። የዚህ መንፈስ መታየት በሁለት መንገድ የሚገለጽ ነው። አንደኛው በመንፈስ ቅዱስ ኃይል ሌላ ርኩስ መንፈስ የሆነ ደባል መንፈስ መምጣት፣ መጀመሩንና በእንቅስቃሴ ላይ መሆኑን የምናውቅበት የእግዚአብሔር መንገድ ነው። ሌላውና ሁለተኛው ደግሞ፤ እንደዚህ ዓይነቱ ክስተት የሚታየን እኛ ዘንድ ሌላ ተመሳሳይ መንፈስ በመኖሩ ነው። በሌላ አነጋገር ያየነው እኛ ውስጥ ባለና በተደበቀው መንፈስ አማካኝነት ነው። መናፍስቱ በአንድ ዓይነት ተፈጥሯቸው የተነሳ ሲተያዩ ይተዋወቃሉ። መንፈሱ በተለያየ መልክ፣ ገጽታ፣ አቋምና ሁኔታ በድንገት ዞር ብሎ ታይቶና ብዥታ ፈጥሮ ወዲያውኑ እልም ብሎ ይሰወራል። ይህ ወቅት ዲያብሎስ ለሥራ እየተንቀሳቀሰና እያንዣበበ፤ የሚውጠውን እየፈልገ መሆኑን የሚጠቁም ቀጥተኛ ምልክት ነው። "ዲያብሎስ የሚውጠውን ፈለጎ እንደሚያገሳ አንበሳ ይዞራል።" (1ኛ.ጴጥ.5፡9) በተመሳሳይ አንዳንድ ጊዜ ሰዎች በተለይ ሕጻናት ጸጉሩ የተንጨባረረ፤ መልከ-ጥፉ የሆነና በገሃዱ አለም ውስጥ የሌለ አስፈሪ ፍጡር ወዘተ...አጠገባቸው ተቀምጦ ወይም ተኝቶ ይታያቸዋል። ይህ እነሱ የሚያዩት ፍጡር ግን፤ በተመሳሳይ አጠገባቸው ላለ ሌላ ሰው የምታይ አይደለም። ምክንያቱ ደግሞ ከፍ ብሎ እንደተጠቀሰው የክፉውን መንፈስ ገጽታ ያዩት ውስጣቸው በሚገኘው ክፉው መንፈስ በኩል ስለሆነ ነው። አንዳንድ ሰዎች እንደዚህ ዓይነቱን አጋጣሚ መንፈስ ቅዱስ እንደተገለጸላቸው አድርገው ሲናገሩ ይደመጣሉ። ይህ ፈጽሞ ትክክል አይደለም። ጸሎት ለማያደርግ፣ ምስጋና ሌለሌው፣ በቅዱስ ቁርባን መንፈስና ጸጋ ላልኖረ፤ በየጊዜው የአምልኮት ክብር ለማያሳይ ሰው፤ ሰይጣን ውልብ ባለበ'ት ቁጥር በመንፈስ ቅዱስ ታየኝ ቢል የሚሰራ አይሆንም። በእርግጥ በመንፈስ ቅዱስ በኩል ክፉው መንፈስ የሚታይ ቢሆንም በዚህ ቅዠት በሚመስል አስጨናቂ መልኩ ግን አይደለም። "አንተ ግን በአምላክህ በእግዚአብሔር ዘንድ ፍጹም ሁን። የምትወርሳቸው እነዚህ አሕዛብ ሞራ ገላጮችንና ምዋርተኞችን ያደምጣሉ፤ አምተ ግን እንዲህ ታደርግ ዘንድ አምላክህ እግዚአብሔር ከልክሎሃል።" (ዘዳግ.18፡13-14) ሌላው ሰው ላይ ያደረው ሰይጣን፤ ቅዱሳንን አስመስሎ በመናገር፤ ቅዱስ ሚካኤል አዞኛል፣ እንዲህ አድርጉ እያለ መናገር ከጀመረ፤ ተናጋሪውንና አድማጩን ሰው፤ ሁለቱም እንዲመጻደቁ በማድረግ፤ በመንፈሳዊ የመለወጥ ጥበቡን በማሳደግ ወደ ጥንቆላ አካሄድ ሥልቱን ይቀይራል። እንዲህ አይነቱ መንፈስ፤ በብዙ ጠበል ቦታዎች እየዞረ ጠበሉን በመለማመድ መጓዝና ገዳማትን በመልመድ፤ በመንፈሳዊው ቦታ መንፋሳዊ ልምምድን በማድረግ፤ የክፋት ሥራውን ከዓለማዊው ሥፍራ ከሚያመጣው ችግር የበለጠ አደገኛ ያደርጋል። እግዚአብሔር ተናገር ብሎኛል! የሚል ሰይጣን ምንጊዜም ለማሳሳት የሚጠቀምበት ዘዴ መሆኑን ካልታወቀ፤ መንፈሳዊ ቃልቻ ወይም ጠንቋይ የመሆኑ ዕድል ሰፊ ነው። ዛሬ በዚህ መንፈስ ሥር የሚመሩ እማሆዮችና አባሆዮች በከተማችን ውስጥ በጣም ብዙ ናቸው። 2ኛ.ቆሮ 11፡14 "ይህም ድንቅ አይደለም፤ ሰይጣን ራሱ የብርሃንን መልአክ እንዲመስል እራሱን ይለውጣልና። እንግዲህ አገልጋዮች ደግሞ የጽድቅን አገልጋዮች እንዲመስሉ ራሳቸውን ቢለውጡ ታላቅ ነገር አይደለም፤ ፍጻሜያቸውም እንደ ሥራቸው ይሆናል።" #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

«የዲያብሎስ መንፈስ ሲያዝ» ሰይጣን በተፈጥሮው የታወቀ ውሸታም ቢሆንም፤ በእግዚአብሔር ኃይል ሲያዝ ግን፤ በግድ እውነቷን ያወጣታል። በሰዎች ላይ ያለው ርኩስ መንፈስ ተይዞ፤ ስይጣኑ ወይም አጋንንቱ ብዛቱን፤ ማንነቱንና ተልዕኮውን በሚናዘዝበት ወቅት፤ የሚከተሉትን ጠባያት ይስተዋላሉ። ፩. ሰውየው ከዘር የተላለፈ የዛር ወይም የውቃቢ መንፈስ ካለበት፤ ግለሰቡ በራሱ አንደበት የሚለፈልፈውን ሰይጣን፤ በሙሉ ልቡ ሆኖ ቢሰማውም፤ ምላሱን ለማቆምም ሆነ ለመቆጣጠር አይቻለውም። ፪. አንዳንድ ጊዜ ደግሞ፤ ሰውየውን ወሰድ መለስ እያደረገው፤ በግማሽ ልቦናው ሰይጣኑ የሚናገረውን ይሰማል። ግማሹን ደግሞ አይሰማውም። በተመሣሣይ፤ በዚህም ጊዜ ግለሰቡ በራሱ አንደበት የሚናዘዘውን ሰይጣን፤ በግማሽ ልቦናው ሆኖ ቢሰማውም አሁንም ምላሱን ለማቆምም ሆነ ለመቆጣጣር አይቻለውም። አንዳንድ ጊዜ በሰዎች ላይ የሚታየው ተለዋዋጭ ጠባይ ከዚህም ጋር በተጨማሪነት ይያያዛል። ፫. ሰይጣኑ ወደ ግለሰቡ ተልኮ የገባ የመተት መንፈስ ከሆነ፤ ሰውየው በራሱ አንደበት የሚለፈልፈውን ሰይጣን ሙሉ በሙሉና በፍጹም አለማዳመጥ ብቻ ሳይሆን የሚናገረውን ነገር ሁሉ ጨርሶ አያውቀውም። #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube

ሸር ይደረግ የተለግራም ቻናሉ https://t.me/boost/hailegebriel2021

ሳጥናኤል ከማዕረጉ ሲወድቅ ሁለት ነገር አጥቷል ዘመናዊ ጠንቋዮች እና ደብተራዎች ሰው የተከለከለውን አብዝቶ ማድረግ ይወዳል! #ethiopia 😭😰😂🙄 https://youtu.be/OdJ4bxwR58E

«ሦስቱ አርዕሰተ ኃጣውእ» ፩. ስስት (ማቴ.፬፥፫ የሚፈታተነውም ቀርቦ ‹‹አንተ የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንክስ እነዚህን ድንጋዮች ዳቦ እንዲሆኑ እዘዝ›› በማለት ሰይጣን የመጀመሪያውን ፈተና ጌታችን በተጠመቀ ጊዜ የባሕሪ አባቱ በሰማይ ሆኖ “የምወደው ልጄ” ሲል ሠምቷልና ‹‹የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንክ›› አለ፡፡ ዮሴፍ የወንድሞቹን ምግብ ይዞ በተራበ ጊዜ እግዚአብሔር ድንጋዩን ዳቦ አድርጎ እንዳበላውም ያውቃልና ‹‹እነዚህን ድጋዮች ዳቦ እንዲሆኑ እዘዝ›› አለው፡፡ ዲያብሎስ በሁለቱም በኩል አሸናፊ የሚያደርገውን ፈተና ይዞ ነው የቀረበው፡፡ ይኸውም ‹‹እንዳልኩት ድንጋዩን ወደ ዳቦ ቢለውጥ የሰይጣን ታዛዥ ብዬ አስነቅፈዋለሁ፤ እምቢ ቢለኝ ደግሞ እግዚአብሔር ለዮሴፍ ድንጋዩን ዳቦ አድርጎ አብልቶታል፤ ይህ ግን እግዚአብሔር አይደለምና እምቢ አለ›› ብዬ አምላክነቱን አጠራጥራለሁ” የሚል ነው፡፡ ዲያብሎስ ብዙ ጊዜ ለተፈታኙ ከፍተኛ ጥንቃቄ የሚፈልጉ ለፈታኙ(ለራሱ) ደግሞ በሁለቱም በኩል ድል ሊያስገኙ የሚችሉ ብዙ ፈተናዎችን በአይሁድ እያደረ ለጌታአችን አቅርቧል፡፡ ፪. ትዕቢት (ሰይጣን በስስት ጌታችን ፈትኖ ድል ቢደረግም ተስፋ ሳይቆርጥ እንዲህ እያለ በትዕቢት ይፈትነው ጀመር፡፡ “ከዚህ በኋላ ዲያብሎስ ወደ ቅድስት ከተማ ወስዶ በቤተ መቅደስ ጫፍ ላይ አቆመው፡፡ አንተ በእውነት የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንክ ከዚህ መር ብለህ ወደታች ውረድ ይጠብቅህ ዘንድ ስለ አንተ መላእክቱን ያዝዝልሃል እግርህም በድንጋይ እንዳትሰነካከል በእጃቸው ያነሱሀል ተብሎ ተጽፏል አለው፡፡” “… ወሰደው…”፡- ሲል ሰይጣን ጌታችንን የሚወስደው ሆኖ ሳይሆን ፈቃዱን አውቆ ሔደለት ሲል ነው፡፡ የሰይጣን ፈቃድ ምን ነበር? ቢሉ ‹‹በመጀመሪያው ፈተና ድል ያደረገኝ በበረሃ ስለሆነ ነው እነጂ ካህናትን ድል በምነሳበት በቤተ መቅደስ ቢሆን መች ድል ይነሳኝ ነበር›› የሚል ስለነበር ይህን ፈቃዱን አውቆ ምክንያት ለማሳጣት ወደ ቤተመቅደስ ሔዷልና ‹‹ወሰደው›› ተባለ፡፡ ፫. ፍቅረ ነዋይ (ሰይጣን በሁለቱ ታላላቅ ኃጢያቶች ጌታችንን መርታት ቢያቅተው በሌላ ኃጢአት ይፈትነው ጀመር፡፡ ይኸውም ፍቅረ ነዋይ ነው፡፡ “ከዚህ በኃላ ዲያብሎስ እጅግ ረዥም ወደሆነ ተራራ አውጥቶ የዓለሙን ሁሉ መንግስታት ክብራቸውን ሁሉ አሳየው፡፡ ‹ብትሰግድልኝ እጅ ብትነሣኝም ይህን ሁሉ እሰጥሀለሁ› አለው፡፡” #Subscribe #Like #Share    👇👇👇👇 www.youtube.com/@haileG2239 www.youtube.com/@pagumentube