ch
Feedback
💎🎀«المرأة الصالحة كنز من كنوز الدنيا»💎🎀

💎🎀«المرأة الصالحة كنز من كنوز الدنيا»💎🎀

前往频道在 Telegram

💎ሀያዕ ሲወሳ ለሴት ልጅ ጌጧ ነውና ሁሌም አብራ ትወሳለች፣ #ሴት ልጅና #ሀያዕ አብረው የሚኖሩ መቼም የማይነጣጠሉ ጥምሮች ናቸው። 👉 ሴት ልጅ ስትፈጠርም በሀያዕ ዘውድ አሸብርቃ ነው። 💎ይህንን ዘውድ ከራሷ የገፈፈች ሴት ግን ህያው ከሆኑ ሰዎች መሀል እንደምትንቀሳቀስ በድን ትሆናለች።

显示更多
9 060
订阅者
+624 小时
-97
-11130
帖子存档
«ነገ ቂያማ ቀን እጣ ፈንታህ ምንድን ነው። 1) ዑመር ኢብን አል-ከጣብ (رضي الله عنه) “ራሳችሁን ከመመርመራችሁ በፊት ራሳችሁን መርመሩ፤ ተመዝናችሁ ከመመዝናችሁ በፊት ራሳችሁን መዝኑ፤ ለታላቁ ቀን ተዘጋጁ።” 👉 ይህ ቃል ቂያማ ቀን ቀርቦ እንደሚመጣ እና ዛሬ ንስሐ መግባት እንዳለብን ያስታውሳል። t.me/Abuebrahim22322

🔖የአላህ መልእክተኛ ስለሏሁ አለይሂ ወሰለም እንዲህ አሉ፦ «በሰጋጅ ፊት ለፊት የሚያልፍ ሰው ከወንጀል በርሱ ላይ ያለበትን ቢያውቅ፤ በሰጋጁ ፊት ለፊት ከማለፍ 40 ቢቆም ለርሱ በተሻለው ነበር።»
🔖የአላህ መልእክተኛ ስለሏሁ አለይሂ ወሰለም እንዲህ አሉ፦ «በሰጋጅ ፊት ለፊት የሚያልፍ ሰው ከወንጀል በርሱ ላይ ያለበትን ቢያውቅ፤ በሰጋጁ ፊት ለፊት ከማለፍ 40 ቢቆም ለርሱ በተሻለው ነበር።» =

🔹 ሁለተኛው ፕሮግራም ተ       ጀ              መ                     ረ   🔊 ኡስታዝ ሙሐመድ አያሌው - ሐፊዘሁላህ ተዓላ- 😎 t.me/+KgW1mviu_thiOGQ0 😎 t.me/+KgW1mviu_thiOGQ0

⚠️ ለ"online ኡስታዝ" ተብዬዎች የተላለፈ ከባድ ማስጠንቀቂያ! ይህ በዲን ስም ለሚነግዱ፣ አደራ ለሚበሉና እህቶችን ለሚያውኩ "በሚዲያ ቁረአን እናቀራለን ለሚሉ ኡስታዞች" የተሰጠ ጠንካራ ማሳሰቢያ! —** ቁርአን የልባችን ብርሃን፣ የነፍሳችን ምግብ እና የቂያማ ቀን አማላጃችን ነው። ይህንን ታላቅ የአላህ ቃል ማስተማር የነቢያት ቅርስ እንጂ የገንዘብ ማጋቢያ ወጥመድ አይደለም። ሆኖም ግን በቅርብ ጊዜ በሚዲያ ላይ "ኡስታዝ" የሚለውን ክቡር ስም ተገን አድርገው፣ የእህቶቻችንን አደራ የሚበሉና የዲን ንግድ ውስጥ የገቡ ጥቂት ግለሰቦች የብዙ እህቶቻችንን ህይወት እያመሰቃቀሉ ይገኛሉ። ዛሬ የምናነሳው ጉዳይ የብዙ እህቶቻችንን ልብ የሰበረ፣ የእምነት ጥንካሬያቸውን የፈተነና በዝምታ የታለፈ ትልቅ ጠባሳ ነው። ቁርአን መቅራትና ማቅራት የነቢያት ታላቅ ቅርስ እንጂ፣ የሰው ኪስ ማድረቂያ ወይም የሴቶች መጀንጀኛ ድልድይ አይደለም። ሆኖም ግን፣ "ኡስታዝ" የሚለውን ክቡር ስም ተገን አድርገው፣ በአላህ ቃል ስም የሚነግዱ ጥቂት ግለሰቦች የኡማውን ክብር እያቆሸሹ ይገኛሉ። 📍 ለእነዚህ "ኡስታዞች" የቀረበ ግልጽ መልፅክት! 1. "ታማኝነት" (አማና) የት ሄደ? አንዲት እህታችን ቁርአን ልቅራ ብላ ከፊታችሁ ስትቀመጥ፣ እናንተ በስልካችሁ ቻት የምታደርጉ፣ የት ላይ እንደደረሰች የማታውቁ፣ ስህተቷን ሳታርሙ "ማሻአላህ" እያላችሁ የምታሳልፉ ሰዎች ሆይ— አላህን አትፈሩም? ይህቺ እህት ቁርአን መማር የፈለገችው ከአላህ ጋር ለመገናኘት ነው፤ እናንተ ግን በዝንታችሁና በቸልተኝነታችሁ በአላህና በእሷ መካከል ግርዶሽ ሆናችኋል። 2. የድሆችን እና የቤተሰብን ሀቅ አትብሉ! ብዙዎቹ እህቶቻችን ቤተሰቦቻቸው በረሃብ እየተሰቃዩ፣ ካለቻቸው ጥቂት የቀን ገቢ ላይ ቀንሰው ነው ለእናንተ ክፍያ የሚከፍሉት። የአራት እና የአምስት ወር ክፍያ ቀድማችሁ ተቀብላችሁ፣ ግማሽ ሱራ ሳታቀሩ "በቃሽ" ብላችሁ የምታባርሩ ሰዎች— ይህ የምትበሉት ብር ለእናንተም ሆነ ለቤተሰባችሁ "ሀራም" (የእሳት ሲሳይ) እንጂ በረካ አይሆንም። ስራውን በአግባቡ ሳትሰሩ የምትቀበሉት እያንዳንዱ ሳንቲም በቂያማ ቀን ይጠየቅባችኋል። 3. "ኡስታዝነት" የሴቶች መጀንጀኛ ዘዴ አይደለም! በዲን ስም ተሸሽጋችሁ፣ በውስጥ መስመር (Inbox) እየገባችሁ የተማሪዎቻችሁን ስነ-ልቦና የምትሰርቁ፣ ከአላማቸው የምታዘናጉና ክብራቸውን የምትነኩ ግለሰቦች ሆይ— የቁርአን መምህርነት ስም አይገባችሁም! እናንተ የዲን ተኩላዎች እንጂ መሪዎች አይደላችሁም። የሙስሊም ሴቶች ክብር የአላህ አደራ መሆኑን አትርሱ። 💡 ተማሪ እህቶቻችን ምን ማድረግ አለባቸው? እህቴ ሆይ! በአላህ መንገድ ላይ የሚደርስብሽ መከራ ሁሉ ምንዳ አለው። ነገር ግን አትታለዪ፦ ይህ በደል የብዙዎች መሆኑን እንረዳለን፤ ነገር ግን ዝምታው ሊበቃ ይገባል። ብራችሁንም ጊዜያችሁንም እንዳትበዘበዙ የሚከተሉትን ጥንቃቄዎች አድርጉ፦ *   🚩 ሴት መምህራንን (ኡስታዛቶችን) ፈልጉ፦ ከወንድ ጋር ከመቀራት ይልቅ እውቀቱና ተቅዋው ያላቸውን ሴት መምህራን መፈለግ ለዲናችሁም ለክብራችሁም አስተማማኝ ነው። *   🚩 ለክፍያ አትቸኩሉ፦ ምንም አይነት አስተማማኝ ማስረጃ ሳይኖራችሁ የብዙ ወር ክፍያ በአንዴ አትክፈሉ። ጥራቱን እያያችሁ በየወሩ ክፈሉ። *   🚩 ድምፃችሁን አውጡ፦ በደል ሲደርስባችሁ ዝም አትበሉ። ለሌሎች እህቶች ንገሩ፣ አጋልጡ። ዝምታችሁ ሌላ እህት ለተመሳሳይ በደል እንድትዳረግ በር ይከፍታል። *   🚩 የታወቁ መርከዞችን ምረጡ፦ በግለሰብ ደረጃ "አቀራለሁ" ከሚሉ ይልቅ ተጠያቂነትና ክትትል ባለባቸው ታዋቂ የኦንላይን መርከዞች መመዝገብ ብክነትን ይቀንሳል። #### ⚠️ ከጉዳዩ በስተጀርባ ያሉ ተጨማሪ አደጋዎች ይህ ችግር ከገንዘብ ብክነት ባለፈ የሚከተሉትን አደጋዎች ይዞ መጥቷል፦ *   የእምነት መላላት፦ እህቶች በእነዚህ ሰዎች ምክንያት መላውን የሃይማኖት መምህራን በጥርጣሬ እንዲያዩና ከዲን ትምህርት እንዲርቁ ያደርጋል። *   የቁርአን ስርአት መበላሸት፦ ስህተት ሳይታረም "ማሻአላህ" እየተባለ የሚታለፍ ከሆነ፣ ትውልዱ ቁርአንን በተሳሳተ መረጃና አቀራር እንዲይዝ ያደርጋል። *   የዳዕዋው ዘርፍ መርከስ፦ በዲን ስም የሚነግዱ ሰዎች በበዙ ቁጥር፣ እውነተኛዎቹና አላህን የሚፈሩ ኡስታዞች ስማቸው አብሮ እንዲጠፋ ያደርጋል። 📢 የመጨረሻ መልዕክት! እውነተኛ አላህን የሚፈሩ፣ ሌት ተቀን የሚያቀሩ፣ የሰውን ገንዘብ የማይመኙ ምርጥ ኡስታዞች አሉን፤ አላህ ያብዛቸው፣ ይጠብቃቸውም። ነገር ግን እነዚህን ጥቂት በዝባዦች ማጋለጥና መገሰጽ የሁላችንም ግዴታ ነው። አንቺ የተበደልሽ እህቴ ሆይ! አላህ ላወጣሽው ወጪና ለደከምሽው ድካም ምንዳሽን ይክፈልሽ። በእነዚህ መጥፎ ሰዎች ምክንያት የቁርአንን መንገድ እንዳትተዪው፤ አላህ የተሻለ መምህር ይወፍቅሻል። "እናንተ ያመናችሁ ሆይ! አላህን ፍሩ፤ ከእውነተኞቹም ጋር ሁኑ።" (አል-ተውባህ፡ 119) t.me/Abu_hibetillah_Asselfiy t.me/Abu_hibetillah_Asselfiy

ታላቅ የዳዕዋ እና የገቢ ማሰባሰቢያ ፕሮግራም እናሆ የፊታችን ጁመአ ከምሽቱ 3:00 በመርከዝ ኢብኑ አባስ በታላላቅ የሱና መሻይኾችና ኡስታዞች በአይነቱ ልዩ ፕሮግራም ተዘጋጅቶ እየጠበቃችሁ ነው። በፕ
ታላቅ የዳዕዋ እና የገቢ ማሰባሰቢያ               ፕሮግራም እናሆ የፊታችን ጁመአ ከምሽቱ 3:00 በመርከዝ ኢብኑ አባስ በታላላቅ የሱና መሻይኾችና ኡስታዞች በአይነቱ ልዩ ፕሮግራም ተዘጋጅቶ እየጠበቃችሁ ነው። በፕሮግራሙ ላይ የሚታደሙት ተጋባዥ እንግዶቻችን 1) ሸይኽ አወል አሕመድ (አቡ አማር) ሐፊዘሁሏህ 2) ኡስታዝ ኸድር አሕመድ (አቡ ሐቲም) ሐፊዘሁሏህ 3) ኡስታዝ አብዱል መሊክ ሐፊዘሁሏህ 4) ኡስታዝ አቡ ኢምራን ሐፊዘሁሏህ 5) ኡስታዝ ሙሐመድ አያሌው ሐፊዘሁሏህ 6) አስታዝ ዓሊይ ዩሱፍ (አቡ ሐሳን) ሐፊዘሁሏህ 7) አቡ ኡሰይሚን ሐፊዘሁሏህ 8)ኡስታዝ አብዱል ፈታህ ሐፊዘሁሏህ እና ሌሎችም ስማቸው ያልተጠቀሱ ብርቅዬ የሱና ኡስታዞች ወንድሞችም ፕሮግራሙን ባማረ እና በደመቀ መልኩ ያሳምሩታል። ፕሮግራሙ የሚመሩት              አቡ ዑበይዳ እና አቡ ማሒ             ማሳሰቢያ እንዳትቀሩ (መቅረት አይደለም ማርፈድም አይቻልም)      አድስ ነገርም አለ የሚነገራችሁ (ተናገሪያለሁ ከወዲሁ) ➥በየት ነው የምትገኙት ለምትሉን አድራሻችን ይሄውhttps://t.me/+lmLw2jJXwF45Zjdk        ተቀላቀሉ ሼርም አድርጉ

﴿وَالَّذينَ يَبيتونَ لِرَبِّهِم سُجَّدًا وَقِيامًا﴾

"ሥርዓትን ከማን ተማርክ?" ሲሉት "ሥርዓት ከሌለው ሰው " አለ አሉ። ሥርዓት የሌለው ሰው እውነትም ሥርዓት ያስተምራል። እሱን ባየን ቁጥር እንደርሱ ላለመሆን እንጥራለን። እንደሱ ከመሆንም በአላህ እንጠበቃለን። =

አል-ኸጣቢ "አል-ዑዝላህ"ከተሰኘ ድረሰታቸው የተወሰደ፦ ​"ብቸኝነትን የመረጥኩት ሰዎችን ስለጠላሁ ሳይሆን፣ ልቤን ከአላህ ጋር ለማገናኘትና ራሴን ለመፈተሽ የሚያስችለኝን ሰላም ስላጣሁ ነው። በብቸኝነት ውስጥ የነፍስን ድምጽ መስማት ይቻላል።" አቡ ኡበይዳ t.me/AbuOubeida

🔖ሷሊሆችን ሷሊህ ያስባላቸዉ ወንጀል አለመስራታቸዉ ሳይሆን፦ወንጀል ሰርተዉ ተዉበት ማድረጋቸዉ ፦ወደ አላህ መመለሳቸዉ ነዉ። ~ t.me/https_Asselfya

አንዳንዴ ግን በጣም ከሚገርመኝ ውሸት መካከል ያላንተ መኖር አልችልም ያለ አንቺ መኖር አልችልም ሚለው ቃል ነው እኛ ህይወታቸው ውስጥ ከመኖራችን በፊት እኮ ኖረዋል እኛ ስንኖር ኖረዋል ከኛም ሲለዩ ይኖራሉ ውሀ አየር ወይ ደሞ ምግብ አደለንም ሰው ነን እንመጣለን እንሄዳለን ምንአልባት ብዙ መላመድ ይኖራል ግን ደሞ ማይካድ ሀቅ አለ የእኛ ምንላቸው ቤተሰቦቻችን እንኳን በህይወት ሳይኖሩ ህይወታችን ቀጥሏል

📍አሁን የوَصِيَّةُ ابْنِ قُدَامَة ደርስ በቀጥታ ስርጭት  ሊጀመር ነው ➖➖➖➖➖➖➖➖➖➖ 🎙በአቡ  ሒበቲላህ  ሁሰይን ጀ       መ              ረ https://t.me/tdarna_islam?livestream=48698b8bbed34151dc

ተቀድሟል ካልሄዱበት አሳውቃለሁ ።

አሰላሙአለይኩም ~ አድስ ከኢቶ የመጣሸ እህት ካለሸ ስራ የፈታሸ በ1500ሪያል ነይ የሆነ ስራ አለ @Umu_Abdella_t

▫️ውድ እህቴ ይህ የምትጠይቂው ጥያቄ የብዙ እህቶቻችን የልብ ትርታ፣ የብዙ ቤተሰቦች ጭንቀት ነው። ✔️እህቴ... ምክሬን የምጀምረው «የሴት ልጅ እድሜ እንደ ጤዛ ነው» በሚለው ሀቅ ነው። ጤዛ ተኝቶ
▫️ውድ እህቴ ይህ የምትጠይቂው ጥያቄ የብዙ እህቶቻችን የልብ ትርታ፣ የብዙ ቤተሰቦች ጭንቀት ነው። ✔️እህቴ... ምክሬን የምጀምረው «የሴት ልጅ እድሜ እንደ ጤዛ ነው» በሚለው ሀቅ ነው። ጤዛ ተኝቶ ሲነቁ ይጠፋል፤ የሴት ልጅም ወጣትነትና ውበት እንደዚሁ ነው። እድሜ መቆሚያ የለውም፤ ጊዜው ደግሞ ፈታኝ ነው። እናትሽ የሚጨቀጭቁሽ ይህ «ጤዛነትሽ» እያሳሰባቸው፣ ነገ እድሜሽ ገፍቶ ብቻሽን እንዳትቀሪ ካላቸው የናትነት ፍቅርና ስስት የመነጨ ነው። 🎯ወደ ዋናው ነጥብ ስመጣ፤ «ሁለተኛ መሆንን መፍራትና እንደ ነውር መቁጠር» ውድ እህቴ! ዛሬ ላይ ብዙ ሴቶች «ከሌሎች እህቶች ምን ይጎድለኛል?»፣ «እንዴት ተደራቢ እሆናለሁ?» በሚል ስሜትና በፊልም በተለከፈ አስተሳሰብ ምክንያት ወርቃማ እድሎችን እያበላሹ፣ በመጨረሻም ወይ ፈላጊ በማጣት ወይም የማይሆን ሰው አግብቶ በመጦር ይቆጫሉ። 💭ልንገርሽ ስሚኝ! በድናችን ሁለተኛ ሚስት ማለት ግማሽ ሚስት ወይም ትርፍ ሚስት ማለት አይደለም። ሁለተኛ ሚስት ማለት ልክ እንደ መጀመሪያዋ ሚስት ሙሉ መብት ያላት፣ ክብር ያላት፣ የቤት እመቤት ናት። ሁለተኛ፣ ሶስተኛ ወይም አራተኛ መሆን ነውርም፣ ውርደትም፣ መቀነስም አይደለም። እስቲ ቆም ብለሽ አስቢ፤ እናቶቻችን (የነብዩ ﷺ ሚስቶች)፣ ምርጥ የሆኑት ሶሀብያቶች አብዛኞቹ እኮ ሁለተኛ፣ ሶስተኛና አራተኛ ሆነው ነው የኖሩት። ታዲያ ለእነሱ ያልሆነው ውርደት ለአንቺ እንዴት ውርደት ይሆናል?ይህ ዲን የሰጠሽ መብት እንጂ ባህሉ የሰጠሽ ስም አይደለም። 🎀እህቴ ሆይ! ላንቺ የሚጠቅምሽ ብቸኛ ሚስት ሆኖ ከማይረባና ዲን ከሌለው፣ አላህን ከማይፈራ ሰው ጋር መኖር ወይስ አላህን ከሚፈራ፣ ዲን ካለው፣ ከሚያከብርሽና ከሚንከባከብሽ ሰው ጋር ሁለተኛ ሆኖ በክብር መኖር? ምርጫው ግልፅ ነው። ስንትና ስንት ብቸኛ ነኝ ብለው ያገቡ እህቶች ዛሬ በትዳራቸው ሲሰቃዩ እናያለን። በአንጻሩ ደግሞ ስንትና ስንት በሁለተኛነት የገቡ እህቶች፣ ባሎቻቸው አላህን የሚፈሩ በመሆናቸው ምክንያት የልብ ሰላም አግኝተው፣ ዲናቸውን ጠብቀው ይኖራሉ። አሁን ላይ እድሜሽ በሃያዎች መጨረሻ ላይ ነው። ነገ ወደ ሰላሳዎቹ ስትገቢ ምርጫዎችሽ እየጠበቡ መምጣታቸው አይቀርም። የመጣው ሰው አላህን የሚፈራ፣ ስነ-ምግባሩ ያማረ፣ ሊያስተዳድርሽ አቅም ያለው ከሆነ፤ መስፈርቱን ካሟላ 2ኛ፣ 3ኛ፣ 4ኛም ቢሆን እሺ ብለሽ ማግባት የብልህ ሴት ውሳኔ ነው። 🌟ስለዚህ መፍተሔ ብየ የምመክርሽ፦ ✅️የእናትሽን ምክር ስሚ።እናትሽ "አግቢ" የምትለው ካየችው የህይወት ተሞክሮ ነው። የምትሰሪው ስራ፣ የምታገኘው ደሞዝ፣ የለበስሽው ዘመናዊ ልብስ የባልን ቦታ አይተካም፣ የልጅን ጣም አይሰጥም። ✅️መስፈርትሽን ቀለል አድርጊ።እንዲህ ካልሆነ፣ ካልተማረ፣ ካልከበረ...የሚሉ መስፈርቶችሽን ወደ ጎን ትተሽ፤ ዲን አለው ወይ? አላህን ይፈራል ወይ? ጥሩ ስነ-ምግባር አለው ወይ? የሚለውን ብቻ አጥብቀሽ ያዢ። ✅️ሁለተኛ መሆንን አትጥይ። ሸይጣን የሚያስፈራራሽን ሀሳብ ትተሽ፤ አላህ የፈቀደውን ሀላል አትግፊ። ጥሩ ወንድ ከመጣ አግብቶ የፈታ ነው፣ ወይም ሚስት አለው ብለሽ አትመልሺ። ጨዋና ዲን ያለው ባል በዘመናችን ውድ ነው። ካገኘሽው አትልቀቂው። ✅️ዱዓ አድርጊ። ያ አላህ! ለአንተ ብዬ፣ ዲኔን ለመጠበቅ ብዬ የመጣውን ሀላል ተቀብያለሁና አንተ ደግሞ ህይወቴን አሳምርልኝ፣ ባሌን መልካም አድርግልኝ፣ትዳሬን የተባረከ አድርግልኝ ብለሽ ለምኚው። 💡ውድ እህቴ! ትዳር የኢማን ግማሽ ነው። ግማሽ ኢማንሽን ለመሙላት፣ እራስሽን ከፊትና ለመጠበቅ፣ እናትሽንም ለማስደሰት ስትይ፤ ከመጣው አማራጭ ውስጥ መርጠሽ፣ ቁጥር ሳትቆጥሪ በሀላል ተሳሰሪ። አላህ መልካም፣ ሩህሩህና አላህን ፈሪ የሆነ ባል ይስጥሽ። መጨረሻሽን ያሳምረው። t.me/Sle_qelbachn1 t.me/Sle_qelbachn1

🔖ጣፋጭ ቲላዋ ~ለደረቀው ቀልባችን ~