Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት 的分析概览
频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 335 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 5 641,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 191 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 335 名订阅者。
根据 15 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -80,过去 24 小时变化为 -1,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 22.23%。内容发布后 24 小时内通常能获得 10.47% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 409 次浏览,首日通常累积 1 605 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 22。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።”
凭借高频更新(最新数据采集于 16 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
15 335
订阅者
-124 小时
-117 天
-8030 天
帖子存档
የ2018 ዓ.ም የጥቀት በዓል በጃንሜዳ ተረኛ አዘጋጅ
የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለም እና ደብረ ትጉኀን ቅዱስ ገብርኤል ቤ/ክ
፨፨፨ #በጽዮን ስም የተመሠረቱና ዐቢይ ዓመታዊ ክብረ በዓላቸው ኅዳር 21 የኾኑ፤
✣ርዕሰ አድባራት ወገዳማት አኵሱም ደብረ ጽዮን ማርያም (ከክርስቶስ ልደት 980 ዓመታት በፊት በቀዳማዊ አፄ ምኒልክ ዘመን ታቦቷ የመጣው)
✣ርዕሰ አድባራት ወገዳማት አዲስ ዓለም ደብረ ጽዮን ማርያም (በዳግማዊ አፄ ምኒልክ ተመሠረተች)
✣ዝዋይ ደብረ ጽዮን ማርያም (ደቡብ ሸዋ)
✣ሳዶቅ አምባ ማርያም (በ1670 ዓ.ም በአባ ሳዶቅ የተመሠረተች ፥ ሰሜን ተራሮች)
✣እንፍራንዝ ደብረ ጽዮን ማርያም (ጥንታዊዋ ደብር)
✣ ርዕሰ አድባራት ወገዳማት ደረስጌ ደብረ ጽዮን ማርያም (በወርቅና በዕንቊ ተደርጋ በራስ ውቤ የታነጸች፤ ዳግማዊ አፄ ቴዎድሮስ የነገሠባት፤ ስሜን፣ ራስ ደጀን አጠገብ)
✣ ደብረ ጽዮን ሰላም አድርጊው ቅድስት ማርያም (ባሕርዳር)
✣ ደብረ ማርቆስ ጽርሐ ጽዮን አብማ ማርያም
✣ አውጉስታ ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤ/ክ (አ/አ ጦርኃይሎች)
✣ አርባ ምንጭ ደብረ ጽዮን ማርያም
✣ ደብረ ጽዮን ማርያም (ነቀምት)
✣ ርዕሰ አድባራት ለንደን ደብረ ጽዮን ማርያም (እንግሊዝ ፥ ለንደን)
/በቀጨኔ.ደ.ሰ መድኀኔዓለም ወደብረ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚዲያ እና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ክፍል የተዘጋጀ/
#share
፨Facebook
https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool
፨YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w
፨Telegram
https://t.me/Finotehiwott
፨Tiktok
http://tiktok.com/@finotehiwot
፨Website www.finotehiwotsundayschool.com
#Share #like
መልክአ ማርያም.pdf4.62 MB
#ኅዳር 21
#ጽዮን ማርያም
እንኳን ለኅዳር ጽዮን ማርያም (ጽላተ ኪዳን ወይም ታቦተ ሕጉ) ክብረ በዓል በሰላምና በጤና አደረሳችሁ፤
ኅዳር 21 የታቦተ ጽዮን (ጽላተ ኪዳን ወይም ታቦተ ሕጉ) ዓመታዊ ክብረ በዓል የምናከብረው፤
1.በሊቀ ካህናት ኤሊ ዘመን በሕዝበ አስራኤል ኀጢአት ምክንያት ታቦተ ጽዮን በታሪኳ ለመጀመሪያ ጊዜ በአሕዛብ (ኢሎፍላውያን) እጅ ተማርካ ዳጐን የተባለ የአሕዛብ ጣዖትን ቀጥቅጣ አድቅቃ የተመለሰችበት፡፡ (1ሳሙ. ከ1-6)
2. ታቦተ ጽዮን መፍቀሬ ጥበብ ቅዱስ ሰሎሞን ወዳሠራው ቤተ መቅደስ (በዓለም ላይ እስካሁን ያልታየ ድግስ ደግሶ) የገባችበት፡፡ / (1ኛ ነገ. 8፥2፣ 2ኛ ዜና. 5፥1፣ ስንክሳር ዘሐምሌ 23)
3. በቀዳማዊ ምኒልክ ቀዳማዊ ንጉሥ (ዕብነ ሐኪም) አማካኝነት ታቦተ ጽዮን ወደ ኢትዮጵያ የገባችበት:: (ክብረ ነገሥት፣ መጽሐፈ ምሥጢር፣ መጻሕፍተ ሰሎሞን ወሲራክ አንድምታ መቅድም፣ …)
4. በንጉሥ አፄ ባዜን (በ4 ዓ/ም አካባቢ) አማናዊት ጽዮን ድንግል ማርያም ዋልድባን፣ ደብረ ዐባይን፣…… ሌሎችንም መካናት በስደት ከልጇ ጋር ባርካ አኵስም ጽዮን መጥታ የገባችበትና የባረከችበት፤ በወቅቱም አኵስምና አካባቢዋ በብርሃን ጎርፍ የተጥለቀለቁበት በመኾኑ፤ (ታሪከ ዋልድባ፣ ታሪከ አኵስም፣ ..)
5.በ4ኛው መቶ ክ/ዘመን በቅዱሳን ጻድቃን ነገሥታት አብርሃ ወአጽብሐ አማካኝነት መስዋዕተ ኦሪት ሲሰዋባት የቆየችው አኵስም ጽዮን፤ ጽዮን ማርያም ተብላ 12 መቅደሶች ያሏት በወርቅና በዕንቊ ያሸበረቀች ቤ.ክ ሠርተው ቅዳሴ ቤት የተከበረበትና ክርስትና ብሔራዊ ሃይማኖት ሆኖ የታወጀበት፡፡
6. ነቢያት ስለ እመቤታችን በተለያየ ኅብረ መልክዕና አምሳል (ዕዝራ በሃገር መንፈሳዊት፥ በአምሳለ ብእሲት፤ ሕዝቅኤል በተዘጋች ቤተመቅደስ፤ ዘካርያስ በተቅዋመ ወርቅ፣ ……) ያዩበት
6.1 እረኛው ሔርማ ጻድቅ ቤተ ክርስቲያንን በአምሳለ ብእሲት በራእይ የተመለከተበት
6.2 ቅዱስ ጎርጎርዮስ ገባሬ መንክራት ዘሀገረ ሮሜ የሚዘከርበት
7. በየጊዜው (በዮዲት ጉዲትና በግራኝ አማካኝነት ስትፈርስ) ወደ ዝዋይ፣ ወደ ጣና ቂርቆስ፣ …… ትሰደድ ነበርና:: ተመልሳ ስትታነጽም (ከዮዲት ወረራ በኋላ፤ ከግራኝ ወረራ በኋላ አፄ ፋሲል፤ በአዲስ መልክ አፄ ኃይለ ሥላሴ ካነጹ በኋላ) ቅዳሴ ቤቷ የተከበረው ኅዳር 21 ቀን ስለኾነ ነው።
በሁሉም ቦታ የሚባለውን የኅዳር ፳፩ ሥርዐተ ማኅሌት አቅርበንላችኋል፤ ዚቁንና ወረቡን እንደየደብራችሁ የአቋቋም ይትበሃል ትቆሙ ዘንድ፤ የላይ ቤት በሚቆባቸው አድባራት ዚቅ ዘግምጃ ቤት የሚለውን ተመልከት፤ የታች ቤት በሚቆባቸው አድባራት ዚቅ ዘበዓታ የሚለውን ተመልከት፡፡ በተጨማሪ የሸዋ ወረብን (እንደ አዲስ አለም ማርያምና እንጦጦ ማርያም ባሉት) የሚባለውን አብረን አዘጋጅተነዋል፡፡
/በቀጨኔ.ደ.ሰ መድኀኔዓለም ወደብረ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚዲያ እና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ክፍል የተዘጋጀ/
#share
፨Facebook
https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool
፨YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w
፨Telegram
https://t.me/Finotehiwott
፨Tiktok
http://tiktok.com/@finotehiwot
፨Website www.finotehiwotsundayschool.com
#Share #like
#ጾመ ነቢያት (#የገና ጾም)
፠ ከ7ቱ አጽዋማት (ዐቢይ ጾም፣ ጾመ ፍልሠታ፣ ጾመ ሐዋርያት፣ ጾመ ነቢያት፣ ጾመ ድኅነት፣ ጾመ ነነዌ ና ጾመ ገሃድ) መካከል አንዱ ነው፡፡
፠ ኅዳር 15 ቀን ተጀምሮ እስከ ልደት ለአርባ ሦስት ቀናት የሚጾም ጾም ነው፡፡
፠ ይህንን ጾም በዘመነ ብሉይና በዘመነ ሐዲስ ብዙ ቅዱሳን ጾመውታል፤ በዚህም ምክንያት የሚከተሉት ስያሜዎች አሉት፡፡ እነርሱም፤
፩. ጾመ_አዳም፤ አዳም ዕፀ በለስን በልቶ ከገነት ከተባረረ በኋላ በፈጸመው በደል አዝኖ ተክዞ አለቀሰ (እንባ ቢያልቅበት እዥ እስከሚያፈስ፤ እዥ ቢያልቅበት ደም በዓይኑ እስከሚፈስና ዓይኑ ይቡስ ወይም ደረቅ እስከሚሆን ድረስ አለቀሰ) ፥ ጾመ፣ ጸለየ፡፡ ከልብ የሆነ ጸጸቱን፣ ዕንባውን፣ በራሱ መፍረዱንም እግዚአብሔር አይቶ ተስፋ ድኅነት ሰጠው፡፡ ‹‹ከአምስት ቀን ተኩል በኋላ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ፣ በደጅህ ድኼ፣ በዕፀ መስቀል ተሰቅዬ፣ ሞቼ አድንሃለሁ፡፡›› የሚል ነው፡፡ /ገላ. ፬፥፬፣ መጽ.ቀሌምንጦስ/ ስለዚህ ጾሙ የተሰጠው ተስፋ ፥ የተቆጠረው ሱባኤ ስለተፈጸመበት ‹‹ጾመ አዳም›› ይባላል፡፡
፪. ጾመ_ነብያት፤ ነቢያትም የምሥጢረ ሥጋዌ ነገር ተገልጦ ስለታያቸው፣ ክርስቶስ ለሰው ልጅ የሚከፍለውን የፍቅር ዋጋ በትንቢት ተመልክተው ጾመውታልና ጾመ ነቢያት ይባላል፡፡ ይህ ጾም ከአባታችን አዳም እስከ መጥምቁ ዮሐንስ ድረስ የተነሱ አበውና እናቶች: ድኅነትንና ረድኤትን ሲሹ የጾሙት ጾም ነው:: በተለይ አባታችን አዳም: ቅዱስ ሙሴ: ቅዱስ ኤልያስ፣ ቅዱስ ዳንኤል ና ቅዱስ ዳዊት በጾማቸው የተመሰከረላቸው ቅዱሳን ናቸው:: (ዘዳ 9:19, ነገ. 19:8፣ ዳን. 9:3፣ መዝ. 68:10, 108:24) ቅዱሳን ነቢያት በጭንቅ በመከራ ሆነው የጾሙት ጾም ወደ መንበረ ጸባኦት ደርሶ ወልድን ከዙፋኑ ስቦታል፤ ለሞትም አብቅቶታል::
፫. ጾመ_ሐዋርያት፤ ሐዋርያት ‹‹ትንሣኤን ዐቢይ ጾምን ጾመን እናከብራለን፣ ልደትን ምን ሥራ ሠርተን እናከብረዋለን?›› ብለው ከልደተ ክርስቶስ በፊት ያሉትን ፵፫ ዕለታት ጾመዋልና፡፡
፬. ጾመ_ማርያም፤ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እግዚአብሔር አምላክ ቅድስናዋን አይቶ በቅዱስ ገብርኤል ብሥራት ወልደ አምላክን ያለ ሰስሎተ ድንግልና በግብረ መንፈስ ቅዱስ ጸንሳ እንደምትወልደው ቢነግራትም የትሕትና እናት ናትና ‹‹ምን ሠርቼ የሰማይና ምድርን ፈጣሪ እችለዋለሁ?›› ብላ ጌታን ከመውለዷ አስቀድማ ጾማለችና ‹‹ጾመ ማርያም›› ይባላል፡፡
፭. ጾመ_ፊልጶስ፤ ሐዋርያው ፊልጶስ በአረማውያን ዘንድ ገብቶ እያስተማረ ሳለ በሰማዕትነት ሲሞት፤ አስክሬኑ ከደቀ_መዛሙርቱ ስለተሰወረ፤ እግዚአብሔር የተሰወረውን የመምህራቸውን አስክሬን እንዲገለጽላቸው ከኅዳር ፲፮ ጀምረው ጾመው በሦስተኛው ቀን የመምህራቸው አስክሬን ተመልሶላቸዋል፤ ነገር ግን አስከሬኑ ቢመለስላቸውም ጾሙን ግን እስከ ልደት ቀጥለዋል፡፡
፮. ጾመ_ስብከት፤ የወልደ እግዚአብሔርን ሰው መሆን ያስተማሩበት፥ የሰው ልጆች ተስፋ የተመሰከረበት፥ የምስራች የተነገረበት ስለሆነ ጾመ ስብከትም ይባላል፡፡
፯. ጾመ_ልደት፤ የጾሙ መጨረሻ (መፍቻ) በዓለ ልደት ስለሆነ ‹‹ጾመ ልደት›› ይባላል፡፡
ጾምን ትእዛዝ ስለሆነ ብቻ ሳይሆን የፍቅርና የበረከት ምንጭ በመሆኑ ጭምር ደስ እያለን ብንጾመው የቅዱሳኑ በረከት ያድርብናል፡፡
/በቀጨኔ.ደ.ሰ መድኀኔዓለም ወደብረ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚዲያ እና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ክፍል የተዘጋጀ/
#share
፨Facebook
https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool
፨YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w
፨Telegram
https://t.me/Finotehiwott
፨Tiktok
http://tiktok.com/@finotehiwot
፨Website www.finotehiwotsundayschool.com
#Share #like
የወይራ ሠፈር ኆኅተ ገነት ቅድስት አርሴማ ቤተ ክርስቲያን ሙሉ በሙሉ በእሳት ቀጠሎ ወደመ።
ኅዳር ፲፬/፳፻፲፰ ዓ/ም
በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት በኮሎፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ሥር የወይራ ሠፈር ገነተ ሰማይ ቅድስት አርሴማና መንበረ ብርሃን እጨጌ አቡነ ዮሐንስ ቤተ ክርስቲያን የሚገኝ ሲሆን ዛሬ ሌሊት በእሳት አደጋ ምክንያት የቅድስት አርሴማ ቤተ ክርስቲያን ሙሉ በሙሉ ወድሟል።
የቃጠሎው መነሻ የኤሌክትሪክ መስመር ችግር እንደሆነም የተገለጸ ሲሆን ከታቦቱ በስተቀር ሌሎች ንዋየተ ቅድሳት ሙሉ በሙሉ በአደጋው ምክንያት መውደማቸው ነው የተገለጸው።
ሊያገለግሉበት ሲሄዱ ቦታውን ያጡት ሊስቀድሱበት የገሰገሱበት ቤተ ክርስቲያን በእሳት እንዳልሆነ ሆኖ ሲያዩት ልባቸው የከዳቸው ካህናትና ምእመናን በከፍተኛ ኀዘን ላይ እንደሚገኙም የደረሰን መረጃ ያለመክታል።
አቤቱ ማረን ይቅር በለን!
© የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ
+5
ሥርዐተ ማኅሌት ዘኅዳር ፲፫
በዓለ አዕላፍ መላእክት
✤ ልዩ አዋጅ ዘኅዳር አእላፍ መላእክት ✤
የኅዳር አዕላፍ መላእክት የማኅሌቱ ሥርዐት በዋነኝነት ‹‹የመልክአ አዕላፍን›› የሚከተል ነው፡፡ ነገር ግን እንደ አዲስ አበባ ደብረ ሲና እግዚአብሔር አብ ቤተክርስቲያን ያሉት ደግሞ ‹‹መልክአ እግዚአብሔር አብን›› ይከተላሉ።
በዚህ ሥርዓተ ማኅሌት ውስጥ ‹‹የመልክአ አእላፍ››ን ቁመት የሚቆሙ አድባራት ያስቀደምን ሲሆን በመቀጠልም የአዲስ አበባ ደብረ ሲና እግዚአብሔር አብ ቤተክርስቲያንን ሥርዓተ ማኅሌት አያይዘን አስቀምጠናል።
‹‹የመልክአ አዕላፍ››ን ቁመት የሚቆሙ አድባራት እንደ አጣጣሚ ሚካኤል እና ፊት ሚካኤል ያሉትን ከነዚቆቻቸው አስቀምጠንላችኋል።
✤ መልካም በዓል ይሁንላችሁ✤
#ኅዳር_13_በዓለ_እግዚአብሔር_አብ_ወአእላፍ_መላእክት፤ በደብረ ሲና ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ካቴድራል
፨የዚህ ደብር ታሪክ እንዲህ ነው፤ በደብሩ የሚገኘው የእግዚአብሔር አብ ታቦት #በደብራችን_በቀጨኔ_ደብረ_ሰላም ይገኝ ነበር፤ በታላላቅ አባቶችም ይህ ታቦት ወጥቶ ወደ አሁኑ እግዚአብሔር አብ ቤ.ክ ሥፍራ እንደሚሄድ #የበቁ_አባቶች_ይናገሩ_ነበር፡፡ እንደተናሩትም ሐምሌ 29፤ 1969 ዓ.ም ታቦተ ሕጉ ከቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለም ወጥቶ ወደ ተዘጋጀለት መቃኞ ቤት አረፈ፣ ቤተ_ክርስቲያኑም እራሱን ችሎ እስኪቆም ድረስ የደብራችን የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለም አገልጋዮች #በቅዳሴ፣በማኀሌት እና በሰዓታት ያገለግሉ ነበር ::
ከዚህም በኋላ ጥር 19 ቀን 1971 ዓ.ም የመጀመሪያው ቤተ_ክርስቲያን አልቆ ተመርቋል። የቤተ_ክርስቲያኑ ዲያቆናት ፣ ቀሳውስት እና መሪጌቶችም በጊዜያዊነት ተቀጥረው ነበር ሆኖም የአገልግሎት ፍቅር ያደረባቸው የቀጨኔ ደብረ ሰላም ሊቃውንት አልግሎታቸውን አላቆሙም ነበር። ታላቁ ሊቅ አለቃ ኤልያስ ነቢየ ልዑል ከመኖርያ ቤታቸው ቀጨኔ ድረስ በምጣት ለደብሩ ታላቅ አሰተዋጽዖ አድርገዋል።
እሁን ያለው ሕንፃ ቤ.ክ የደብተራ ኦሪት እና የኖኀ መርከብን ቅርጽ ይዞ በቅድስቱ አካባቢ ያለው አሠራር ደግሞ ክቧን ቤ.ክ ሆኖ ተሰርቶ በ2009 ዓ.ም በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ተመርቋል፡፡ የቅዱስ እግዚአብሔር አብ ታቦትም ኅዳር 13 እልፍ አእላፋት መላእክት በሚከብሩበት ዕለት ይከብራል።
በዚሁ ደብር ኅዳር 25 #የሰማዕቱ_ቅዱስ_መርቆሬዎስ በዓልም ይከበራል ( ታቦቱ በድርብነት አለ)
የእግዚአብሔር ቸርነት የአእላፍ መላእክት ተራዳኢነት አይለየን
/በቀጨኔ.ደ.ሰ መድኀኔዓለም ወደብረ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚዲያ እና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ክፍል የተዘጋጀ/
#share
፨Facebook
https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool
፨YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w
፨Telegram
https://t.me/Finotehiwott
፨Tiktok
http://tiktok.com/@finotehiwot
፨Website www.finotehiwotsundayschool.com
#Share #like#ኅዳር 13
#እንኳን_ለቅዱስ_አግዚአብሔር አብ በዓልና_ለአእላፍ_መላእክት_በዓለ_ሢመት እንዲሁም ቅዱስ_ሚካኤል ለሰው ልጆች ምሕረትን ከኅዳር 12 ጀምሮ እስከ 13 ድረስ ከአምላኩ ምሕረትን ለሚለምንበት በዓል በሰላም አደረሳችኁ፡፡
፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨፨ ፨ ፨፨ ፨ ፨፨ ፨ ፨፨ ፨ ፨፨ ፨
#ኀዳር_13 ቀን በቅድስት ቤተ_ክርስቲያን ሊቃውንት #አእላፍ መላእክት እየተባለ ይጠራል ፤ 99ኙ ነገደ መላእክት በአንድ ላይ የሚከብሩበት ቀን ነው እነዚህም ሥጋ የሌላቸው ረቂቃንና ለዓለም ሁሉ የሚማልዱ ናቸው ፡፡
፨ ፨ ፨፨ ፨ ፨
እግዚአብሔር ቅዱሳን መላእክትን ሲፈጥራቸው በነገድ 100 በክፍለ ነገድ 10 አድርጓቸዋል ፡፡ በ3 ሰማያትና በ10 ዓለማት ላይም ይገኛሉ፡፡ መላእክት ያሉባቸው ከተሞች #ኢዮር #ራማ #ኤረር ይባላሉ ፡፡ አሥሩ ነገዶች ከነአለቆቻቸው አንዲህ ናቸው
1. አጋዕዝት (ቀድሞ አለቃቸው ሳጥናኤል የነበረ ፤ አሁን የተረፉት በቅዱስ ሚካኤል ስር ናቸው)
2. ኪሩቤል (አለቃቸው ቅዱስ #ኪሩብ )
3. ሱራፌል (አለቃችወ ቅዱስ #ሱራፊ ፤ ለበለጠ ኀዳር 24 ይጠብቁን)
4. ኃይላት (አለቃቸው ቅዱስ ሚካኤል )
5. አርባብ (አለቃቸው ቅዱስ ገብርኤል )
6. መናብርት (አለቃቸው ቅዱስ ሩፋኤል)
7. ሥልጣናት (አለቃቸው ቅዱስ ሱርያል )
8. መኳንንት (አለቃቸው ቅዱስ ሰዳካኤል )
9. ሊቃናት (አለቃቸው ቅዱስ ሰላታኤል)
10. መላእክት (አለቃቸው ቅዱስ አናንኤል) ናችው፡፡
ከእነዚህም
፨ አጋዕዝት ፣ኪሩቤል ፣ ሱራፌልና ኃይላት መኖርያቸው በኢዮር(3ኛው ሰማይ ) ነው ፡፡
፨አርባብ ፣መናብርትና ሥልጣናት መኖርያቸው በራማ ነው ፡፡
፨መኳንንት ፣ሊቃናትና መላእክት ደግሞ የሚኖሩት በኤረር ነው (1ኛው ሰማይ )
፨ ፨ ፨፨ ፨ ፨፨ ፨ ፨
(ከእልፍ አእላፋት አለቃዎች ስሞች በጥቂቱ)፡፡ ጸሎትነ ትብጻሕ (ሰላም ለክሙ) ለመላእክተ ምሕረት፤
#ሚካኤል_ወገብርኤል፥
#ሱራፌል_ወኪሩቤል(፬ቱ እንስሳ)፥
#ዑር(ራ)ኤል_ወሩፋኤል (፳፬ቱ ካህናተ ሰማይ)፥
#ሱርያል_ወፋኑኤል፥
#አፍኒን_ወራጕኤል፥
#ሳቁኤል_ወአቅናኤል፥
#ብርናኤል_ወሱባኤል፥
#ፍናኤል_ወሰላታኤል፥
#ሰዳካኤል_ወኤልናኤል፥
#አናንኤል_ወኢየሩማኤል፥
#ግርማኤል_ወድርማኤል ፥
#ድማህኤል_ወአድማኤል፥
#ሙራኤል_(ምናቴር_አብያቴር)፥
#ሱታ(ስቱ)ኤል_ወሱርያል፤ ……. ፨
፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨
የመላእክት ተፈጥሮ እመኀበ አልቦ ኀበ ቦ (ካለመኖር ወደመኖር ) ነው ፡፡ አይራቡም አይጠሙም ፤አይዋለዱም ፣ አይሞቱም ፣ ዕረፍት የላቸውም ፤ምስጋናቸው እረፍታቸው ፤እረፍታቸው ምስጋናቸው ነው እንጂ(አኮቴቶሙ ዕረፍቶሙ ወዕረፍቶሙ አኮቴቶሙ) እንዲል፡፡ ተፈጥሯቸው እጅግ ረቂቅ ነው፡፡ ተግባራቸውም ዘወትር እግዚአብሔርን ማመስገን ነው፡፡
#መላአክ ማለት ተላላኪ (አገልጋይ ) ነውና ከፈጣሪ ወደ ሰው ልጆች ለምሕረትም ፤ ለመዓትም ይላካሉ፡፡ ምሕረትን ያወርዳሉ ፡፡ ልመናን ያሳርጋሉ ቅጡ ሲባሉም ይቀጣሉ እንደዚሁም ሁሉ ወቅትንም የሚቆጣጠሩ አሉ ፤ ስለ ሰው ልጆች ይማልዳሉ (ዘካ 1÷12 ) ምሥጢርም የሚገልፁም አሉ(ዳን 9÷21) መላእክት ተራዳኢም ናቸው (ኢያ 5÷13)፣
እንዳንሰናከል ይጠብቁናል (መዝ 90÷11 ) ፣ያድናሉ ( መዝ 33÷7 ) ፣የፀጋ ስግደትም ይገባቸዋል (መሳ 13÷20)፣ በፍርድ ቀንም ኀጥአንን ከጻድቃን ያለያያሉ (ማቴ 25 ÷31) እነሆ እግዚአብሔር ይፈርድ ዘንድ ቅዱሳን መላእክቶቹን አስከትሎ ይመጣል እንዲል ፡፡
፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨
እልፍ አእላፋት ወትእልፊት ቅዱሳን ንጹሐን መላእክት ቆሙ በአገልግሎት ጸንተው በአንድነት ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ አምላክ በማለት፡፡
ምልጃቸው እና ጠብቆታቸው አይለየን አሜን ፡፡
፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨ ፨
ኀዳር 13 ክብረ በዓሉ ከሚከበርባቸው ቦታዎች ጥቂቶቹን እነሆ
1. ግሸን ደብረ ከርቤ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ቤ/ክ (መስቀሉ የሚገኝበት)፤
2. ጠዳ ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ቤ/ክ (ጎንደር፤ ከ44ቱ ታቦታተ ጎንደር አንዱ)፤
3. ጎርዶማ እግዚአብሔር አብ ቤ/ክ
(በሰሜን ሸዋ)፤
4. ደብረ ሲና ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ቤ/ክ (አዲስ አበባ)፤
5. ቦሌ ኆኅተ ብርሃን ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ቤ/ክ (አዲስ አበባ)
6. ቦሌ ቡኒ ደብረ ቤቴል ቅዱስ እግዚአብሔር አብ ቤ/ክ (አዲስ አበባ)
/በቀጨኔ.ደ.ሰ መድኀኔዓለም ወደብረ.ት.ቅ.ገብርኤል ቤ.ክ ፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚዲያ እና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ክፍል የተዘጋጀ/
#share
፨Facebook
https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool
፨YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w
፨Telegram
https://t.me/Finotehiwott
፨Tiktok
http://tiktok.com/@finotehiwot
፨Website www.finotehiwotsundayschool.com
#Share #like
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
