Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት 的分析概览
频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 369 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 5 619,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 193 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 369 名订阅者。
根据 24 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -18,过去 24 小时变化为 1,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 23.10%。内容发布后 24 小时内通常能获得 8.16% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 551 次浏览,首日通常累积 1 254 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 22。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።”
凭借高频更新(最新数据采集于 25 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
15 369
订阅者
+124 小时
+477 天
-1830 天
帖子存档
በኦሮምያ ክልል በምዕራብ አርሲ ዞን ሻሸመኔና አካባቢው; በጅማ በምሥራቅ አርሲ አሰላ በምዕራብ ሐረርጌ ጭሮ በደቡብ ምዕራብ ሸዋ አዲስ አበባ አዋሳኝ ከተሞች በሃይማንታቸው ምክንያት በእሥር ላይ የሚገኙ ምእመናን ምግብና ውሃ እንዳያገኙ ተደርገዋል።
++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++
"ሕገ ወጡን ቡድን በሃይማኖት አባትነት ተቀበሉ በነፍሳችሁ ላይ ሹሟቸው" በሚል በኦሮምያ ክልል በምዕራብ አርሲ ዞን ሻሸመኔና አካባቢው; በጅማ በምሥራቅ አርሲ አሰላ በምዕራብ ሐረርጌ ጭሮ የሃይማኖት አባቶቻችን; የወረዳ ሊቃነ ካህናት; የአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች የሰበካ ጉባኤ አመራሮች ሰባክያንና ዲያቆናት እንዲሁም ወጣቶች በሃይማንኖቸው ምክንያት በጸጥታ ኃይሎች እየታደኑና እየታፈሱ በእሥር ላይ ይገኛሉ።
ከየአህጉረ ስብከቱ በሚደርሱን መረጃዎች ምእመናን ምግብና ውሃ እንዳያገኙ ተደርገዋል። በሀገራችን ሕገ መንግሥትና ኢትዮጵያ በፈረመቻቸው ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ድንጋጌዎች በሕግ ጥላ ሥር የሚገኙ ዜጎች ሕጋዊ መብታቸው ሊጠበቅ ይገባል። አስተያየት ሰጪዎች ከሕግ ውጪ በቤተመቅደሳቸው ደጃፍ የተገደሉብን ኃዘን ሳያንስ የሃይማኖት አባቶቻችንና ቤተሰቦቻችን በግፍ ታሥረውብናል ሲሉ አስተያየት ሰጥተውናል። የሰብአዊ መብት ኮሚሽንና የሕዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም ኃላፊዎችን ለማግኘት ያደረግነው ጥረት አልተሳካም።
EOTC TV
+++++++++++++++++++++++++++++++++++++++
በኮምቦልቻ ከተማ ሕገ ወጡ ደም አፍሳሽ ቡድን ወደ ከሚሴ ለማምራት ገብቷል የሚል መረጃ በከተማው በመሰራጨቱ ከፍተኛ የሆነ የህዝ ቁጣ ቀስቅሷል!
ሕገ ወጡ ቡድን ወደ ከሚሴ ለማምራት በኮምቦልቻ አየር ማረፊያ በከሰአት በረራ ከተማው ውስጥ ገብተዋል የሚል መረጃ በከተማዋ በመሰራጨቱ የአብያተ ክርስቲያናት ደውል በከተማዋ ተደውለዋል።
ተሚማ ጉዳዩን ለማጣራት ባደረገችው ጥረት በከተማዋ በከሰአት በረራ የገቡት የተለያዩ ከፍተኛ የመንግስት ባለ ስልጣናት እንደሆኑ ማረጋገጥ ቢቻልም ነገር ግን የቤተ ክርስቲያኗን ልብስ አውልቀው ከማኅበረሰቡ ጋር ተቀላቅለው ገብተዋል የሚል ስጋት በመፈጠሩ የከተማዋ ነዋሪ በቁጣ ወደ አደበባዮች እና ወደ አብያተ ክርስቲያናት ወጥቷል።
በአሁን ሰአት በሁሉም አብያተ ክርስቲያናት ጸሎት እና ትምህርተ ወንጌል እየተሰጠ ይገኛል።
ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ እና ብፁዕ አቡነ ያዕቆብ በሻሸመኔ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን በትናንትናው ዕለት በጸጥታ ኃይሎች በተወሰደው እርምጃ የተጎዱ ምእመናንን ጎብኙ።
ጥር 28 ቀን 2015 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)
++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++
የሻሸመኔ ኦርቶዶክሳውያን በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ መሰረት የሕገ ወጡን ቡድን ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን አናስገባም በማለት ቅጽራቸውን ሲጠብቁ ቢውሉም ለሕገ ወጡ ቡድን ከለላ የሰጠው የጸጥታ ኃይል በንጹሃን ላይ እርምጃ መውሰዱ ይታወቃል።
በዚህም ሰማዕትነትን የተቀበሉ ምእመናን እንዳሉ ሁሉ በርካቶች ከፍታኛ እና ቀላል ጉዳት ደርሶባቸው ወደ ሐዋሳ የተለያዩ ሆስፒታሎች ተወስደዋል።
እስካሁን ባለን መረጃም በሐዋሳ ሪፈራል ሆስፒታል 6፣ በያኔት ሆስፒታል፣ በአላቲዮን ሆስፒታል 8 ምእመናን ሕክምና እየተደረገላቸው ይገኛሉ።
የሲዳማ፣ ጌዲዮ፣ አማሮ፣ ቡርጂና ምዕራብ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ እና ብፁዕ አቡነ ያዕቆብ የጆርጂያና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እነዚህን ምእመናን በሐዋሳ በመገኘት አጽናንተዋል፤ ሀዘናቸውንም ገልጸዋል ሲል የማኅበረ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት ዘግቧል።
በኦሮሚያ ያለችውን ቤተ ክርስቲያን በኃይል እየተቆጣጠረ የሚገኘው ሽብርተኛውና ወራሪው ስብስብ በሻሸመኔ ከተማ 35 ምዕመናንን በከባድ መሳሪያ በማስጨፍጨፍ በዛሬው ዕለት ወደ ሻሸመኔ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን በመግባት ፎቶ የመነሳት መርሐግብር ማካሄዱን ለመገንዘብ ተችሏል !
በምዕራብ አርሲና በሌሎች አካባቢዎች በየአብያተ ክርስቲያናቱ ፎቶ ትነሱ ይሆናል እንጂ ያስጨፈጨፋችሁት እና የልጆቹን ደም ረግጣችሁ በመግባት የቀለዳችሁበት ኦርቶዶክሳዊ ምዕመን የደረሰበትን ሰቆቃ መቼውንም አይረሳውም !
ለሕግ የበላይነት በእጅጉ እቆረቆራለሁ የሚለው የኢትዮጵያ መንግስት ሽብርተኞችን እና ወራሪዎችን መደገፍ ሊያቆም ይገባል !
ቅዱስ ሲኖዶስ በነነዌ ጾም የሚከናወነውን ሥርዓተ ጸሎት አስመልክቶ መግለጫ ሰጠ፡፡
በጾመ ነነዌ የሚከናወነውን ሥርዓተ ጸሎት አስመልክቶ ቅዱስ ሲኖዶስ አሁን መግለጫ ሰጥቷል፤ በዚህም የምእመናን ድርሻ ምን እንደሆነ ተገልጿል፡፡
ሁሉም ምእመናን እና ምእመናት በጾመ ነነዌ በሦስቱም ቀናት ጥቁር ልብስ መልበስ፣ በጸሎት መርሐ ግብሩ ተገኝቶ ጸሎት መጸለይ እና የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን እና የአባቶችን መልእክት ሰምቶ መተግበር እንደሚገባው ቅዱስ ሲኖዶስ ዛሬ በሰጠው መግለጫ አሳውቋል፡፡
የጸሎት መርሐ ግብሩም ጠዋት ኪዳን እና ምሕላ፣ ቅዳሴ፣ የሰርክ የዐውደ ምሕረት መርሐ ግብር እንዲሁም ማታ የቤተሰብ ጸሎት ናቸው፡፡
በመጨረሻም ምእመናን ለጸሎት ወደ ቤተ ክርስቲያን በሚሄዱበት ጊዜ ለጸሎት ከሚያስፈልጉ መጽሐፍት ውጪ ሌላም ምንም ዓይነት መፈክር ይዞ መምጣት የማይቻል መሆኑን አስረድተዋል።
++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++
ቤተ ክርስቲያን መብት እንዲያስከብር ስትጠይቅ በዝምታ የሰነበተው መንግሥት ከደቂቃዎች በፊት ከሳሽ ሆኖ መግለጫ አውጥቷል።
የኢፌዴሪ የመንግሥት ጉዳዮች ኮሙዩኒኬሽን በዛሬው ዕለት ባወጣው መግለጫ ተቋማት አንድነታቸውን ጠብቀው እንዲዘልቁ የሚጠበቅበትን ሲወጣ ቆይቷል ብሏል።
ነገር ግን ደስ ሲላቸው ሀገር ናት እያሉ የሚያንቆለጳጵሷት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን አንድነቴ ላይ ፈተና ተደቅኗል ብላ አንድነቷን ለመሸርሸር የሞከሩ አካላት ላይ እርምጃ እንዲወስድ ብትጠይቅም ጆሮ አልሰጣትም። ጠቅላይ ሚኒስትሩም ሕግ የማስከበር ፍላጎት እንደሌላቸው በጥር 23ቱ ንግግራቸው ገልጸዋል።
ሌላው በዛሬው መግለጫ መንግሥት የተፈጠረው ጉዳይ በውይይት እንዲፈታ መክሯል። መልሶ ደግሞ በቤተ ክርስቲያኗ ሥርዓት መሠረት ይላል። ይህ ጉዳይ የቤተ ክርስቲያኗን መመሪያ ካለመረዳት የመነጨ ይመስላል።
ቤተ ክርስቲያን በሥርዓቷ መሠረት በጉዳዩ ላይ ቀኖናዊ ውሳኔ በመወሰን ችግር ፈጣሪዎቹን ለይታለች። ቀጥሎ የሚደረገው የሚያደርጉት ሕገ ወጥ እንቅስቃሴ መንግሥት እንዲያስቆም መጠየቅ ነው። ነገር ግን ዛሬ ከሳሽ ሆኖ የመጣው መንግሥት ያንን ለማድረግ ፈቃደኛ አልሆነም። ሁለት እኩል ኃይላት እንደሆኑ በማስመሰል ተወያዩ ማለት አሳዛኝ ነው። ቅዱስ ሲኖዶስም በጥር 24ቱ መግለጫ ይህንኑ አሳውቋል።
ሌላውና በመጨረሻ ልናነሳ የወደድነው ሚዲያዎች ችግሩን የሚያባብሱ ነገሮችን ከማቅረብ መቆጠብ አለባቸው ያለውን ነው።
ነጻ ሆነው እንዲዘግቡ ኃላፊነት ያለባቸው የመንግሥት ሚዲያዎች በጉዳዩ ላይ ትንፍሽ ሳይሉ ሰንብተው ዛሬ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን መግለጫን ለመዘገብ መጣደፋቸው ያስተዛዝባል። ከዚያ በተለየ መልኩ ግን ቤተ ክርስቲያን ላይ የደረሰውን ነገር ከቤተ ክርስቲያኗ ሚዲያዎች ጀምረው የተለያዩ የሀገር ውስጥና የውጪ ሀገር ሚዲያዎች ከፍተኛ ሽፋን ሰጥተውታል። የተፈጠረውን ነገር አትዘግቡ የማለት አምባገነንነት ወዴት ያደርሰን ይሆን?
አስቸኳይ መረጃ፡፡፡
የመንግስት አካላት ዛሬ እሑድ 4ስዓት ተደራደሩ ወይም ለሕገ ወጡ ቡድን ንብረት አስረክቡ ብለው አባቶችን እያስገደዱ ይገኛሉ።
_---------
በምዕራብ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት በጭሮ/አሰበ ተፈሪ ከተማ በሕገ ወጥ የተሾሙት አካላት በጥር 27/2015 ዓ/ም እንደሚመጡ በቂ መረጃ ለሕቡ ሰለደረሰ ምዕመናን ቤተ ክርስቲያናቸውን ከሕገ ወጦች ወረራ በንቃት እንዲጠብቁ ብሎ ቅዱስ ሲኖዶስ ባስተላለፈው መመሪያ መሠረት በከተማው የሚገኙትን 4 አብያተ ክርስቲያናት በንቃት እየጠበቀ መዋሉ ማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን መዘገቡ ይታወቃል፡፡
ከቀኑ 11፡45 ስዓት ላይ የመጡት ሕገወጥ ቡድን ለመንግሥት አካል እንደማይመለሱ ሲነግሩት ሙሉ ወጪ ችሎ እንዲያድሩ አድርጓል። በዚህ መሀል 10 የማይሞሉ ዱላ ይዘው እየዘፈኑ ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲመጡ እነሱን ትቶ ቤተክርስቲያ እየጠበቁ ባሉት ላይ ተኩስ ተከፈተ።
በተኩስና አስለቃሽ ጭስ እስከ 2ስዓት ምዕመናን ሲያዋክብም አምሽቷል፡፡ ቤተ ክርስቲያንን ሙሉ ከበው ህዝቡን በተኩስ፣ አስለቃሽ ጭስ፣ በዱላ እያሰቃዩ ሙሉ ህዝቡን እንዳስወጡና የሀገረ ስብከት ስራ አስኪያጅ አንዳንድ የመምሪያ ሓላፊዎች ሞታችን በልደታ ብለው ግቢ ውስጥ ቀርተዋል፡፡
እስከምሽቱ 4ስዓት ላይም ቤተክርስቲያን ማን እንደሚገባ መመሪያ ከመንግስት እንጠብቃለን ብለው ከቆዩ በኋላ እና 5 ሰዓት ላይ ከሆቴል ጠርተው ሕገወጡን ቡድን አስገብተዋል፡፡ የጸጥታ እና የመንግስት አካላት ዛሬ እሑድ 4ስዓት ተደራደሩ ወይም ለሕገ ወጡ ቡድን ንብረት አስረክቡ ብለው አባቶችን እያስገደዱ ይገኛሉ።
አባቶች ግን በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ የምንመራ እንጂ በግል ምንወስነው አይደለም ብለዋል።
የጸጥታ ኃይሎች ተደራድረው ገብተዋል ለማለት ሥራ አስኪያጁን ጨምሮ የመምሪያ ኃላፊዎችን አስገድደው ፎቶ ለማንሳት ሲሞክሩ እንደነበረ ለማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን መረጃውን ያደረሱን ገልጸዋል።
ጅማ ደብረ መዊዕ መድኃኔዓለም ሙሉ ለሙሉ በኦሮሚያ ልዩ ኃይል ተሰብሯል። የደብሩን ካህናት፣ ዲያቆናትና ወጣቶችን ወደ ወረዳ 2 ፖሊስ ጣቢያ ወስደው አስረዋቸዋል።
ዛሬ በሻሸመኔ የተከሰተው ነገ በጅማ እንዳይፈጠር ሥጋት ላይ መሆናቸውን ምእመናን ገልጸዋል።
ጅማ ደብረ/መዊ/መድኀኔዓለም ቤተክርስቲያን በአሁኑ ሰዓት የጸጥታ ኀይሎች በራሳቸው ጉልበት ጊቢ ውስጥ ገብተው ይገኛሊ ። አንዲሁም በአከባቢው ያሉትን ወጣቶችን አፍሰው እየወሰዱ ይገኛል።
ነገ በ28 ከጠዋቱ 5 ሰዓት ላይ አዲሱን ጳጳስ የአካባቢው ምእመና ን እንዲቀበሉ እያስገደዱ የሚቃወሙትን ደግሞ እያሰሩ ነው።
ጅማ ደብረ/መዊ/መድሐኒዓለም ቤተክርስቲያን በአሁኑ ሰዓት ፖሊሶች በራሳቸው ጉልበት ጊቢውስጥ ገብተው ይገኛል አንዲሁም በአከባቢው ያሉትን ወጣቶችኝ ቤተክርስቲያንን የሚጠብቅትን በሙሉ አፍሰው እየወሰዱ ይገኛል። በመሆኑ ይህ መልዕክት ህዝበ ክርስቲያኖች በሙሉ ለሁሉም ህዝብ እንድታስተላልፊ በእግዚዓብሔር ሰም እጠይቃችሁለው አንድ የሀይማኖታችን ግዴታ ነው።
ነገ በ28 ከጠዋቱ 5 ሰዓት ላይ አዲሱ ጳጳስ በግድ በጉልበት እንድንቀበለው ብለው ከአሁኑ የሚቃወሙትን ወደ እስር ቤት እያስገቡ ነው። ከአሁን ሰዓት ጀምሮ እራሳቹን አዘጋጁ ለሀይማኖታችኝ መቆም አለብን።
ነገ ከለሊቱ 12 ሰዓት ጀምሮ ከደብረ/መዊ/መድሐኒዓለም ቤተክርስቲያን እንድትገኙ በእግዚአብሔር ስም ጥያቄያችንን እናስተላልፋለን።
ሼር አድርጉ
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
