uz
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Kanalga Telegram’da o‘tish

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት analitikasi

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 369 obunachidan iborat bo'lib, Din & Maʼnaviyat toifasida 5 619-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 193-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 369 obunachiga ega bo‘ldi.

24 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni -18 ga, so‘nggi 24 soatda esa 1 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 23.10% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 8.16% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 3 551 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 1 254 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 22 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 25 Iyun, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & Maʼnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 369
Obunachilar
+124 soatlar
+477 kunlar
-1830 kunlar
Postlar arxiv
በኦሮምያ ክልል በምዕራብ አርሲ ዞን ሻሸመኔና አካባቢው; በጅማ በምሥራቅ አርሲ አሰላ በምዕራብ ሐረርጌ ጭሮ በደቡብ ምዕራብ ሸዋ አዲስ አበባ አዋሳኝ ከተሞች በሃይማንታቸው ምክንያት በእሥር ላይ የሚገኙ ምእመናን ምግብና ውሃ እንዳያገኙ ተደርገዋል። ++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++ "ሕገ ወጡን ቡድን በሃይማኖት አባትነት ተቀበሉ በነፍሳችሁ ላይ ሹሟቸው" በሚል በኦሮምያ ክልል በምዕራብ አርሲ ዞን ሻሸመኔና አካባቢው; በጅማ በምሥራቅ አርሲ አሰላ በምዕራብ ሐረርጌ ጭሮ የሃይማኖት አባቶቻችን; የወረዳ ሊቃነ ካህናት; የአድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች የሰበካ ጉባኤ አመራሮች ሰባክያንና ዲያቆናት እንዲሁም ወጣቶች በሃይማንኖቸው ምክንያት በጸጥታ ኃይሎች እየታደኑና እየታፈሱ በእሥር ላይ ይገኛሉ። ከየአህጉረ ስብከቱ በሚደርሱን መረጃዎች ምእመናን ምግብና ውሃ እንዳያገኙ ተደርገዋል። በሀገራችን ሕገ መንግሥትና ኢትዮጵያ በፈረመቻቸው ዓለም አቀፍ የሰብአዊ መብት ድንጋጌዎች በሕግ ጥላ ሥር የሚገኙ ዜጎች ሕጋዊ መብታቸው ሊጠበቅ ይገባል። አስተያየት ሰጪዎች ከሕግ ውጪ በቤተመቅደሳቸው ደጃፍ የተገደሉብን ኃዘን ሳያንስ የሃይማኖት አባቶቻችንና ቤተሰቦቻችን በግፍ ታሥረውብናል ሲሉ አስተያየት ሰጥተውናል። የሰብአዊ መብት ኮሚሽንና የሕዝብ እንባ ጠባቂ ተቋም ኃላፊዎችን ለማግኘት ያደረግነው ጥረት አልተሳካም። EOTC TV +++++++++++++++++++++++++++++++++++++++

በኮምቦልቻ ከተማ ሕገ ወጡ ደም አፍሳሽ ቡድን ወደ ከሚሴ ለማምራት ገብቷል የሚል መረጃ በከተማው በመሰራጨቱ ከፍተኛ የሆነ የህዝ ቁጣ ቀስቅሷል! ሕገ ወጡ ቡድን ወደ ከሚሴ ለማምራት በኮምቦልቻ አየር ማረፊያ በከሰአት በረራ ከተማው ውስጥ ገብተዋል የሚል መረጃ በከተማዋ በመሰራጨቱ የአብያተ ክርስቲያናት ደውል በከተማዋ ተደውለዋል። ተሚማ ጉዳዩን ለማጣራት ባደረገችው ጥረት በከተማዋ በከሰአት በረራ የገቡት የተለያዩ ከፍተኛ የመንግስት ባለ ስልጣናት እንደሆኑ ማረጋገጥ ቢቻልም ነገር ግን የቤተ ክርስቲያኗን ልብስ አውልቀው ከማኅበረሰቡ ጋር ተቀላቅለው ገብተዋል የሚል ስጋት በመፈጠሩ የከተማዋ ነዋሪ በቁጣ ወደ አደበባዮች እና ወደ አብያተ ክርስቲያናት ወጥቷል። በአሁን ሰአት በሁሉም አብያተ ክርስቲያናት ጸሎት እና ትምህርተ ወንጌል እየተሰጠ ይገኛል።

ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ እና ብፁዕ አቡነ ያዕቆብ በሻሸመኔ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን በትናንትናው ዕለት በጸጥታ ኃይሎች በተወሰደው እርምጃ የተጎዱ ምእመናንን ጎብኙ። ጥር 28 ቀን 2015 ዓ.ም (ተ.
ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ እና ብፁዕ አቡነ ያዕቆብ በሻሸመኔ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን በትናንትናው ዕለት በጸጥታ ኃይሎች በተወሰደው እርምጃ የተጎዱ ምእመናንን ጎብኙ። ጥር 28 ቀን 2015 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ) ++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++ የሻሸመኔ ኦርቶዶክሳውያን በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ መሰረት የሕገ ወጡን ቡድን ወደ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን አናስገባም በማለት ቅጽራቸውን ሲጠብቁ ቢውሉም ለሕገ ወጡ ቡድን ከለላ የሰጠው የጸጥታ ኃይል በንጹሃን ላይ እርምጃ መውሰዱ ይታወቃል። በዚህም ሰማዕትነትን የተቀበሉ ምእመናን እንዳሉ ሁሉ በርካቶች ከፍታኛ እና ቀላል ጉዳት ደርሶባቸው ወደ ሐዋሳ የተለያዩ ሆስፒታሎች ተወስደዋል። እስካሁን ባለን መረጃም በሐዋሳ ሪፈራል ሆስፒታል 6፣ በያኔት ሆስፒታል፣ በአላቲዮን ሆስፒታል 8 ምእመናን ሕክምና እየተደረገላቸው ይገኛሉ። የሲዳማ፣ ጌዲዮ፣ አማሮ፣ ቡርጂና ምዕራብ አርሲ አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ዮሴፍ እና ብፁዕ አቡነ ያዕቆብ የጆርጂያና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እነዚህን ምእመናን በሐዋሳ በመገኘት አጽናንተዋል፤ ሀዘናቸውንም ገልጸዋል ሲል የማኅበረ ቅዱሳን ብሮድካስት አገልግሎት ዘግቧል።

በኦሮሚያ ያለችውን ቤተ ክርስቲያን በኃይል እየተቆጣጠረ የሚገኘው ሽብርተኛውና ወራሪው ስብስብ በሻሸመኔ ከተማ 35 ምዕመናንን በከባድ መሳሪያ በማስጨፍጨፍ በዛሬው ዕለት ወደ ሻሸመኔ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን በመግባት ፎቶ የመነሳት መርሐግብር ማካሄዱን ለመገንዘብ ተችሏል ! በምዕራብ አርሲና በሌሎች አካባቢዎች በየአብያተ ክርስቲያናቱ ፎቶ ትነሱ ይሆናል እንጂ ያስጨፈጨፋችሁት እና የልጆቹን ደም ረግጣችሁ በመግባት የቀለዳችሁበት ኦርቶዶክሳዊ ምዕመን የደረሰበትን ሰቆቃ መቼውንም አይረሳውም ! ለሕግ የበላይነት በእጅጉ እቆረቆራለሁ የሚለው የኢትዮጵያ መንግስት ሽብርተኞችን እና ወራሪዎችን መደገፍ ሊያቆም ይገባል !

ቅዱስ ሲኖዶስ በነነዌ ጾም የሚከናወነውን ሥርዓተ ጸሎት አስመልክቶ መግለጫ ሰጠ፡፡ በጾመ ነነዌ የሚከናወነውን ሥርዓተ ጸሎት አስመልክቶ ቅዱስ ሲኖዶስ አሁን መግለጫ ሰጥቷል፤ በዚህም የምእመናን ድርሻ ምን እንደሆነ ተገልጿል፡፡ ሁሉም ምእመናን እና ምእመናት በጾመ ነነዌ በሦስቱም ቀናት ጥቁር ልብስ መልበስ፣ በጸሎት መርሐ ግብሩ ተገኝቶ ጸሎት መጸለይ እና የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን እና የአባቶችን መልእክት ሰምቶ መተግበር እንደሚገባው ቅዱስ ሲኖዶስ ዛሬ በሰጠው መግለጫ አሳውቋል፡፡ የጸሎት መርሐ ግብሩም ጠዋት ኪዳን እና ምሕላ፣ ቅዳሴ፣ የሰርክ የዐውደ ምሕረት መርሐ ግብር እንዲሁም ማታ የቤተሰብ ጸሎት ናቸው፡፡ በመጨረሻም ምእመናን ለጸሎት ወደ ቤተ ክርስቲያን በሚሄዱበት ጊዜ ለጸሎት ከሚያስፈልጉ መጽሐፍት ውጪ ሌላም ምንም ዓይነት መፈክር ይዞ መምጣት የማይቻል መሆኑን አስረድተዋል። ++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++++

ቤተ ክርስቲያን መብት እንዲያስከብር ስትጠይቅ በዝምታ የሰነበተው መንግሥት ከደቂቃዎች በፊት ከሳሽ ሆኖ መግለጫ አውጥቷል። የኢፌዴሪ የመንግሥት ጉዳዮች ኮሙዩኒኬሽን በዛሬው ዕለት ባወጣው መግለጫ ተቋማት አንድነታቸውን ጠብቀው እንዲዘልቁ የሚጠበቅበትን ሲወጣ ቆይቷል ብሏል። ነገር ግን ደስ ሲላቸው ሀገር ናት እያሉ የሚያንቆለጳጵሷት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን አንድነቴ ላይ ፈተና ተደቅኗል ብላ አንድነቷን ለመሸርሸር የሞከሩ አካላት ላይ እርምጃ እንዲወስድ ብትጠይቅም ጆሮ አልሰጣትም። ጠቅላይ ሚኒስትሩም ሕግ የማስከበር ፍላጎት እንደሌላቸው በጥር 23ቱ ንግግራቸው ገልጸዋል። ሌላው በዛሬው መግለጫ መንግሥት የተፈጠረው ጉዳይ በውይይት እንዲፈታ መክሯል። መልሶ ደግሞ በቤተ ክርስቲያኗ ሥርዓት መሠረት ይላል። ይህ ጉዳይ የቤተ ክርስቲያኗን መመሪያ ካለመረዳት የመነጨ ይመስላል። ቤተ ክርስቲያን በሥርዓቷ መሠረት በጉዳዩ ላይ ቀኖናዊ ውሳኔ በመወሰን ችግር ፈጣሪዎቹን ለይታለች። ቀጥሎ የሚደረገው የሚያደርጉት ሕገ ወጥ እንቅስቃሴ መንግሥት እንዲያስቆም መጠየቅ ነው። ነገር ግን ዛሬ ከሳሽ ሆኖ የመጣው መንግሥት ያንን ለማድረግ ፈቃደኛ አልሆነም። ሁለት እኩል ኃይላት እንደሆኑ በማስመሰል ተወያዩ ማለት አሳዛኝ ነው። ቅዱስ ሲኖዶስም በጥር 24ቱ መግለጫ ይህንኑ አሳውቋል። ሌላውና በመጨረሻ ልናነሳ የወደድነው ሚዲያዎች ችግሩን የሚያባብሱ ነገሮችን ከማቅረብ መቆጠብ አለባቸው ያለውን ነው። ነጻ ሆነው እንዲዘግቡ ኃላፊነት ያለባቸው የመንግሥት ሚዲያዎች በጉዳዩ ላይ ትንፍሽ ሳይሉ ሰንብተው ዛሬ የመንግሥት ኮሙኒኬሽን መግለጫን ለመዘገብ መጣደፋቸው ያስተዛዝባል። ከዚያ በተለየ መልኩ ግን ቤተ ክርስቲያን ላይ የደረሰውን ነገር ከቤተ ክርስቲያኗ ሚዲያዎች ጀምረው የተለያዩ የሀገር ውስጥና የውጪ ሀገር ሚዲያዎች ከፍተኛ ሽፋን ሰጥተውታል። የተፈጠረውን ነገር አትዘግቡ የማለት አምባገነንነት ወዴት ያደርሰን ይሆን?

አስቸኳይ መረጃ፡፡፡ የመንግስት አካላት ዛሬ እሑድ 4ስዓት ተደራደሩ ወይም ለሕገ ወጡ ቡድን ንብረት አስረክቡ ብለው አባቶችን እያስገደዱ ይገኛሉ። _--------- በምዕራብ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት በጭሮ/አሰበ ተፈሪ ከተማ በሕገ ወጥ የተሾሙት አካላት በጥር 27/2015 ዓ/ም እንደሚመጡ በቂ መረጃ ለሕቡ ሰለደረሰ ምዕመናን ቤተ ክርስቲያናቸውን ከሕገ ወጦች ወረራ በንቃት እንዲጠብቁ ብሎ ቅዱስ ሲኖዶስ ባስተላለፈው መመሪያ መሠረት በከተማው የሚገኙትን 4 አብያተ ክርስቲያናት በንቃት እየጠበቀ መዋሉ ማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን መዘገቡ ይታወቃል፡፡ ከቀኑ 11፡45 ስዓት ላይ የመጡት ሕገወጥ ቡድን ለመንግሥት አካል እንደማይመለሱ ሲነግሩት ሙሉ ወጪ ችሎ እንዲያድሩ አድርጓል። በዚህ መሀል 10 የማይሞሉ ዱላ ይዘው እየዘፈኑ ወደ ቤተ ክርስቲያን ሲመጡ እነሱን ትቶ ቤተክርስቲያ እየጠበቁ ባሉት ላይ ተኩስ ተከፈተ። በተኩስና አስለቃሽ ጭስ እስከ 2ስዓት ምዕመናን ሲያዋክብም አምሽቷል፡፡ ቤተ ክርስቲያንን ሙሉ ከበው ህዝቡን በተኩስ፣ አስለቃሽ ጭስ፣ በዱላ እያሰቃዩ ሙሉ ህዝቡን እንዳስወጡና የሀገረ ስብከት ስራ አስኪያጅ አንዳንድ የመምሪያ ሓላፊዎች ሞታችን በልደታ ብለው ግቢ ውስጥ ቀርተዋል፡፡ እስከምሽቱ 4ስዓት ላይም ቤተክርስቲያን ማን እንደሚገባ መመሪያ ከመንግስት እንጠብቃለን ብለው ከቆዩ በኋላ እና 5 ሰዓት ላይ ከሆቴል ጠርተው ሕገወጡን ቡድን አስገብተዋል፡፡ የጸጥታ እና የመንግስት አካላት ዛሬ እሑድ 4ስዓት ተደራደሩ ወይም ለሕገ ወጡ ቡድን ንብረት አስረክቡ ብለው አባቶችን እያስገደዱ ይገኛሉ። አባቶች ግን በቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ የምንመራ እንጂ በግል ምንወስነው አይደለም ብለዋል። የጸጥታ ኃይሎች ተደራድረው ገብተዋል ለማለት ሥራ አስኪያጁን ጨምሮ የመምሪያ ኃላፊዎችን አስገድደው ፎቶ ለማንሳት ሲሞክሩ እንደነበረ ለማኅበረ ቅዱሳን ቴሌቪዥን መረጃውን ያደረሱን ገልጸዋል።

ጅማ ደብረ መዊዕ መድኃኔዓለም ሙሉ ለሙሉ በኦሮሚያ ልዩ ኃይል ተሰብሯል። የደብሩን ካህናት፣ ዲያቆናትና ወጣቶችን ወደ ወረዳ 2 ፖሊስ ጣቢያ ወስደው አስረዋቸዋል። ዛሬ በሻሸመኔ የተከሰተው ነገ በጅማ እንዳይፈጠር ሥጋት ላይ መሆናቸውን ምእመናን ገልጸዋል።

ጅማ ደብረ/መዊ/መድኀኔዓለም ቤተክርስቲያን በአሁኑ ሰዓት የጸጥታ ኀይሎች በራሳቸው ጉልበት ጊቢ ውስጥ ገብተው ይገኛሊ ። አንዲሁም በአከባቢው ያሉትን ወጣቶችን አፍሰው እየወሰዱ ይገኛል። ነገ በ28 ከጠዋቱ 5 ሰዓት ላይ አዲሱን ጳጳስ የአካባቢው ምእመና ን እንዲቀበሉ እያስገደዱ የሚቃወሙትን ደግሞ እያሰሩ ነው።

ጅማ ደብረ/መዊ/መድሐኒዓለም ቤተክርስቲያን በአሁኑ ሰዓት ፖሊሶች በራሳቸው ጉልበት ጊቢውስጥ ገብተው ይገኛል አንዲሁም በአከባቢው ያሉትን ወጣቶችኝ ቤተክርስቲያንን የሚጠብቅትን በሙሉ አፍሰው እየወሰዱ ይገኛል። በመሆኑ ይህ መልዕክት ህዝበ ክርስቲያኖች በሙሉ ለሁሉም ህዝብ እንድታስተላልፊ በእግዚዓብሔር ሰም እጠይቃችሁለው አንድ የሀይማኖታችን ግዴታ ነው። ነገ በ28 ከጠዋቱ 5 ሰዓት ላይ አዲሱ ጳጳስ በግድ በጉልበት እንድንቀበለው ብለው ከአሁኑ የሚቃወሙትን ወደ እስር ቤት እያስገቡ ነው። ከአሁን ሰዓት ጀምሮ እራሳቹን አዘጋጁ ለሀይማኖታችኝ መቆም አለብን። ነገ ከለሊቱ 12 ሰዓት ጀምሮ ከደብረ/መዊ/መድሐኒዓለም ቤተክርስቲያን እንድትገኙ በእግዚአብሔር ስም ጥያቄያችንን እናስተላልፋለን። ሼር አድርጉ