Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት 的分析概览
频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 368 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 5 616,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 192 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 368 名订阅者。
根据 25 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -4,过去 24 小时变化为 -1,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 20.07%。内容发布后 24 小时内通常能获得 8.16% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 085 次浏览,首日通常累积 1 254 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 17。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።”
凭借高频更新(最新数据采集于 26 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
15 368
订阅者
-124 小时
+357 天
-430 天
帖子存档
ከሐሙስ እስከ ቅዳሜ የሚቆይ የጸሎት መርኀ-ግብር ።
#ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ለ3 ቀናት የሚቆይ #ጸሎት_አወጀች፡፡
በዛሬው ዕለት የቅዱስ ሲኖዶስ የመክፈቻ ጸሎት በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ቅድስት ማርያም ገዳም ከተጠናቀቀነ በኋላ ሁሉም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን ከዛሬ ጀምሮ ለሚቀጥሉት ሦስት ቀናት የጸሎትና የሱባኤ ጊዜ እንዲሆን አዋጅ መታወጁን ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የኒዮርክ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ገልጸዋል፡፡
#_#_#_#_#_#_#_
#በዚህም መሠረት ሰንበት ትምህርት ቤታችን ከነገ
#ሐሙስ (18/05/2015) ጀምሮ እስከ #ቅዳሜ(20/05/2015) የሚቆይ
#የመሐረነ_አብ የጸሎት መርኀ-ግብር ስላዘጋጀ ሁላችንም #ከ11:30 ጀምሮ በመገኘት የጸሎቱ ተሣታፊ እንድሆን ይሁን ።
ከሐሙስ እስከ ቅዳሜ የሚቆይ የጸሎት መርኀ-ግብር ።
#ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ለ3 ቀናት የሚቆይ #ጸሎት_አወጀች፡፡
በዛሬው ዕለት የቅዱስ ሲኖዶስ የመክፈቻ ጸሎት በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ቅድስት ማርያም ገዳም ከተጠናቀቀነ በኋላ ሁሉም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን ከዛሬ ጀምሮ ለሚቀጥሉት ሦስት ቀናት የጸሎትና የሱባኤ ጊዜ እንዲሆን አዋጅ መታወጁን ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር) የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና የኒዮርክ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ገልጸዋል፡፡
#_#_#_#_#_#_#_
#በዚህም መሠረት ሰንበት ትምህርት ቤታችን ከነገ
#ሐሙስ (18/05/2015) ጀምሮ እስከ #ቅዳሜ(20/05/2015) የሚቆይ
#የመሐረነ_አብ የጸሎት መርኀ-ግብር ስላዘጋጀ ሁላችንም #ከ11:30 ጀምሮ በመገኘት የጸሎቱ ተሣታፊ እንድሆን ይሁን ።
ሰበር ዜና
መጋቤ ሐዲስ አባ ጸጋ ዘአብ አዱኛ በሕገ ወጥ መንገድ በተከናወነው "ሢመተ ጳጳሳት" በመሳተፋቸው በመጸጸት ይቅርታ ጠየቁ !
ተ.ሚ.ማ
መጋቤ ሐዲስ አባ ጸጋ ዘአብ አዱኛ በሕገ ወጥ መንገድ በተከናወነው "ሢመተ ጳጳሳት" በመሳተፋቸው በመጸጸት ይቅርታ ጠየቁ !
ጥር 17 ቀን 2015 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)
መጋቤ ሐዲስ አባ ጸጋ ዘአብ አዱኛ በሕገ ወጥ መንገድ በተከናወነው "ሢመተ ጳጳሳት" በመሳተፋቸው በመጸጸት ይቅርታ ጠየቁ።
መጋቤ ሐዲስ አባ ጸጋ ዘአብ የይቅርታ ደብዳቤያቸውን ለቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ (ዶ/ር አቅርበዋል።
ብፁዕነታቸው የይቅርታ ደብዳቤያቸውን የተቀበሉ ሲሆን የቅዱስ ሲኖዶስን ምላሽ እንዲጠብቁ ምክር ለግሰዋል።
እንኳን ለቅድሱ ጊዮርጊስ ስባረ ዓፅሙ (ዝርወተ አጽሙ ) በሰላም አደረሳቹሁ
፠ ዐላውያን ነገሥታት በደብረ ይድራስ ተራራ ላይ የሊቀ ሰማዕቱን ሥጋውንና አጥንቱ በመንኰራኵር ፈጭተው በነፋስ ለበተኑበት፤ ነገር ግን ለአምላካችን የታመነ ሰማዕት በመሆኑ ያረፈበት መሬትና ዕፅዋት ጊዮርጊስ ቅዱስ ለእግዚአብሔር እያሉ ያመሰገኑበት ነው፡፡
------------
....ነገሥታቱም ጊዮርጊስን ሙታኖችን ብታስነሳ በአምላክህ እናምናለን አሉ ፤በጸሎቱ ሙታኖችም አስነሳላቸው በጌታቸንም ስም አምነው በእርሱ ስም አስተማሩ ጥምቀትንም ተቀበሉ ፡፡የቀሩት ነገሥታት ግን ሰይጣናትን ነው ያሳየኸን ብለው ተከራከሩ ፡፡
※ ከአንዲት እምበለት ቤት ተቀምጦ ምግብ ልትፈልግለት ሄዳ በተመለሰች ጊዜ ቤቷ ላይ ተአምር አየች ፤ የክርስቲያኖች አምላክ በሰው ተመስሎ እኔ ጋር መጣ ብትል ቅዱስ ጊየርጊስም #_እኔ_አምላክ_አይደለሁም_የአምላክ_ባርያ_ነኝ እነጂ አላት፡፡ የአምላክ
አገልጋይ ከሆንክ ቸርነትህ እንድትደርሰኝ እለምናለሁ አለችው ልጇንም በመስቀል ምልክት አማትቦበት ከዕውርነት አድኖታል ፡
※ ንጉሡም ተአምር ማድረጉን በሰማ ጊዜ በመንኰራኵርም ፈጨው ከከተማ ውጪ ወስደው ጣሉት ከሞትም ተነሣ ተመለሶም ወደ ነገሥታቱ ሄደ ፡፡ንጉሡም አድንቆ ይለምንው ጀመር በመንግሥቱ ላይ ሁለተኛ ያደርገው ዘንድ ቃል ገባለት ቅዱስ ጊዮርጊስ
እየዘበት ነገ ጠዋት ለአማልክቶች እሰዋለሁ ብሎት አደረ ፡፡ በሚጸልይበትም ጊዜ የንጉሡ ሚስት ሰምታ ጠየቀችው እርሱም ስለ ጌታችን አስተምራት አመነች ፡፡ በማግሥቱም ንጉሡ ሰውን ሰብስቦ እንደሚጠብቀውና እውነት መስሎ በታያት ጊዜ አዘነች ፡፡እርሱም
ልጅሽን በምድር ላይ አኑሪው አላት ከዚያም ወደ አጵሎን (ጣዖቱ) ሂድ ወደ እኔም እንዲመጣ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እዘዘው አለው ፡፡ ልጁም ድኖ ቅዱሱ እንዳለው ሄዶ አዘዘው ፡፡ በጣዖቱም የነበረው እርኩስ መንፈስ ወጥቶ እኔ ሰውን የማስት
እንጅ አምላክ አይደለሁም አለው ፡፡ ቅዱስ ጊዮርጊስም ምድር ትውጠው ዘንድ አዘዛት ወዲያውኑ ዋጠችው ጣዖቱንም ከአገልጋዮቻቸው ጋር አጠፋቸውን ንጉሡም ከወገኖቹ ጋር አፈረ፡፡
ሙሉውን ታሪክ እዚህ ያንብቡ ----> https://t.me/medihanaelem/6273
፠ እንደ ጎንደር አበራ ጊዮርጊስ ባሉት ክብረ በዓሉ ወደ ባሕረ ጥምቀቱ ወርዶና አድሮ ነው በዓሉ የሚከበረው፡፡
በጎንደር በጥር ወር የሚከበሩ በዓላት ወደ ጥምቀተ ባሕር በመውጣት የሚከበሩ ናቸው፡፡ ለምሳሌ ጥር 18 አበራ ጊዮርጊስ፤ ጥር 21 ሎዛ ማርያም፣ ጥር 22 ቅዱስ ዑራኤል (በዓታ ያለው)፤ ጥር 25 ቅዱስ መርቆሬዎስ (በተለይ በገጠሩ አካባቢ፡፡)
እርሱ እንደ ንብ አውራ ፈረሱ እንደ አሞራ፤
ጊዮርጊስ፥ ጊዮርጊስ፥ ጊዮርጊስ ኢትዮጵያን አደራ፡፡
ሰአል ለነ ጊዮርጊስ፤
ሰማዕተ ኢየሱስ ክርስቶስ፡፡
ዘሐረፀከ ዱድያኖስ፤
ወወገረከ ደብረ ይድራስ፤
ዘዘረወከ በነፋስ፡፡
ዛሬ ከምሽት ጀምሮ !
በጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ዙሪያ የተመደቡት የመንግሥት ጥበቃዎች ተነሥተዋል።
[ ትእዛዙ የማን እንደሆነ ባልታወቀ ሁኔታ ዛሬ ምሽት ላይ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ዙሪያ ጥበቃ ሲያደርጉ የቆዩ የመንግሥት የጥበቃ አካላት እንዲነሱ መደረጋቸውን ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ገልጸዋል።
# Orthodox_Book_Review
የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት በአዲስ አበባ የሚገኘውን የ"አባ" ሳዊሮስ ፣ የ"አባ" ኤዎስጣቴዎስን እና የ"አባ" ዜና ማርቆስን ማረፊያ ቤት አሸገ !
የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት በአዲስ አበባ የሚገኘውን የ"አባ" ሳዊሮስ ፣ የ"አባ" ኤዎስጣቴዎስን እና የ"አባ" ዜና ማርቆስን ማረፊያ ቤት አሽጓል።
በትናንትናው ዕለት 3ቱ አባቶች ሕገ ቤተ ክርስቲያንን እና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን ለመናድ እና ሲኖዶሳዊ አንድነትን ለመከፋፈል በማቀድ 26 መነኮሳትን ሾመናል በማለት መግለጫ መስጠታቸው ይታወሳል።
ጥር 15 ቀን 2015 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)
ጉባኤ ከለባቶቹ
#የተመደቡበት_ሀገረ_ስብከት_እና_ስማቸው
1.አባ ገ/ማርያም ነጋሳ - አባ ገብርኤል - ምዕራብ ወለጋ
2.አባ ተ/ሃይማኖት ወልዱ - አባ ባስልዮስ - ድሬዳዋ
3.አባ ገብርኤል ወ/ዮሐንስ - አባ ጢሞቴዎስ -ጉራጌ ሶዶ
4.አባ ገ/እግዚአብሔር ታደለ - አባ ጳውሎስ - ምዕራብ አርሲ
5.አባ ሚካኤል ገ/ማርያም - አባ ኤልሳዕ - ከምባታ
6.አባ ኃይሉ እንዳለ - አባ ገሪማ - ምሥራቅ ሐረርጌ
7.አባ ተ/ማርያም ስሜ - አባ ተ/ሃይማኖት - ጉጂ ሊበን
8.አባ ኃ/ኢየሱስ መንግስቱ - አባ ዕዝራ - ከፋ
9.አባ ወ/ኢየሱስ ኢፋ - አባ ኢያሱ - ቄለም ወለጋ
10.አባ ጳውሎስ ከበደ - አባ ዳንኤል - ሀዲያ
11.አባ ኃ/ኢየሱስ ተስፋዬ - አባ በርሱማ - ምሥራቅ ወለጋ
12.አባ ገ/ኢየሱስ ገለታ - አባ ሚናስ - ሆሮ ጉዱሩ
13.አባ ጸጋዘአብ አዱኛ - አባ ኤጲፋንዮስ - ምሁር ገዳም የበላይ ኃላፊ
14.አባ ኃ/ማርያም ጌታቸው - አባ አቤል - ምዕራብ ሐረርጌ
15.አባ ወ/ጊዮርጊስ ኃ/ሚካኤል - በርተሎሚዎስ - ከሚሴ
16.አባ እስጢፋኖስ ገብሬ - አባ ራጉኤል - ባሌ ረዳት ጳጳስ
17.አባ ገ/መድኅን ገ/ማርያም - አባ ዑራኤል - ጎፋ ባስኬቶ
18.አባ ኃ/ሚካኤል ንጉሤ - አባ አኖሬዎስ - ጊኒር
19.አባ አብርሃም መስቀሌ - አባ ኒቆዲሞስ - ዳውሮ,ኮንታ
20.አባ ንዋየ ሥላሴ አክሊሉ - አባ ሀ/ማርያም - ምዕራብ ጉጂ
21.አባ ኪ/ማርያም ቶሎሳ - አባ ተ/ሃዋርያት - ጅማና የም
22.አባ ወ/ማርያም ጸጋ - አባ አብሳዲ - ቦረና
23.አባ አምደሚካኤል ኃይሌ - አባ መርቆሬዎስ - አሩሲ
24.አባ መርሐጽድቅ ኃ/ማርያም - አባ ደቅስዮስ - ጌዴኦ,ቡርጁ,አማሮ
25.አባ ሞገስ ኃ/ማርያም - አባ ኤፍሬም - መናገሻ.ጋራ መ/ዓለምና ,ደ/ፀሐይ ቅ ጊዮርጊስ የበላይ ኃላፊ
26.አባ ገ/ኢየሱስ ንጉሤ - አባ አልዓዛር - ቡኖ በደሌ
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
