Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት 的分析概览
频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 381 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 5 584,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 199 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 381 名订阅者。
根据 03 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 21,过去 24 小时变化为 -7,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 21.13%。内容发布后 24 小时内通常能获得 9.50% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 250 次浏览,首日通常累积 1 462 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 16。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።”
凭借高频更新(最新数据采集于 04 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
15 381
订阅者
-724 小时
+117 天
+2130 天
帖子存档
#እያዘንን_ጻፍንላቹህ_፤ #በአሰቦት_ገዳም የተከሰተውን #የእሳት ቃጠሎ #share
#ደብረ_ወገግ
ውስተ ሃገረ አዲስ አበባ ህየ ነበርነ ወበከይነ፤
ውስተ ኵሃቲሃ ሰቀልነ እንዚራቲነ፤
ሶበ ተዘከርናሃ ዘተውዕያ ለሞዕራብ ሐረርጌ ቤተ ክርስቲያን እምነ፡፡
(በሃገረ አዲስ አበባ ተቀምጠን፤ በዛፎችዋ ላይ መሰንቆዎቻችንን ሰቀልን፤ ለሞዕራብ ሐረርጌ ያለች የተቃጠለች እናት ቤተ ክርስቲያንና ባሰብናት ጊዜም አለቀስን፡፡)
ከዚህ በፊት ማለትም ኅዳር 3 /2012 ዓ.ም. #በምሥራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት የሚገኙ 2ት አብያተ ክርስቲያናትና በተለያዩ ቦታዎች (በተለይም በቀርሳና ወተር) በሚገኙ ምዕመናን ላይ ከፍተኛ ጥቃት መድረሱን የምስራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት መግለጹንና፡፡ የተቃጠሉት አብያተ ክርስቲያናትም፤
#ዋቅጅራ_መድኀኔ_ዓለም_
#ጥንታዊና_ታሪካዊቷ_ገንዲድ_ቅድስት_ማርያም_ቤተ_ክርስቲያን_መሆናቸውን እናስታውሳለን አሁን ድግሞ በምዕራብ ሐረርጌ በሚገኘው በታላቁ #ደብረ_ወገግ_የአሰቦት_ሥላሴ_አባ_ሳሙኤል_ገዳም ከእሑድ ጀምሮ የተነሣው ሰው ሠራሽ እሳት በታላቁ ገዳማችን ላይ ከፍተኛ ቃጠሎ እና ውድመት ማስከተሉን ሁላችንም አይተናል:: አሣቱ አሁንም ቀጥሏል::
#ውድመት
#በገዳመ አሰቦት ሥላሴ ሃገር በቀል የሆኑት ጥንታውያኑ እጸዋት ሙሉ በሙሉ በእሳቱ ወድመዋል።
#የቅዱሳን መሸሸጊያ፣ መሠወሪያ እና የአርምሞ የሱባኤ መያዣው ተፈጥሮአዊው ጥብቅ ደን ወድሟል።
#የከብቶቻቸው ቀለብና መኖ የነበረው ሳር በእሳቱ ወድሟል።
ቤተ ክርስቲያንን እስከ መሠረቷ ድረስ ፈጽሞ አፍርሱ የሚሉትን ጎስቋሎችን የሚበቀላቸው አምላካችን ብፁዕ ነው፡፡ /መዝ. 136/
#ለመርዳት
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አሰቦት ቅርንጫፍ
ለአሰቦት ደብረ ወገግ ገዳም
የባንክ ሂሳብ ቁጥር 1000153218618
አሰቦት – ኢትዮጵያ
✤✤ #ደብረ_ወገግ_፤
፠ ‹‹ደብረ ወገግ›› ከ2-5 ዓ.ም. እመቤታችን ከነልጇ ስተሰደድ ለ6 ወር የተቀመጠችበት ሲኾን፤ ደብረ ወገግ የሚለው ስያሜ የተገኘው ከመላእክት ነው፡፡ ድርሳነ ዑራኤል በሰፊው እንደሚያትተው ቅዱስ ዑራኤል በ34ዓ.ም. የጌታችንን ደም በብርሃን ጽዋ ተቀብሎ ዓለምን እየረጨ ሲቀድሳት የያዘውን ጽዋ በደብረ ወገግ ላይ ቆሞ ሳለ ነው ጨልጦ ያንጠፈጠፈው፡፡ ያንጊዜም ደብረ ወገግን የብርሃን ውጋገን ሲያጥለቀልቀው በመታየቱ መላእክትም ቦታውን ‹‹ደብረ ወገግ›› (የብርሃን ተራራ) ብለው ሰይመውታል፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም ‹‹ወደፊት ፈጣሪውን የሚያገለግል ታላቅ ጻድቅ ይወጣባታልና ይህችን ቦታ ባርካት›› ብሎ ቅዱስ ዑራኤልን በነገረው መሠረት ባርኳት አርጓል፡፡
፠ በደብረ ወገግ ቦታ ላይ ብዙ ጊዜ የብርሃን ምሰሶ ተተክሎ መታየቱን የበቁ ገዳማውያን ብቻ ሳይሆኑ በከተማ ያሉና ለመሳለም ወደ ቦታው የሄዱ ደገኛ ሰዎችም በዐይናቸው ያዩትን ይናገራሉ፡፡ በገዳሙ ዙሪያ እጅግ በጣም ብዙ ስውራን ቅዱሳን እንዳሉ በግልጽ ይታወቃል፡፡
፠ ገዳሙ በግራኝ ወረራ ወቅት ከጠፋ በኋላ እንደገና መልሶ የቀናው በ1911ዓ.ም. በታላቁ ሊቅና መናኝ በአለቃ ገብረ መድኅን ነው (ለአፄ ኀይለ ሥላሴ በማሳሰብ)፡፡ በ1912 ዓ.ም. የአቡነ ሳሙኤልን ቤተ ክርስቲያንን በሣር ክዳን ሠሩ፤ በዓመቱ በ1918 ዓ.ም. ደግሞ የቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያንን መሥራት ጀምረው ፍጻሜውን ሳያዩ እርሳቸው ቢያርፉም፤ በ1919 ዓ.ም. የሕንፃ ቤተ ክርስቲያኑ ሥራ ተጠናቋል፡፡
#በ1929 ዓ.ም. በሶማልያ በኩል በገባው የፋሽስት ኢጣልያ ጦር ገዳሙ ተዘርፏል፥ የቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያንም ፈርሷል፡፡ በወቅቱ በገዳሙ ከነበሩት ከ500 በላይ መነኰሳት መካከል ከፊሉ ታቦቱን ይዘው ወደ ደብረ ሊባኖስ ገዳም ሲሸሹ ከፊሎቹ ደግሞ ወደ ሞቃዲሾ ተወስደው ታስረዋል፡፡ ከጣሊያን ወረራ በኋላ መነኰሳቱ በ1936 ዓ.ም. ተሰባስበው ወደ አሰቦት መጡ፡፡ ከ22 ዓመት በኋላ ደግሞ የቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን በግርማዊ ቀዳማዊ ንጉሠ ነገሥት ዐፄ ኃይለ ሥላሴ ትእዛዝ በ1952 ዓ.ም. ተሠራ፡፡ በደርግ ዘመነ መንግሥት ሶማሊያ ኢትጵያን ስትወርር ገዳሙ ላይ አደጋ ለመጣል የመጡ ጠላቶች በተአምራት ያለቁበት ነበር፤ የጃራ ጦር የሚባሉ ገዳሙን ለማጥፋትም መጡ ጠላቶች እንዲሁ በተአምራት አብደው የተመለሱበት ታላቅ ገዳም ነው፡፡ ግንቦት 16 ቀን 1984 ዓ.ም. በአክራሪ ኃይል የገዳሙን መነኰሳትና የአካባቢው ምዕመናን ላይ የከፋ አደጋ ጥሏል፤ ብዙዎችም ሰማዕት ሁነዋል፡፡
፠በአሰቦት ደብረ ወገግ ገዳም ውስጥ የተሰወሩ እጅግ በርካታ ቅዱሳን ስለመኖራቸው በገድለ #አቡነ_ሳሙኤል መቅድም ውስጥ በሰፊው ተጠቅሷል፡፡ አሁንም ሆነ ወደፊት በቦታው ላይ የተሰወሩት ቅዱሳን ለገዳማውያኑም ሆነ በዓለም ለሚኖሩ ምግባርን ከሃይማኖት አስተባብረው ለያዙ ሰዎች እየተገለጡላቸው ይታዩዋቸዋል፣ መልእክትም ይነግሯቸዋል፡፡ እንዲሁም ስውራኑ ባሉበት ቦታ የከበሮ ድምጽ ይሰማል፣ ዕጣን ይሸታል፣ ቀንና ሌሊት አራዊት ሲሰግዱበትና ሲጠብቁት ይታያል፡፡ ለአብነትም በ1972ዓ.ም. ሐምሌ 7 ብዙ ሰው እያያቸው አባ መዘምር የተሠወሩበት ታለቅ ገዳም ነው፡፡
/የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/
ቤተ ክርስቲያንን እስከ መሠረቷ ድረስ ፈጽሞ አፍርሱ የሚሉትን ጎስቋሎችን የሚበቀላቸው አምላካችን ብፁዕ ነው፡፡ /መዝ. 136/
/የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/
#share
Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool
YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w
Telegram https://t.me/medihanaelem
#እያዘንን_ጻፍንላቹህ_፤
ውስተ ሃገረ አዲስ አበባ ህየ ነበርነ ወበከይነ፤
ውስተ ኵሃቲሃ ሰቀልነ እንዚራቲነ፤
ሶበ ተዘከርናሃ ዘተውዕያ ለሞዕራብ ሐረርጌ ቤተ ክርስቲያን እምነ፡፡
(በሃገረ አዲስ አበባ ተቀምጠን፤ በዛፎችዋ ላይ መሰንቆዎቻችንን ሰቀልን፤ ለሞዕራብ ሐረርጌ ያለች የተቃጠለች እናት ቤተ ክርስቲያንና ባሰብናት ጊዜም አለቀስን፡፡)
ከዚህ በፊት ማለትም ኅዳር 3 /2012 ዓ.ም. #በምሥራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት የሚገኙ 2ት አብያተ ክርስቲያናትና በተለያዩ ቦታዎች (በተለይም በቀርሳና ወተር) በሚገኙ ምዕመናን ላይ ከፍተኛ ጥቃት መድረሱን የምስራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ገልጿል፡፡ የተቃጠሉት አብየተ ክርስቲያናትም፤
#ዋቅጅራ_መድኀኔ_ዓለም_
#ጥንታዊና_ታሪካዊቷ_ገንዲድ_ቅድስት_ማርያም_ቤተ_ክርስቲያን_መሆናቸውን እናስታውሳለን አሁን ድግሞ በምዕራብ ሐረርጌ በሚገኘው በታላቁ #ደብረ_ወገግ_የአሰቦት_ሥላሴ_አባ_ሳሙኤል_ገዳም ከእሑድ ጀመሮ የተነሣው ሰው ሠራሽ እሳት በታላቁ ገዳማችን ላይ ከፍተኛ ቃጠሎ እና ውድመት ማስከተሉን ሁላችንም አይተናል።
#ውድመት
#በገዳመ አሰቦት ሥላሴ ሃገር በቀል የሆኑት ጥንታውያኑ እጸዋት ሙሉ በሙሉ በእሳቱ ወድመዋል።
#የቅዱሳን መሸሸጊያ፣ መሠወሪያ እና የአርምሞ የሱባኤ መያዣው ተፈጥሮአዊው ጥብቅ ደን ወድሟል።
#የከብቶቻቸው ቀለብና መኖ የነበረው ሳር በእሳቱ ወድሟል።
ቤተ ክርስቲያንን እስከ መሠረቷ ድረስ ፈጽሞ አፍርሱ የሚሉትን ጎስቋሎችን የሚበቀላቸው አምላካችን ብፁዕ ነው፡፡ /መዝ. 136/
#ለመርዳት
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አሰቦት ቅርንጫፍ
ለአሰቦት ደብረ ወገግ ገዳም
የባንክ ሂሳብ ቁጥር 1000153218618
አሰቦት – ኢትዮጵያ
✤✤ #ደብረ_ወገግ_፤
፠ ‹‹ደብረ ወገግ›› ከ2-5 ዓ.ም. እመቤታችን ከነልጇ ስተሰደድ ለ6 ወር የተቀመጠችበት ሲኾን፤ ደብረ ወገግ የሚለው ስያሜ የተገኘው ከመላእክት ነው፡፡ ድርሳነ ዑራኤል በሰፊው እንደሚያትተው ቅዱስ ዑራኤል በ34ዓ.ም. የጌታችንን ደም በብርሃን ጽዋ ተቀብሎ ዓለምን እየረጨ ሲቀድሳት የያዘውን ጽዋ በደብረ ወገግ ላይ ቆሞ ሳለ ነው ጨልጦ ያንጠፈጠፈው፡፡ ያንጊዜም ደብረ ወገግን የብርሃን ውጋገን ሲያጥለቀልቀው በመታየቱ መላእክትም ቦታውን ‹‹ደብረ ወገግ›› (የብርሃን ተራራ) ብለው ሰይመውታል፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም ‹‹ወደፊት ፈጣሪውን የሚያገለግል ታላቅ ጻድቅ ይወጣባታልና ይህችን ቦታ ባርካት›› ብሎ ቅዱስ ዑራኤልን በነገረው መሠረት ባርኳት አርጓል፡፡
፠ በደብረ ወገግ ቦታ ላይ ብዙ ጊዜ የብርሃን ምሰሶ ተተክሎ መታየቱን የበቁ ገዳማውያን ብቻ ሳይሆኑ በከተማ ያሉና ለመሳለም ወደ ቦታው የሄዱ ደገኛ ሰዎችም በዐይናቸው ያዩትን ይናገራሉ፡፡ በገዳሙ ዙሪያ እጅግ በጣም ብዙ ስውራን ቅዱሳን እንዳሉ በግልጽ ይታወቃል፡፡
፠ ገዳሙ በግራኝ ወረራ ወቅት ከጠፋ በኋላ እንደገና መልሶ የቀናው በ1911ዓ.ም. በታላቁ ሊቅና መናኝ በአለቃ ገብረ መድኅን ነው (ለአፄ ኀይለ ሥላሴ በማሳሰብ)፡፡ በ1912 ዓ.ም. የአቡነ ሳሙኤልን ቤተ ክርስቲያንን በሣር ክዳን ሠሩ፤ በዓመቱ በ1918 ዓ.ም. ደግሞ የቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያንን መሥራት ጀምረው ፍጻሜውን ሳያዩ እርሳቸው ቢያርፉም፤ በ1919 ዓ.ም. የሕንፃ ቤተ ክርስቲያኑ ሥራ ተጠናቋል፡፡
#በ1929 ዓ.ም. በሶማልያ በኩል በገባው የፋሽስት ኢጣልያ ጦር ገዳሙ ተዘርፏል፥ የቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያንም ፈርሷል፡፡ በወቅቱ በገዳሙ ከነበሩት ከ500 በላይ መነኰሳት መካከል ከፊሉ ታቦቱን ይዘው ወደ ደብረ ሊባኖስ ገዳም ሲሸሹ ከፊሎቹ ደግሞ ወደ ሞቃዲሾ ተወስደው ታስረዋል፡፡ ከጣሊያን ወረራ በኋላ መነኰሳቱ በ1936 ዓ.ም. ተሰባስበው ወደ አሰቦት መጡ፡፡ ከ22 ዓመት በኋላ ደግሞ የቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን በግርማዊ ቀዳማዊ ንጉሠ ነገሥት ዐፄ ኃይለ ሥላሴ ትእዛዝ በ1952 ዓ.ም. ተሠራ፡፡ በደርግ ዘመነ መንግሥት ሶማሊያ ኢትጵያን ስትወርር ገዳሙ ላይ አደጋ ለመጣል የመጡ ጠላቶች በተአምራት ያለቁበት ነበር፤ የጃራ ጦር የሚባሉ ገዳሙን ለማጥፋትም መጡ ጠላቶች እንዲሁ በተአምራት አብደው የተመለሱበት ታላቅ ገዳም ነው፡፡ ግንቦት 16 ቀን 1984 ዓ.ም. በአክራሪ ኃይል የገዳሙን መነኰሳትና የአካባቢው ምዕመናን ላይ የከፋ አደጋ ጥሏል፤ ብዙዎችም ሰማዕት ሁነዋል፡፡
፠በአሰቦት ደብረ ወገግ ገዳም ውስጥ የተሰወሩ እጅግ በርካታ ቅዱሳን ስለመኖራቸው በገድለ #አቡነ_ሳሙኤል መቅድም ውስጥ በሰፊው ተጠቅሷል፡፡ አሁንም ሆነ ወደፊት በቦታው ላይ የተሰወሩት ቅዱሳን ለገዳማውያኑም ሆነ በዓለም ለሚኖሩ ምግባርን ከሃይማኖት አስተባብረው ለያዙ ሰዎች እየተገለጡላቸው ይታዩዋቸዋል፣ መልእክትም ይነግሯቸዋል፡፡ እንዲሁም ስውራኑ ባሉበት ቦታ የከበሮ ድምጽ ይሰማል፣ ዕጣን ይሸታል፣ ቀንና ሌሊት አራዊት ሲሰግዱበትና ሲጠብቁት ይታያል፡፡ ለአብነትም በ1972ዓ.ም. ሐምሌ 7 ብዙ ሰው እያያቸው አባ መዘምር የተሠወሩበት ታለቅ ገዳም ነው፡፡
/የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/
ቤተ ክርስቲያንን እስከ መሠረቷ ድረስ ፈጽሞ አፍርሱ የሚሉትን ጎስቋሎችን የሚበቀላቸው አምላካችን ብፁዕ ነው፡፡ /መዝ. 136/
/የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/
🧑🎓👩🎓
በወርኀ ጥር እና የካቲት #ምርቃታችሁን ላደረጋችሁ ለሰ/ት/ቤት #አባል ወንድምና እህቶቻችን በሙሉ፤እንኳን ደስ አላችሁ::
#ሳራ ሙሉነህ ,A.A Medical college, Nursing ,BSc.
#ጌታቸው ሳሙኤል,ከአኵሱም ዩኒቨርሲቲ, Electrical Engineering ,BSc
#ሮቤል ገ/መድኀን , ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ, Civil Engineering, BSc
#ካሌብ አየነው, ኮተቤ ሜ/ፖ ዩኒቨርሲቲ,Sport Science, BA
#ቤተልሔም ኢዮብ ,CPU college, Accounting, diploma
🧑🎓👩🎓
መልዕክት ከምስካየ ኅዙናን መድኀኔዓለም ገዳም ተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ት ቤት
"ወንድሞች በኅብረት ቢቀመጡ፥ እነሆ መልካም ነው፤ እነሆም ያማረ ነው"
(መዝ. ፻፴፪፥፩)
አጥቢያ ሰንበት ትምህርት ቤታችን የኾነው የቀጨኔ ደብረ ሰላም
መድኀኔ ዓለም እና ደብረ ትጉኃን ቅዱስ ገብርኤል ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ት/ቤት በገጠመው "የቋሚ ቦታ ይሰጠን" ጥያቄ መሠረት፣ ከባድ ፈተና ላይ መውደቁ ይታወቃል!
የፈተናዎች ኹሉ መውጫ መድኃኔዓለም ነውና፣ የወንድሞቻችንን እና የእኅቶቻችንን ችግር ሲያሳስበው የቆየው ሰንበት ት/ቤታችን ረቡዕ ከቀን 15 እስከ ቀን 17 ድረስ ለሦስት ቀን የሚቆይ የጸሎት መርሐ ግብር ከቀኑ 11:30 ጀምሮ ተዘጋጅቷል።
ስለ ኾነም በጸሎት መርሐ ግብሩ ትሳተፉ ዘንድ፣ የሰንበት ትምህርት ቤቱ ችግር ተፈቶ ማየት የምትናፍቁ ኹሉ ተጠርታችኋል።
"ኑ በጋራ ወደ ሐዘንተኞች መጠጊያ ለኾነ መድኀኔዓለም እናመልክት"
አድራሻ፦ 6ኪሎ ዩኒቨርስቲ ከፍ ብሎ፣ ምስካየ ሕዙናን መድኀኔዓለም ገዳም፣ ተምሮ ማስተማር ሰንበት ት/ቤት አዳራሽ።
#ምኵራብ፤ ሦስተኛው ሳምንት
ሦስተኛው ሳምንት ምኵራብ ይባላል፡፡ ጌታ በምኵራብ ማስተማሩን የሚዘከርበት ሳምንት ሲሆን ‹‹#ቦአ_ኢየሱስ_ምኩራበ_አይሁድ›› የሚልና ይህን የመሰለ ጌታ በምኩራብ ማስተማሩን የሚያዘክር ምስጋና የሚቀርብበት ሳምንት ነው፡፡
በብሉይ ኪዳን ዘመን በኢሩሳሌም የአይሁድ ቤተመቅደስ ነበራቸው፡፡ ናቡከደነጾር ኢየሩሳሌምን በወረረ ጊዜ ግን ቤተመቅደሱን አፈረሰ፤ ሕዝቡንም ወደ ባቢሎን አፈለሰ፡፡ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ አይሁድ በሚኖሩባቸው ስፍራዎች ሁሉ ለጸሎት ቤት ይሰሩ ነበር፤ በዚህም ምክንያት ጌታችን መድኃኒታችንኢየሱስ ክርስቶስ በኢየሩሳሌም እየተዘዋወረ በሚያስተምርበት ጊዜ ብዙ ምኵራቦች ነበሩ፡፡ ሐዋርያት በሚያስተምሩበት ወቅት ከአንዳንድ ቦታዎች በቀር በምኵራቦች ገብተው ወንጌልን አስተምረዋል፡፡
በብሉይ ዘመን ቢያንስ ዐስር የጎለመሱ ወንዶች (የቤተሰብ ኃላፊዎች) በቦታው ከተገኙ እነዚህን ምኵራቦችን ለመስራት ይፈቀድላቸው ነበር፡፡ ነገር ግን ዋናው ቤተ መቅደሱ ያለው በኢየሩሳሌም ብቻ ነበር፡፡
በምኵራብ ውስጥም የኦሪት የሕግ መጻሕፍትና በቅዱሳን ነቢያት የተጻፉ ጽሑፎች በብራና ጥቅልል ይገኛሉ፡፡ ምዕመኑ እንዲሰማቸው እንደ መድረክ ባለ ቦታ ላይ ካህናትና መምህራን ቆመው መጻሕፍትን ያነባሉ፤ ቃለ እግዚአብሔርንም ያስተምሩ ነበር፡፡
በኦሪቱ ምኵራብን የሚመሩት አለቆች ጥፋተኛ ሰው ሲገኝ፤ በመግረፍ ወይም ከምኵራብ በማስወጣት ሊቀጡ ስልጣን ነበራቸው፡፡ አገልጋይ ወይም የሚራዱ ወጣቶችም ልጆችን በማስተማር ጥቅሎችን በማቅረብ በተጨማሪ የአለቆችን ትዕዛዝ በመፈጸም ያገለግላሉ፡፡
በየሰንበቱ ሕዝብ ሁሉ በምኵራብ ተሰብስበው አምልኮታቸውን ይፈጸሙ ነበር፤ በአምልኮታቸው ውስጥም ጸሎት፤ ከሕግና ከነቢያት ንባብ፤ ስብከትና ቡራኬ ነበር፡፡
በዚህ በምኩራብ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሰንበት ተገኝቶ ሕዝቡን አስተምሯል፤ ሕሙማንን ፋውሷል፡፡ #የኢሳይያስን_መጽሐፍ_ምዕራፍ_፷፩ን አንብቧል፡፡ በዚህ በዐቢይ ጾም ሦስተኛ ሳምንት(ምኵራብ) የሚታሰበውም ይህ ነው፡፡
፨ ‹‹ወደ አደገበትም ወደ ናዝሬት መጣ፤ እንደ ልማዱም በሰንበት ቀን ምኵራብ ገባ ሊያነብም ተነሳ፡፡›› ሉቃ. 4፥16
፨ ‹‹ወደ ገዛ አገሩም መጥቶ እስኪገረሙ ድረስ በሚገባቸው ያስተምራቸው ነበር፡፡›› ማቴ. 13፥52
፨ ‹‹ሰንበትም በሆነ ጊዜ በምኵራብ ያስተምር ጀመር፡፡››ማር 6፥1
፨ በዕለቱ ቅዳሴ ላይ የሚነበቡ ምንባባትም፤ #ጌታችን_ቤተ_መቅደሱን_የንግድ_ማዕከል_ያደረጉትን_ዓይቶና_አዝኖ_ነጋዴዎቹን_ከነመንጋቸው_በጅራፍ_እንዳስወጣቸውና ‹‹ይህን ቤተ መቅደስ አፍርሱት በሦስተኛው ቀን እኔ እሠራዋለሁ፡፡›› ብሎ ስለመ ሞቱና ስለ ትንሣኤው ማስተማሩን የሚገልጽ ነው፡፡
፨፨፨ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፨፨፨
Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool
YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w
Telegram https://t.me/medihanaelem
meskel melelt kulu neger yaden emtsare .jpg0.56 KB
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
