uz
Feedback
Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት

Kanalga Telegram’da o‘tish

የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት analitikasi

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 381 obunachidan iborat bo'lib, Din & Maʼnaviyat toifasida 5 584-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 199-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 381 obunachiga ega bo‘ldi.

03 Iyul, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 21 ga, so‘nggi 24 soatda esa -7 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 21.13% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 9.50% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 3 250 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 1 462 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 16 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
“የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።”

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 04 Iyul, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Din & Maʼnaviyat toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 381
Obunachilar
-724 soatlar
+117 kunlar
+2130 kunlar
Postlar arxiv
#እያዘንን_ጻፍንላቹህ_፤ #በአሰቦት_ገዳም የተከሰተውን #የእሳት ቃጠሎ #share #ደብረ_ወገግ ውስተ ሃገረ አዲስ አበባ ህየ ነበርነ ወበከይነ፤ ውስተ ኵሃቲሃ ሰቀልነ እንዚራቲነ፤ ሶበ ተዘከርናሃ ዘተውዕያ ለሞዕራብ ሐረርጌ ቤተ ክርስቲያን እምነ፡፡ (በሃገረ አዲስ አበባ ተቀምጠን፤ በዛፎችዋ ላይ መሰንቆዎቻችንን ሰቀልን፤ ለሞዕራብ ሐረርጌ ያለች የተቃጠለች እናት ቤተ ክርስቲያንና ባሰብናት ጊዜም አለቀስን፡፡) ከዚህ በፊት ማለትም ኅዳር 3 /2012 ዓ.ም. #በምሥራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት የሚገኙ 2ት አብያተ ክርስቲያናትና በተለያዩ ቦታዎች (በተለይም በቀርሳና ወተር) በሚገኙ ምዕመናን ላይ ከፍተኛ ጥቃት መድረሱን የምስራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት መግለጹንና፡፡ የተቃጠሉት አብያተ ክርስቲያናትም፤ #ዋቅጅራ_መድኀኔ_ዓለም_ #ጥንታዊና_ታሪካዊቷ_ገንዲድ_ቅድስት_ማርያም_ቤተ_ክርስቲያን_መሆናቸውን እናስታውሳለን አሁን ድግሞ በምዕራብ ሐረርጌ በሚገኘው በታላቁ #ደብረ_ወገግ_የአሰቦት_ሥላሴ_አባ_ሳሙኤል_ገዳም ከእሑድ ጀምሮ የተነሣው ሰው ሠራሽ እሳት በታላቁ ገዳማችን ላይ ከፍተኛ ቃጠሎ እና ውድመት ማስከተሉን ሁላችንም አይተናል:: አሣቱ አሁንም ቀጥሏል:: #ውድመት #በገዳመ አሰቦት ሥላሴ ሃገር በቀል የሆኑት ጥንታውያኑ እጸዋት ሙሉ በሙሉ በእሳቱ ወድመዋል። #የቅዱሳን መሸሸጊያ፣ መሠወሪያ እና የአርምሞ የሱባኤ መያዣው ተፈጥሮአዊው ጥብቅ ደን ወድሟል። #የከብቶቻቸው ቀለብና መኖ የነበረው ሳር በእሳቱ ወድሟል። ቤተ ክርስቲያንን እስከ መሠረቷ ድረስ ፈጽሞ አፍርሱ የሚሉትን ጎስቋሎችን የሚበቀላቸው አምላካችን ብፁዕ ነው፡፡ /መዝ. 136/ #ለመርዳት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አሰቦት ቅርንጫፍ ለአሰቦት ደብረ ወገግ ገዳም የባንክ ሂሳብ ቁጥር 1000153218618 አሰቦት – ኢትዮጵያ ✤✤ #ደብረ_ወገግ_፤ ፠ ‹‹ደብረ ወገግ›› ከ2-5 ዓ.ም. እመቤታችን ከነልጇ ስተሰደድ ለ6 ወር የተቀመጠችበት ሲኾን፤ ደብረ ወገግ የሚለው ስያሜ የተገኘው ከመላእክት ነው፡፡ ድርሳነ ዑራኤል በሰፊው እንደሚያትተው ቅዱስ ዑራኤል በ34ዓ.ም. የጌታችንን ደም በብርሃን ጽዋ ተቀብሎ ዓለምን እየረጨ ሲቀድሳት የያዘውን ጽዋ በደብረ ወገግ ላይ ቆሞ ሳለ ነው ጨልጦ ያንጠፈጠፈው፡፡ ያንጊዜም ደብረ ወገግን የብርሃን ውጋገን ሲያጥለቀልቀው በመታየቱ መላእክትም ቦታውን ‹‹ደብረ ወገግ›› (የብርሃን ተራራ) ብለው ሰይመውታል፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም ‹‹ወደፊት ፈጣሪውን የሚያገለግል ታላቅ ጻድቅ ይወጣባታልና ይህችን ቦታ ባርካት›› ብሎ ቅዱስ ዑራኤልን በነገረው መሠረት ባርኳት አርጓል፡፡ ፠ በደብረ ወገግ ቦታ ላይ ብዙ ጊዜ የብርሃን ምሰሶ ተተክሎ መታየቱን የበቁ ገዳማውያን ብቻ ሳይሆኑ በከተማ ያሉና ለመሳለም ወደ ቦታው የሄዱ ደገኛ ሰዎችም በዐይናቸው ያዩትን ይናገራሉ፡፡ በገዳሙ ዙሪያ እጅግ በጣም ብዙ ስውራን ቅዱሳን እንዳሉ በግልጽ ይታወቃል፡፡ ፠ ገዳሙ በግራኝ ወረራ ወቅት ከጠፋ በኋላ እንደገና መልሶ የቀናው በ1911ዓ.ም. በታላቁ ሊቅና መናኝ በአለቃ ገብረ መድኅን ነው (ለአፄ ኀይለ ሥላሴ በማሳሰብ)፡፡ በ1912 ዓ.ም. የአቡነ ሳሙኤልን ቤተ ክርስቲያንን በሣር ክዳን ሠሩ፤ በዓመቱ በ1918 ዓ.ም. ደግሞ የቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያንን መሥራት ጀምረው ፍጻሜውን ሳያዩ እርሳቸው ቢያርፉም፤ በ1919 ዓ.ም. የሕንፃ ቤተ ክርስቲያኑ ሥራ ተጠናቋል፡፡ #በ1929 ዓ.ም. በሶማልያ በኩል በገባው የፋሽስት ኢጣልያ ጦር ገዳሙ ተዘርፏል፥ የቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያንም ፈርሷል፡፡ በወቅቱ በገዳሙ ከነበሩት ከ500 በላይ መነኰሳት መካከል ከፊሉ ታቦቱን ይዘው ወደ ደብረ ሊባኖስ ገዳም ሲሸሹ ከፊሎቹ ደግሞ ወደ ሞቃዲሾ ተወስደው ታስረዋል፡፡ ከጣሊያን ወረራ በኋላ መነኰሳቱ በ1936 ዓ.ም. ተሰባስበው ወደ አሰቦት መጡ፡፡ ከ22 ዓመት በኋላ ደግሞ የቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን በግርማዊ ቀዳማዊ ንጉሠ ነገሥት ዐፄ ኃይለ ሥላሴ ትእዛዝ በ1952 ዓ.ም. ተሠራ፡፡ በደርግ ዘመነ መንግሥት ሶማሊያ ኢትጵያን ስትወርር ገዳሙ ላይ አደጋ ለመጣል የመጡ ጠላቶች በተአምራት ያለቁበት ነበር፤ የጃራ ጦር የሚባሉ ገዳሙን ለማጥፋትም መጡ ጠላቶች እንዲሁ በተአምራት አብደው የተመለሱበት ታላቅ ገዳም ነው፡፡ ግንቦት 16 ቀን 1984 ዓ.ም. በአክራሪ ኃይል የገዳሙን መነኰሳትና የአካባቢው ምዕመናን ላይ የከፋ አደጋ ጥሏል፤ ብዙዎችም ሰማዕት ሁነዋል፡፡ ፠በአሰቦት ደብረ ወገግ ገዳም ውስጥ የተሰወሩ እጅግ በርካታ ቅዱሳን ስለመኖራቸው በገድለ #አቡነ_ሳሙኤል መቅድም ውስጥ በሰፊው ተጠቅሷል፡፡ አሁንም ሆነ ወደፊት በቦታው ላይ የተሰወሩት ቅዱሳን ለገዳማውያኑም ሆነ በዓለም ለሚኖሩ ምግባርን ከሃይማኖት አስተባብረው ለያዙ ሰዎች እየተገለጡላቸው ይታዩዋቸዋል፣ መልእክትም ይነግሯቸዋል፡፡ እንዲሁም ስውራኑ ባሉበት ቦታ የከበሮ ድምጽ ይሰማል፣ ዕጣን ይሸታል፣ ቀንና ሌሊት አራዊት ሲሰግዱበትና ሲጠብቁት ይታያል፡፡ ለአብነትም በ1972ዓ.ም. ሐምሌ 7 ብዙ ሰው እያያቸው አባ መዘምር የተሠወሩበት ታለቅ ገዳም ነው፡፡ /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/ ቤተ ክርስቲያንን እስከ መሠረቷ ድረስ ፈጽሞ አፍርሱ የሚሉትን ጎስቋሎችን የሚበቀላቸው አምላካችን ብፁዕ ነው፡፡ /መዝ. 136/ /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/ #share Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem

#እያዘንን_ጻፍንላቹህ_፤ ውስተ ሃገረ አዲስ አበባ ህየ ነበርነ ወበከይነ፤ ውስተ ኵሃቲሃ ሰቀልነ እንዚራቲነ፤ ሶበ ተዘከርናሃ ዘተውዕያ ለሞዕራብ ሐረርጌ ቤተ ክርስቲያን እምነ፡፡ (በሃገረ አዲስ አበባ ተቀምጠን፤ በዛፎችዋ ላይ መሰንቆዎቻችንን ሰቀልን፤ ለሞዕራብ ሐረርጌ ያለች የተቃጠለች እናት ቤተ ክርስቲያንና ባሰብናት ጊዜም አለቀስን፡፡) ከዚህ በፊት ማለትም ኅዳር 3 /2012 ዓ.ም. #በምሥራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት የሚገኙ 2ት አብያተ ክርስቲያናትና በተለያዩ ቦታዎች (በተለይም በቀርሳና ወተር) በሚገኙ ምዕመናን ላይ ከፍተኛ ጥቃት መድረሱን የምስራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ገልጿል፡፡ የተቃጠሉት አብየተ ክርስቲያናትም፤ #ዋቅጅራ_መድኀኔ_ዓለም_ #ጥንታዊና_ታሪካዊቷ_ገንዲድ_ቅድስት_ማርያም_ቤተ_ክርስቲያን_መሆናቸውን እናስታውሳለን አሁን ድግሞ በምዕራብ ሐረርጌ በሚገኘው በታላቁ #ደብረ_ወገግ_የአሰቦት_ሥላሴ_አባ_ሳሙኤል_ገዳም ከእሑድ ጀመሮ የተነሣው ሰው ሠራሽ እሳት በታላቁ ገዳማችን ላይ ከፍተኛ ቃጠሎ እና ውድመት ማስከተሉን ሁላችንም አይተናል። #ውድመት #በገዳመ አሰቦት ሥላሴ ሃገር በቀል የሆኑት ጥንታውያኑ እጸዋት ሙሉ በሙሉ በእሳቱ ወድመዋል። #የቅዱሳን መሸሸጊያ፣ መሠወሪያ እና የአርምሞ የሱባኤ መያዣው ተፈጥሮአዊው ጥብቅ ደን ወድሟል። #የከብቶቻቸው ቀለብና መኖ የነበረው ሳር በእሳቱ ወድሟል። ቤተ ክርስቲያንን እስከ መሠረቷ ድረስ ፈጽሞ አፍርሱ የሚሉትን ጎስቋሎችን የሚበቀላቸው አምላካችን ብፁዕ ነው፡፡ /መዝ. 136/ #ለመርዳት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አሰቦት ቅርንጫፍ ለአሰቦት ደብረ ወገግ ገዳም የባንክ ሂሳብ ቁጥር 1000153218618 አሰቦት – ኢትዮጵያ ✤✤ #ደብረ_ወገግ_፤ ፠ ‹‹ደብረ ወገግ›› ከ2-5 ዓ.ም. እመቤታችን ከነልጇ ስተሰደድ ለ6 ወር የተቀመጠችበት ሲኾን፤ ደብረ ወገግ የሚለው ስያሜ የተገኘው ከመላእክት ነው፡፡ ድርሳነ ዑራኤል በሰፊው እንደሚያትተው ቅዱስ ዑራኤል በ34ዓ.ም. የጌታችንን ደም በብርሃን ጽዋ ተቀብሎ ዓለምን እየረጨ ሲቀድሳት የያዘውን ጽዋ በደብረ ወገግ ላይ ቆሞ ሳለ ነው ጨልጦ ያንጠፈጠፈው፡፡ ያንጊዜም ደብረ ወገግን የብርሃን ውጋገን ሲያጥለቀልቀው በመታየቱ መላእክትም ቦታውን ‹‹ደብረ ወገግ›› (የብርሃን ተራራ) ብለው ሰይመውታል፡፡ ቅዱስ ሚካኤልም ‹‹ወደፊት ፈጣሪውን የሚያገለግል ታላቅ ጻድቅ ይወጣባታልና ይህችን ቦታ ባርካት›› ብሎ ቅዱስ ዑራኤልን በነገረው መሠረት ባርኳት አርጓል፡፡ ፠ በደብረ ወገግ ቦታ ላይ ብዙ ጊዜ የብርሃን ምሰሶ ተተክሎ መታየቱን የበቁ ገዳማውያን ብቻ ሳይሆኑ በከተማ ያሉና ለመሳለም ወደ ቦታው የሄዱ ደገኛ ሰዎችም በዐይናቸው ያዩትን ይናገራሉ፡፡ በገዳሙ ዙሪያ እጅግ በጣም ብዙ ስውራን ቅዱሳን እንዳሉ በግልጽ ይታወቃል፡፡ ፠ ገዳሙ በግራኝ ወረራ ወቅት ከጠፋ በኋላ እንደገና መልሶ የቀናው በ1911ዓ.ም. በታላቁ ሊቅና መናኝ በአለቃ ገብረ መድኅን ነው (ለአፄ ኀይለ ሥላሴ በማሳሰብ)፡፡ በ1912 ዓ.ም. የአቡነ ሳሙኤልን ቤተ ክርስቲያንን በሣር ክዳን ሠሩ፤ በዓመቱ በ1918 ዓ.ም. ደግሞ የቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያንን መሥራት ጀምረው ፍጻሜውን ሳያዩ እርሳቸው ቢያርፉም፤ በ1919 ዓ.ም. የሕንፃ ቤተ ክርስቲያኑ ሥራ ተጠናቋል፡፡ #በ1929 ዓ.ም. በሶማልያ በኩል በገባው የፋሽስት ኢጣልያ ጦር ገዳሙ ተዘርፏል፥ የቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያንም ፈርሷል፡፡ በወቅቱ በገዳሙ ከነበሩት ከ500 በላይ መነኰሳት መካከል ከፊሉ ታቦቱን ይዘው ወደ ደብረ ሊባኖስ ገዳም ሲሸሹ ከፊሎቹ ደግሞ ወደ ሞቃዲሾ ተወስደው ታስረዋል፡፡ ከጣሊያን ወረራ በኋላ መነኰሳቱ በ1936 ዓ.ም. ተሰባስበው ወደ አሰቦት መጡ፡፡ ከ22 ዓመት በኋላ ደግሞ የቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን በግርማዊ ቀዳማዊ ንጉሠ ነገሥት ዐፄ ኃይለ ሥላሴ ትእዛዝ በ1952 ዓ.ም. ተሠራ፡፡ በደርግ ዘመነ መንግሥት ሶማሊያ ኢትጵያን ስትወርር ገዳሙ ላይ አደጋ ለመጣል የመጡ ጠላቶች በተአምራት ያለቁበት ነበር፤ የጃራ ጦር የሚባሉ ገዳሙን ለማጥፋትም መጡ ጠላቶች እንዲሁ በተአምራት አብደው የተመለሱበት ታላቅ ገዳም ነው፡፡ ግንቦት 16 ቀን 1984 ዓ.ም. በአክራሪ ኃይል የገዳሙን መነኰሳትና የአካባቢው ምዕመናን ላይ የከፋ አደጋ ጥሏል፤ ብዙዎችም ሰማዕት ሁነዋል፡፡ ፠በአሰቦት ደብረ ወገግ ገዳም ውስጥ የተሰወሩ እጅግ በርካታ ቅዱሳን ስለመኖራቸው በገድለ #አቡነ_ሳሙኤል መቅድም ውስጥ በሰፊው ተጠቅሷል፡፡ አሁንም ሆነ ወደፊት በቦታው ላይ የተሰወሩት ቅዱሳን ለገዳማውያኑም ሆነ በዓለም ለሚኖሩ ምግባርን ከሃይማኖት አስተባብረው ለያዙ ሰዎች እየተገለጡላቸው ይታዩዋቸዋል፣ መልእክትም ይነግሯቸዋል፡፡ እንዲሁም ስውራኑ ባሉበት ቦታ የከበሮ ድምጽ ይሰማል፣ ዕጣን ይሸታል፣ ቀንና ሌሊት አራዊት ሲሰግዱበትና ሲጠብቁት ይታያል፡፡ ለአብነትም በ1972ዓ.ም. ሐምሌ 7 ብዙ ሰው እያያቸው አባ መዘምር የተሠወሩበት ታለቅ ገዳም ነው፡፡ /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/ ቤተ ክርስቲያንን እስከ መሠረቷ ድረስ ፈጽሞ አፍርሱ የሚሉትን ጎስቋሎችን የሚበቀላቸው አምላካችን ብፁዕ ነው፡፡ /መዝ. 136/ /የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት/

🧑‍🎓👩‍🎓 በወርኀ ጥር እና የካቲት #ምርቃታችሁን ላደረጋችሁ ለሰ/ት/ቤት #አባል ወንድምና እህቶቻችን በሙሉ፤እንኳን ደስ አላችሁ:: #ሳራ ሙሉነህ ,A.A Medical college, Nursin
🧑‍🎓👩‍🎓 በወርኀ ጥር እና የካቲት #ምርቃታችሁን ላደረጋችሁ ለሰ/ት/ቤት #አባል ወንድምና እህቶቻችን በሙሉ፤እንኳን ደስ አላችሁ:: #ሳራ ሙሉነህ ,A.A Medical college, Nursing ,BSc. #ጌታቸው ሳሙኤል,ከአኵሱም ዩኒቨርሲቲ, Electrical Engineering ,BSc #ሮቤል ገ/መድኀን , ሚዛን ቴፒ ዩኒቨርሲቲ, Civil Engineering, BSc #ካሌብ አየነው, ኮተቤ ሜ/ፖ ዩኒቨርሲቲ,Sport Science, BA #ቤተልሔም ኢዮብ ,CPU college, Accounting, diploma 🧑‍🎓👩‍🎓

መልዕክት ከምስካየ ኅዙናን መድኀኔዓለም ገዳም ተምሮ ማስተማር ሰ/ት/ት ቤት "ወንድሞች በኅብረት ቢቀመጡ፥ እነሆ መልካም ነው፤ እነሆም ያማረ ነው" (መዝ. ፻፴፪፥፩) አጥቢያ ሰንበት ትምህርት ቤታችን የኾነው የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለም እና ደብረ ትጉኃን ቅዱስ ገብርኤል ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ት/ቤት በገጠመው "የቋሚ ቦታ ይሰጠን" ጥያቄ መሠረት፣ ከባድ ፈተና ላይ መውደቁ ይታወቃል! የፈተናዎች ኹሉ መውጫ መድኃኔዓለም ነውና፣ የወንድሞቻችንን እና የእኅቶቻችንን ችግር ሲያሳስበው የቆየው ሰንበት ት/ቤታችን ረቡዕ ከቀን 15 እስከ ቀን 17 ድረስ ለሦስት ቀን የሚቆይ የጸሎት መርሐ ግብር ከቀኑ 11:30 ጀምሮ ተዘጋጅቷል። ስለ ኾነም በጸሎት መርሐ ግብሩ ትሳተፉ ዘንድ፣ የሰንበት ትምህርት ቤቱ ችግር ተፈቶ ማየት የምትናፍቁ ኹሉ ተጠርታችኋል። "ኑ በጋራ ወደ ሐዘንተኞች መጠጊያ ለኾነ መድኀኔዓለም እናመልክት" አድራሻ፦ 6ኪሎ ዩኒቨርስቲ ከፍ ብሎ፣ ምስካየ ሕዙናን መድኀኔዓለም ገዳም፣ ተምሮ ማስተማር ሰንበት ት/ቤት አዳራሽ።

#ምኵራብ፤ ሦስተኛው ሳምንት ሦስተኛው ሳምንት ምኵራብ ይባላል፡፡ ጌታ በምኵራብ ማስተማሩን የሚዘከርበት ሳምንት ሲሆን ‹‹#ቦአ_ኢየሱስ_ምኩራበ_አይሁድ›› የሚልና ይህን የመሰለ ጌታ በምኩራብ ማስተማሩን የሚያዘክር ምስጋና የሚቀርብበት ሳምንት ነው፡፡ በብሉይ ኪዳን ዘመን በኢሩሳሌም የአይሁድ ቤተመቅደስ ነበራቸው፡፡ ናቡከደነጾር ኢየሩሳሌምን በወረረ ጊዜ ግን ቤተመቅደሱን አፈረሰ፤ ሕዝቡንም ወደ ባቢሎን አፈለሰ፡፡ ከዚህ ጊዜ ጀምሮ አይሁድ በሚኖሩባቸው ስፍራዎች ሁሉ ለጸሎት ቤት ይሰሩ ነበር፤ በዚህም ምክንያት ጌታችን መድኃኒታችንኢየሱስ ክርስቶስ በኢየሩሳሌም እየተዘዋወረ በሚያስተምርበት ጊዜ ብዙ ምኵራቦች ነበሩ፡፡ ሐዋርያት በሚያስተምሩበት ወቅት ከአንዳንድ ቦታዎች በቀር በምኵራቦች ገብተው ወንጌልን አስተምረዋል፡፡ በብሉይ ዘመን ቢያንስ ዐስር የጎለመሱ ወንዶች (የቤተሰብ ኃላፊዎች) በቦታው ከተገኙ እነዚህን ምኵራቦችን ለመስራት ይፈቀድላቸው ነበር፡፡ ነገር ግን ዋናው ቤተ መቅደሱ ያለው በኢየሩሳሌም ብቻ ነበር፡፡ በምኵራብ ውስጥም የኦሪት የሕግ መጻሕፍትና በቅዱሳን ነቢያት የተጻፉ ጽሑፎች በብራና ጥቅልል ይገኛሉ፡፡ ምዕመኑ እንዲሰማቸው እንደ መድረክ ባለ ቦታ ላይ ካህናትና መምህራን ቆመው መጻሕፍትን ያነባሉ፤ ቃለ እግዚአብሔርንም ያስተምሩ ነበር፡፡ በኦሪቱ ምኵራብን የሚመሩት አለቆች ጥፋተኛ ሰው ሲገኝ፤ በመግረፍ ወይም ከምኵራብ በማስወጣት ሊቀጡ ስልጣን ነበራቸው፡፡ አገልጋይ ወይም የሚራዱ ወጣቶችም ልጆችን በማስተማር ጥቅሎችን በማቅረብ በተጨማሪ የአለቆችን ትዕዛዝ በመፈጸም ያገለግላሉ፡፡ በየሰንበቱ ሕዝብ ሁሉ በምኵራብ ተሰብስበው አምልኮታቸውን ይፈጸሙ ነበር፤ በአምልኮታቸው ውስጥም ጸሎት፤ ከሕግና ከነቢያት ንባብ፤ ስብከትና ቡራኬ ነበር፡፡ በዚህ በምኩራብ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሰንበት ተገኝቶ ሕዝቡን አስተምሯል፤ ሕሙማንን ፋውሷል፡፡ #የኢሳይያስን_መጽሐፍ_ምዕራፍ_፷፩ን አንብቧል፡፡ በዚህ በዐቢይ ጾም ሦስተኛ ሳምንት(ምኵራብ) የሚታሰበውም ይህ ነው፡፡ ፨ ‹‹ወደ አደገበትም ወደ ናዝሬት መጣ፤ እንደ ልማዱም በሰንበት ቀን ምኵራብ ገባ ሊያነብም ተነሳ፡፡›› ሉቃ. 4፥16 ፨ ‹‹ወደ ገዛ አገሩም መጥቶ እስኪገረሙ ድረስ በሚገባቸው ያስተምራቸው ነበር፡፡›› ማቴ. 13፥52 ፨ ‹‹ሰንበትም በሆነ ጊዜ በምኵራብ ያስተምር ጀመር፡፡››ማር 6፥1 ፨ በዕለቱ ቅዳሴ ላይ የሚነበቡ ምንባባትም፤ #ጌታችን_ቤተ_መቅደሱን_የንግድ_ማዕከል_ያደረጉትን_ዓይቶና_አዝኖ_ነጋዴዎቹን_ከነመንጋቸው_በጅራፍ_እንዳስወጣቸውና ‹‹ይህን ቤተ መቅደስ አፍርሱት በሦስተኛው ቀን እኔ እሠራዋለሁ፡፡›› ብሎ ስለመ ሞቱና ስለ ትንሣኤው ማስተማሩን የሚገልጽ ነው፡፡ ፨፨፨ ወስብሐት ለእግዚአብሔር ፨፨፨ Facebook https://www.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool YouTube https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w Telegram https://t.me/medihanaelem

Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት - Telegram kanali @finotehiwott statistikasi va tahlili