ch
Feedback
Commercial Bank of Ethiopia - Official

Commercial Bank of Ethiopia - Official

前往频道在 Telegram

Commercial Bank of Ethiopia is the leading bank in Ethiopia, established in 1942. Pioneer to introduce modern banking to the country with 1,971 branches and service outlet across the country. @ www.facebook.com/combanketh @ www.twitter.com/combankethiopia

显示更多

📈 Telegram 频道 Commercial Bank of Ethiopia - Official 的分析概览

频道 Commercial Bank of Ethiopia - Official (@combankethofficial) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 210 703 名订阅者,在 经济与金融 类别中位列第 267,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 77

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 210 703 名订阅者。

根据 01 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 2 600,过去 24 小时变化为 184,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 已认证(Telegram 官方确认)
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 8.74%。内容发布后 24 小时内通常能获得 5.34% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 18 411 次浏览,首日通常累积 11 249 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 36

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
Commercial Bank of Ethiopia is the leading bank in Ethiopia, established in 1942. Pioneer to introduce modern banking to the country with 1,971 branches and service outlet across the country. @ www.facebook.com/combanketh @ www.twitter.com/combanketh...

凭借高频更新(最新数据采集于 02 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 经济与金融 类别中的关键影响点。

210 703
订阅者
+18424 小时
+6297
+2 60030
帖子存档
588 ቢሊየን ብር ለግሉ ዘርፍ! 90.7% የብድር ድርሻ ለኢኮኖሚው ዋና አንቀሳቃሽ ======================= "የግሉን ዘርፍ ማበረታታት የሀገር ኢኮኖሚ ፈጣን ዕድገትን የሚያረጋግጥ ቁልፍ ኃይል ነው" ሲሉ አቶ አቤ ሳኖ ገልጸዋል። በ2018 የበጀት ዓመት ከተለቀቀው 648 ቢሊየን ብር ጠቅላላ ብድር ውስጥ 588.11 ቢሊየን ብር (90.7%) ለግሉ ዘርፍ መመደቡ፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለሀገሪቱ ኢኮኖሚ ዕድገት፣ ለኢንቨስትመንት፣ ለሥራ ፈጠራ እና ለአምራችነት የሚያደርገውን ጠንካራ አስተዋፅኦ ያንጸባርቃል።

707.47 ቢሊየን ብር ========== ይህ ቁጥር የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት ወስጥ ብቻ ያሰባሰበው ተቀማጭ ሲሆን ከስድስት አመት የሰባስብ ከነበረው ተቀማጭ የ 13 እጥፍ ነው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሁሌም የሚተማመኑበት ባንክ! #CBE #CommercialBankOfEthiopia #Success #Performance

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በቀጣዩ አዲስ የበጀት ዓመት ከ1 ትሪሊየን ብር በላይ ብድር ማዘጋጀቱን አስታወቀ። ህብረተሰቡ የብድሩ ተጠቃሚ እንዲሆን ጥሪ አቶ አቤ ሳኖ አቅርበዋል።

የአቶ አቤ ምስጋና! **** የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ ባንካችን በ2018 በጀት ዓመት ላስመዘገበው ስኬት መሠረት ለሆኑት መላው ደንበኞች ታላቅ ምስጋና አቅርበዋል። አቶ አቤ አስቻይ የኢኮኖሚ ሥርዓት በሀገራችን መዘርጋቱ ለተመዘገበው ውጤት ምክንያት በመሆኑ ይህን ላደረገው መንግስት ምስጋና አቅርበዋል። በገበያው ላይ ተወዳዳሪ ሆኖ የላቀውን ድርሻ ለመውሰድ ትልቅ ቁርጠኝነትን እንደሚጠይቅ የገለፁት አቶ አቤ፣ ለመላው የባንኩ ሠራተኞች እና አመራሮች ትጋት እና ቁርጠኝነት እንዲሁ ላቅ ያለ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የባንካችንን መልካም ነገር ለህዝባችን ለሚያደርሱት የሚዲያ አካላትም ከአቶ አቤ ታላቅ ምስጋና ተችሯቸዋል። ***** የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሁሌም የሚተማመኑበት ባንክ! #cbe #commercialbankofethiopia #Profit #performance

ስፔን ከ ኦስትሪያ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ በሀገሬ ቴሌቪዥን ***** የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የ2026 የፊፋ ዓለም ዋንጫ ጨዋታዎችን በስያሜ ስፖንሰርነት በሀገሬ ቴሌቪዥን በቀጥታ ስርጭት ሲያቀርብላችሁ ታ
ስፔን ከ ኦስትሪያ  የጥሎ ማለፍ ጨዋታ በሀገሬ ቴሌቪዥን ***** የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የ2026 የፊፋ ዓለም ዋንጫ ጨዋታዎችን በስያሜ ስፖንሰርነት በሀገሬ ቴሌቪዥን በቀጥታ ስርጭት ሲያቀርብላችሁ ታላቅ ደስታ ይሰማዋል፡፡ ዛሬ ምሽት 4፡00 ሰዓት ስፔን ከ ኦስትሪያ የሚያደርጉትን የጥሎ ማለፍ ጨዋታ በሀገሬ ቴሌቪዥን በቀጥታ ስርጭት እንድትከታተሉ እንጋብዛለን። **** የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሁሌም የሚተማመኑበት ባንክ! #cbe #hageretv #FWC26 #WeAre26 #FIFAWorldCup #WorldCup2026 #Somos26

የተከበራችሁ የባንካችን ደንበኞች፡ ቀነ ገደቡ ሰኔ 30 ከመጠናቀቁ በፊት ሂሳባችሁን ከፋይዳ መታወቂያችሁ ጋር አስተሳስሩ! ************** የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በሰጠው መመሪያ መሠረት የባ
የተከበራችሁ  የባንካችን ደንበኞች፡ ቀነ ገደቡ ሰኔ 30 ከመጠናቀቁ በፊት ሂሳባችሁን ከፋይዳ መታወቂያችሁ ጋር አስተሳስሩ! ************** የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በሰጠው መመሪያ መሠረት የባንክ ሂሳብ ከፋይዳ መታወቂያ ጋር ለማስተሳሰር እስከ ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም ቀነ ገደብ በተሰጠባቸው ከተሞች የምትገኙ የባንካችን ደንበኞች ቀነ ገደቡ ሊጠናቀቅ ጥቂት ቀናት ብቻ ስለቀሩት የማስተሳሰሩን ሥራ በአፋጣኝ በመፈፀም ራሳችሁን ከአላስፈላጊ መጉላላት እንድትጠብቁ እናሳስባለን።    የማስተሳሰር ቀነ ገደቡ እስከ ግንቦት 06 ቀን 2018 ዓ.ም በነበረባቸው ከተሞች የምትገኙ እና በወቅቱ ያላስተሳሰራችሁ ደንበኞች እንዲሁ ሂሳባችሁን ከፋይዳ መታወቂያችሁ ጋር በማስተሳሰር በሂሳባችሁ ላይ ወጪ ከማድረግ የተጣለውን እግድ ማስነሳት እንደምትችሉ እንገልፃለን።    ደንበኞች የፋይዳ መታወቂያ ቁጥራቸውን (FAN) ይዘው በባንካችን ቅርንጫፎች በመገኘት ወይም ባሉበት ሆነው በበይነ መረብ ማስተሳሰሪያ አማራጭ (https://cbefayda.cbe.com.et) ሂሳባቸውን ከፋይዳ መታወቂያቸው ጋር ማስተሳሰር ይችላሉ።   በዚህ አጋጣሚ የፋይዳ መታወቂያ ያላወጣችሁ ደንበኞች ወደሚቀርባችሁ የባንካችን ቅርንጫፍ ማንነታችሁን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ይዛችሁ በመቅረብ መመዝገብ እና የፋይዳ ቁጥራችሁን ማግኘት የምትችሉ መሆኑን በአክብሮት እናሳውቃለን። ******* የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሁሌም የሚተማመኑበት ባንክ! #cbe #fayda

የዓመቱ የመጨረሻ ሩጫ እንዳያመልጥዎ! ******* የእንጦጦ ፓርክ ሲቢኢ ሩጫ (ENTOTO PARK CBE RUN) የዓመቱ የመጨረሻ ሩጫ ቅዳሜ ሰኔ 27 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል፡፡ በውድድሩ ለመሳተ
የዓመቱ የመጨረሻ ሩጫ እንዳያመልጥዎ! ******* የእንጦጦ ፓርክ ሲቢኢ ሩጫ (ENTOTO PARK CBE RUN) የዓመቱ የመጨረሻ ሩጫ ቅዳሜ ሰኔ 27 ቀን 2018 ዓ.ም ይካሄዳል፡፡ በውድድሩ ለመሳተፍ ትኬቱን ባሉበት በሲቢኢ ብር ፕላስ መተግበሪያ ሚኒ አፕስ በነፃ አሁኑኑ ይቁረጡ! ለበለጠ መረጃ፡ www.entotoparkcberun.com ******** ሲቢኢ ብር ፕላስ መተግበሪያ ለመጫን የሚከተሉትን ሊንኮች ይጠቀሙ፡ ለአንድሮይድ ስልኮች፡ https://play.google.com/store/apps/details?id=prod.cbe.birr ለአይፎን ስልኮች፡ https://apps.apple.com/us/app/cbebirr/id1600841787 #cbe #cbebirr #cbebirrplus #ethiopia #greatethiopianrun #entotopark

ተጨማሪ ጉርሻ ያግኙ! **** ውድ ደንበኞቻችን፡ ከውጭ ሀገራት በ #EthioDirect ፣ #CashGo ፣ #Botim ፣ #WegenSend ፣ #LakiRemit ፣ #EthioPay ፣ #ArifPay ፣
ተጨማሪ ጉርሻ ያግኙ! **** ውድ ደንበኞቻችን፡ ከውጭ ሀገራት በ #EthioDirect ፣ #CashGo ፣ #Botim ፣ #WegenSend ፣ #LakiRemit ፣ #EthioPay ፣ #ArifPay ፣  #ArkiSend  ፣ #50Lomi  ፣ #DestaPay እና #MojoMoney ዲጂታል የገንዘብ መላኪያ መተግበሪያዎች ገንዘብ ሲላክልዎ በእለታዊ የውጭ ምንዛሬ የመሸጫ ተመን ላይ ተጨማሪ 7.881 በመቶ ጉርሻ፤  እንዲሁም ከባንካችን ጋር በሚሠሩ ዓለም አቀፍ የሐዋላ አስተላላፊዎች በኩል ገንዘብ ሲላክልዎ በእለታዊ የውጭ ምንዛሬ የመሸጫ ተመን ላይ ተጨማሪ 7.25 በመቶ  ጉርሻ የምናበረክትልዎ መሆኑን በደስታ እንገልፃለን! *** የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሁሌም የሚተማመኑበት ባንክ! For more currency exchange rates: https://combanketh.et/exchange-rates?srcPage=home #exchangerate #CBE #commercialbankofethiopia #Birr #rate #currency #Ethiopia combanketh.et

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አዲስ በተጀመረው የበጀት ዓመት ከ1 ትሪሊየን ብር በላይ ብድር ማዘጋጀቱን አስታወቀ። ********** በዋናው መስሪያ ቤት ዛሬ በተሰጠው ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም መግለጫ ላይ የባንካችን ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ እንደተናገሩት ባንካችን የብድር ተደራሽነቱን ለማስፋት በሚያደርገው ጥረት ዲጂታል የብድር አማራጮችን ጨምሮ የተበዳሪዎችን ቁጥር ከ1.17 ሚሊዮን በላይ ማድረስ ተችሏል። አቶ አቤ ዛሬ በጀመርነው በጀት ዓመት ባንካችን ባለፈው በጀት ዓመት ሰጥቶ ከነበረው የብድር መጠን 68.7 በመቶ በመጨመር ከአንድ ትሪሊየን ብር (ብር 1,092,990,000) በላይ ብድር ማዘጋጀቱን ገልጸው፣ ህብረተሰቡ የብድሩ ተጠቃሚ እንዲሆን ጥሪ አቅርበዋል።

በኢትዮጵያ 70 በመቶ የሚሆነው ዲጂታል ክፍያ የሚፈጸመው በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዲጂታል የክፍያ አማራጮች መሆኑ ተገለጸ። ******* ዛሬ የባንካችን ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ በዋናው መስሪያ ቤት በ
+5
በኢትዮጵያ 70 በመቶ የሚሆነው ዲጂታል ክፍያ የሚፈጸመው በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዲጂታል የክፍያ አማራጮች መሆኑ ተገለጸ። ******* ዛሬ የባንካችን ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ በዋናው መስሪያ ቤት በሰጡት መግለጫ እንዳመለከቱት፤ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከሚንቀሳቀሰው ጠቅላላ የገንዘብ መጠን 90 በመቶ የሚሆነው ባንካችን በዘረጋው ዲጂታል የክፍያ ስርዓት ሲሆን፣ ይህም ኢትዮጵያ ውስጥ በዲጂታል የክፍያ አማራጮች ከሚንቀሳቀሰው የገንዘብ መጠን ውስጥ 70 በመቶ የሚሆነውን የገበያ ድርሻ መያዝ እንዳስቻለው አመልክተዋል። በተጠናቀቀው በጀት ዓመት 22.24 ትሪሊየን ብር የግብይት መጠን ያላቸው 3.48 ቢሊዮን ዲጂታል ግብይቶች ተከናውነዋል ያሉት አቶ አቤ፣ ለተመዘገበው የላቀ አፈፃፀም ደንበኞችን እና የባንኩን ሰራተኞች አመስግነዋል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በተለያዩ የአፈፃፀም መለኪያዎች ከፍተኛ ውጤት አስመዘገበ። · አቶ አቤ ሳኖ ደንበኞችን ጨምሮ ለተገኘው ከፍተኛ ውጤት ድርሻ ለነበራቸው ሁሉ ምስጋና አ
+9
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በተለያዩ የአፈፃፀም መለኪያዎች ከፍተኛ ውጤት አስመዘገበ። ·         አቶ አቤ ሳኖ ደንበኞችን ጨምሮ ለተገኘው ከፍተኛ ውጤት ድርሻ ለነበራቸው ሁሉ ምስጋና አቅርበዋል **************   የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የተመዘገበውን አፈፃፀም በተመለከተ በተዘጋጀ ጋዜጣዊ መግለጫ  ላይ እንደተናገሩት ባንካችን  በተለያዩ የአፈፃፀም መለኪያዎች ከፍተኛ ውጤት ያስመዘገበ ሲሆን የገበያ ድርሻውንም ማሳደግ ችሏል።   ባንካችን  ትናንት ባጠናቀቅነው በጀት ዓመት ከ707.4 ቢሊየን ብር በላይ ተቀማጭ ገንዘብ በማሰባሰብ ታላቅ ስኬት ያስመዘገበ ሲሆን ጠቅላላ ተቀማጭ ገንዘቡ ከ2.4 ትሪልዮን ብር በላይ ተሻግሯል።    በአገራችን ባንኮች ታሪክ ይህን ያህል ተቀማጭ ገንዘብ በአንድ ዓመት ውስጥ ሲሰበሰብ በታሪክ የመጀመሪያው መሆኑን የገለፁት አቶ አቤ፣ የባንኩ ጠቅላላ ተቀማጭ ከ6 ዓመት በፊት ከነበረው በ4 እጥፍ ማደጉን አመልክተዋል።   ባንካችን ባለፈው በጀትዓመት ከ648.02 ቢሊዮን ብር በላይ ብድር መስጠቱን የገለፁት አቶ አቤ፣ ከ90.7 በመቶ በላይ (588.11 ቢሊዮን ብር) የሚሆነው ብድር ለግሉ ዘርፍ መሰጠቱን ገልፀዋል።   አቶ አቤ በ2019/20 በጀት ዓመት ባንኩ ከሰጠው ብድር ለግሉ ዘርፍ የተሰጠው 10 በመቶ አካባቢ እንደነበር ገልፀው፣ የዘንድሮው አፈፃፀም ባንኩ ለግሉ ዘርፍ የሰጠውን ከፍተኛ ትኩረት እንደሚያሳይ ገልፀዋል።   በባንካችን የተሰጠ ጠቅላላ የብድር መጠን 1.64 ትርሊዮን ብር መድረሱንም ነው አቶ አቤ የገለፁት።   ባንካችን በብድር አሰባሰብም ያስመዘገበው ውጤት ከፍተኛ መሆኑን የገለፁት አቶ አቤ፣ 546.26 ቢሊዮን ብር ብድር መሰብሰቡን አመልክተዋል።   አቶ አቤ የባንኩ የተበላሸ ብድር ምጣኔ ከ1.4 በመቶ በታች እንደነበር ገልፀው፣ ይህም ባንካችን በብድር አሰባሰብ ዙሪያ እየሠራ ያለውን ውጤታማ ሥራ እንደሚያመለክት አስረድተዋል።   በውጭ ምንዛሬ ግኝትም በተመሳሳይ ከፍተኛ ውጤት መመዝገቡን የገለፁት አቶ አቤ፣ በዓመቱ ከ5.6 ቢሊዮን ዶላር በላይ ማግኘቱን ተናግረዋል።   በዲጂታል ክፍያ ዘርፍም ከፍተኛ ውጤት እንደተመዘገበ የገለፁት አቶ አቤ፣ በዓመቱ በ3.48 ቢሊዮን የገንዘብ ዝውውሮች ከ22.24 ትሪሊዮን ብር በላይ ገንዘብ በባንካችን ዲጂታል የክፍያ አማራጮች መንቀስቀሱን አስረድተዋል።   የባንካችን ዲጂታል የክፍያ አፈፃፀም በሀገር ደረጃ 70 በመቶ ድርሻ እንዳለው እና ይህም በዲጂታል ክፍያ ዘርፍ ባንካችን የሀገራችን ዋልታ መሆኑን ያስመሰከረበትእንደሆነ አቶ አቤ አመልክተዋል።     አቶ አቤ ባንካችን በአጠቃላይ የገበያ ድርሻውን ያሳደገበትን አፈፃፀም ማስመዝገቡን ገልፀው፣ በተቀማጭ ገንዘብ 50.1 በመቶ፣ በብድር 48.3 በመቶ፣ በጠቅላላ ሀብት 50.1 በመቶ እንዲሁም በካፒታል 45.4 በመቶ የገበያ ድርሻ መያዙን አስረድተዋል።   አቶ አቤ ባንካችን ላስመዘገበው የላቀ ውጤት ባንካችንን አምነው አብረው እየሠሩ ያሉ  ደንበኞች ከፍተኛ ምስጋና እንደሚገባቸው ገልፀዋል።   የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጥሩ መልክ የሀገር መልክ ነፀብራቅ መሆኑን የገለፁት አቶ አቤ፣ አስቻይ የኢኮኖሚ ሥርዓት በሀገራችን መዘርጋቱ ለተመዘገበው ውጤት ምክንያት በመሆኑ ይህን ላደረገው መንግስት ምስጋና አቅርበዋል።   በገበያው ላይ ተወዳዳሪ ሆኖ የላቀውን ድርሻ ለመውሰድ ትልቅ ቁርጠኝነትን እንደሚጠይቅ የገለፁት አቶ አቤ፣ ለመላው የባንኩ ሠራተኞች ትጋት እና ቁርጠኝነት እንዲሁ ላቅ ያለ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።   የባንካችንን መልካም ነገር ለህዝባችን ለሚያደርሱት የሚዲያ አካላትም ከአቶ አቤ ታላቅ ምስጋና ተችሯቸዋል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በታሪኩ ከፈተኛ የሆነውን ከ80 ቢሊዮን ብር በላይ ትርፍ አስመዘገበ። ******* ባንካችን በተለያዩ የአፈፃፀም መለኪያዎች ከፍተኛ ውጤት ባስመዘገበበት የተጠናቀቀው የ2018
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በታሪኩ ከፈተኛ የሆነውን ከ80 ቢሊዮን ብር በላይ ትርፍ አስመዘገበ። ******* ባንካችን በተለያዩ የአፈፃፀም መለኪያዎች ከፍተኛ ውጤት ባስመዘገበበት የተጠናቀቀው የ2018 በጀት ዓመት (2025/26FY) ከ272 ቢሊዮን ብር በላይ ገቢ በማግኘት ከ80 ቢሊዮን ብር በላይ ትርፍ ማስመዝገብ ችሏል።   የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሪዚዳንት አቶ አቤ ሳኖ የዓመቱን አፈፃፀም በተመለከተ በተዘጋጀ ጋዜጣዊ መግለጫ  ላይ እንደተናገሩት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የተመዘገበው የትርፍ መጠን ካለፈው  በጀት ዓመት ተመሳሳይ ወቅት አፈፃፀም ጋር ሲነፃፀር የ146.3 በመቶ ብልጫ ያለው ነው።   አቶ አቤ ባንካችን ዛሬ በተጀመረው በጀት ዓመት 120 ቢሊዮን ብር ትርፍ ለማግኘት እንደታቀደም ተናግረዋል።

እንኳን ደስ አላችሁ፤ እንኳን ደስ አለን! የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በአንድ ዓመት ውስጥ ከ707.4 ቢሊዮን ብር በላይ ተቀማጭ ገንዘብ በማሰባሰብ ታሪካዊ አፈፃፀም አስመዘገበ። ***************
እንኳን ደስ አላችሁ፤ እንኳን ደስ አለን!   የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በአንድ ዓመት ውስጥ ከ707.4 ቢሊዮን ብር በላይ ተቀማጭ ገንዘብ በማሰባሰብ ታሪካዊ አፈፃፀም አስመዘገበ። ********************   የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ባጠናቀቅነው የ2018 በጀት ዓመት (2025/26 FY) ከ707.4 ቢሊዮን ብር በላይ ተቀማጭ ገንዘብ በማሰባሰብ ጠቅላላ ተቀማጭ ገንዘቡን ከ2.4 ትሪልዮን ብር በላይ በማድረስ ታሪካዊ ውጤት አስመዝግቧል።    የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ይህ ታሪካዊ ውጤት እንዲመዘገብ ላስቻሉት መላው የባንኩ ደንበኞች ታላቅ ምስጋና ያቀርባል!   ****** የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሁሌም የሚተማመኑበት ባንክ!

ዴሞክራቲክ ኮንጎ ከ እንግሊዝ የጥሎ ማለፍ ጨዋታ በሀገሬ ቴሌቪዥን ***** የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የ2026 የፊፋ ዓለም ዋንጫ ጨዋታዎችን በስያሜ ስፖንሰርነት በሀገሬ ቴሌቪዥን በቀጥታ ስርጭት ሲያቀ
ዴሞክራቲክ ኮንጎ ከ እንግሊዝ  የጥሎ ማለፍ ጨዋታ በሀገሬ ቴሌቪዥን ***** የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የ2026 የፊፋ ዓለም ዋንጫ ጨዋታዎችን በስያሜ ስፖንሰርነት በሀገሬ ቴሌቪዥን በቀጥታ ስርጭት ሲያቀርብላችሁ ታላቅ ደስታ ይሰማዋል፡፡ ዛሬ ምሽት 1፡00 ሰዓት ዴሞክራቲክ ኮንጎ ከ እንግሊዝ  የሚያደርጉትን የጥሎ ማለፍ ጨዋታ በሀገሬ ቴሌቪዥን በቀጥታ ስርጭት እንድትከታተሉ እንጋብዛለን። **** የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሁሌም የሚተማመኑበት ባንክ! #cbe #hageretv #FWC26 #WeAre26 #FIFAWorldCup #WorldCup2026 #Somos26

ምቾትዎ እንደተጠበቀ ባሉበት ሂሳብዎን ያስተዳድሩ! ************ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የኢንተርኔት ባንኪንግ አገልግሎት በማንኛውም ሰዓት፣ በየትኛውም ቦታ እና ሀገር ሆነው ሂሳብዎን በአግባቡ
ምቾትዎ እንደተጠበቀ ባሉበት ሂሳብዎን ያስተዳድሩ! ************ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የኢንተርኔት ባንኪንግ አገልግሎት በማንኛውም ሰዓት፣ በየትኛውም ቦታ እና ሀገር ሆነው ሂሳብዎን በአግባቡ ማስተዳደር ይችላሉ! • ደመወዝ ለመክፈል እና ሌሎችንም ክፍያዎች ለመፈፀም • ግብርዎን ለመክፈል • የአየር ትኬት ለመቁረጥ • የረዥም ጊዜ የባንክ ሂሳብ መግለጫ ለማግኘት • ለሌሎችም በርካታ አገልግሎቶች በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የኢንተርኔት ባንኪንግ አገልግሎት ይጠቀሙ፡፡ አገልግሎቱን ለማግኘት በአቅራቢያዎ ወደሚገኝ የባንካችን ቅርንጫፍ ጎራ ይበሉ! *************** የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሁሌም የሚተማመኑበት ባንክ! #cbe #digitalbanking #banking #ethiopia #internetbanking

ተጨማሪ ጉርሻ ያግኙ! **** ውድ ደንበኞቻችን፡ ከውጭ ሀገራት በ #EthioDirect ፣ #CashGo ፣ #Botim ፣ #WegenSend ፣ #LakiRemit ፣ #EthioPay ፣ #ArifPay ፣
ተጨማሪ ጉርሻ ያግኙ! **** ውድ ደንበኞቻችን፡ ከውጭ ሀገራት በ #EthioDirect ፣ #CashGo ፣ #Botim ፣ #WegenSend ፣ #LakiRemit ፣ #EthioPay ፣ #ArifPay ፣  #ArkiSend  ፣ #50Lomi  ፣ #DestaPay እና #MojoMoney ዲጂታል የገንዘብ መላኪያ መተግበሪያዎች ገንዘብ ሲላክልዎ በእለታዊ የውጭ ምንዛሬ የመሸጫ ተመን ላይ ተጨማሪ 7.881 በመቶ ጉርሻ፤  እንዲሁም ከባንካችን ጋር በሚሠሩ ዓለም አቀፍ የሐዋላ አስተላላፊዎች በኩል ገንዘብ ሲላክልዎ በእለታዊ የውጭ ምንዛሬ የመሸጫ ተመን ላይ ተጨማሪ 7.25 በመቶ  ጉርሻ የምናበረክትልዎ መሆኑን በደስታ እንገልፃለን! *** የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሁሌም የሚተማመኑበት ባንክ! For more currency exchange rates: https://combanketh.et/exchange-rates?srcPage=home #exchangerate #CBE #commercialbankofethiopia #Birr #rate #currency #Ethiopia combanketh.et

photo content
+3