ch
Feedback
የጥበብ ማዕድ

የጥበብ ማዕድ

关闭频道

ዝም ብለህ ተቀላቀል! https://t.me/+EpyhX7mXLpE5MDc8 የጥበብ

显示更多

📈 Telegram 频道 የጥበብ ማዕድ 的分析概览

频道 የጥበብ ማዕድ 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 318 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 5 524,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 224

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 318 名订阅者。

根据 03 九月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -469,过去 24 小时变化为 -15,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 6.03%。内容发布后 24 小时内通常能获得 1.93% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 924 次浏览,首日通常累积 296 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 11

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
ዝም ብለህ ተቀላቀል! https://t.me/+EpyhX7mXLpE5MDc8 የጥበብ

凭借高频更新(最新数据采集于 04 九月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。

15 318
订阅者
-1524 小时
-1017 天
-46930 天
帖子存档
አይን ያለውን ጥርስ ያህል ጥርስም ጥርስ የለውም!

#አንዳንዴ ደህና መሆንህ ሕክምና ባለማድረግህም ሊሆን ይችላል።

የሆነው ሁሉ ባይሆን ዛሬ የተለየ ቀን ይሆን ነበር። .

፡ የሔደን ስንወቅስ        ባጠፋው ረግመን ዛሬ ሚባል ጠፋን             ፍርሐት ደጋግመን ፡ የነካካን ሁሉ          መስሎን ረብ የለሽ በተዋበ ሰማይ      በበጋው ገላችን                 ከደመና ስንሸሽ ከእልፍኝ ከተምን      መግፋትም ታደልን              በምላሳችን ላንቃ እውነት መቼ ኖረን        እድሜ ተደርድሮ                   ህይወት ግን እቃቃ።         አቡ(አላዛር ቴዎድሮስ)

ከውሸት በላይ ጎጂ እውነት የለም።

እንዴት ነው!?
እንዴት ነው!?

ፍርሐት የገደለህ ቀን ብልጥ ሰዎች ይቀብሩሃል።

🙂
🙂

እየሠሩ መጠየቅ ና እየጠየቁ መስራት አንድ አይደሉም።

At the end of the day እንዳይሆኑብን የፈራናቸው መጥፎ ነገሮች እንዳሰብነው መጥፎ አደሉም፤ እንዲሆኑልንም የጓጓንላቸው ጥሩ ነገሮች አደሉም። በፈራነው አልጠፋንም ፤ በጓጓነውም አላረፍንም�
At the end of the day እንዳይሆኑብን የፈራናቸው መጥፎ ነገሮች እንዳሰብነው መጥፎ አደሉም፤ እንዲሆኑልንም የጓጓንላቸው ጥሩ ነገሮች አደሉም። በፈራነው አልጠፋንም ፤ በጓጓነውም አላረፍንም🙂

አንዳንዴ ማትጣላው ሰው ያስቀይምሃል። ...

‎በራሴ ላይ የጨከንኩ ይመስለኛል። ‎ይህን ሐሳብ ዛሬ በድንገት አላሰብኩትም። ለረጅም ጊዜ በውስጤ እየተጓዘ ነበር፤ እኔ ግን ስሙን አልጠራሁትም። ራሴን ስወቅስ፣ ስገስጽ፣ ስጠይቅ እና ከራሴ በጣም ብዙ ነገር ስጠብቅ እንደ ጥንካሬ ነበር የምቆጥረው። ‎ ‎በአንዱ ምሽት ግን ብቻዬን ተቀምጬ ነበር። ቤቱ ጸጥ ብሏል። ስልኬ ከጎኔ ተዘግቷል። ማንም የሚያየኝ የለም። ማንም የምናገረውን የሚሰማ የለም። በዚያ ጸጥታ ውስጥ ግን አንድ ድምፅ በጣም ግልጽ ሆኖ ተሰማኝ። ‎ ‎የራሴ ድምፅ። ‎ ‎“እንዴት እንዲህ አደረግሽ?” ‎ ‎“ይህን እንዴት አላየሽም?” ‎ ‎“ከዚህ በላይ ማሰብ አትችዪም ነበር?” ‎ ‎እነዚህን ጥያቄዎች ብዙ ጊዜ ሰምቻቸዋለሁ። ከሌሎች ሰዎች ሳይሆን ከራሴ። ‎ ‎ሌላ ሰው ሲሳሳት ግን ታሪኩን ለመስማት እሞክራለሁ። ምን እንዳደረገ ብቻ አልመለከትም፤ ምን እንዳስገደደው፣ ምን እንዳስፈራው፣ ምን እንደጎዳው እጠይቃለሁ። ‎ ‎እኔ ስሳሳት ግን ታሪኬን እረሳለሁ። ‎ ‎ስህተቱን ብቻ አያለሁ። ‎ ‎ምናልባት ይህ ነው በራሴ ላይ የጨከንኩበት ቦታ። ‎ ‎ከራሴ የጠበቅኩት ነገር በጣም ብዙ ነበር። ሁልጊዜ ጠንካራ እንድሆን ፈለግሁ። ሁልጊዜ ትክክል እንድሆን ፈለግሁ። ሰዎች ሲሄዱ እንዳልሰበር፣ ነገሮች ሲያልቁ እንዳልወድቅ፣ ሕይወት ሲከብድ እንዳልደክም ከራሴ ጠበኩ። ‎ ‎ ማልቀስ እንኳን እንደ ድክመት የቆጠርኩበት ጊዜ አለ። ‎ ‎“በርቺ።” ‎ ‎ይህን ቃል ለራሴ ብዙ ጊዜ ተናግሬያለሁ። ‎ ‎ግን አንዳንድ ጊዜ ሰው መበርታት አያስፈልገውም። አንዳንድ ጊዜ መደገፍ ይፈልጋል። አንዳንድ ጊዜ “ትችያለሽ” የሚል ሰው ሳይሆን፣ “እንኳንም አልቻልሽ፤ እረፊ” የሚል ድምፅ ያስፈልገዋል። ‎ ‎ያን ምሽት ራሴን ለረጅም ጊዜ አሰብኳት። ‎ ‎ስንት ጊዜ ተሰብራ እንደተነሳች አሰብኩ። ‎ ‎ስንት ጊዜ ማንም ሳያውቅ እንዳለቀሰች አሰብኩ። ‎ ‎ስንት ጊዜ “ደህና ነኝ” ብላ ውስጧ ግን ምንም ደህና እንዳልነበረ አሰብኩ። ‎ ‎ለምንድ ነው እኔ በራሴ ላይ የምጨክ ነው? ለሌሎች የማሳየውን ርህራሄ እንኳን ለምን አልሰጣትም? ‎ ‎ለምን ሌሎችን ይቅር ማለት ቀላል ሆኖ ለራሴ ግን ይቅርታ መስጠት እንደ ክህደት ይሰማኛል? ‎ ‎ምናልባት ራሴን ይቅር ማለት ስህተቴን ማጽደቅ መስሎኝ ነበር?። ‎ ‎አላውቅም። ‎ ‎አሁን ግን ይህን አላምንም። ‎ ‎ራስን ይቅር ማለት የተሳሳተውን ትክክል ማድረግ አይደለም። የተሳሳተውን ተቀብሎ ከዚያ በኋላ መኖርን መማር ነው። ‎ ‎ያለፈውን መቀየር አልችልም። ያኔ የተናገርኩትን መልሼ ልውሰድ አልችልም። የተሳሳተውን ውሳኔ እንዳልወሰንኩ ማድረግ አልችልም። የጠፋውን ጊዜም መመለስ አልችልም። ‎ ‎ግን አንድ ነገር እችላለሁ። ‎ ‎ያንን የቀድሞ ራሴን መጥላቴን ግን ማቆም እችላለሁ። ‎ ‎ዛሬ በጣም የምተቻት ያቺ ልጅ ያኔ የምታውቀውን ብቻ ነበር የምታውቀው። የነበራትን ጥቂት ጥበብ፣ ጥቂት ተስፋ፣ ጥቂት ድፍረት ይዛ ቀኗን ትገፋ ነበር። ‎ ‎ስለዚህ ዛሬ በእሷ ላይ ለመፍረድ ከመቆም ይልቅ ከጎኗ ለመቆም እፈልጋለሁ። ‎ ‎“አዎ፣ ተሳስተሻል።” እላታለሁ። ‎“አዎ፣ አንዳንድ ሰዎችን በተሳሳተ መንገድ አምነሻል።” ‎“አዎ፣ አንዳንድ ውሳኔዎችሽ ሊለወጡ ቢችሉ ደስ ይለኝ ነበር።” ‎ ‎“ግን እኔ አሁንም እወድሻለሁ።” ‎ ‎ምናልባት ይህ ለራሴ ለመጀመሪያ ጊዜ የምናገረው እውነተኛ የርህራሄ ቃል ነው። ‎ ‎ከዚህ በኋላ እሻሻላለሁ። እማራለሁ። እለወጣለሁ። ግን ራሴን እየጠላሁ አይደለም። ‎ ‎እንደሚያስፈልገኝ ልገስጻት እችላለሁ፤ እንደሚገባት ግን ልያዛት እችላለሁ። ‎ ‎ስትወድቅ እጇን ልይዛት። ‎ስትደክም ላሳርፋት። ‎ስታለቅስ ልተዋት። ስትሳሳት ልምራት። ‎ስትፈራ ከጎኗ ልቆም። ‎ ‎ምክንያቱም ዓለም ለእኔ ሁልጊዜ ርህሩህ አትሆንም። ሰዎችም ሁልጊዜ አይረዱኝም። ሕይወትም ሁልጊዜ አትቀልልልኝም። ‎ ‎እንግዲያስ እኔ ለራሴ ለምን ሌላ ዓለም እሆናለሁ? ‎ ‎ምናልባት ሕይወቴ ውስጥ ከሁሉ በላይ ይቅርታ የሚገባት ሰው እኔ ራሴ ነኝ። ‎ ‎እና ምናልባት ከዛሬ ጀምሮ በራሴ ላይ መጨከን ሳይሆን፣ ራሴን መያዝ መማር አለብኝ። ‎ ‎ምክንያቱም እስከዛሬ ራሴን እየገፋሁ ነው የኖርኩት፤ ‎አሁን ግን ከራሴ ጋር ... ‎ ©️ ሶሪት ‎

የቅርብህ ሰው ላንተ የተገደበ አዘኔታ አለው መጠኑን ካስጨረስው ግን ጉዳትህን እንደ ዜና ያዳምጠዋል።

ምን እያሰብኩ እንደሆነ ሃሳቤ እንኳን ለሌላ ሰው ለኔም  አይገባኝም። እኔ ሃሳብ ውስጥ ስገባ ደመና የሆንኩ ይመስለኛል ሰውነቴ እንደ ቁልል አፈር ተሸርሽሮ ብንን ብሎ ወደ ሰማይ ይጎናል። እኔን ለእኔና ለሃሳቤ ትቶ እሱ አየር ላይ ይንፈላሰሳል። ማሰቤን አልተውኩም አስባለሁ ከራሴ ጋር አወራለሁ..... «እኔ የ25 አመት ወጣት ነኝ ካሳለፍኩት መከራና ስቃይ ጋር ሲተያይ ሃያ አምስት አመት ሳይሆን አንድ ምዕተ ዓመት ያሳለፍኩ ነው ሚመስለኝ። እንደ አያቴ አረጅ ይሆን? የልጅ ልጅ አይ ይሆን? በዚህች እድሜዬ ብዙ ነገር አይቻለሁ ካየሁትም ነገር አንድ ጥሩ ነገር የለም። ምናለ ባልወለድ በእናቴ ማህፀን ደም ሳለሁ እዛው በፈሰስኩ እላለሁ። ሃገር አለኝ ብየ አፌን ሞልቸ አወራለሁ ግን በሃገሬ እንደፈለኩ መንቀሳቀስ አልችልም 10km መሄድ እፈራለሁ። እና አረጅ ይሆን....... ሰዎች በወሬ መኃል « እዚች ዓለም ላይ አምሳ አመት ኑሪያለሁ» ሲሉ በነሱ አምሳ አመት ኑሮ መቅናት ጀምሬያለሁ። ሰው ሰውነቱን ያጣበት ህሊናውን ከቦታው ነቅሎ ባዶ ስጋውን ተሸክሞ በሚዋልልበት በዚ ዘመን እንዴት አረጃለሁ። ለመሆኑ ከአሁን በኋላ የራሴ ቤት ይኖረኝ ይሆን? ኤጭ!! ደሞ የምን ቤት ነው.... ስራ አገኝ ይሆን? ኡፍፍፍፍ!!...... ደሞ የምን ስራ ነው ሃገሩ ሰላም ይሆን ይሆን?........ ሁሉም ነፃነቴን አስጠብቃለሁ በሚል አጉል ዲስኩርና እብሪተኝነት ጫካ ገብቶ እንደኔ አይነቱን የሕይወት ጥፍጥናን ማጣጣም ሚጀምረውን የእጣ ፈንታ ፅዋውን ይደፉበታል። የራሱን ጥቅም ለማስጠበቅ ብሎ በብሔሩና በጎሳው ጥላ ስር ይጠለላል። ድሮ « እለወጣለሁ፣ አገባለሁ፣ ልጅ እወልዳለሁ» የሚል ተስፋ ከፊት ለፊቴ ይብለጨለጭ ነበረ አሁን ግን ያ ብልጭልጩ ተስፋዬ ጠይሟል ። አባት የገዛ፤ የአብራኩ ክፋይ የሆነችውን ልጁን ይደፍራል!! ፣ ይጦረኛል፣ ይንከባከበኛል ፣ ብለው ዋጋ ከፍለው ከሰውነት ተራ ጎድለው ያሳደጉት ልጅ የወላጆቹን ነፍስ ይነጥቃል። ምነው ባልተወለድኩ ማለቴን አልተውም። ድሮ ጎረቤት ለጎረቤት ቡና ይጠጣሉ፣ ታመው ይጠያየቃሉ፣ ዘይትና ሽንኩርት ይዋዋሳሉ፣ ትኩስ እንጀራ በድቁስ ይበላሉ፣ .... ይሄንን የጓረቤት ፍቅር ለአሁኑ ህፃናቶች ባወራ ሚስቁብኝ ይመስለኛል። ምክኒያቱም የአሁን ጉርብትና ፍቅር እንደሌለው አጥሩን ብቻ ማሳየት በቂ ነው ። እና ይሄን ሁሉ ሚያሳየኝ መወለዴ አይደል? ባልወለድ ...።                        ✍️ Henok

የጠገብክለት ሳይሆን የደከምክለት ነው ጥሩ እንቅልፍ የሚገኝ።

የምታውቀውን ርዕስ ላለማውራት ውስጥን ማስቻል ራስን የመግዛት ጥበብ ነው።

ምን ያህል ባይገባን ነው ፍቅራችንን እንደ ሃጥያት የደበቅነው? . ..

ፀፀትን የመሰለ ደስታም በረከትም የለም።             ልብ ላለው ሰው!

በቃ!! ይሀው ነው ጥቁር እውነት 💔
በቃ!! ይሀው ነው ጥቁር እውነት 💔