የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
前往频道在 Telegram
2 639
订阅者
+124 小时
+167 天
+5630 天
帖子存档
🔴#ስንክሳር የካቲት_27
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
የካቲት ሃያ ሰባት በዚች ቀን የአንፆኪያ አገር ሊቀ ጳጳሳት #ቅዱስ_አንስጣስዮስ አረፈ፣ ኢትዮጵያዊው ጻድቅ #አቡነ_ዓምደ_ሥላሴ እረፍታቸው ነው፡፡
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅዱስ_አንስጣስዮስ_ሊቅ
የካቲት ሃያ ሰባት በዚች ቀን በታላቁ ንጉስ በቈስጠንጢኖስ ዘመን የከበረ አባት የአንፆኪያ አገር ሊቀ ጳጳሳት ትምህርቱ በአለም የመላ አንስጣስዮስ አረፈ።
የከበሩ አባቶችም በኒቅያ ከተማ የአንድነት ስብሰባ በአደረጉ ጊዜ በዚህ ጉባኤ ከተሰበሰቡት ሊቃውንት አንዱ እርሱ ነው በዚህም ጉባኤ ተስማምተው አርዮስን ከባልንጀሮቹ ጋር አውግዘው ለይተውታል ባልንጀሮቹም የቂሳርያ አውሳቢዮስ የኒቆምድያ አውሳቢዮስና አርናሲስ ናቸው። እነዚህም በ አብያተ ክርስቲያናት ሁሉ ታውቀዋል።
እንዚህ የከበሩ አባቶች ስርአትን ሰርተው ወደ የሀገራቸው በተመለሱ ጊዜ እነዚህ ከኤጲስቆጶስነት ሹመት የተሻሩት ወደ ኢየሩሳሌም የሚሄዱ መስለው ወጡ ወደ አንፆኪያም ከተማ ገብተው ለአንዲት አመንዝራ ሴት ዘንድ ተሰበሰቡ ብዙ ገንዘብም ሊሰጣት ቃል ገቡላት ወደ ቤተክርስቲያን እንድትገባ ይህ አባት ከእርሷ ጋር እንዳመነዘረ የወለደችውም ልጅ የእርሱ እንደሆነ በዚህ ቅዱስ አባት አንስጦስዮስ ላይ ለካህናቱና ለህዝቡ እንድትናገር አስተማሩዋት።
ህዝቡም እንዲህ አሏት አንቺ ሀሰተኛ ነሽ በዚህ ቅዱስ አባትም ላይ ሀሰትን ተናግረሻል በከበረ ወንጌል ካልማልሽ በቀር ቃልሽን አንቀበልም አሏት። እርሷም ስለገንዘብ ፍቅር በሀሰት ማለች። ከዚህም በኃላ ለንጉስ ነግረው ከመንበረ ሲመቱ ወደ አጥራኪያ ደሴት አሳደዱት በስደትም ሳለ በርሷ አረፈ።
ነገር ግን ለእነዚህ ከሀዲያን ወዮላቸው የእግዚአብሄርን ልጅ ከመለኮቱ ባህርይ ለይተው ፍጡር ነው ብለውታልና ይህንንም ንፁህ አባት ሰይጣን አባታቸው እንዳስተማራቸው ከአመንዝራ ጋር አንድ ሆነው በተንኮል ከመንበረ ሲመቱ አውጥተውታልና።
እግዚአብሄር ግን ቸል አላለም ይህን አባት ከአሳደዱት በኃላ ያቺ አመንዝራ ሴት ጭንቅ በሆነ ደዌ ተይዛ ብዙ ተሰቃየች ለሞትም ተቃረበች ያን ጊዜም ይህ ሁሉ የደረሰባት በከበረ ወንጌል በሀሰት ስለማለች እንድሆነ ተገነዘበች። በአንፆኪያም ሰዎች ሁሉ ፊት በደሏን አመነች እንዲህም አለቻቸው፦ ይህ ቅዱስ አንስጣስዮስ ከዝሙት ንፁህ ነው እነዚያ ከሀዲያን ብዙ ገንዘብ ሰጥተውኝ በእርሱ ላይ ሀሰትን እንድናገር በከበረ ወንጌልም በሀሰት እንድምል አደረጉኝ እንጂ።
የአንፆኪያ አገር ሰዎችም ኃጢአቷን ማመኗን በሰሙ ጊዜ እጅግ አዘኑ ካህናቱም በፀሎትና በቅዳሴ ጊዜ ስሙን የሚያነሱ ሆኑ ዩሀንስ አፈወርቅም አመሰገነው በመታሰቢያውም ቀን ስለ ውለታው የውዳሴ ድርሳን ጽፎለታል::
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ጻድቁ_አቡነ_ዓምደ_ሥላሴ
ዳግመኛም በዚህች ቀን አቡነ ዓምደ ሥላሴ እረፍታቸው ነው፡፡ አቡነ ዓምደ ሥላሴ የትውልድ ሀገራቸው ጎጃም ሲሆን በዐፄ ሱስንዮስ ዘመን የነበሩ ድንቅ ድንቅ ተአምራትን ያደርጉ የነበሩ ገዳማዊ መነኩሴ ናቸው፡፡ ጻድቁ ማኅበረ ሥላሴን ያቀኑ ታላቅ አባት ሲሆኑ በተለይም አንድ የሚታወቁበት ትልቅ ታሪክ አላቸው፡፡ እርሱም ዐፄ ሱስንዮስ ካቶሊካውያን ደግፈው 8ሺህ የሀገራችንን ሊቃውንት በአንድ ቀን ባሳረዱ ጊዜ ንጉሡ ወዲያው ‹‹ኦርቶዶክስ ይርከስ ካቶሊክ ይንገስ›› ብሎ ያወጀበት ምላሱ ተጎልጉሎ ወጣ፡፡ እንደ አርዮስም ሆዱ አብጦ አንጀቱ ተልቶ ሊሞት ባለ ሰዓት አቡነ ዓምደ ሥላሴ አዘዞ ድረስ ሄደው ‹‹ፋሲል ይንገሥ ኦርቶዶክስ ሃይማኖት ትመለስ የሱስንዮስም ምላስ ይመለስ›› በማለት ተጎልጉሎ የወጣውን ምላሱን በመስቀላቸው ቢባርኩት ምላሱ ተመልሶለታል፡፡
ዐፄ ሱስንዮስ ግን ለካደበት ክህደት ቅጣቱ ነውና በመቅሰፍቱ ሳይድን በዚያው ታሞ ማቆ ማቆ ክፉ አሟሟት ሞቷል፡፡ ከዚህ በኋላ አቡነ ዓምደ ሥላሴ የዐፄ ፋሲልን ሹመትና ሃይማኖትን በአዋጅ አጽንተው ተመልሰው ወደ ገዳማቸው ማኅበረ ሥላሴ ገዳም ገብተዋል፡፡ ዐፄ ፋሲልንም የማኅበረ ሥላሴን ገዳም ግዛቱን ከሱዳን እስከ ጣቁሳ ድረስ እንዲሆን በአዋጅ ወስነው ሰጥተውት ነበር ነገር ግን ላይጠቀምበትና ላይጸና ነገር የደርግ መንግሥት የገዳሙን ሥርዓት ከማፍረሱም በላይ ርስት ጉልቱን ነጥቆ ወሰደበት፡፡
በደርቡሾች ወረራ ጊዜ እንግሊዞች አጋጣሚውን ተጠቅመው የአቡነ ዓምደ ሥላሴን ቅዱስ ገድል ዘርፈው ወስደውታል፡፡ ዛሬ በእንግሊዝ ሀገር ገድለ አቡነ ዓምደ ሥላሴ ይገኛል፡፡ ጻድቁ የካቲት 27 ቀን ያረፉ ሲሆን ዐፅማቸው በዚያው በመሠረቱት በማኅበረ ሥላሴ ገዳም በክብር ተቀምጧል፡፡
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ለዘለዓለሙ ከእኛ ጋር ትሁን አሜን፡፡https://t.me/finotebirhan12
ለሰንበት ትምህርት ቤታችን አባላት በሙሉ
የወጣት ትምህርት ክፍል ከፊታችን ቅዳሜ 02/06/2015 ዓ.ም ጀምሮ በቅዳሜ መደበኛ ትምህርት አዲስ ተከታታይ ትምህርት እንጀምራለን።
ርዕስ:- ታላቁ ሊቅ ቅዱስ አትናቴዎስ ህይወቱና ትምህርቱ
ሰዓት ስለምታከብሩ እናመሰግናለን።
የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ 4ኛው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፩ኛ ዓመት መታሰቢያ በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ተከናወነ ።
መ/ር ኃይሉ በላይ
(EOTC TV //የካቲት 25 ቀን 2015 ዓም አዲስ አበባ)
የቅዱስነታቸው ፩ኛ የዕረፍት ዓመት ሲታሰብ በኦርቶዶክሳዊት ሥርዓተ አምልኮ መሠረት በያራሬዳውያን ሊቃውንት መዋሥዕቱ እንዲሁም በካህናቱ መጽሐፈ ግንዘቱ በሚያዘው የጸሎት ሥርዓት መሠረት በመካነ መቃብራቸው ጸሎቱ ተከናውናል።
በዚሁ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የኒውዮርክ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ሌሎች ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሥራ ሓላፊዎች የአዲስ አበባ አድባራትና ገዳማት አስተዳዳሪዎች ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እንዲሁም የቅዱስ አባታችን የአገልግሎት ልጆች ምዕመናን ተገኝተዋል።
ከጸሎተ ፍትሐቱ በኋሏ የመንበረ ፓትርያርክ ጠ/ቤተክህነት ካህናት አስተዳደር መምሪያ ሓላፊ በሆኑት በመምህር ዕንቆ ባሕርይ ተከስተ አስተባባሪነት በዐውደ ምሕረቱ በሊቃውንት የጾመ ዐቢይን ሥርዓት መሠረት በማድረግ ዝማሬ ቀርቧል።
በመቀጠልም በብፁዕ አቡነ ሚካኤል የደቡብ ጎንደር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ትምህርትና ምስክርነት ተሰጥቷል።
ብፁዕነታቸው በትምህርታቸው ሲያብራሩ የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ፬ኛ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ የኑሮ ቅድስናን የሙሉ እውቀት ባለቤትነት እንዲሁም ጥበባዊ መሪነታቸውና የአባትነት ክብራቸውን በተግባር ያሳዩ አባት መሆናቸውን አስታውሰዋል።
በመጨረሻ ቃለ በረከት የሰጡት ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊና የኒውዮርክ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በበኩላቸው ቅዱስ አባታችን ትናንት የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በዓለ ሢመተ ፓትርያርክ አከበርን ዛሬ ደግሞ ሌላኛውን የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ ፓትርያርክ ክህነታቸውን በክብር ለጌታቸው የመለሱትን ፩ኛ ዓመት ዕረፍት መታሰቢያ እያከበርንነው ብለዋል።
አያይዘውም ብፁዕነታቸው በርካታ ብፁዓን አባቶች በዚህ የቅዱስነታቸው ፩ኛ ዓመት የመታሰቢያ ቀን መገኘት የነበረባቸውና ለመምጣትም ዝግጁ የነበሩ ቢሆንም በወቅታዊ ጉዳዮች ምክንያት ከመንግሥት አካላት ጋር ስብሰባ በመኖሩ መሆኑን ገልጸው ። ከዚሁ ጋር አያይዘው በየካቲት ፳፫ ቀን የቅዱስ ጊዮርጊስ በዓል በማክበር ላይ በሚገኙ በፒያሳ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን ታቦተ ሕጉ ወጥቶ ስብሐተ እግዚአብሔር እየቀረበ በነበረበት ሰዓት አስለቃሽ ጭስ በመወርወሩ ለብዙ ሰዎች መጎዳት ምክንያት እንደነበረም በማዘን ገልጸዋል።
ይሁን እንጂ ይህ ሁሉ ፈተና እኛን ዕረፍት በማሳጣት እንዳንረጋጋ በማሰብ ነው። እናም እነሱ በተኮሱ ቁጥር እኛ አቅጣጫ አንስትም በማለት የቅዱስ ሲኖዶስ ሚዛናዊ አካሔድን አስታውቀዋል።
የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ በረከታቸው ይድረሰን!
Eotc
🔴#ስንክሳር የካቲት_26
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
የካቲት ሀያ ስድስት በዚህች እለት #ነቢይ_ሆሴዕ አረፈ፣ የከበረ #ቅዱስ_ሳዶቅ በሰማእትነት አረፈ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅዱስ_ሆሴዕ_ነቢይ
የካቲት ሀያ ስድስት በዚህች እለት ዖዝያ ይባል የነበረ እውነተኛ ነቢይ ሆሴእ አረፈ። ዳግመኛም ይህ ነቢይ በአራቱ የይሁዳ ነገስታት ዘመን ትንቢት ተናገረ። እሊህመ ዖዝያን ኢዮአታም አካዝ ህዝቅያስ ናቸው። በትንቢቱም ድንቆች ስራዎችን ተናገረ የእስራኤልንም ልጆች ብሎም ጠራቸው እግዚአብሔርም ቁጣውን ከእርሳቸው እንደማይመልስ አስረዳቸው።
እንዲህም አለ የእስራኤል ልጆች ቁጥራቸው እንደማይሰፈርና እንደማይቁጠር የባህር አሸዋ ቢሆን ከጥቂት በቀር አይተርፍም አለ። ስለ አህዛብም በእግዚአብሔር ማመን ተናገረ እንዲህም አለ እኔ ወገኖቼ ያልሆኑትን እጠራቸዋለሁ እነርሱም ይሰሙኞል።
ዳግመኛም ስለ መድኃኒታችን መከራ መቀበልና በከበረ ደሙ ስለ መዳናችን ስለ ትንሳኤውም እንዲህ ብሎ ተናገረ።እሱ በመከራ ገርፎ ይድነናል እርሱም በመከራ አቁስሎ ይቅር ይለናል ሲያድነንም በሁለተኛው ቀን ነው ።
በሶስትኛውም ቀን ድነን በሱ ፊት እንነሳለን እግዚአብሔርንም አውቀን እንከተለው ዘንድ ስለ ሞት ስልጣን መሻር ስለ መቃብርም መሸነፍ እንዲህ ብሎ ትንቢት ተናገረ ሞት ይዘህ ማስቀረትህ መቃብርስ ድል መንሳትህ ወዴት ነው ትንቢትን እየተናገረ ሰባ ዓመት ያህል ኑሮ በበጎ ሽምግልና አረፈ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅዱስ_ሳዶቅ
በዚህችም እለት የከበሩ ሳዶቅና ከእርሱ ጋር የሆኑ ሁለት ሺህ ስምንት ሰዎች በሰማእትነት አረፉ። ይህንንም የከበረ ሳዶቅን ለፀሀይ ይሰግድ ዘንድ የፋርስ ንጉስ ብርህም ፈለገው ቅዱሱም ለፈጣሪዋ እንጂ ለዚች ለምትታይ ፀሀይ ልሰግድ ከእናቴ ማህፀን አልወጣሁም ብሎ መለሰለት።
ብርህም ንጉስም መልሶ ለዚች ፀሀይ አምላክ አላትን አለው ቅዱስ ሳዶቅም አለሙን ሁሉ የፈጠረ ክርስቶስ አምላክ ነው አለው ።ንጉሱም የቅዱስ ሳዶቅን ራስ በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ የከበረ ሳዶቅም ቁሞ ወደ እግዚአብሄር ፀለየ ከዚህም በኃላ ራሱን ዘንበል አድርጎ ቆረጡት።
ያን ጊዜ ከሰማይ ብርሀን በላዩ ወረደ ከዚያ ያሉትም ሁሉ አይተው እኛ ሁላችንም በቅዱስ ሳዶቅ አምላክ የምናምን ክርስቲያን ነን ብለው ጮኹ ንጉሱም ሁሉንም ራሶቻቸውን በሰይፍ እንዲቆርጡ አዘዘ የሰማእትነት አክሊልንም በመንግስተ ሰማያት ተቀበሉ ቊጥራቸውም ሁለት ሺህ ስምንት ነፍስ ናቸው።
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ለዘለዓለሙ ከእኛ ጋር ትሁን አሜን፡፡https://t.me/finotebirhan12
በአንዲትም ዕለት ለደቀ መዛሙርቱ እነሆ ዓለም አለፈ አላቸው በጠየቁትም ጊዜ ንጉሥ ቴዎዶስዮስ ሞተ አለ በአንዲትም ዕለት ሦስት መቶ የወርቅ ዲናር የያዘ እንግዳ በአንድ ቄስ ቤት አደረ በተኛ ጊዜ ስለ ገንዘቡ ቄሱ ገደለውና ወስዶ ከአንድ መነኵሴ ደጅ ጣለው ለቅዱስ አቡፋናም በነገሩት ጊዜ ከሟቹ ላይ እንዲጥሉበት ቆቡን ሰጣቸው ሲጥሉበትም ሟቹ ተነሣ ስለ ገንዘቡ ቄሱ እንደ ገደለው ነገራቸው እጅግም አደነቁ።
በአንዲትም ዕለት አንድ ሰው ቡራኬ ሊቀበል ወደርሱ ሲመጣ ልጁ በጉዞ ላይ ሞተ ልጁንም ተሸክሞ ወደ ቅዱስ አቡፋና ሔደ በፊቱም ሰግዶ ተባርኮ ተመለሰ ያን ጊዜ የሞተው ብላቴና ተነሥቶ አባቱን ተከተለው።
ከቆመ ጀምሮ ዐሥራ ስምንቱ ዓመት በተፈጸመ ጊዜ ዕረፍቱን አውቆ ቅዱስ ቍርባንን ተቀበለ ወደ መኖሪያውም ሒዶ ራሱን ዘንበል አድርጎ ነፍሱን በእግዚአብሔር እጅ ሰጠ።
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ለዘለዓለሙ ከእኛ ጋር ትሁን አሜን፡፡https://t.me/finotebirhan12
🔴#ስንክሳር የካቲት_25
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
የካቲት ሃያ አምስት በዚች ቀን የከበሩ #ቅዱስ_አውሳንዮስ፣ #ቅዱስ_ፊልሞና፣ #ቅድስት_ሉቅያ ድንግልም በሰማዕትነት ሞቱ፣ የከበረ ሐዲስ #ቅዱስ_እንጦኒ (ረውሕ) በሰማዕትነት ሞተ፣ ከግብጽ አገር ከእስሙናይን አውራጃ የሆነ የከበረ አባት #ቅዱስ_አቡፋና አረፈ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅዱሳን_አውሳንዮስ_ፊልሞና_እና_ቅድስት_ሉቅያ_ድንግል
የካቲት ሃያ አምስት በዚች ቀን የከበሩ አውሳንዮስና ፊልሞና ስሟ ሉቅያ የሚባል አንዲት ድንግልም በሰማዕትነት ሞቱ።
እሊህ ቅዱሳንም በአፍራቅያ ሀገር ሳለ በከበረ ሐዋርያ ጳውሎስ ትምህርት ያመኑ ናቸው ከሀድያንም ዝሑራ በሚባል ኮከብ ስም ለሚጠሩት ለአርታዳሚ ጣዖት በዓልን በአደረጉ ጊዜ አይተው በስሕተታቸው ሊዘብቱ እሊህ ቅዱሳን ተሰብስበው ወደ ጣዖቱ ቤት ገቡ ሰዎችም ለጣዖቱ ሲሠዉና ከፍ ከፍ ሲያደርጉት በአዩአቸው ጊዜ በክብር ባለቤተ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ፍቅር እሳትነት ልባቸው ነደደ ከጣዖቱም ቤት ወጥተው ወደ ክርስቶሳዊት ቤተ ክርስቲያን ሔደው የክብር ባለቤት የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብሩንና ልዕልናውን አብዝተው አመሰገኑ።
ከዚያ ካሉት አንድ ሰው በሰማቸው ጊዜ በጣዖታቸው ላይ እንደ ዘበቱ የተናገሩትን ልብ ብሎ በመኰንኑ ዘንድ ወነጀላቸው መኰንኑም በፈረስ ተቀምጦ ሔደ ከወታደሮቹም ጋር ቤተ ክርስቲያኒቱን ከበባት ከምእመናንም ሰዎች የሸሹ አሉ። እሊህንም ሦስቱን ቅዱሳን ያዛቸው የብረት ዘንጎችን በእሳት አግለው በቅዱሳኑ ጐኖች ውስጥ አደረጉት ከዚህም በኋላ የከበረ አውሳንዮስን ወደ ጒድጓድ ወረወሩትና ነፍሱን እስከ ሰጠ ድረስ በደንጊይ ወገሩት።
የከበረ ፊልሞናንና የከበረች ሉቅያን ግን ብዙ ጊዜ በጸና ሥቃይ ያሠቃዩአቸው ጀመር ነፍሳቸውንም ይወስድ ዘንድ እግዚአብሔርን ለመኑት እርሱም ልመናቸውን ተቀብሎ ነፍሳቸውን ወሰደ።
በመንግሥተ ሰማያትም የሰማዕትነት አክሊልን ተቀበሉ እነሆ የምስክርነታቸውና የሃይማኖታቸው መታሰቢያ ተጽፎአል።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#የከበረ_ሐዲስ_እንጦኒ
በዚችም ዕለት የከበረ ሐዲስ እንጦኒ በሰማዕትነት ሞተ ይህም ረውሕ የሚባል ነው። ይህም ከከበሩ ዐረቦች ወገን የቆሮስ ሰው የሆነ ብዙ ገንዘብ ያለው ነው በሰማዕታት አለቃ በቴዎድሮስ ገዳም አጠገብ በወንዝ ዳርቻ የሚኖር ነው ይህም ጐልማሳ አብያተ ክርስቲያናትን የሚቃወም ሁኖ ቅዱስ ቍርባንን በመስረቅ ኀብስቱን ይበላዋል የከበረ ደሙንም ከጽዋው ውስጥ ይጠጣል የመሠዊያውንም ልብስ ገፎ በእሳት ያቃጥለዋል በክርስቲያን ሃይማኖትም ላይ ይዘብታል።
መኖሪያ ቤቱ ከከፍታ ቦታ ላይ ስለ ሆነ ካህናት ሲያገለግሉ ይታዩት ነበር። በአንዲትም ዕለት በቅዳሴ ጊዜ ቤተ ክርስቲያን ተከፍቶ አየ በፈረስም ተቀምጦ መጣ የቅዱስ ቴዎድሮስንም ሥዕል ተመልክቶ በፍላፃዎች ወጋው ። አንዲቱም ፍላፃ ተመልሳ መሐል እጁን ነደፈችው በጭንቅም ከእጁ ላይ መዘዛት ይህንንም ለማንም አልነገረም።
በሌላዪቱም ዕለት በወንበሩ ላይ ተቀምጦ ሳለ መሥዋዕትን ተሸክመው ወደ መቅደስ ሲገቡ ካህናትን አያቸው በጻሕሉም ውስጥ ነጭ በግ ተኝቶ ከበላዩ ነጭ ርግብ ሲጋርደው በቅዳሴውም ፍጻሜ ያ በግ በየመለያያው የተከፋፈለ ሆኖ ካህናቱም ከተከፋፈለው ሥጋውን ሲቀበሉ ደሙንም ከጽዋው ውስጥ ሲቀበሉ አየ እጅግም አደነቀ። በልቡም የክርስቲያን ሃይማኖት እጅግ ድንቅ ነው በእውነትም የከበረ ክቡር ነው አለ። ዳግመኛም ያ በግ ተመልሶ እንደ ቀድሞው ኑሮው ሕያው ሁኖ አየ ከዚህም በኋላ ከመቀመጫው ወርዶ ወደ ቤተ ክርስቲያን ደጃፍ ሔዶ ያየውን ሁሉ ለካህናቱ ነገራቸው እነርሱም ሰምተው ስለዚህ ድንቅ ሥራ ደስ አላቸው።
በዚያችም ሌሊት ተግቶ ሲጸልይ ሊቅ ቴዎድሮስ ተገለጠለት እርሱም በፈረሱ ላይ ተቀምጦ ነበር እንዲህም አለው እነሆ በእኔ ላይ ሥዕሌን እስከ ወጋህ ድረስ ክፉ ሠራህ በክብር ባለቤት ክርስቶስ ሥጋ ላይም ዘበትክ አሁንም ከክህደትህ ተመልሰህ በክብር ባለቤት በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ እመን አለው ይህንም ብሎ ከእርሱ ተሠወረ።
በማግሥቱም በፈረሱ ላይ ሁኖ ወደ ኢየሩሳሌም ሔደ ወደ ሊቀ ጳጳሳቱም ገብቶ ከእርሱ የሆነውን ሁሉ ነገረው ሊቀ ጳጳሳቱም ሰምቶ እግዚአብሔርን አመሰገነው እርሱንም በሕዝብ ፊት አጠምቅህ ዘንድ እፈራለሁ ነገር ግን ወደ ዮርዳኖስ ወንዝ ሒድ ጌታችን ክርስቶስም የሚያጠምቅህን ይሰጥሃል አለው።
እርሱም ሰምቶ ወደ ዮርዳኖስ ሔዶ ወደ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ገባ የሌሊቱም እኩሌታ ሲሆን የብርሃን እናት ቅድስት ድንግል እመቤታችን ማርያም ነጭ ሐር ግምጃ ለብሳ ተገለጠችለት ከእርሷም ጋር በንጹሕ ልብስ የተሸለመች ሴት ነበረች በእጅዋም ይዛ አነሳችውና አትዘን እኔ ካንተ ጋር እኖራለሁና አለችው።
ሲነጋም ወደ ዮርዳኖስ ወንዝ በሔደ ጊዜ ሁለት ገዳማውያን መነኰሳትን አገኛቸው እነርሱም በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አጠመቁት። ስሙንም እንጦንስ ብለው ሰየሙት የምንኲስና ልብስ አሰኬማንም አልብሰው በሰላም አሰናበቱት ወደ ደማስቆም ሔዶ ወደ ቤቱ ገባ።
ባልንጀሮቹና ወገኖቹም በአዩት ጊዜ የለበሰከው ምንድን ነው አሉት እኔ ክርስቲያን ነኝ አላቸው በዚያንም ጊዜ ይዘው በሜዳ ውስጥ እየጐተቱ ወደ መኰንኑ እስኪያደርሱት ይደበድቡት ነበር። መኰንኑም ወደ እሥር ቤት እንዲጨምሩት አዘዘ በታላቅ ሥቃይም ዐሥራ ሰባት ሌሊት በዚያ ኖረ እነሆ በላዩ ብርሃን ወረደ እንዲህም የሚል ቃል ሰማ እንጦንዮስ ሆይ አክሊል ተዘጋጅቶልሃልና አትፍራ ብርሃንን የለበሱ ሁለት አረጋውያንም መጥተው በራሱ ላይ የብርሃን አክሊልን አኖሩ በነጋ ጊዜም ወደ አደባባይ ወስደው ራሱን በሰይፍ ቆረጡትና በዕንጨት ላይ ሰቀሉት።
በሌሊትም በላዩ ብርሃን ወረደ ጠባቆችም አይተው ከዕንጨት ላይ አወረዱት በጤግሮስም አቅራቢያ ቀበሩት ከመቃብሩም ድንቆች ተአምራቶች ተገለጡ፡፡
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#አባ_አቡፋና
በዚችም ዕለት ከግብጽ አገር ከእስሙናይን አውራጃ የሆነ የከበረ አባት አቡፋና አረፈ። ይህም አባት ከቶ ብርሃን በሌለበት ዋሻ ውስጥ የሚኖር ሁኖ በየሁለት ቀን ይጾማል የሚበላውም የሚጠጣውም በመለኪያ ተለክቶ ነው በሌሊትም በመዓልትም አምስት መቶ ጊዜ ይጸልያል።
በአንዲትም ዕለት ወንድሞች ሊጐበኙት ወደርሱ መጡ እንጀራንም አጣ ሦስት እንጀራንም በአገኘ ጊዜ ለሃያ ሰዎች አቀረበላቸው እነርሱም በልተው ጠገቡ ተአምራትንም እያደረገ በሽተኞችንም እየፈወሰ ኖረ።
ከዚህም በኋላ እንዲህ የሚል ቃል ከሰማይ ወደርሱ መጣ አቡፋና ሆይ ዐሥራ ስምንት ቀረህ የከበረ አቡፋናም ዐሥራ ስምንት ዕለታት እንደሆኑ አስቦ እሊህ ዕለቶች እስቲፈጸሙ ቆመ ከዚህም በኋላ ሱባዔዎች ናቸው ብሎ ይህንንም በመቆም ፈጸመ እንደገና ወሮች ይሆናሉ ቢሆኑስ ብሎ ይህንንም በመቆም ሳያጓድል አደረሰ። ዳግመኛም እንዲህ የሚል ቃል ወደርሱ መጣ አቡፋና ሆይ ዐሥራ ስምንት ዓመት ናትና ጽና በርታ አለህ እግዚአብሔር አለው በዚያንም ጊዜ ፈጽሞ ጸና።
በዋሻው ደጃፍ የውኃ ምንጭ ነበረ ምሳርንም ወረወረበት ምሳሩም ነቢይ ኤልሳዕ እንዳደረገው በውኃ ላይ ተንሳፈፈ። የከበረች የአርባ ቀንን ጾም ከሦስት ቀኖች በቀር ሳይበላ ፈጸመ። ሲበላም ሲያንቀላፋም ግድግዳ ተጠግቶ ነው እግሮቹም እንደዝሆን እግር እስከሚሆኑ እንዲህ ተጋደለ።
🔴#ስንክሳር የካቲት_24
#ቅዱስ_አጋቢጦስ
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
የካቲት ሃያ አራት በዚች ቀን የከበረ አባት ኤጲስቆጶስ አጋቢጦስ አረፈ። ይህም አባት በከሀድያን ነገሥታት በዲዮቅልጥያኖስና በመክስምያኖስ ዘመን ነበር። ወላጆቹም ደጎች ምእመናን ነበሩ የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት አስተምረውት ዲቁና ተሾመ።
ከዚህም በኋላ እናትና አባቱን ትቶ ወደ አንድ ገዳም ሔዶ የሸመገሉ መነኰሳትን አገለገለ። ከእርሳቸውም በጎ አምልኮትን ተማረ አረጋውያኑንም እያገለገለ በገድል ተጠመደ ያለማቋረጥም በጾም በጸሎትና በስግደት ይተጋል ከጥዋትም እስከ ምሽት በመጾም የሽንብራ አሠር የሚመገብ ሆነ።
ከእንቅልፍም ጋር ሊታገል በወደደ ጊዜ ከሽምብራ አሠር ጋር አመድ እየተመገበ ሰማንያ ቀን ኖረ በዚህም ተጋድሎ ውስጥ እያለ ኃይሉ ግን ይጨመርለት ነበር። ለአረጋውያንም አገልግሎቱን አላስታጐለም ሲጠራቸውም ጌቶቼ ይላቸዋል የጽድቅንና የትሩፋትን ሥራ ሁሉ ፈጸመ።
እግዚአብሔርም የሚያስደንቁ ብዙዎች የሆኑ ታላላቅ ተአምራቶችን በእጆቹ ገለጠ። ከእርሳቸውም አንዲቷን ብላቴና አዳናት እርሷም እንደ ዕንጨት የደረቀች እስከምትሆን ብዙ ዘመን ጭንቅ በሆነ ደዌ ታማ የኖረች ናት። ዳግመኛም ብዙ ሰዎችን ያጠፋውን ታላቅ ከይሲ በጸሎቱ ገደለው። ከሰውና ከእንስሳም አስጨናቂ የሆኑ በሽታዎችን አሰወገደ።
የተጋድሎውና የኃይሉ ጽናት ወሬው በተሰማ ጊዜ ስሙ ሉክያኖስ የሚባል መኰንን ወደርሱ ልኮ አስመጥቶ ያለ ውዴታው በግድ የጭፍራ አለቃ አድርጎ ሾመው እርሱ ግን ተጋድሎውን አልተወም ጾምንም ጸሎትንም የትሩፋትን ሥራ የሚጨመር ሆነ እንጂ የቀደመ ሥራውን አልተወም በጥቂት ቀኖችም ዲዮቅልጥያኖስንና መክስምያኖስን እግዚአብሔር አጠፋቸው አምላክን የሚወድ ጻድቅ ሰው ቈስጠንጢኖስ ነገሠ ይህም ቅዱስ ከጭፍራ ውስጥ ይወጣ ዘንድ ምክንያት የሚሻ ሆነ።
ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ እጅግ የሚወደው መልከ መልካም የሆነ ወጣት ብላቴና ነበር ክፉ ጋኔንም ተጫነበት በቀንም በሌሊትም ታላቅ ሥቃይን የሚያሠቃየው ሆነ ቅዱስ አጋቢጦስንም ከሚያውቁት ውስጥ አንድ ሰው በአየው ጊዜ የወታደር አለቃ አጋቢጦስ ቢመጣ በአዳነህ ነበር አለው የታመመውም እርሱ በንጉሥ ጭፍራ ሥርዓት ውስጥ ያለ በውኑ ይህን ሥራ መሥራት ይችላልን አለ ሰውዬውም ገድሉንና ሥራውን ሁሉ አስረዳው። ጋኔን ያደረበትም በእውነት ሊያድነኝ ይችላልና ከዚህ ከአስጨናቂ ደዌ ያድነኝ ዘንድ የወታደር አለቃ አጋቢጦስን ፈጥናችሁ አምጡልኝ አለ።
ንጉሥም ይህን በአወቀ ጊዜ ቅዱስ አጋቢጦስን እንዲአመጡለት አዘዘ በመጣ ጊዜም በወጣቱ ላይ ጸለየ በከበረ መስቀልም አማተበው በዚያንም ጊዜ በእግዚአብሔር ኃይል ዳነ ንጉሡም በዚህ ደስ ብሎት ቅዱስ አጋቢጦስን አከበረው ምን እንዳደርግልህ ትሻለህ አለው እርሱም ንጉሡን ከወታደርነት ውስጥ አሰናብተኝ አለውና አሰናበተው አስቀድሞ ወደ ነበረባትም ቦታው ተመለሰ ብዙ ዘመናትም እጅግ እየተጋደለ ኖረ።
ከዚህም በኋላ የዚያች አገር ኤጲስቆጶስ ይዞ ቅስና ሾመው ይህም ኤጲስቆጶስ በሞተ ጊዜ ቅዱስ አጋቢጦስን ይሾምላቸው ዘንድ ሕዝቡ ሊቀ ጳጳሳቱን ለመኑት እርሱም ሾመላቸው መልካም ተናጋሪዎች የሆኑትን የክርስቶስን መንጋዎች በበጎ አጠባበቅ ጠበቃቸው።
እግዚአብሔርም የትንቢትን ጸጋ የተሠወረውንም የማወቅ ድንቆች ተአምራቶችንም የማድረግ ሀብትን ሰጠው። በሥውር ኃጢአትን የሚሠሩትን ኃጢአተኞች የሚገሥጻቸው ሆነ በንስሐም እስኪመለሱ ከመቅደስ ያርቃቸዋል።
ዳግመኛም በገድሉ መጽሐፍ ተጽፎ የተገኘ የታላቅ ወንዝ ወራጅ ውኃን በመስቀሉ አቁሞ ወደ ሌላ መንገድ መለሰው የዕውር ዐይኖችንም ገለጠ ለምጻሞችንም አነጻ ብዙዎች በሽተኞችንም አዳነ።
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘለዓለም አሜን።https://t.me/finotebirhan12
ቀንደኛ የሆኑ መናፍቃንን መንገድ ላይ በሚያገኝበት ጊዜ እንዲሁ ያደርግ ነበር:: ወደ ሮም በተጓዘበት ወቅት መርቅያን የተባለውን መናፈቅ አየውና ትኩር ብሎ በመመልከት ሲቃወመው መርቅያን “ታውቀኛለህን” አለው:: ፖሊካርፐስም “አዎን አውቅሃለሁ፤ አንተ የዲያብሎስ የበኩር ልጁ ነህ” ብሎ መልሶለታል:: ቅዱስ ሄሬኔዎስም ለመናፍቃን ምላሽ በጻፈው መጽሐፉ ውስጥ ፍሎሪነስ ለተባለው መናፍቅ መልስ በሰጠበት ክፍል ስለፖሊካርፐስ እንዲህ ሲል ዘግቧል:- “. . . ነግር ግን ይህ ቅዱስ [ፖሊካርፐስን ነው] እንዳንተ ትምህርት ያለ የተሳሳተ ትምህርት ሲሰማ እንደልማዱ ፈጥኖ ጆሮውን በመያዝ እንዲህ በማለት ይጮሃል ‘አቤቱ ቸር ፈጣሪዬ ሆይ እስከዚህ ዘመን ድረስ ያቆየኸኝ ይህን ነገር ልታሰማኝ ነውን?’ . . .ወዲያውም ይህን ዓይነት የክህደት ትምህርት የሰማበትን ሥፍራ ለቆ እያለቀሰ በፍጥነት ይወጣል::”
የቅዱስ ፖሊካርፐስ የሰማዕትነቱ ዜና የተገኘው የራሱ የሆነችው የሰምርኔስ ቤተ ክርስቲያን ሰማዕትነቱን በአካል በተከታተሉ ወንድሞች አማካኝነት ጽፋ ለሌሎች አብያተ ክርስቲያናት ከበተነችው መልእክት ነው:: በጥንቷ ቤተ ክርስቲያን የሰማዕታት የሰማዕትነታቸው ሁኔታ፣ ሳይፈሩ ሰውነታቸውን ለሰይፍ ለስለት እንዴት እንደሰጡ፣ ስለ ክርስቶስ ለመመስከር እንዴት ይጨክኑ እንደነበር በሙሉ ዜና ገድላቸው እየተጻፈ በየአብያተ ክርስቲያናቱ ይሰራጭ ነበር:: እንደ አግናጥዮስ ሁሉ (በሮም) ፖሊካርፐስ ሰማዕት በሆነበት ጊዜም በሰምርኔስ ከተማ የሕዝብ በዓል ተደርጎ ነበር:: እንደልማዳቸው በዓሉ በሚከበርበት በእስታድየማቸው የአራዊት ትርኢት ነበር:: አሬኒከስ የተባለ አንድ ክርስቲያንም የአሕዛብ ጣዖታትን ካላመለክህ ለአራዊት እንሰጥሃለን ብለውት አሻፈረኝ ብሎ በመፅናቱ በዚያ በአራዊት ተበልቶ ሰማዕት ሆነ:: በዚህ ጊዜም ሕዝቡ ክርስቲያኖች እንዲህ እንዲፀኑ የሚያስተምራቸው ዋነኛው ፖሊካርፐስ ነው እርሱ ተይዞ ይምጣ እያሉ ጮሁ::
ቅዱስ ፖሊካርፐስ የሞት ፍርድ ሲፈረድበት ፀንቶ በከተማዋ ቢቆይም ምእመናን እንዲሸሽ እያለቀሱ ስለለመኑት ባጠገብ ወዳለች መንደር ሸሸ::በዚያ ሳለ ሰማዕት እንደሚሆን በራእይ ተረድቶ እንደሚሞት ለወንድሞችና እህቶች ነገራቸው:: ወዲያው በጥቆማ ተይዞ ወደ ሰምርኔስ ከተማ እያንገላቱ ወስደው ሕዝብ በተሰበሰበበት በበዓሉ አደባባይ አቆሙት:: እርሱም ክርስቶስ በሕዝብ አደባባይ ቆሞ የተቀበለውን መከራ እያሰበ የመከራው ተካፋይ ስላደረገው በፍጹም ደስታ መከራውን ይቀበል ነበር:: በሕዝቡ ፊት አቁሞ የሚያናዝዘው ሹም ክርስቶስን እንዲክድ ብዙ ማግባቢያዎችንና ማስፈራሪያዎችን ቢያቀርብለትም ያለፍርሃት ፀንቶ ክርስቲያንነቱን ስለመሰከረ በእሳት እንዲቃጠል ተፈረደበት:: ወታደሮቹ እሳቱ ውስጥ ከገባ በኋላ የሚያመልጠን መስሏቸው ለማጠር ሲዘጋጁ አይቶ “ወደ እሳቱ እንድገባ ያበረታኝ ጌታዬ በእሳቱ ውስጥም ፀንቼ እንድቆይ ያስችለኛል” አላቸው:: ወታደሮቹ እጅና እግሩን አስረው ወደ እሳቱ ሲያቀርቡት አይኑን ወደ ሰማይ አቅንቶ እንዲህ በማለት የመጨረሻ ጸሎት አደረገ:- “አቤቱ ልዑል እግዚአብሔር የተወደደው ልጅህ የኢየሱስ ክርስቶስ አባት ሆይ በልጅህ አንተን እንድናውቅ ሆነናል:: የመላእክትና የኀይላት እንዲሁም የፍጥረታት ሁሉ ፈጣሪ አንተ ነህ፤ ፍጥረታትም ሁሉ የሚኖሩት ባንተ ነው:: በመንፈስ ቅዱስ አጋዥነት ለዘላለማዊ ሕይወት ትንሣኤ ያለፍርሃት ከክርስቶስ መከራ ተካፋይ ከሆኑት ከሰማዕታት ወገን እንድቆጠር ስላደረግኸኝ እና በዚህች ቀንና ሰዓት በሚገባ ስላስተማርኸኝ አመሰግንሃለሁ:: እንደ እነርሱ ዛሬ በፊትህ ተቀብያለሁና እንደ መልካምና የተወደደ መሥዋዕት አድርገህ ተቀበልልኝ:: አንተ አስቀድመህ እንዳሳየኸኝ እና እንዳዘጋጀኸኝ : አንተ እውነተኛና ታማኝ አምላክ ነህና ስለሁሉ ነገር አመሰግንሃለሁ፣ አከብርሃለሁ፣ ከፍ ከፍ አደርግሃለሁ:: ከሰማያዊው ዘላለማዊ ሊቀ ካህናት ከተወደደው ልጅህ ኢየሱስ ክርስቶስ: ከእርሱ ጋር ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ክብርና ምስጋና ለአንተ ይሁን ዛሬም ዘወትርም ለዘላለሙ አሜን!”
የጸሎቱ ይዘት ዛሬ ቤተ ክርስቲያናችን ከምታስተምረው ምሥጢረ ሥላሴ ጋር አንድ አይነት ሲሆን ይህንኑም የመሰለ ጸሎት አላት:: በዚህም የቅድስት ቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ጥንታዊና ከምንጮቹ ከሐዋርያት የተረከበችው ለመሆኑ ታላቅ ማስረጃ ነው:: ቅዱሱ ጸሎቱን ሲጨርስ በእሳቱ ውስጥ ወረወሩት:: በቅዱሳኑ ላይ አድሮ ተአምር የሚሠራ እግዚአብሔር ለምእመናን መጽናኛ የሚሆን ድንቅ ተአምርን አደረገ:: እሳቱ የቅዱሱን ሰውነት ዙሪያውን እንደግድግዳ ከቦ የማያቃጥለው ሆነ;: ሕዝቡም እሳቱ እንዳላቃጠለው ባዩ ጊዜ በጦር ተወግቶ ይሙት እያሉ ጮሁ፤ ወታደሮቹም በጦር ወጉትና በዚህ ሰማዕትነቱን ፈጸመ:: ክርስቲያኖች እንዳያመልኩት በሚል የከበረ ሥጋውን አቃጠሉ፤ በዚህ ጊዜ ደስ የሚያሰኝ የእጣንና የሽቶ መአዛ ሸተተ:: ክርስቲያኖችም ተረፈ አፅሙን በክብር ወሰደው ቀበሩት ቤተ ክርስቲያንም በስሙ ሠሩለት:: (ወ/ሮ ዘውዴ ገ/እግዚአብሔር፣ ቅዱስ ፖሊካርፐስ ሐዋርያዊ ጳጳስ ወሰማዕት፣ 2001 ዓ,ም.)
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን ለእኛም የሰማዕታት ጽናታቸውን አድሎ ከበረከታቸው ይክፈለን ለዘለዓለሙ አሜን።https://t.me/finotebirhan12
በዚህች ቀን የክቡር ፋሲለደስ ልጅ የከበረ አውሳብዮስ በሰማዕትነት አረፈ። ይህም የከበረ ፋሲለደስ ለአንፆኪያ መንግስት የሰራዊት አለቃ ነው ለመንግስት ልጆችም አባታቸው ነው እርሱም ከፋርስ ሰዎች ጋር በጢርነት ውስጥ እያለ ዲዮቅልጥያኖስ የክብር ባለቤት ጌታችንን ክርስቶስን ክዶ ጣኦትን እንዳመለከ ሰማ።
እጅግ አዝኖ ወደ ልጁ ወደ አውሳብዮስ ልኮ ይህንን ነገረው የከበሩ የቤተ መንግስት ሰዎች ዘመዶቹን ዳግመኛ ጠራቸው እነርሱም የንጉስ ልጅ ዮስጦስ አባዲር ገላውዴዎስና ቴዎድሮስ ከእርሳቸውም ጋር ያሉትን ጠርቶ ስለ ከሀዲው ንጉስ ነገራቸው።
ሁሉም እጅግ አዘኑ ዳግመኛም እንዲህ አላቸው እኔ ስለ ፈጣሪዬ ስለ ክርስቶስ ስም ደሜን አፈሳለሁ ሁሉም በዚህ በጎ ምክር ተስማምተው እርስ በርሳቸው ተማማሉ።ጠላቶቻቸውንም ድል አድርገው ወደ ሀገራቸው በተመለሱጊዜ ንጉሱ ከሰራዊቱ ጋር ወጥቶ በደስታ ተቀበሏቸው።
ከዘህም በኃላ የቅዱስ ፊቅጦር አባት ህርማኖስ ለቅዱሳኑ ጣዖትን እንዲአቀርብላቸውና አንዲሰግዱለት ንጉሱን መከረው ንጉሱም ህርማኖስ እንደ መከረው አደረገ። በዚያንም ጊዜ ቅዱሳንን ጠርቶ እነዲህ አላቸው እኔ እጅግ እንደምወዳችሁ እናንተ ታውቃላችሁ አሁንም ለአጶሎን ሰግዳችሁ ልቤን ደስ ታሰኙ ዘንድ ከእናንተ እሻለሁ።
ቅዱሳንም ሰምተው እጅግ ተቆጡ አውሳብየስም ንጉሱን ሊገድል ሰይፉን መዘዘ ንጉሱም ሸሽቶ ተሸሸገ ከንጉስም ባለሟሎች ብዙዎችን ሰራዊቱንም ጭምር ገደለ የከበረ ፋሲለደስም ባይከለክላቸው ከንጉስ ቤት ምንም ሰው ባልቀራቸው ነበር።
ከዚህም በኃላ ደግሞ አውሳብዮስን ወደ ግብፅ አገር ወስደው በዚያ ይገድሉት ዘንድ ህርማኖስ ንጉሱን መከረው እርሱ በዚች ሀገር ከኖረ ያገር ሰዎችን በላይህ ያስነሳብሀልና ያሰብከውን ምንም ምን መስራት አትችልም አለው።
ንጉሱም ቅድስ አውሳብዮስን ፅኑዕ ስቃይን ያሰቃዩት ዘንድ ወደ ግብፅ አገር ወደ ቅፍጥ ገዥ ሉልያኖስ ዘንድ እንዲወስዱት ፃፈ ወደ መኮንን ሉልያኖስም በደረሰ ጊዜ በመንኮራኩር ሀዋሳቱን በመቁራረጥ በግርፋት አሰቃዩት። ደግመኛም በብረት ምጣድ ውስጥ አበሰሉት ጌታችንም መልአኩን ልኮ ከመከራው ሁሉ አዳነው አፅናንቶና አረጋግቶ ያለ ጉዳት አስነሳው።
ነፍሱንም ተድላ ደስታ ወዳለበት ገነት ወሰዳት የፃድቃንና የሰማእታትንም መኖሪያ አየ ለርሱና ለአባቱ ለዘመዶቹም ያዘጋጀላቸውን ቦታዎች አይቶ ነፍሱ እጅግ ደስ አላት።
ከዚህም በኃላ ወደ እሳት ማንደጃ ውስጥ ይጨምሩት ዘንድ መኮንኑ አዘዘ ያን ጊዜ ከእግዚአብሔር የታዘዘ መልአከ ወርዶ እሳቱን እንደ ጠል አቀዝቅዞ ያለ ጥፋት የከበረ አውሳብዮስን አውጣው።
መኮንን ሆይ ራሱን በሰይፍ እንዲቆርጡ እዘዝ ከእርሱም ትግል ታርፋለህ እርሱም የአውሳብዮስን የከበረች ራሱን በሰይፍ ይቆርጡ ዘንድ አዘዘና ቆረጡት የሰማእትነት አክሊልንም በመንግስተ ሰማያት ተቀበለ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅዱስ_ፖሊካርፐስ_ሐዋርያዊ_ሰማዕት
በዚህች ቀን የሰርምኔሱ ሊቀ ጳጳስ ሐዋርያዊው ሰማዕት ቅዱስ ፖሊካርፐስ መታሰቢያው ነው፡፡ ቅዱስ ፖሊካርፐስ የተወለደው ከክርስቲያን ቤተሰቦች በ70 ዓ.ም. በጥንታዊቷ ሰምርኔስ ከተማ (ቱርክ ውስጥ የአሁኗ እዝሚር) ነው፡፡ ቤተሰቦቹን በልጅነቱ ስላጣ ካሊቶስ/ካሊስታ የተባለች ደግ ክርስቲያን አሳድጋዋለች፡፡ ከእርሷም በኋላ የሰምርኔስ ከተማ ጳጳስ ቡኩሎስ ወስዶ ትምህርተ ሃይማኖትን በሚገባ እያስተማረ አሳድጎታል:: ይህ ቅዱስ ቡኩሎስ የቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ ደቀ መዝሙር ስለነበር ቅዱስ ፖሊካርፐስ ዮሐንስ ወንጌላዊን እና ሌሎችንም ሐዋርያት የማግኘት ዕድል ነበረው:: ቅዱስ ቡኩሎስ ቅንዓቱንና ትጋቱን አይቶ ዲቁና ሾመው፤ ቀጥሎም ቅስናን ሾመውና የቅርብ ረዳቱ አደረገው:: ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ ሐዋርያዊ ጉዞ በሚያደርግበት ወቅት አስከትሎት ይሄድ ነበር፤ ከሌሎች ሐዋርያት ረዘም ላለ ጊዜ በምድር ላይ ስለነበር ለብዙ ዓመታት የእርሱ ደቀ መዝሙር ሆነ:: ቅዱስ ቡኩሎስ ካረፈ በኋላ ቅዱስ ዮሐንስ የሰምርኔስ ከተማ ጳጳስ አድርጎ ሹሞታል::
ቅዱስ ፖሊካርፐስ ወንጌልን ከሐዋርያት በተለይም ከዮሐንስ በቀጥታ እየሰማ ያደገ፣ የሐዋርያትን ትውፊት በሚገባ የወረሰ፣ በሥራዎቹ በሙሉ እነርሱን መስሎ እነርሱን አክሎ የተነሣ አባት ነው፤ ቁጥሩም ከሐዋርያውያነ አበው መካከል ነው:: የሰምርኔስን ቤተ ክርስቲያን በሚገባ የጠበቀእና በካህናትና ምእመናን ዘንድም እጅግ ተወዳጅ የነበረ አባት ነው:: ብዙ ደቀ መዛሙርትን ያፈራ ሲሆን ከእነዚህም ታላላቆቹ ቅዱስ ሄሬኔዎስ እና ቅዱስ ፓፒያስ ይገኙበታል:: የአንጾኪያው ጳጳስ ቅዱስ አግናጥዮስ ቅዱስ ፖሊካርፐስን እጅግ ይወደውና ያከብረው ነበር:: ሁለቱ ቅዱሳን ሰፊ የሆነ የዕድሜ ልዩነት የነበራቸው ቢሆንም በሐዋርያት መካከል አዋቂውም ሕፃኑም ቃላቸውን ለመስማት ይሰበሰብ ስለነበር በዚያ ተዋወቁ:: ስለዚህም ሁለቱም የዮሐንስ ወንጌላዊ ደቀ መዛሙርት ናቸው:: ቅዱስ አግናጥዮስ ለሰማዕትነት ወደ ሮም ሲጓዝ ለመጨረሻ ጊዜ ተገናኝተው እንዲህ ብሎታል:- “የአንጾኪያን ቤተ ክርስቲያን አደራ፤ እኔ መልእክት ላልጻፍሁላቸው አብያተ ክርስቲያናት አንተ ጻፍላቸው::” በዚህም ምክንያት ለፊልጵስዩስ ክርስቲያኖች ደብዳቤ ጽፎ ለሌሎች አብያተ ክርስቲያናት የተጻፉ የአግናጥዮስ መልእክታትንም ጨምሮ ልኮላቸዋል:: በመጨረሻም ቅዱስ አግናጥዮስ ለግሉ በስሙ ደብዳቤ ጽፎለታል፤ ይህም ለግለሰብ የጻፈው ብቸኛው መልእክት ነው::
ቅዱስ ፖሊካርፐስ ጠንካራ የኦርቶዶክስ እምነት ጠበቃ ነበር:: ዘመኑ መናፍቃን ከቀናችው የሐዋርያት ትምህርት የወጣ ልዩ ልዩ ትምህርቶችን ያፈሉበትና ምእመናንን የሚያደናግሩበት ወቅት ስለነበር እነርሱን በመርታት ትክክለኛውን የሐዋርያት ወንጌል ያስተምር ነበር:: በምንፍቅና ትምህርት የተወሰዱ ብዙዎችንም ወደ ቀናችው ትምህርት መልሷል:: ደቀ መዛሙርቱንም “ልጆቼ እባካችሁ ከስህተት ራቁ” እያለ በተደጋጋሚ ይመክራቸው ነበር:: በአስተምህሮውም ሁሉ መምህሩን ወንጌላዊ ዮሐንስን ይመስል ነበር:: ለምሳሌ ወደ ፊልጵስዩስ ከጻፈው መልእክቱ ብንመለከት:- “ማንም ኢየሱስ በሥጋ እንደመጣ የማያምን ፀረ-ክርስቶስ ነው:: በመስቀል ላይ መከራ መቀበሉን የማያምንም ዲያብሎስ ነው:: ማንም የክርስቶስን ትምህርት ለራሱ እንደሚመቸው የሚያጣምም፤ ትንሣኤና የመጨረሻ ፍርድ የለም የሚል ይህም የሰይጣን የበኩር ልጅ ነው” ይህም ነገረ ሥጋዌን የካዱትን በሚመለከት የጻፈው ሲሆን ከሐዋርያው ቃል ጋር በእጅጉ ይመሳሰላል:- “የእግዚአብሔርን መንፈስ በዚህ ታውቃላችሁ፤ ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ እንደ መጣ የሚታመን መንፈስ ሁሉ ከእግዚአብሔር ነው፥ኢየሱስ ክርስቶስም በሥጋ እንደ መጣ የማይታመን መንፈስ ሁሉ ከእግዚአብሔር አይደለም፤ ይህም የክርስቶስ ተቃዋሚው መንፈስ ነው፤ ይህም እንዲመጣ ሰምታችኋል፥” (1ዮሐ. 4፥2-3):: በእስያ ብቻ ሳይሆን ሮም ድረስ ሐዋርያዊ ጉዞ በማድረግ በዚያ በነበሩ መናፍቃን የተወሰዱትን ምእመናን አስተምሮ መልሷል::
ቅዱስ ፖሊካርፐስ ከሐዋርያት ትምህርት የወጣ አስተምህሮ ሲሰማ ያለቅስ ነበር፤ እጅግም ስለሚዘገንነው ሥፍራውን ለቆ ይወጣ ነበር:: ይህንንም ከሐዋርያው ዮሐንስ እንደተማረው ያደርግ ነበር፤ በነገር ሁሉ እርሱን ይመስለው ነበርና:: ቅዱስ ሄሬኔዎስ ቅዱስ ፖሊካርፐስ እንዲህ ሲል ተሰማ በማለት ጽፏል: “ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊ በኤፌሶን ወደ አንድ መታጠቢያ ክፍል ሲገባ መናፍቁ ቀሪንጦስን አየውና ‘ከዚህ እንሽሽ የእውነት ጠላቷ ቀሪንጦስ በዚህ አለና’ እያለ ወዲያውኑ ክፍሉን ለቆ ወጣ::” እርሱም
🔴#ስንክሳር የካቲት_23
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
የካቲት ሀያ ስሶት በዚህች ቀን #ቅዱስ_ጊዮርጊስ ሊቀ ሰማዕታት አባቶቻችንን አድዋ ላይ የረዳበት ነው፣ የክቡር ፋሲለደስ ልጅ የከበረ #ቅዱስ_አውሳብዮስ በሰማዕትነት አረፈ፣ የሰርምኔሱ ሊቀ ጳጳስ ሐዋርያዊው ሰማዕት #ቅዱስ_ፖሊካርፐስ መታሰቢያው ነው፡፡
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅዱስ_ጊዮርጊስ_ሊቀ_ሰማዕታት
የካቲት ሀያ ስሶት በዚህች ቀን ቅዱስ ጊዮርጊስ ሊቀ ሰማዕታት አባቶቻችንን አድዋ ላይ የረዳበት ነው፡፡ በዚያን ወራት ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ ልደት ከአንድ ሺህ ስምንት መቶ ሃምሳ አራት ዓመት በኋላ የኢትዮጵያው ንጉሠ ነገሥት ዳግማዊ አጤ ምኒልክ በነገሡ በሃያ ስድስት ዓመት የምኒልክ የጦር አለቃ ገበየሁ ድል ከአደረጋቸው በኋላ እንደገና ምኒልክም ወግተው ኢትዮጵያን በቅኝ አገዛዝ ሊገዙ የሮም ሰዎች መጡ።
ከዚህም በኋላ የኢትዮጵያው ንጉሠ ነገሥት፡ ዳግማዊ አጤ (ዓፄ) ምኒልክ መስከረም ፯ ቀን ፲፰፻፹፰ (1888፡ዓ.ም ) ላይ "እግዚአብሔር በቸርነቱ፡ እስከ አሁን ጠላት አጥፍቶ አገር አስፍቶ አኖረኝ፡፡ እኔም እስከ አሁን በእግዚአብሔር ቸርነት ገዛሁ፡፡ እንግዲህ ብሞትም ሞት የሁሉ ነውና ስለ እኔ ሞት አላዝንም፡፡ ደግሞ እግዚአብሔር አሳፍሮኝ አያውቅም፡፡ እንግዲህም ያሳፍረኛል ብዬ አልጠራጠርም፡፡ አሁንም አገር የሚያጠፋ፤ ሃይማኖት የሚለውጥ ጠላት፤ እግዚአብሔር የወሰነልንን የባህር በር አልፎ መጥቷልና እኔም የአገሬን ከብት ማለቅ፤ የሰውን መድከም አይቼ እስከ አሁን ዝም ብለው ደግሞ እያለፈ እንደ ፍልፈል መሬት ይቆፍር ጀመር፡፡ አሁን ግን በእግዚአብሔር ረዳትነት አገሬን አሳልፌ አልሰጠውም፡፡ የአገሬ ሰው፤ ከአሁን ቀደም የበደልሁህ አይመስለኝም አንተም እስከ አሁን አላስቀየምኸኝም፡፡ ስለዚህ ስንቅህን በአህያ አመልህን በጉያህ ይዘህ ጉልበት ያለህ በጉልበትህ እርዳኝ፡፡ ጉልበት የሌለህ ለልጅህ፤ለሚስትህ፤ ለሃይማኖትህ ስትል በኀዘን እርዳኝ፡፡ ወስልተህ የቀረህ ግን በኋላ ትጣላኛለህ አልተውህም፡፡ ማርያምን! በዚህ አማላጅ የለኝም"፡፡ ዘመቻዬም በጥቅምት ነውና የሸዋ ሰው እስከ ጥቅምት እኩሌታ ድረስ ወረይሉ ከተህ ላግኝህ" ብለው አዋጅ አስነገሩ፡፡ ዳግኛም በፈረሶታቸው መጣብር ላይ በጦራቸው አንደበት ላይ የመስቀል ምልክት እንዲያደርጉ ጭፍሮችን አዘዛቸው መስቀል ጠላትን ድል አድራጊ እንደሆነ አስቀድሞ ያውቅ ነበርና።
አዋጁን ካስነገሩ በኋላ ከዚያም ተነሥቶ ወደ ትግራይ ክፍለ አገር ዘመቱና ከትግራይ አውራጃ አንዷ የምትሆን አድዋ የምትባል አገር ደረሱ፡፡ የሣህለ ማርያም (ዳግማዊ ምኒልክ) ሚስት ወለተ ሚካኤል (እቴጌ ጣይቱም) በንጉሡ ትዕዛዝ ታቦተ ጊዮርጊስን አስይዘው ከሊቀ ጳጳሱ ከአባ ማቴዎስ እንዲሁም ከቀሳውስቱና ከመነኰሳቱ ጭምር ከንጉሡ ጋር ወደ ጦርነቱ ተጓዘች፡፡በዚያም ጊዜ የአክሱም ጽዮን መነኰሳትና ካህናት የእመቤታችንን ሥዕል ይዘው ወደ ንጉሡ ወደ ምኒልክ መጥተው ከሊቀ ጳጳሱ ከነአቡነ ማቴዎስ ጋር ተቀላቀሉ ከዚያም ሌሊቱን ሙሉ ጸሎት ምሕላ ሲያደርሱ አደሩ።
ቅዳሜ ማታ ለእሑድ አጥቢያ የካቲት ሃያ ሁለት ቀን ነው ንጉሡ ሣህለ ማርያም (ምኒልክ) የጦር ልብሱን ለብሰው ከሠራዊቱ ጋር ወደ ጦር ግንባር ሄደ፡፡ ከዚያም ከሮማውያን የጠላት ጦር ጋር ተገናኝቶ ከሌሊቱ ዐሥራ አንድ ሰዓት ጦርነቱን ጀመረ፡፡ የንጉሡ የሣህለ ማርያም (የምኒልክ) ሚስት ወለተ ሚካኤል (እቴጌ ጣይቱም) ሌሊት በታቦተ ቅዱስ ጊዮርጊስና በእመቤታችን ሥዕል ፊት በጸሎትና በስግደት እያደረች ሲነጋ ወደጦርነቱ ቦታ በመሄድ እጅግ ለሚያስደንቅ የአነጋገሯ ኃይል ቃል በጦርነቱ መካከል እየተገኘች ለንጉሡ ወታደሮች የሞራልና የብርታት ድጋፍ ትሰጣቸው ነበር። በእውነትም ለተመለከታት ሁሉ እንደ ኃይለኛ ተጋዳይ አርበኛ ትመስል ነበር እንጂ የሴቶች የተፈጥሮ ባሕርይ በእርሷ ላይ አይታይባትም ነበር። የንጉሡም ወታደሮች የንግሥቲቱን የጀግንነት አነጋገር በሰሙ ጊዜ በእሳት ላይ እንደተጣደ የብረት ምጣድ ልባቸው ጋለ ይልቁንም ላም እንዳየ አንበሳና የፍየል መንጋ እንዳየ ነብር እየተወረወሩ በጦርነቱ መካከል በመግባት የጠላትን ጦር በሰይፍ ይጨፈጭፋት ነበር። መጽሐፍ ሹመትን ሽልማትን ያየ አርበኛ ከጦርነት ከሰልፍ ወደኋላ አያፈገፍግም ብሎ ተናግሯልና፡፡ በዚያም ጊዜ ንጉሡ ሣህለ ማርያም (ምኒልክ) በጦርነቱ መካከል ሳለ ሊቀ ጳጳሱ አባ ማቴዎስ እንዲሁም የአክሱም መነኰሳትና ሌሎቹ ካህናት በሙሉ ታቦተ ጊዮርጊስንና ሥዕለ ማርያምን ይዘው ከንጉሡ በስተኋላ በደጀንነት ቆመው ጸሎተ ምህላ ያደርሱ ነበር። ንግሥቲቱ ወለተ ሚካኤል (እቴጌ፡ጣይቱም) በጸሎት ጊዜ በመዓልትም በሌሊትም ከእነርሱ አትለይም ነበር። የጽዮን አገልጋዮችም በእግዚአብሔር የሕጉ ታቦት ፊት መለከት ይነፉ ነበር።
በዚህም ዕለት ይኸውም የካቲት ሃያ ሦስት ቀን በሮማውያንና በኢትዮጵያውያን መካከል ከፍተኛ ጦርነት ሆነ በዚህም ጊዜ በሰማይ ታላቅ ተአምር ተደረገ። ማለትም የቀስተ ደመና ምልክት ታየ ከዚያም ከቀስተ ደመናው ውስጥ መልኩ አረንጓዴ የመሰለ ጢስ ይወጣ ነበር፡፡ ከዚህም ጢስ ውስጥ እንደ ክረምት ነጐድጓድ ያለ ድምጽ ተሰማ፡፡ ከዚህም የነጐድጓድ ድምጽ የተነሳ በሮማውያን ወታደሮች ዘንድ ከፍተኛ ድንጋጤና ሽብር ሆነ ለመዋጋት አልቻሉም፡፡ ይልቁኑ ኃያሉ ገባሬ ተአምር ማር ቅዱስ ጊዮርጊስ በአምባ ላይ ፈረሱ ተቀምጦ ከነፋስ ሩጫ ይልቅ እየተፋጠነ በአየር ላይ በተገለጸ ጊዜ በግንባራቸው ፍግም እያሉ ወደቁ፡፡ "የኢትዮጵያ ህዝብ አምላካቸው ሊረዳቸው መጣ እንግዲህ ማን ያድኅነናል" አሉ ምድርም ጠበበቻቸው በዚህን ጊዜ የኢትዮጵያ ሠራዊት የሮምን የጦር ሠራዊት ፈጁዋቸው የተረፉትንም ማረኳቸው ፈጽመውም እስኪያጠፏቸው ድረስ በሮማውያን ላይ በእግዚአብሔር ሥልጣን የኢትዮጵያውያን እጅ እየበረታ ሄደ፡፡ ከዚህም በኋላ የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ሣህለ ማርያም (ምኒልክ) በእግዚአብሔር ኃይልና በተአምራት አድራጊው በቅዱስ ጊዮርጊስ ተራዳይነት የሮማውያንን የጦር ሠራዊት ድል አድርገው የድል አክሊል ተቀዳጅተው ተመለሱ፡፡
ስለዚህም በዳዊት የምስጋና ቃል የድል ዘውድ ያቀዳጀኝን እግዚአብሔር "ባለ ዘመኔ ሁሉ አመሰግነዋለሁ ለፈጣሪዬ እዘምራለሁ" አለ ሕዝቡም ሁሉ "በክብር ከፍ ከፍ ያለ እግዚአብሔርን በፍጹም ምስጋና እናመስግነውለን የሮማውያንን ኃይል ቀጥቅጦ አጥፍቷልና ሠረገሎቻቸውንም ሠባብሯልና ሠራዊቱንም ሁሉ በምድር ላይ በትኗልና" እያሉ አመሰገኑ። በፈጣሪው በኢየሱስ ክርስቶስ ኃይል በጦርነቱ መካከል የረዳውን ቅዱስ ጊዮርጊስንም በፍጹም ማድነቅ አደነቁ። የሮማም የጦር ሠራዊት በኢትዮጵያውያን ፊት ተዋረዱ ዳግመኛም በኢትዮጵያ ላይ ራሳቸውን ከፍ ከፍ አላደረጉም። በምኒልክም ዘመነ መንግሥት ኢትዮጽያ ከጦርነት ለዓርባ ዓመት ያህል አረፈች።
የኢትዮጵያው ንጉሠ ነገሥት ምኒልክ ከአደዋ ጦርነት ከተመለሱ በኋላ በአዲስ አበባ በምትበል ከተማው መካከል በቅዱስ ጊዮርጊስ ስም ቤተክርስቲያን አሠራ። ስሟንም ገነተ ጽጌ ብለው ሰየሟት። ቅዱስ ጊዮርጊስ በጦርነት ቦታ ሁሉ ይረዳው ነበርና። ልመና ክብሩ በኛ ለዘላለሙ በዕውነት ይደረግል። በረከቱ ከእኛ ጋር ትሁን እኛንም በቅዱስ ጊዮርጊስ አማላጅነት ይማረን ለዘለዓለሙ አሜን!!! (ገድለ ቅዱስ ጊዮርጊስ ተአምር 17)
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅዱስ_አውሳብዮስ_ሰማዕት
🔴#ስንክሳር የካቲት_22
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
የካቲት ሃያ ሁለት በዚች ቀን የኤጲስቆጶስ #ቅዱስ_አባ_ማሩና የዕረፍቱ መታሰቢያና #የፋርስ_ሰማዕታት ሥጋቸው የፈለሰበት ነው፣ ታላቅና ክቡር የሆነ መስተጋድል #ቅዱስ_አባ_ቡላ መታሰቢያው ነው።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅዱስ_አባ_ማሩና_ጻድቅ
የካቲት ሃያ ሁለት በዚች ቀን የኤጲስቆጶስ አባ ማሩና የዕረፍቱ መታሰቢያና በከሀዲ በዲዮቅልጥያኖስ ዘመን በፋርስ አገር ለተገደሉ ሰማዕታት ሥጋቸው የፈለሰበት ነው።
ኤጲስቆጶስ ማሩናንም ስለ ድንቆች ተአምራቶቹ ስለ ትሩፋቱና ስለ ጽድቁ የአኖሬዎስና የአርቃዴዎስ አባት ታላቁ ቴዎዶስዮስ ንጉሥ ወደ ፋርስ ንጉሥ ላከው ከእርሱም ጋር እጅ መንሻ በመካከላቸው ስለ አለው ፍቅር ተላከ። ወደ ሳቦር ወደ ፋርስ ንጉሥም በደረሰ ጊዜ ታላቅ ክብርንም አከበረው በቤተ መንግሥቱም እልፍኝ ውስጥ አኖረው። ይህ ቅዱስም የንጉሡ ልጅ ጋኔን አድሮባት እንደታመመች በሰማ ጊዜ የከበረ አባ ማሩና ብላቴናዪቱን ጠርቶ በፊቱ አቁሞ በላይዋ ጸለየ ጋኔኑም ከእርሷ ወጥቶ ዳነች ንጉሡም ልጁ እንደዳነች አይቶ እጅግ ደስ አለው የአባማሩናንም ፍቅርና አክብሮት ጨመረ።
ከዚህም በኋላ አባ ማሩና በፋርስ ሀገር በሰማዕትነት ስለሞቱ የከበሩ ሰማዕታት ሥጋቸውን ስለ መሰብሰብ ከንጉሥ ዘንድ ፈለገ ንጉሡም የሰማዕታትን ሥጋቸውን ይሰበስቡ ዘንድ ቤተ ክርስቲያንም ሠርተው በውስጧ ሥጋቸውን ያኖሩ ዘንድ አዘዘ ያች ቤተ ክርስቲያንም በዚች ዕለት ከበረች።
ዳግመኛም በታላቋ ከተማ ውስጥ በከበረ አባ ማሩና ስም ያማረች ቤተ ክርስቲያንን ሠሩ እርሷም ማረፊያ የተባለች ናት። ከዚህም በኋላ ይህ አባት ወደ ንጉሥ ቴዎዶስዮስ ተመልሶ በሮሜ አገር ሁለት ዓመት ተቀመጠ የእነዚያ ሰማዕታት ቤተ ክርስቲያን በከበረችበት በዚች ዕለት አረፈ ከቤተ ክርስቲያኒቱም ክብር ጋር በዓሉንና መታሰቢያውን የሚያከብሩለት ሆኑ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ቅዱስ_አባ_ቡላ
ዳግመኛም በዚህች ቀን ታላቅና ክብር የሆነ አቢብ የተባለ መስተጋድል አባ ቡላ መታሰቢያው ነው። የዚህም ቅዱስ የአባቱ ስም አብርሃም የእናቱም ስም ሐሪክ ነው እነርሱም ከሮሜ አገር ሉፊ ከሚባል አውራጃ ናቸው በዘመናቸውም ከሀዲው ንጉሥ መክስምያኖስ በክርስቲያን ወገኖች ላይ መከራ ስለ አመጣ ስደት ሁኖ ነበርና እነርሱም በስደት ብዙ ዘመን ኖሩ።
ልጅንም በአጡ ጊዜ የተባረከ ልጅን ይሰጣቸው ዘንድ በጾም በጸሎት ተወስነው ወደ እግዚአብሔር ለመኑ የእግዚአብሔርም መልአክ በሕልም ተገለጠላቸውና ፍሬ የመላበትን ዘለላ ሰጣቸው።
ይህም ቅዱስ በተፀነሰ ጊዜ በቤታቸው አጠገብ ታላቅ ዛፍ በቀለ በቅጠሉም ላይ በሮማይስጥ ቋንቋ ቡላ የእግዚአብሔር አገልጋይ በጽዮንም አድሮ የሚኖር የያዕቆብ ፈጣሪ ያከበረው የሚል ጽሑፍ ነበረበት።
በተወለደም ጊዜ ክርስትና ሳያስነሡ ዓመት ሙሉ አኖሩት እመቤታችን ማርያምም ለሮሜ ሊቀ ጳጳሳት ለሰለባስትርዮስ ተገልጣ ወደ አብርሃም ቤት ሒዶ ሕፃኑን እንዲአጠምቀው አዘዘችው እርሱም ሒዶ የክርስትና ጥምቀትን አጠመቀው ስሙንም ቡላ ብሎ ሰየመው እናትና አባቱም ሳይነግሩት ቡላ ስለ ሰየመው አደነቁ ዕፁብ ዕፁብ አሉ።
ከዚህም በኋላ ሊቀ ጳጳሳቱ በጸለየ ጊዜ የቊርባን ኅብስትና ወይን የተመላ ጽዋ ከሰማይ ወረደ እርሱም ቀድሶ ሥጋውንና ደሙን ከሕፃኑ ጋር አቀበላቸው በዚያንም ጊዜ ሕፃኑ የአንድ ዓመት ልጅ ሲሆን በባሕርይ በህልውና በመለኮት ከወልድ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር አንድ የሆነ አብ በግብር በአካል በሰም ልዩ ነው በባሕርይ በህልውና በመለኮት ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር አንድ የሆነ ወልድ በግብር በአካል በስም ልዩ ነው በባሕርይ በህልውና በመለኮት በአብ ከወልድ ጋር አንድ የሆነ መንፈስ ቅዱስ በግብር በአካል በስም ልዩ ነው ብሎ ተናገረ።
ከጥቂት ዘመንም በኋላ አባትና እናቱ ኅዳር ሰባት ቀን ሙተው ሕፃኑ ብቻውን ቀረ። ሕፃኑም ዐሥር ዓመት በሆነው ጊዜ ለጣዖት መስገድን የሚያዝ ከሀዲ መኰንን መጣ ቅዱስ ቡላም በሰማ ጊዜ ወደ መኰንኑ ሒዶ የረከሱ አማልክቶቹን ረገመ መኰንኑም በአካል ታናሽነቱን አይቶ እጅግ አደነቀ በዚያንም ጊዜ በችንካር እንዲቸነክሩት ሥጋውንም እንዲሠነጣጥቁት ቆዳውንም ከዐጥንቱ እንዲገፉ እጆቹንና እግሮቹንም በመጋዝ እንዲቆርጡ ጀርባውንም እንዲገርፉ በሾተሎችና በጦሮች መካከል አድርገው ከመንኰርኵር ውስጥ እንዲጨምሩት ዳግመኛም በመንገድ ላይ እንዲጐትቱት አዘዘ የመላእክት አለቃ ሚካኤልም መጥቶ አዳነው ያለ ጉዳትም ጤነኛ አደረገው።
ከዚህም በኋላ ወደ ሌላ መኰንን ሒዶ እርሱንና የረከሱ ጣዖቶቹን ረገመ መኰንኑም ተቆጥቶ በሚያዝያ ወር ዐሥራ ስምንት ቀን ራሱን በሰይፍ ቆረጠው ቅዱስ ሚካኤልም ከሰማይ ወርዶ ከሙታን ለይቶ አስነሣው ወደ አንድ ገዳምም ወስዶ የምንኲስና ልብስንና አስኬማን በመስቀልም ምልክት አለበሰው። እንዲህም አለው ከቅዱሳን ጻድቃን አንድነት ትሆን ዘንድ እግዚአብሔር አዝዞሃል።
ያን ጊዜም ቅዱስ አባ ቡላ ከደረቅ ተራራ ላይ ወጣ ያለ ማቋረጥም በውስጧ እየተጋደለ ኖረ። የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስን መከራውንና ስቅለቱን በአሰበ ጊዜ ከረጅም ዕንጨት ላይ በመውጣት ራሱን ወደታች ሁል ጊዜ ይወረውር ነበር።
በአንዲትም ቀን ከዛፍ ላይ በተወረወረ ጊዜ ሰይጣን ሊገድለው ስለ በረታበት ሞተ ያን ጊዜም ክብር ይግባውና መድኃኑታችን ከሞት አነሣውና እንዲህ አለው ከእንግዲህ ስምህ ቡላ አይሁን አቢብ ይባል እንጂ የብዙዎች አባት ትሆናለህና።
እርሱም የክርስቶስን ፍቅር እጅግ ጨመረ ፊቱንም እየጸፋ ሥጋውን በየጥቂቱ እየቆረጠ ጀርባውንም ሰባት መቶ ጊዜ እየገረፈ ኖረ ጌታችንም ይፈውሰው ነበር በየእሑድም ቀን ከቅድስት ድንግል እመቤታችን ማርያም እንደተወለደ በሌሎች ቀኖችም እንደተያዘና ከአይሁድ መከራ እንደ ተቀበለ ሁኖ ይገለጽለት ነበር።
ስለዚህም ሳይበላ ሳይጠጣ አርባ ሁለት ዓመት ኖረ ዳግመኛም ናላው ፈስሶ እስቲአልቅ ዐሥራ ሁለት ወር በራሱ ተተክሎ ኖረ። በአንዲትም ቀን የጌታችንን መከራ በአሰበ ጊዜ ሰይፉን በአንጻሩ ተከለ ከዕንጨት ላይም ወጥቶ በላዩ ወድቆ ሞተ ቅድስት ድንግል እመቤታችን ማርያምም ከአእላፍ መላእክት ጋር መጥታ የእኔና የልጄ ወዳጅ ሰላምታ ይድረስህ አለችው። ከበድኑም ቃል ወጥቶ የሰማይና የምድር ንግሥት እመቤቴ ሰላምታ ይገባሻል አላት እርሷም በከበሩ እጆቿ ዳሥሣ ከሞት አስነሣቸው።
ዕድሜውንም ፈጽሞ ከዚህ ዓለም የሚወጣበት ጊዜ ሲደርስ ክብር ይግባውና ጌታችን ክርስቶስ በእጁ ልዩ የሆኑ አክሊሎችን የሚያበሩ ልብሶችንም ይዞ ተገለጠለት። ወዳጄ አቢብ ሆይ በማያልቅ ተድላ ደስታ ደስ አሰኝህ ዘንድ ወደ እኔ ና ስምህን ለሚጠራ መታሰቢያህን ለሚያደርግ እኔ ኃጢአቱን አስተሠርይለት ዘንደ በራሴ ማልኩልህ። ወይም ለተራቆተ የሚያለብሰውን ለተራበም የሚያጠግበውን ለተጠማ የሚያጠጣውን የገድልህን መጽሐፍም የሚጽፈውን ወይም የሚያነበውንና የሚሰማውን በጸሎትህም የሚታመኑትን ሁሉ እስከ ዐሥር ትውልድ እምራቸዋለሁ። ይህንም ብሎ አፉን ሳመው በደረቱም ላይ አድርጎ ወደአየር አወጣው የመላእክትንም ምስጋና በሰማች ጊዜ ነፍሱ ከሥጋው ተለየች ወደ ሰማያዊት ኢየሩሳሌም ገባች። የእረፍቱ ቀንም ጥቅምት ሃያ አምስት ይከበራል፡፡ (የጥቅምት 25 ስንክሳር)
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ለዘለዓለሙ ከእኛ ጋር ትሁን አሜን፡፡https://t.me/finotebirhan12
ዜና ዕረፍት
ብፁዕ አቡነ ዮሐንስ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የመቀሌ ፍሬምናጦስ አባ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን መንፈሳዊ ኮሌጅ የበላይ ኃላፊ ሊቀ ጳጳስ በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ።
በረከታቸው ይደርብን
Eotc
የሥራ ማስታወቂያ
የሥራው አይነት: Graphics Designer
ሁኔታ: በቋሚነት
የሚፈለገው ሙያ: Graphics Design
የሥራ ልምድ:1ዓመት
ጾታ:ሴት/ወንድ
ብዛት:1
ደሞዝ:በስምምነት
የስራ ቦታ :ቦሌ ሸገር ህንጻ
ለበለጠ መረጃ በዚህ ስልክ ቁጥር ይደውሉ:0922964325/0960694450
የሥራ ማስታወቂያ
የሥራው አይነት: Recption
ሁኔታ: በቋሚነት
የሚፈለገው ሙያ: መሠረታዊ የኮምፒውተር ዕውቀት
የሚፈለግው ችሎታ: ከሰው ጋር ቶሎ መግባባት:ሥራ ለመልመድ ዝግጁ መሆን።
ጾታ:ሴት
ብዛት:1
ደሞዝ:በስምምነት
ለበለጠ መረጃ በዚህ ስልክ ቁጥር ይደውሉ:0922964325/0960694450
ወደ መንበረ ሢመቱም በደረሰ ጊዜ ሕዝቡ በታላቅ ደስታ ተቀበሉት በዕለተ ሆሣዕና የእስራኤል ሕዝብ መድኃኒታችንን እንደተቀበሉት። ከዚህም በኋላ በትምህርቱና በድርሰቶቹ ቤተ ክርስቲያን ብርሃን ሆነች ቃሉም እጅግ ጣዕም ያለው እርሱም የመንፈስ ቅዱስን ጸጋ የተመላ ነው። በመንበረ ሢመቱም አርባ ዘመን ኖረ እግዚአብሔርንም አገልግሎ በሰላም አረፈ።
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ቅዱሳኑ ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ለዘለዓለሙ ከእኛ ጋር ትሁን አሜን፡፡https://t.me/finotebirhan12
🔴#ስንክሳር የካቲት_21
አንድ አምላክ በሆነ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም
የካቲት ሃያ አንድ በዚህችም ዕለት የከበረ የሐዋርያው የጳውሎስ ደቀ መዝሙር የሆነ #ቅዱስ_አናሲሞስ በሰማዕትነት አረፈ፣ የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት የከበረ አባት #አባ_ገብርኤል አረፈ፣ የሀገረ ስሐ ኤጲስቆጶስ የከበረ አባት #አባ_ዘካርያስ አረፈ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#ሰማዕት_አናሲሞስ_ሐዋርያ
የካቲት ሃያ አንድ በዚህችም ዕለት የከበረ የሐዋርያው የጳውሎስ ደቀ መዝሙር የሆነ ቅዱስ አናሲሞስ በሰማዕትነት አረፈ። ይህም ቅዱስ አስቀድሞ ከሮሜ ሰዎች ወገን ለሚሆን ስሙ ፊልሞና ለሚባል ለሮሜ ሰው አገልጋይ ሆኖ ነበር ይህም ፊሊሞና በሮሜ በአስተማረ ጊዜ በቅዱስ ጳውሎስ ትምህርት በጌታችን አመነ ይህ ፊሊሞናም ከዚያ ከሮሜ አገር ወደ አስባንያ ሔደ።
ይህንንም አገልጋዩን አናሲሞስን ከእርሱ ጋር ወሰደው ሰይጣን ግን አናሲሞስን አሳተው ልቡንም ለወጠውና የጌታውን ገንዘብ ሰረቀ ጌታውም እንደሚቀጣው አውቆ ሸሽቶ ወደ ሮሜ ተመልሶ ሔደና በዚያ ተቀመጠ።
በእግዚአብሔርም ፈቃድ ወደ ከበረ ሐዋርያ ጳውሎስ ሔደ ትምህርቱንም ሰምቶ በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመነ ለቅዱስ ጳውሎስም ደቀ መዝሙሩ ሆነ። ነገር ግን የጌታውን ገንዘብ በመስረቁ በአናሲሞስ ልብ ጽኑ ሀዘን አደረ ለሐዋርያ ጳውሎስም የሠራውን ሁሉ ነገረው ሐዋርያ ጳውሎስም አትፍራ ልብህም አይዘን አለው ወደ ጌታው ወደ ፊልሞናም መልእክትን ጻፈለት ይቺም ስለ አናሲሞስ የጻፋት ከመልእክቶቹ አንዲቱ ናት።
በመልእክቱም እንዲህ አለ እኔ በእሥራቴ ጊዜ ስለወለድኩት ልጄ እማልድሃለሁ ይኸውም አናሲሞስ ነው። የቀድሞው ሥራው አልጠቀመህም ነበር ዛሬ ግን ላንተም ለኔም እጅግ የሚጠቅም ሁኗል አሁንም ወዳንተ ልኬዋለሁና ልጄ እንድመሆንህ ተቀበለው። የበደለህ በደልም ቢኖር ወይም የሚከፍልህ ቢኖር በኔ ላይ አድርገው።
ይህ የከበረ አናሲሞስም ወደ ፊልሞና ወደ ጌታው በደረሰ ጊዜ በማመኑና በመጸጸቱ ደስ አለው ሐዋርያው እንዳዘዘውም አደረገለት እጅግም ወደደው ብዙ ገንዘብም ሰጠው እርሱ ግን ምንም ምን አልወሰደም እኔ በክርስትና ባለጸጋ ሁኜአለሁ አለ እንጂ።
ከዚህም በኋላ ሸኙትና ወደ ሮሜ አገር ተመለሰ በሰማዕትነት እስከ ሚሞትበት ጊዜ ሐዋርያ ጳውሎስን የሚያገለግልው ሆነ። ይህም ቅዱስ ካህን ሆኖ ተሾመ ሐዋርያትም በሥርዓት መጽሐፋቸው በአንቀጽ ሰባ ሰባት ሰማንያ አንድ በኃምሳ ሦስትና በኃምሳ ሰባት በምስጋና አስታውሰውታል እንደ ታማኝ ካህንም ነው አሉ።
ከሐዋርያው ጳውሎስም የምስክርነት ሞት በኋላ የንጉሥ ጭፍራ አለቃ ይህን ቅዱስ ይዞ ወደ አንዲት ደሴት ሰደደው የዚያችን ደሴት ሰዎች ሃይማኖትን እያስተማራቸው ኖረ የክርስትና ጥምቀትንም አጠመቃቸው።
ከብዙ ቀኖችም በኋላ የንጉሥ የጭፍራ አለቃ ወደዚያች ደረሰ የከበረ አናሲሞስንም ሕያው ሁኖ የክብር ባለቤት የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ሃይማኖት ለሰዎች ሲያስተምር አገኘው ጽኑ ግርፋትንም ገርፈው ጭኖቹን እንዲሰበሩ አዘዘ ምስክርነቱንም ፈጸመ። የሰማዕትነት አክሊልንም በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#አባ_ገብርኤል
በዚህችም ቀን የእስክንድርያ ሊቀ ጳጳሳት የከበረ አባት አባ ገብርኤል አረፈ፡፡ እርሱም ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት ኃምሳ ሰባተኛ ነው። ይህም አባት በታናሽነቱ በአስቄጥስ ገዳም መነኰሰ በጾም በጸሎት በስግደት እየተጋ ፍጹም ተጋድሎን በመጋደል ተጠምዶ ኖረ በውስጡም ትሕትና ፍቅር ቅንነት አለው።
በአንዲትም ዕለት ስሙ መክሲሞስ ወደሚባል አረጋዊ ቤት ገባ እርሱም ልጄ ከሰው ለምን ትሸሻለህ አንተ ግን በወንዶችና በብዙ ሴቶች መካከል ትኖር ዘንድ አለህ አለው እርሱ ግን የሽማግሌውን የቃሉን ትርጓሜ አላስተዋለም ከጠላትም ወጥመድ ያድነው ዘንድ ሁል ጊዜ በማልቀስ እግዚአብሔርን የሚለምን ሆነ።
ከእርሱም አስቀድሞ የነበረ ሊቀ ጳጳሳት አባ ሚካኤል በአረፈ ጊዜ ይህን አባት ይዘው ያለ ውዴታው ሊቀ ጳጳሳት አድርገው ሾሙት አረጋዊ አባ መክሲሞስ ትንቢት እንደ ተናገረለት በተሾመም ጊዜ በአስቄጥስ ገዳም ተቀምጦ የቀድሞውን ተጋድሎውንና አገልግሎቱን ቸለል አላለም።
ስለ አብያተ ክርስቲያንም ጉዳይ ወደ እስክንድርያ ወደ ምስር ይሔድ ዘንድ ግድ በአሉት ጊዜ ይሔዳል ፈጥኖም ወደ አስቄጥስ ገዳም ይመለሳል።
እርሱም በዕድሜው ጐልማሳ ስለሆነ እንስሳዊት ፍትወት ትነሣሣበት ነበር እርሱም ያጠፋት ዘንድ ለጾም ለጸሎት ለስግደትም መትጋትን ያበዛል ሊያበርዳትም ባልተቻለው ጊዜ ለአንድ አረጋዊ ተናዘዘለት እርሱም እንዲህ አለው፦ ይህች እንስሳዊት ፍትወት ከጾምና ከጸሎት ከስግደት ጋር ያለ ትሕትና ሥራ አትጠፋም በበለጠ ግን ትሕትና መድኃኒቷ ነውና።
ይህንንም በሰማ ጊዜ የጉድፍ መጐተቻ ከብረት ሠራ አጭር የሆነ የቆሸሸ ልብስ በመልበስ በሌሊት ተነሥቶ የመነኰሳቱን መንደር እይዞረ ቆሻሻውን ጠርጎ ተሸክሞ ወስዶ ከራቀ ቦታ ይጥለዋል። ይህንንም ሥራ እይሠራ ሁለት ዓመት ያህል ኖረ እግዚአብሔርም ንጽሕናውንና የልቡን ትሑትነት ተመልክቶ የባሕርይ የሆነውን ፍትወት አራቀለት።
ይህም አባት በገድል እንደተጠመደ ሁኖ መንጋዎቹ በቀናች ሃይማኖት ይጸኑ ዘንድ እያስተማራቸውና እየገሠጻቸው እየመከራቸውም ዐሥራ ሁለት ዓመት ኑሮ በሰላም አረፈ።
✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞✞
#አባ_ዘካርያስ
በዚህችም ቀን የሀገረ ስሐ ኤጲስቆጶስ የከበረ አባት አባ ዘካርያስ አረፈ። ይህም አባት የጸሐፊዎች ወገን ነው አባቱ ግን ጸሐፊነቱን ትቶ ቅስና ተሾመ ስሙም ዮሐንስ ነው።
ልጁ ዘካርያስም በአደገ ጊዜ ትምህርቶችን ሁሉ ጽሕፈትንም የጽርእና የሮማውያንን ጥበብ የቤተ ክርስቲያንንም ሕግ ተማረ የንጉሥም የጭፍራ አለቃ ወሰደውና በንጉሡ ቤት ጸሐፊነት ሾመው። በጽሕፈቱም የሀገረ ስሐ መኰንን የሆነው ስሙ አብጥልማዎስ የሚባል ወዳጅ ሆነው እነርሱም ወደ አስቄጥስ ገዳም ሒደው ይመነኵሱ ዘንድ ተስማሙ።
በዚያንም ጊዜ በአስቄጥስ ገዳም ከአባ ዮሐንስ ደብር አንድ መነኰስ ወደነርሱ መጣ አብረውትም ይሔዱ ዘንድ ተስማሙ መኳንንቶችም ይህን በሰሙ ጊዜ መሔድን ከለከሉዋቸው።
ከጥቂት ቀኖች በኋላም ለእግዚአብሔር የተሳላችሁትን ስለት ለምን አትፈጽሙም የሚላቸውን ራእይ አዩ በዚያንም ጊዜ በሥውር ወጡ እነርሱ ግን መንገዱን አያውቁትም ነበር አንድ መነኰስም ተገለጠላቸውና ወደ አስቄጥስ ወደ አባ ዮሐንስ ገዳም መርቶ አደረሳቸው፡፡መኳንንቱም መሔዳቸውን በሰሙ ጊዜ ከንጉሥ ዘንድ ደብዳቤ ተቀብለው በመላክ ከገዳም ሊአስወጡአቸው ተስማሙ የክብር ባለቤት ጌታችንም ምክራቸውን በተነ።
በመነኰሱም ጊዜ በብዙ ተጋድሎ ተጠመዱ ይልቁንም አባ ዘካርያስ በዚያም ወራት አረጋውያን አባ አብርሃምና አባ ገዐርጊ ነበሩ ወደ እርሳቸው እየመጡ በሥራቸው ሁሉ ያረጋጉዋቸውና ያጸኑዋቸው ነበር።
የሀገረ ስሐ ኤጲስቆጶስም በአረፈ ጊዜ ሕዝቡ አባ ዘካርያስን አሰቡት እርሱንም ይሾምላቸው ዘንድ ስለ አባ ዘካርያስ እየለመኑ ወደ ሊቀ ጳጳሳቱ የመልእክት ደብዳቤ ጻፉ። ሊቀ ጳጳሳቱም ወደ አስቄጥስ ገዳም ልኮ አባ ዘካርያስን ወደ እርሱ አስመጣው በሀገረ ስሐ ላይም ኤጲስቆጶስነት ሾመው ሊቀ ጳጳሳቱም እጁን በላዩ በጫነ ጊዜ የእግዚአብሔርን ኃይል አየ በላዩ ወርዷልና ፊቱም በብርሃን ተጋረደ።
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
