የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
前往频道在 Telegram
2 620
订阅者
+324 小时
+207 天
+3730 天
帖子存档
++++ሰማያዊው ዜማ++++
''ዝክረ ቅዱስ ያሬድ''
ልዩ የምስጋና እና የዝማሬ መርሐግብር
ግንቦት 10 እና 11
በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ከ11:00 ጀምሮ በደብራችን አውደ ምሕረት
የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
ሰማያዊው ዜማ
''ዝክረ ቅዱስ ያሬድ''
ልዩ የምስጋና እና የዝማሬ መርሐግብር
ግንቦት 10 እና 11
በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ከ11:00 ጀምሮ በደብራችን አውደ ምሕረት
የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
በትላንትናው እለት ቅዱስ ሲኖዶስ የሚወያይባቸውን ፳፬ አጀንዳዎችን መርምሮ አጸደቀ።
የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት ምልዓተ ጉባኤ የግንቦት ፮ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም ውሎን አስመልክቶ መጋቤ ሃይማኖት አባ አብርሃም የቅዱስ ሲኖዶስ ምክትል ጸሐፊና የሰሜን አፍሪካ ሀገረ ስብክት ሥራ አስኪያጅ ማምሻውን ማብራሪያ ሰጥቷል።
በማብራሪያቸው ላይ ምልዓተ ጉባኤው ሰባት አባላት ያሉት የአጀንዳ አርቃቂ ኮሚቴ መሰየሙ አስታውሰው በቋሚ ሲኖዶስ ተዘጋጅቶ የቀረበውን አጀንዳ በመመርመርና በማሻሻል ለቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በማቅረብ 24 አጀንዳዎችን ጉባኤው አጽድቆ ወደ ውይይት ገብቷል ብለዋል።
በዚህም በዛሬው የጉባኤው ውሎ
አጀንዳ 1.
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ያስተላለፉትን መልእክት በማጽደቅ የሥራ መመሪያ ሆኖ እንዲያገለግል ወስኗል።
አጀንዳ 2.
የቅዱስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤትን ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርትን ከግንቦት ፳፻፲፮ እስከ ግንቦት ፳፻፲፯ ዓ.ም በቋሚ ሲኖዶስና በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የተወሰኑ ውሳኔዎችን በተመለከተ የአፈጻጸም ሪፖርት በመጋቤ ብርሃናት አባ ተክለ ያሬድ ተክለ ጎርጎርዮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ምክትል ጸሐፊ በንባብ ተደምጦ ጉባኤውም ያለውን ሪፖርት አዳምጦ አጽድቋል፡፡
"በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቁአት ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ።”
ሐዋርያት ፳፥፳፰
©የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
በትላንታው እለት ቅዱስ ሲኖዶስ የሚወያይባቸውን ፳፬ አጀንዳዎችን መርምሮ አጸደቀ።
የቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት ምልዓተ ጉባኤ የግንቦት ፮ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም ውሎን አስመልክቶ መጋቤ ሃይማኖት አባ አብርሃም የቅዱስ ሲኖዶስ ምክትል ጸሐፊና የሰሜን አፍሪካ ሀገረ ስብክት ሥራ አስኪያጅ ማምሻውን ማብራሪያ ሰጥቷል።
በማብራሪያቸው ላይ ምልዓተ ጉባኤው ሰባት አባላት ያሉት የአጀንዳ አርቃቂ ኮሚቴ መሰየሙ አስታውሰው በቋሚ ሲኖዶስ ተዘጋጅቶ የቀረበውን አጀንዳ በመመርመርና በማሻሻል ለቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ በማቅረብ 24 አጀንዳዎችን ጉባኤው አጽድቆ ወደ ውይይት ገብቷል ብለዋል።
በዚህም በዛሬው የጉባኤው ውሎ
አጀንዳ 1.
ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ያስተላለፉትን መልእክት በማጽደቅ የሥራ መመሪያ ሆኖ እንዲያገለግል ወስኗል።
አጀንዳ 2.
የቅዱስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤትን ዓመታዊ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርትን ከግንቦት ፳፻፲፮ እስከ ግንቦት ፳፻፲፯ ዓ.ም በቋሚ ሲኖዶስና በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የተወሰኑ ውሳኔዎችን በተመለከተ የአፈጻጸም ሪፖርት በመጋቤ ብርሃናት አባ ተክለ ያሬድ ተክለ ጎርጎርዮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ምክትል ጸሐፊ በንባብ ተደምጦ ጉባኤውም ያለውን ሪፖርት አዳምጦ አጽድቋል፡፡
"በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቁአት ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ።”
ሐዋርያት ፳፥፳፰
©የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሚዲያ
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ሰባት አባላት ያሉት የአጀንዳ አርቃቂ ኮሚቴን ሰየመ
ግንቦት ፮/፳፻፲፯ ዓ.ም
ለ፳፻ ፲ወ፯ ዓ.ም የቅዱስ ሲኖዶስ ርክበ ካህናት ጉባኤ አጀንዳ በማርቀቅ እንዲያቀርቡ ሰባት ሊቃነ ጳጳሳትን የሰየመ ሲሆን ኮሚቴው በቋሚ ሲኖዶስ ተዘጋጅቶ የቀረበውን አጀንዳ በመመርመርና በማሻሻል ለቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በማቅረብ የሚያጸድቅ ይሆናል። የኮሚቴው አባላትም፦
፩.አቡነ ጎርጎርዮስ
፪.አቡነ ቀሌምንጦስ
፫.አቡነ ኤዎስጣቴዎስ
፬.አቡነ ኤልያስ (አርባ ምንጭ)
፭.አቡነ ሩፋኤል
፮.አቡነ ዜና ማርቆስ
፯.አቡነ ኤልሳዕ ሲሆኑ ምልአተ ጉባኤው ከአጀንዳዎቹ መጽደቅ በኋላ የቅዱስ ፓትርያርኩን
የመግቢያ መልእክትና የቅዱስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤትን ሪፖርት ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል።
ምንጭ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
ቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ሰባት አባላት ያሉት የአጀንዳ አርቃቂ ኮሚቴን ሰየመ
ግንቦት ፮/፳፻፲፯ ዓ.ም
ለ፳፻ ፲ወ፯ ዓ.ም የቅዱስ ሲኖዶስ ርክበ ካህናት ጉባኤ አጀንዳ በማርቀቅ እንዲያቀርቡ ሰባት ሊቃነ ጳጳሳትን የሰየመ ሲሆን ኮሚቴው በቋሚ ሲኖዶስ ተዘጋጅቶ የቀረበውን አጀንዳ በመመርመርና በማሻሻል ለቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ በማቅረብ የሚያጸድቅ ይሆናል። የኮሚቴው አባላትም፦
፩.አቡነ ጎርጎርዮስ
፪.አቡነ ቀሌምንጦስ
፫.አቡነ ኤዎስጣቴዎስ
፬.አቡነ ኤልያስ (አርባ ምንጭ)
፭.አቡነ ሩፋኤል
፮.አቡነ ዜና ማርቆስ
፯.አቡነ ኤልሳዕ ሲሆኑ ምልአተ ጉባኤው ከአጀንዳዎቹ መጽደቅ በኋላ የቅዱስ ፓትርያርኩን
የመግቢያ መልእክትና የቅዱስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤትን ሪፖርት ያጸድቃል ተብሎ ይጠበቃል።
ምንጭ የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ክ የሕዝብ ግንኙነት መምሪያ
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
ሰማያዊው ዜማ
''ዝክረ ቅዱስ ያሬድ''
ልዩ የምስጋና እና የዝማሬ መርሐግብር
ግንቦት 10 እና 11
በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ከ11:00 ጀምሮ በደብራችን አውደ ምሕረት
የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
የተንገላታችበትን እዩና በቃ በሉ፤ሁሉን የሚያግባባ ነገር ፈልጉና ችግሮችን በሰላማዊ ውይይት ፍቱ፤ በዚህ አማራጭ እናት ሀገር እፎይታ እንድታገኝ ኣድርጉ፤ ይህንም ለውድ እናት የሚደረግ ካሣ አድርጋችሁ ውሰዱት፤ የቤተ ክርስቲያናችን ወቅታዊ መልእክትና ጥሪም ይህ ነው፤
በመጨረሻም የቤተ ክርስቲያናችን መንፈሳዊ፣ ማኅበራዊ፣ ኢኮኖሚያዊና አስተዳደራዊ አፈጻጸማችን በመገምገም ለቀጣዩ ጊዜ የስራ አቅጣጫን የሚያስቀምጠው የርክበ ካህናቱ የቅዱስ ሲኖዶስ ቀኖናዊ ጉባኤ በዛሬው ዕለት የተጀመረ መሆኑን ለኦርቶዶክሳውያን ሕዝበ ክርስቲያን እናበስራለን።
እግዚአብሔር የተባረከና የተቀደሰ ጉባኤ ያድርግልን!
እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር አሜን!
አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣
ግንቦት ፮ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም
አዲስ አበባ ኢትዮጵያ
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
የግንቦት 2017 ዓ.ም ርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ መጀመርን አስመልክቶ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ያስተላለፉት የጉባኤው መክፈቻ መልእክት እንደሚከተለው ቀርቧል።
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ዋና ስራ አስኪያጅ፣ የባሕር ዳርና የሰሜን ጎጃም አህጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ሄኖክ
የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፤
ብፁዓን ኣበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!!
እንደዚሁም በዚህ ቀኖናዊና ዓመታዊ የርክበ ካህናት የቅዱስ ሲኖዶስ ምልአተ ጉባኤ ላይ የተገኛችሁ በሙሉ፤ ጸጋንና ሐዋርያነትን ያጐናጸፈን ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅድስት ትንሣኤውን በሰላም አክብረን ይህንን ዓመታዊውን የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ ለማካሄድ ስለ ሰበሰበን ክብርና ምስጋና ለእርሱ ይሁን፤ የጉባኤው አባላት የሆናችሁ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳትም እንኳን ለርክበ ካህናት ጉባኤ አደረሳችሁ! እንኳንም በሰላም መጣችሁ!
“ረከብነ ጸጋ ወተሰየምነ ሓዋርያተ ከመ ናስምዖሙ ለአሕዛብ ወይእመኑ በስሙ፡- ከእምነት የሚነሣ መታዘዝ እንዲገኝ ጸጋንና ሐዋርያነትን ተቀበልን” (ሮሜ.፩÷፭)፤
ይህ ሐዋርያዊ አስተምህሮ የኛን ተልዕኮና ተልዕኮው ያስፈለገበትን ምክንያት አጉልቶ ያሳያል፤ የተቀበልነው ስጦታም ምን ያህል ታላቅ እንደ ሆነ ምንባቡ ያስረዳል፤ ሐዋርያው በዚህ መልእክት የቅዱስ ወንጌል ኣስተምህሮ ዋና ግብ ከእምነት የሚነሣ መታዘዝ እንዲገኝ ማድረግ ነው በማለት ያስተምረናል፤ እውነት ነው ድሮውኑም ቢሆን ለእግዚአብሔር መታዘዝ አቅቶን ነው የወደቅነው፤ ዛሬም የምንነሣው ከእምነት የተነሣ መታዘዝን ገንዘብ ስናደርግ ነው፤ ከሁሉ በፊት እምነት ይቀድማል፤ ከሱ በኋላ ደግሞ ለእምነቱ በሙሉ ልብ መታዘዝ ይከተላል፤ ይህ ሲሆን መዳንና ትንሣኤ ይገኛል፤ ዓለም በእግዚአብሔር እየተደረገለት ያለ ጥሪ ይኸው የመታዘዝ ጥሪ ነው፤
ይህንን መለኮታዊ ጥሪ ለዓለም የማድረስ ኃላፊነትም ለኛ ለቅዱስ ሲኖዶስ አባላት የተሰጠ እንደሆነ ሐዋርያው አስገንዝቦአል፤ ኃላፊነቱ ሲሰጠን ከነመሳርያው ነው፤ እሱም ጸጋና ሐዋርያነት ነው፤ እኛም እሱን ተቀብለናል፤ እንግዲያውስ የተቀበልነውን ጸጋና ሐዋርያነት በዓለም ውስጥ ላለው ሕዝበ እግዚአብሔር አገልግሎት ማዋል ከኛ ይጠበቃል፡፡
ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!!
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በአሁኑ ጊዜ የሌለበት ክፍለ ዓለም የለም፤ ምክንያቱም የዚህ ሲኖዶስ ወኪሎች ሊቃነ ጳጳሳት በአፍሪካ፣ በአውሮፓ፣ በሰሜን አሜሪካ፣ በላቲን አሜሪካ፣ በካናዳና በመካከለኛው ምሥራቅ፣ በእስያና በአውስትራሊያ ወዘተ የሚገኙ ሕዝበ እግዚአብሔር ምእመናንን በማገልገል ላይ ይገኛሉና ነው፤ ይህ ዕድል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ መለኮታዊ ተልኮውን በአጽናፈ ዓለም ሁሉ ለማድረስ ምቹ መደላድል ፈጥሮለታል፡፡ከዚህም በመነሣት በየክፍለ ዓለሙ የሚገኙ የቤተ ክርስቲያናችን ሊቃነ ጳጳሳት ከትውልደ ኢትዮጵያውያን ባሻገር የየአካባቢውን ሕዝብ በማስተማርና በማቀፍ የተጣለባችሁን ሐዋርያዊ ተልእኮ በትጋትና በንቃት መወጣት ይኖርባችኋል፡፡
በማዕከል ሆኖ እየመራ የሚገኝ ቅዱስ ሲኖዶስም ለዚህ ተልእኮ ምቹ መደላድል የመፍጠር ኃላፊነቱን በአግባቡ መወጣት ይገባዋል፡፡ በተለይም ትምህርተ ሃይማኖትንና ቀኖና ቤተ ክርስቲያንን የተማሩና በጥልቀት የተገነዘቡ፣ ብስለትም ያላቸው፤ እንዲሁም በቋንቋና በሥነ ልቦና ዕውቀት የላቀ ሀብተ ጸጋ ያላቸውን በሐዋርያነት እያሠለጠነ በአጽናፈ ዓለም ሁሉ ሊያሰማራ ይገባል፡፡
ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!
በብሂለ አበው (ፀሐይ ለመስኮቷ ሳታበራ…) እንደሚባለው ለሌላው በብቃት መድረስ እንችል ዘንድ እኛ የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት የሲኖዶሱ መንበር በሚገኝባት ምድረ ኢትዮጵያ ከመቸውም የተሻለ ስራ በመስራት ለእግዚአብሔር መታዘዝ ሕዝቡንም ማገልገል ይገባናል፤ ሁላችንም እንደ ምንገነዘበው በሲኖዶሳችን ያልታቀፉ ብዙ ወገኖች በሀገር ውስጥ አሉን፤ እነዚህ ወገኖች አንዳንዶቹ በተለያየ ምክንያት ከኛ የወጡ ናቸው፡፡ ይሁን እንጂ የሄዱት ወደ ቤታቸው እንዲመለሱ፣ ሌሎችም ወደ መንጋው እንዲቀላቀሉ በርትቶ መስራት የዚህ ጉባኤ ተቀዳሚ ተልእኮ ነው፤ ምክንያቱም ጸጋንና ሐዋርያነትን የተቀበልንበት ዋናው ምክንያት ይህንን ለማድረግ ነውና፡፡ ከዚህ አኳያ የቤተ ክርስቲያናችን ተደራሽነት በሳሳበት ኣካባቢ ሁሉ የተለየ ትኵረት ሰጥተን መስራትና ተጨባጭ ለውጥ ማምጣት ይኖርብናል፤
ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት!
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ውሉደ ክህነትና ምእመናን የሆን ሁላችን፣ ከሁሉ በፊት ያለንን አቅምና ብቃት በአግባቡ መገንዘብ ይኖርብናል፤ ለእግዚአብሔር ክብርና ምስጋና ይሁንና ለፈጣሪው በቈራጥነት የሚታዘዝ ምእመን፣ ወጣት፣ ካህን አለን፤ ይህ ትልቅ ጸጋ ነው፤ ይህንን ጸጋ እግዚአብሔር፡ ለእግዚአብሔር መንግሥት በሚመች ሁናቴ ዝቅ ብሎ ማገልገል የክብር ክብር ነው፡፡ በመሆኑም ይህንን የእግዚአብሔር ሕዝብ በሓቅ፣ በቅንነት፣ በትጋትና በታማኝነት ቆመን ካገለገልነውና አባትነታችንንና መሪነታችንን በመልካም አሰራር በትክክል በኅሊናው እንዲቀረጽ ካደረግን፣ ይህ ኃይል ከጐናችን እንደማይለይ እርግጠኞች መሆን እንችላለን፤ ይህንን ካሳካን ለኛ የተሰጠ ኃይልና ብቃት በየትም አይገኝም፡፡
በዚህም በዚያም ሃይማኖቱ የሚጠይቀውን ስብእና እና ቁመና ይዘን ከተገኘን፣ ሕዝበ ክርስቲያኑ ያለውን ብቻ ሳይሆን ሕይወቱን ሳይቀር ለመስጠት ወደ ኋላ የማይል የእግዚአብሔር ሕዝብ አለን፤ ስለዚህ ይህንን ማሳካት እንችል ዘንድ ከእምነት የሚነሣ መታዘዝ እንድናስገኝ የተቀበልነውን ጸጋና ሐዋርያነት በክብር እንያዝ፤
ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ ኣባላት!!
ለሕዝበ እግዚአብሔር የምናበረክተው አገልግሎት በመንፈሳዊ ብቻ ሳይሆን በኢኮኖሚውና በማኅበራዊው አገልግሎትም ጭምር ነው፤ ከዚህ አንጻር ሕዝባችን የተሻለ ማኅበራዊ አገልግሎት እንዲያገኝ፣ በኢኮኖሚውም ከድህነት የተላቀቀ እንዲሆን፤ እንደዚሁም ሰላሙና አንድነቱ የተጠበቀ እንዲሆን፣ በማስተማርም በተግባር በመሳተፍም የሕዝቡ መሪዎችና አርኣያ ሆነን መስራት ይገባናል፤በተለይም ከሰላም እጦት የተነሣ በእጅጉ እየተጎዳ ያለውን ሕዝባችን ሰላምና ፍትሕ እንዲያገኝ በጸሎትም በትምህርትም፣ በምክርም ተግተን መስራት አለብን፤
እንዳጋጣሚ ሆኖ የኢትዮጵያ ሕዝብ ከእንግልት የተላቀቀበት ጊዜ ብዙ እንዳልሆነ ይታወቃል፤ ለእንግልት እየተዳረገ ያለውም የሌሎች እጅ ባይለየውም በዋናነት በገዛ ልጆቹ ነው፤ እናት በገዛ ልጆቿ ስትንገላታ ማየት እጅግ አሳዛኝ ነገር ነው፤ እንደዚህ ያለው ነገር በደንብ ያልታሰበበት አካሄድ በብስለትና በንስሓ ማስተካከል አሸናፊነትን እንጂ ተሸናፊነትን አያሳይምና እንዲታሰብበት እንመክራለን፤ ከዚህ አንጻር ኢትዮጵያን ወደ ተሻለ ልማትና ዕድገት እናሻግራለን ብላችሁ እየደከማችሁ ያላችሁ ወገኖቻችን እባካችሁ መለስ ብላችሁ እናታችሁ
ግንቦት 05 ቀን 2017 ዓ.ም. የቅዱስ ሲኖዶስ ርክበ ካህናት ጉባኤ መክፈቻ ጸሎት ተካኼደ።
+++++++++
በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም በተከፈተው የቅድመ ጉባኤ ጸሎት መርሐ ግብር የዳዊት መዝሙር፣ ውዳሴ ማርያም፣ መልክአ ማርያምና መልክአ ኢየሱስ የተጸለየ ሲኾን በተጨማሪም አድኅነነ ሕዝበከ የሚለው የምህላ ጸሎት፣ የሠርክ መስተብቁዕ፣ በዜማ ስብሐተ እግዚአብሔር ቀርቧል፤ ጸሎተ ወንጌልና መጽሐፈ ኪዳን ተደርሷል፤ የዳዊት መዝሙር ልብሰ ተክህኖ በለበሱ ዲያቆናት ተዚሟል። በማቴዎስ ወንጌል (ማቴ18÷18) ላይ የተጻፈው ቃለ ወንጌል ተነቧል።
በቅዱስነታቸው መልካም ፈቃድ ብፁዕ አቡነ ኤልያስ የኖርዲክ ሀገራት ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ መርሐ ግብሩን አስመልክተው ትምህርተ ወንጌል ሰጥተዋል።
በመጨረሻም በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ጸሎትና ቡራኬ የጉባኤ መክፈቻ መርሐ ግብሩ ተጠናቋል።
+++++++
ምንጭ፡- የኢ/ ኦ/ተ/ቤ መገናኛ ብዙኀን አገልግሎት ሥርጭት ገጽ
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
