የጽርሐ ጽዮን ሐዋርያት ጎላ ቅዱስ ሚካኤል የፍኖተ ብርሃን ሰ/ት/ቤት (Official Channel)
前往频道在 Telegram
2 621
订阅者
+124 小时
+227 天
+3830 天
帖子存档
+1
እንኳን ለዐቢይ ጾመ ጾመ ኢየሱስ አራተኛው ሰንበት ደብረ ዘይት(ለእኩለ ጾም) አደረሰን አደረሳችሁ የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ እንደቀጠለ ነው አሁን ደግሞ በቀን ሁለት ምዕራፍ የቅዱስ ጳውሎስ መልእክት የሮሜ መልእክትን መጀመራችን ይታወቃል አሁንም በቀን ሁለት ምዕራፍ ከ2ኛ ቆሮንጦስ ምዕራፍ 11እስከ ኤፊሶን መልእክት ምዕራፍ 5 ድረሰ ንባባችንን እንቀጥል
መልካም የንባብ ጊዜ
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
እጸ መስቀል
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሰውን ልጅ ከዲያብሎስ ባርነት ነጻ ሊያወጣ ሰላምንም ያደርግ ዘንድ በቀራንዮ አደባባይ በመካነ ጎልጎታ በፈቃዱ ተሰቀለ። ሞተ ጥልንም በመስቀሉ ገደለ። ከፍተኛ ወንጀል የሠሩ ሰዎች ብቻ ይሰቀሉበት የነበረው መስቀል ከጌታችን ስቅለት በኋላ የድኅነት ምልክት ሆነ::
ጌታ የተሰቀለበት መስቀል ተአምር በማድረጉ የተመቀኙ አይሁድ መስቀሉን ጉድጓድ ቆፍረው ቀበሩት መስቀሉ የተቀበረበትን ስፍራ የቆሻሻ መጣያ አደረጉት።
ንግሥት እሌኒ ልጇ ቆስጠንጢኖስ ክርስቲያን ከሆነላት ወደ ኢየሩሳሌም ሔዳ መስቀሉን ለመፈለግ እንዲሁም በኢየሩሳሌም ያሉ ቅዱሳት መካናትንና አብያተ ክርስቲያናትን ለማሳነፅ ለእግዚአብሔር ተሳለች፡፡
ከዚህ በኋላ ልጇ ቆስጠንጢኖስ አምኖ በ337 ዓ.ም ተጠመቀ፡፡ ንግስት እሌኒም ወደ ኢየሩሳሌም ሔደች የጌታችንን መስቀል መፈለግ ብትጀምርም ያለበት ስፍራ የሚነግራት ሰው ልታገኝ አልቻለችም፡፡ አይሁድ የተቀበረበትን ቦታ ለማሳየት ፍላጎት ባይኖራቸውም አንድ ኪራኮስ የሚባል አረጋዊ ሰው አስጨንቃ ስለያዘችው መስቀሉ የሚገኝበትን ስፍራ ጠቆማት ነገር ግን ለዘመናት ቆሻሻ ሲጣልበት የነበረ ስፍራ በመሆኑ ተራራ ሰርቷል በቦታው ከነበሩት ከሦስቱ ተራሮች ውስጥ መስቀሉ የሚገኝበት የትኛው እንደሆነ ለይቶ ለማወቅ አልተቻለም፡፡
ንግሥት እሌኒ ከሦስቱ ተራሮች የቱ እንደሆነ ለመለየት በእግዚአብሔር ረዳትነት ደመራ አስደምራ ብዙ እጣንም በመጨመርና በማቃጠል ጸሎት ተያዘ፡፡ የእጣኑ ጢስ ወደ ሰማይ በመውጣት በቀጥታ ተመልሶ መስቀሉ ወዳለበት ተራራ ላይ በማረፍ መስቀሉ ያለበትን ትክክለኛ ስፍራ አመለከታት፡፡
መስከረም አስራ ስድስት ቀን ቁፋሮው ተጀምሮ መጋቢት አስር ቀን ሦስት መስቀሎች ተገኙ፡፡ ነገር ግን ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት መስቀል የትኛው እንደሆነ ለማወቅ ተቸገሩ፡: መስቀሎቹን ወስደው ሙት ላይ ቢያስቀምጡ ጌታችን በዕለተ አርብ የተሰቀለበት መስቀል የሞተውን ሰው አስነሳው ሌሎቹ ሁለቱ መስቀሎች ግን ሙትን ማስነሳት ባለመቻላቸው የጌታችንን መስቀል ለይቶ ማወቅ ተችሏል። ንግስት እሌኒና ክርስቲያኖች ሁሉ ለመስቀሉ ሰገዱለት
የመስቀሉ በረከት በሁላችንም ላይ ይደርብን።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
''ሥርዓተ ቅዳሴ''
ክፍል ሁለት
በዲ/ን አማኑኤል አሽኔ
የቅዳሜ የትምህርት መርሐግብር
የፊታችን ቅዳሜ መጋቢት 13/2017 ዓ.ም ከምሽቱ 11:45 ሰዓት ላይ ቀጠሮዎትን በጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ ያድርጉ ይምጡ ይማሩ በብዙ ያተርፋሉ እንዳይቀሩ።
የቴሌግራም ቻናላችን
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
+9
የሰንበት ትምህርት ቤታችን አገልጋይ የሆነው ወንድማችን ወጣት ዮሴፍ አምሐ
የእግዚአብሔር ፍቅር ክፍል አንድ እና ክፍል ሁለት መጽሐፍ መጋቢት 07 ቀን 2017 ዓ.ም በደብራችን ስብከተ ወንጌል አዳራሽ ተመረቀ። እንኳን ደስ አለህ ወንድማችን ወጣት ዮሴፍ አምሐ እግዚአብሔር ያበርታህ ።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን
https://youtube.com/@finotebirhan12
የፌስቡክ ገጻችን https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የዌብሳይት ገጻችን
https://finotebirhan.com
የዐቢይ ፆም አራተኛ ሳምንት ስያሜ ምን ይባላል?
የሐዘን መግለጫ
የሰንበት ት/ቤታችን አባል የሆነው የወንድማችን ተክሉ ማሞ ወላጅ እናት አርፈዋል ሥርዓተ ፍትሐት ዛሬ መጋቢት 05/2017 ዓ.ም ጠዋት 3:00 በጎላ ቅዱስ ሚካኤል ቤ/ክ ተደርጎ ከሰዓት ከቅዳሴ በኋላ ወደ መኖሪያ ቤታቸው ፊጋ አካባቢ ይመለሳሉ ዛሬውኑ ምሽቱን የእናታችን አስከሬን ወደ መቀሌ ሽኝት የሚደረግ በመሆኑ መገኘት የምትችሉ አባላት በመገኘት እንድናጽናናቸው ይሁን። የእናታችንን ነፍስ ይማርልን ።
ይህ በጽ/ጽ/ሐ/ጎ/ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍ/ብ/ሰ/ት/ቤት እውቅና የተሰጠው የቴሌግራም ቻናል ነው።
https://t.me/finotebirhan12
የዩቲዩብ ቻናላችን https://youtube.com/@finotebirhan12
የቲክቶክ አካውንታችን https://www.tiktok.com/@finotebirhan?_t=8i8eHwFI3Es&_r=1
የፌስቡክ ገጻችን
https://www.facebook.com/Fbirhan?mibextid=2JQ9oc
የዌብሳይት ገጻችን https://finotebirhan.com
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
