ch
Feedback
አረንጓዴ ወርቅ ኢትዮጵያ ቡና - አደገኞቹ

አረንጓዴ ወርቅ ኢትዮጵያ ቡና - አደገኞቹ

前往频道在 Telegram

ለማንኛውም አስተያየት እና መረጃ ➲ @Bunnacoffee12 ስሜት፣ እምነት፣ ወኔ፣ ፍቅር፣ አልሸነፍ ባይነት የሚንፀባረቅበት የታላቁ ክለብ ኢትዮጵያ ቡና ቻናል ነው። ይህ ቻናል ሰለ ውዱ ክለባችን ኢትዮጵያ ቡና 24 ሰዐት መረጃዎችን በፍጥነት ወደእናንተ ያደርሳል። መወያያ ግሩፕ ➲ @BunnaFC

显示更多

📈 Telegram 频道 አረንጓዴ ወርቅ ኢትዮጵያ ቡና - አደገኞቹ 的分析概览

频道 አረንጓዴ ወርቅ ኢትዮጵያ ቡና - አደገኞቹ (@coffeefc) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 188 751 名订阅者,在 体育 类别中位列第 201,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 109

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 188 751 名订阅者。

根据 28 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -4 820,过去 24 小时变化为 -303,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 0.19%。内容发布后 24 小时内通常能获得 0.31% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 355 次浏览,首日通常累积 577 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 12

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
ለማንኛውም አስተያየት እና መረጃ ➲ @Bunnacoffee12 ስሜት፣ እምነት፣ ወኔ፣ ፍቅር፣ አልሸነፍ ባይነት የሚንፀባረቅበት የታላቁ ክለብ ኢትዮጵያ ቡና ቻናል ነው። ይህ ቻናል ሰለ ውዱ ክለባችን ኢትዮጵያ ቡና 24 ሰዐት መረጃዎችን በፍጥነት ወደእናንተ ያደርሳል። መወያያ ግሩፕ ➲ @BunnaFC

凭借高频更新(最新数据采集于 29 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 体育 类别中的关键影响点。

188 751
订阅者
-30324 小时
-1 4127
-4 82030
帖子存档
#ይህ_ጠቅላላ_ጉባኤ_ብቻ_አይደለም… የኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዎች ጠቅላላ ጉባኤ የፊታችን እሁድ ሐምሌ 26 ቀን 2018 ዓ.ም በ4 ኪሎ በአዲስ አበባ ወጣቶች ማዕከል ይካሄዳል። ለበርካታ ዓመታት በተለያዩ
#ይህ_ጠቅላላ_ጉባኤ_ብቻ_አይደለም… የኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዎች ጠቅላላ ጉባኤ የፊታችን እሁድ ሐምሌ 26 ቀን 2018 ዓ.ም በ4 ኪሎ በአዲስ አበባ ወጣቶች ማዕከል ይካሄዳል። ለበርካታ ዓመታት በተለያዩ ምክንያቶች ሲራዘም የቆየው ይህ ጠቅላላ ጉባኤ በመጨረሻ ቁርጥ ያለ ቀን አግኝቷል። አሁን ከእንግዲህ በኋላ "ይራዘማል" ወይም "ይቀራል" የሚል ጥርጣሬ የለም። ምክንያቱም ክለባችን በአዲስ አመራር የለውጥ ጉዞ ላይ ይገኛል። ይህን ለውጥ የሚያጠናክር የደጋፊ አንድነት፣ ጠንካራ ድጋፍ እና የጋራ አመራር ለመፍጠር መምከርና መወያየት ያስፈልገናል። #ወደ_ኋላ_መመለስ_የለም በእለቱ ወደ ኋላ ተመልሰን ያለፈውን ታሪክ ብቻ እየደጋገምን፣ በትናንት ጉዳዮች ላይ እየተወቃቀስንና እየተጨቃጨቅን ብንቆይ፣ ከፊታችን ያለውን ብሩህ ተስፋ እናጨልማለን። የምንፈልገው ግን አንድ ነገር ብቻ ነው፤ ተስፋን ማጠናከር፣ ከለውጡ ጋር አብረን መራመድ እና ኢትዮጵያ ቡናን ወደ ከፍታው የሚመልስ ጠንካራ የደጋፊ ኃይል መፍጠር። #የክለቡ_ፕሬዚዳንት ከጉባኤው የሚጠበቁ ዋና ዋና ኩነቶች መካከል፣ የክለቡ ፕሬዚዳንት ዶክተር እስራኤል ከደጋፊዎች ጋር ለመጀመሪያ ጊዜ በቀጥታ የሚገናኙበት መድረክ መሆኑም በጉጉት ይጠበቃል። ይህ ጉባኤ የተለመደ ስብሰባ አይደለም፤ የኢትዮጵያ ቡናን ደጋፊ የነገ ጉዞ የምንወስንበት መድረክ ነው። ስለዚህ እያንዳንዱ የኢትዮጵያ ቡና ደጋፊ በሙሉ ኃላፊነት በጉባኤው ላይ በመገኘት ሃሳቡን ያበርክት፣ አንድነታችንን ያጠናክር፣ የክለባችንን ነገ በጋራ እንገንባ። "ኢትዮጵያ ቡና የሁላችን ነው፤

📢 የጠቅላላ ጉባኤ ጥሪ የኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ ደጋፊዎች ማኅበር እሁድ ሐምሌ 26 ቀን 2018 ዓ.ም. በ4 ኪሎ በሚገኘው የአዲስ አበባ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ የስብሰባ አዳራሽ ከጠዋቱ 2፡30
📢 የጠቅላላ ጉባኤ ጥሪ የኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ ደጋፊዎች ማኅበር እሁድ ሐምሌ 26 ቀን 2018 ዓ.ም. በ4 ኪሎ በሚገኘው የአዲስ አበባ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ የስብሰባ አዳራሽ ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤውን ያካሂዳል። በመሆኑም መላው የኢትዮጵያ ቡና ቤተሰብ እና ደጋፊ በውቡ ቡናማ ማልያችን ደምቆ በስፍራው በመገኘት በዚህ ታሪካዊ ጉባኤ በንቃት እንዲሳተፍ የደጋፊዎች ማኅበር በአክብሮት ጥሪውን ያቀርባል። በዕለቱ የክለቡ አዲሱ የሥራ አመራር ቦርድ ከደጋፊዎች ጋር በይፋ የመጀመሪያ ትውውቁን ያደርጋል፤ ስለ ክለቡ አቅጣጫ መልእክቱን ያስተላልፋል፣ እንዲሁም ከደጋፊዎች ለሚቀርቡ ጥያቄዎች ምላሽ ይሰጣል። በጠቅላላ ጉባኤው የሚከተሉት ዋና ዋና አጀንዳዎች ይቀርባሉ፦ · የማኅበሩ የሥራ ሪፖርት · የሂሳብ ኦዲት ሪፖርት · የመተዳደሪያ ደንብ ማሻሻያ ላይ ውይይትና ውሳኔ · የሥራ ዘመናቸውን ለጨረሱ የደጋፊዎች ማኅበር አመራሮች ምርጫ ውድ ቡናማዎች! ክለባችን በታሪካዊ የሽግግር ምዕራፍ ላይ ይገኛል። በዚህ ወሳኝ ወቅት የእያንዳንዳችን ተሳትፎ፣ ሐሳብና ድጋፍ ከመቼውም ጊዜ በላይ ያስፈልጋል። የደጋፊዎች ማኅበራችንን በአንድነት እናጠናክር፤ ለክለባችንም ጠንካራ መሠረት እንጣል። “ማንም የማይቀርበት ጉባኤ!” 🗓 ቀን፦ እሁድ (ሐምሌ 26 ቀን 2018 ዓ.ም.) 📍 ቦታ፦ 4 ኪሎ – የአዲስ አበባ ወጣቶችና ስፖርት ቢሮ የስብሰባ አዳራሽ 🕝 ሰዓት፦ ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ እኛ እንገኛለን… አናንተስ? የኢትዮጵያ ቡና ስፖርት ክለብ ደጋፊዎች ማኅበር

የደጋፊነት ክብር በውሳኔ መድረክ ይገለጻል! ለክለባችን ያለን ፍቅር በስታዲየም ጩኸት ብቻ አይገደብም፤ በጉባኤው ላይ በመገኘት ለክለባችን እድገት አስተዋጽኦ ማበርከትም ጭምር ነው። እሁድ ሐምሌ 26
የደጋፊነት ክብር በውሳኔ መድረክ ይገለጻል! ለክለባችን ያለን ፍቅር በስታዲየም ጩኸት ብቻ አይገደብም፤ በጉባኤው ላይ በመገኘት ለክለባችን እድገት አስተዋጽኦ ማበርከትም ጭምር ነው። እሁድ ሐምሌ 26 የአንድነታችንና የጥንካሬያችን መገለጫ ነው። መታወቂያ ያለው ደጋፊ ሁሉ የታደሰም ያልታደሰም  በ4 ኪሎ ተሰባስበን ለክለባችን ያለንን ክብር እናሳውቅ!

ሀድያ ሆሳዕና የመጀመሪያ ተጫዋቹን አስፈረመ አሰልጣኝ ሳምሶን አየለን በዋና አሰልጣኝነት የሾመው ሀድያ ሆሳዕና የመጀመሪያ ተጫዋቹን በእጁ አስገብቷል። ቢኒያም ጌታቸው ደግሞ የክለቡ አዲሱ ተጫዋች ሆኗ
ሀድያ ሆሳዕና የመጀመሪያ ተጫዋቹን አስፈረመ አሰልጣኝ ሳምሶን አየለን በዋና አሰልጣኝነት የሾመው ሀድያ ሆሳዕና የመጀመሪያ ተጫዋቹን በእጁ አስገብቷል። ቢኒያም ጌታቸው ደግሞ የክለቡ አዲሱ ተጫዋች ሆኗል። የቀድሞው የሀምበሪቾ ዱራሜ ፣ አዲስ አበባ ከተማ ፣ ድሬዳዋ ከተማ እና እንዲሁም ፋሲል ከነማ የአጥቂ ስፍራ ተጫዋች ስድስት ወራትን ብቻ በቆየበት ኢትዮጵያ ቡና ሰባት ጎሎችን በማስቆጠር አስደናቂ አቋሙን ማሳየት የቻለ ሲሆን ከቡናማዎቹ ጋር አብሮ የሰራውን አሰልጣኝ ሳምሶን አየለን ጥሪ ተከትሎ ማረፊያው ነብሮቹ ቤት ሆኗል። ቴዎድሮስ ታከለ ነኝ!

ሁለቱም ናይጄሪያዊያን በቡናማዎቹ ይቀጥላሉ አሰልጣኝ ገብረመድህን ሐይሌን ከቀጠረ በኋላ በንቃት በዝውውሩ እየተሳተፈ የሚገኘው ኢትዮጵያ ቡና ከናይጄሪያዊያኑ የመስመር አጥቂ አቡበከር አዳሙ እና ከአማካ
ሁለቱም ናይጄሪያዊያን በቡናማዎቹ ይቀጥላሉ አሰልጣኝ ገብረመድህን ሐይሌን ከቀጠረ በኋላ በንቃት በዝውውሩ እየተሳተፈ የሚገኘው ኢትዮጵያ ቡና ከናይጄሪያዊያኑ የመስመር አጥቂ አቡበከር አዳሙ እና ከአማካዩ ዲቫይን ዋቹኩዋ ጋር ይቀጥላል። አቡበከር ፕሌቱ ዩናይትድን ዲቫይን ደግሞ ቤንደል ኢንሹራንስ የተባሉ የሀገራቸውን ክለቦች ከለቀቁ በኋላ በኢትዮጵያ ቡና ሁለቱም ጥሩ ጊዜን ማሳለፋቸው ይታወሳል። ቴዎድሮስ ታከለ

የ2019 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሚጀመርበትን ቀን ይፋ ሆነ! የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አክሲዮን ማህበር የ2019 ዓ.ም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር መስከረም 30/2019 ዓ.ም እንደሚጀምር
የ2019 የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ የሚጀመርበትን ቀን ይፋ ሆነ! የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ አክሲዮን ማህበር የ2019 ዓ.ም የኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ውድድር መስከረም 30/2019 ዓ.ም እንደሚጀምር ዛሬ ለ18ቱ የሊጉ ተሳታፊ ክለቦች አሳውቋል።

ኢትዮጵያ ቡና በመጨረሻም የሦስቱን ተጫዋቾች ውል ዛሬ አራዘመ ከሰሞኑ ከኢትዮጵያ ቡና ጋር ለመቀጠል እና ላለመቀጠል በሁለት መልክ ሲጓዙ የነበሩት እና ወደ ሌላ ክለብ ሊያመሩ የነበሩት ሦስት ተጫዋቾች
ኢትዮጵያ ቡና በመጨረሻም የሦስቱን ተጫዋቾች ውል ዛሬ አራዘመ ከሰሞኑ ከኢትዮጵያ ቡና ጋር ለመቀጠል እና ላለመቀጠል በሁለት መልክ ሲጓዙ የነበሩት እና ወደ ሌላ ክለብ ሊያመሩ የነበሩት ሦስት ተጫዋቾች በመጨረሻም በዛሬው ዕለት በይፋ ለኢትዮጵያ ቡና ፈርመዋል። በኢትዮጵያ ቡና ያለፉትን አራት አመታት አስደናቂ ብቃታቸውን ሲያሳዩን የነበሩት እና የኢትዮጵያ ቡና የወጣት ቡድን ፍሬ የሆኑት አማካዮቹ ይታገሱ ታሪኩ እና ኤርሚያስ ሹምበዛ እንዲሁም ደግሞ አጥቂው አማኑኤል አድማሱ በመጨረሻም በኢትዮጵያ ቡና የሚያቆያቸውን የሁለት አመት ውል በዛሬው ዕለት መፈራረማቸውን አረጋግጫለሁ። ቴዎድሮስ ታከለ ነኝ!

#ለዋንጫ_ደርሰዋል 👆 የ2018 የኢትዮጵያ ክለቦች ሻምፒዮና የሴቶች ግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ! ውጤት ጅማ ከተማ 0-6 ኢትዮጵያ ቡና 04' ሳምያ ሬድዋን 37' ሳምያ ሬድዋን 42' እድላዊት ከበደ 45+2
#ለዋንጫ_ደርሰዋል 👆 የ2018 የኢትዮጵያ ክለቦች ሻምፒዮና የሴቶች ግማሽ ፍፃሜ ጨዋታ! ውጤት ጅማ ከተማ 0-6 ኢትዮጵያ ቡና 04' ሳምያ ሬድዋን 37' ሳምያ ሬድዋን 42' እድላዊት ከበደ 45+2' ማርያማዊት ፋንቱ 70' ሳምያ ሬድዋን 79' ማርያማዊት ፋንቱ ቡናማዎቹ በርቱልን 👏👆 ሳሚያ እና ማራማዊት የዚህ አመት ከስተቶች 😍

ይታገሱ ታሪኩ አዲስ ክለብ ሊያገኝ ተቃርቧል በኢትዮጵያ እግር ኳስ ውስጥ ከደመቁ ወጣት ተጫዋቾች መካከል አንዱ መሆን የቻለው የአማካይ ስፍራ ተጫዋቹ ይታገሱ ታሪኩ የ2013 የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ
ይታገሱ ታሪኩ አዲስ ክለብ ሊያገኝ ተቃርቧል በኢትዮጵያ እግር ኳስ ውስጥ ከደመቁ ወጣት ተጫዋቾች መካከል አንዱ መሆን የቻለው የአማካይ ስፍራ ተጫዋቹ ይታገሱ ታሪኩ የ2013 የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ አሸናፊውን ክለብ ፋሲል ከነማን ለመቀላቀል ከጫፍ ደርሷል። ከአፍሮ ፂሆን ኮንስትራክሽን ከተገኘ በኋላ በመቀጠል ወደ ኢትዮጵያ ቡና ከ17 አመት በታች በማምራት መጫወት የቻለው ባለፈው የ2017 የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የአመቱ ምርጥ ወጣት ተጫዋች ተብሎ የተመረጠው ተጫዋቹ ከኢትዮጵያ ቡና ጋር ያለውን ውል በማጠናቀቁ ከክለቡ ጋር ድርድር ማድረግ ችሎ የነበረ ቢሆንም ከስምምነት አለመድረሳቸውን ተከትሎ የአፄዎቹ የመጀመሪያ ፈራሚ ለመሆን ከጫፍ ደርሷል። ቴዎድሮስ ታከለ ነኝ

የቡናማዎቹ የተከላካይ ምሰሶ — ራምኬል ጀምስ! 🛡️☕️🔥 የኢትዮጵያ ቡና ቤተሰቦች! ዛሬ ስለ ክለባችን አምበልና በተከላካይ መስመራችን ላይ ትልቅ ተፅዕኖ እየፈጠረ ስለሚገኘው ራምኬል ጀምስ (#3)
የቡናማዎቹ የተከላካይ ምሰሶ — ራምኬል ጀምስ! 🛡️☕️🔥 የኢትዮጵያ ቡና ቤተሰቦች! ዛሬ ስለ ክለባችን አምበልና በተከላካይ መስመራችን ላይ ትልቅ ተፅዕኖ እየፈጠረ ስለሚገኘው ራምኬል ጀምስ (#3) ጥንካሬዎች ጥቂት እንበል። ራምኬል በሜዳ ላይ ያለው ሚና ከተከላካይነትም በላይ ነው! 🧱💪 💥ራምኬል የክለባችን አምበል (Captain) እንደመሆኑ መጠን፣ በመከላከል ክፍሉ ላይ ያለውን ተጫዋቾች በማስተባበርና በወሳኝ ጨዋታዎች ላይ ቡድኑን በማረጋጋት ረገድ የሚደነቅ ብቃት አለው። 💥ራምኬል ቡድኑ በሚቸገርበት ሰዓት ደራሽ በመሆን ይታወቃል። ለዚህም በ 23/24 የውድድር ዘመን ከሻሸመኔ ከተማ ጋር በነበረው ጨዋታ በ 91ኛው ደቂቃ ላይ ያስቆጠራትና ቡድኑን ወደ 4ኛ ደረጃ ያሳደገችው የድል ጎል ትልቅ ማሳያ ናት። 💥ራምኬል ከመከላከል ባለፈ ለጎል የሚሆኑ ኳሶችን በማመቻቸት ረገድ ንቁ ተሳትፎ አለው። በ 52ኛው የሸገር ደርቢ ላይ በመጀመሪያው አጋማሽ ማጠቃለያ ለአቻነቷ ጎል መቆጠር መነሻ የሆነችውን ኳስ አመቻችቶ የሰጠው እሱ ነበር። እንዲሁም ከፋሲል ከነማ ጋር በነበረው ጨዋታ ለዘላለም አባተ ጎል መቆጠር መነሻ የሆነችውን ኳስ በግንባሩ የገጨው ራምኬል ነው። 💥1.84 ሜትር ቁመቱና በአካል ብቃቱ የታገዘ የመከላከል ብቃት ያለው ሲሆን፣ ለሀገራችን ብሔራዊ ቡድን (ዋልያዎቹ) ተሰልፎ መጫወቱና እስካሁን 11 ጨዋታዎችን ማድረጉ ትልቅ ልምድ እንዳለው ያሳያል። ራምኬል ጀምስ የክለባችን የኋላ ደጀን አለኝታና የድል ጉዟችን ቁልፍ አካል ነው! ለዚህ ቆራጥ ተከላካያችን ያላችሁን ክብር በኮሜንት ግለጹለት! 🤎

⚽️ ቡና ካስቆጠራቸው ጎሎች ውስጥ፣ ከምንም በላይ ትዝ የሚልህ/ሽ የትኛው ነው ❓
⚽️ ቡና ካስቆጠራቸው ጎሎች ውስጥ፣ ከምንም በላይ ትዝ የሚልህ/ሽ የትኛው ነው ❓

❓የመጀመሪያ ጊዜ ስታዲየም ገብተህ ቡናን የተመለከትከው መቼ ነበር? ማን ይዞህ/ሽ ገባ?
❓የመጀመሪያ ጊዜ ስታዲየም ገብተህ ቡናን የተመለከትከው መቼ ነበር? ማን ይዞህ/ሽ ገባ?

የኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዎች ማህበር ጠቅላላ ጉባኤ ሀምሌ 26/11/2018 እሁድ 2:30 በ4ኪሎ የአዲስ አበባ ወጣቶች ወክማ አዳራሽ ይካሄዳል በመሆኑም የኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዎች ማህበር መታወቂያ ያለው
የኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዎች ማህበር ጠቅላላ ጉባኤ ሀምሌ 26/11/2018 እሁድ 2:30 በ4ኪሎ የአዲስ አበባ ወጣቶች ወክማ አዳራሽ ይካሄዳል በመሆኑም የኢትዮጵያ ቡና ደጋፊዎች ማህበር መታወቂያ ያለው ሁሉም ያደሰም ያላደሰም ደጋፊ ማሊያ በመልበስ መገኘት ይችላል።

🤎💛 የኢትዮጵያ ክለቦች ሻምፒዮና በድሬዳዋ ከተማ ላይ እየተደረገ ባለው የኢትዮጵያ ክለቦች ሻምፒዮና የሴቶች ውድድር ዛሬ የሩብ ፍፃሜ ጨዋታውን ያከናወነው ቡድናችን ድል ቀንቶታል !! ውጤት 💛ኢት
+3
🤎💛 የኢትዮጵያ ክለቦች ሻምፒዮና በድሬዳዋ ከተማ ላይ እየተደረገ ባለው የኢትዮጵያ ክለቦች ሻምፒዮና የሴቶች ውድድር ዛሬ የሩብ ፍፃሜ ጨዋታውን ያከናወነው ቡድናችን ድል ቀንቶታል !! ውጤት 💛ኢትዮጵያ ቡና 5️⃣-2️⃣ አርባምንጭ ሰላም ⚽️⚽️ ማራማዊት ፋንቱ ⚽️ ወርቅነሽ ፋሮ ⚽️ ደመቀች ፋንታየ ⚽️ ዮርዳኖስ ደሜ አስቆጥረዋል!

የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የ2019 የውድድር ዘመን የተጫዋቾች ዝውውር እና ምዝገባ ጊዜ ላይ የቀን ማሻሻያ ተደርጓል። በዚህም መሠረት የዝውውር ጊዜ እና ምዝገባው ሐምሌ 30/2018 የሚጀምር ሲሆን እ
የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የ2019 የውድድር ዘመን የተጫዋቾች ዝውውር እና ምዝገባ ጊዜ ላይ የቀን ማሻሻያ ተደርጓል። በዚህም መሠረት የዝውውር ጊዜ እና ምዝገባው ሐምሌ 30/2018 የሚጀምር ሲሆን እስከ መስከረም 20/2019 ድረስ ክፍት ሆኖ ይቆያል። @coffeefc @coffeefc

የክለቦችን የክፍያ ጣሪያ በተመለከተ ሊደረግ የነበረው ስብሰባ ተራዘመ ****** የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ አክሲዮን ማህበር ከሁለት አመት በፊት ክለቦች የተገደበ የክፍያ ጣሪያ ስርዓት ሊኖራቸው ይገባ
የክለቦችን የክፍያ ጣሪያ በተመለከተ ሊደረግ የነበረው ስብሰባ ተራዘመ ****** የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ አክሲዮን ማህበር ከሁለት አመት በፊት ክለቦች የተገደበ የክፍያ ጣሪያ ስርዓት ሊኖራቸው ይገባል በሚል ደንብ በማውጣት ወደስራ ገብቶ እንደነበር ይታወሳል፡፡ አንድ ክለብ በአንድ አመት ውስጥ መጠቀም አለበት ተብሎ አስቀድሞ 56 ሚሊዮን በመቀጠል ደግሞ 70 ሚሊዮን ብር ሊያወጣው የሚችለው በጀት ነው ተብሎ ውሳኔ ተሰጥቶበት ወደ ስራ ቢገባም ከአፈፃፀም አኳያ ግን በርካታ ክለቦች ህጉን ተግባራዊ ከማድረግ ይልቅ ከጀርባ በሚደረጉ የገንዘብ ዝውውሮች ምክንያት ደንቡ በሚገባ ተግባራዊ ሳይሆን ቀርቷል፡፡ ህጉ ቢወጣም ተግባራዊ ባለመሆኑ አክብረን እየሰራን ያለነውን ክለቦች እየጎዳ ነው የሚባልለት ይህ የክፍያ ጣሪያ ስርዓትን ለአንዴ እና ለመጨረሻ ለማንሳት አልያም የገንዘብ መጠኑን ከፍ ለማድረግ ከክለቦች ጋር ውይይት ለማድረግ ለሐምሌ 19 ቀጠሮ ተይዞ የነበረ ቢሆንም ቀኑ ተገፍቶ ሐምሌ 23/2018 እንዲሆን አክሲዮን ማህበሩ መወሰኑን ሀገሬ ቴሌቪዥን ያገኘው መረጃ ያመላክታል።

☕ኢትዮጵያ ቡና ከ20 ቀናት በኋላ ወደ ቅድመ ውድድር ይገባል! ⚽የ2019 የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ከተለመደው ጊዜ ቀደም ብሎ ሊጀምር በመሆኑ፣ ክለቦችም የቅድመ ዝግጅታቸውን ቀደመው ሊጀምሩ እንደሚች
☕ኢትዮጵያ ቡና ከ20 ቀናት በኋላ ወደ ቅድመ ውድድር ይገባል! ⚽የ2019 የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ከተለመደው ጊዜ ቀደም ብሎ ሊጀምር በመሆኑ፣ ክለቦችም የቅድመ ዝግጅታቸውን ቀደመው ሊጀምሩ እንደሚችል ይጠበቃል ። ይህም የሚሆነው በውድድሮች መሐል ላይ ለብሔራዊ ቡድን ጨዋታዎች ሊጉ ለተወሰነ ጊዜ ስለሚቋረጥ ለብሔራዊ ቡድን የሚሰጠውን ረጅም እረፍት ታሳቢ ያደረገ ነው። 🏟 አዳማ የመጀመሪያ ምርጫ ኢትዮጵያ ቡናም የቅድመ ውድድር ዝግጅቱን በአዳማ ለማካሄድ አቅዷል። ክለቡ ቡድኑ የሚያርፍበትን ሆቴል እና የልምምድ ሜዳ ለመምረጥ ተወካዮችን ወደ አዳማ መላኩን ለማረጋገጥ ችለናል። 📝 አዳዲስ ፈራሚዎች በሌላ በኩል፣ ወደ ክለቡ ሊቀላቀሉ የሚችሉ አዳዲስ ተጫዋቾች ከዋና አሰልጣኝ ገብረመድህን ሐይሌ ጋር ውይይታቸውን እያካሄዱ ይገኛሉ። ሁሉም ነገር እንደታቀደው ከተጠናቀቀ እና ፊርማቸውን ካኖሩ በኋላ ክለቡ በይፋ የሚያስተዋውቃቸው ይሆናል!

Repost from N/a
🔥 HERE WE GO 🔥 📰 አሁን ከደቂቃዎች በፊት የተጠናቀቁ ትኩስ ትኩስ የዝውውር ዜናዎች ለመኮምኮም ከታች ያለውን Join ሚለውን ይጫኑ 🔥👇
🔥 HERE WE GO 🔥 📰 አሁን ከደቂቃዎች በፊት የተጠናቀቁ ትኩስ ትኩስ የዝውውር ዜናዎች ለመኮምኮም ከታች ያለውን Join ሚለውን ይጫኑ 🔥👇

ፍቅረኛ አሎት?😍🤷‍♂