የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU 的分析概览
频道 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 14 309 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 6 167,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 365 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 14 309 名订阅者。
根据 21 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 502,过去 24 小时变化为 16,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 48.88%。内容发布后 24 小时内通常能获得 13.10% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 0 次浏览,首日通常累积 1 875 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 0。
📝 描述与内容策略
尚未提供频道描述。
凭借高频更新(最新数据采集于 22 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
14 309
订阅者
+1624 小时
+1117 天
+50230 天
帖子存档
ሰሙነ ሕማማት ዕለተ ሐሙስ ሕጽብበተ እግር ፣ ምሴተ ሐሙስ
"ከእራት ተነሣ ልብሱንም አኖረ፥ ማበሻም ጨርቅ ወስዶ ታጠቀ፤ በኋላም በመታጠቢያው ውኃ ጨመረ፥ የደቀ መዛሙርቱንም እግር ሊያጥብና በታጠቀበትም ማበሻ ጨርቅ ሊያብስ ጀመረ። ወደ ስምዖን ጴጥሮስም መጣ፤ እርሱም፦ ጌታ ሆይ፥ አንተ የእኔን እግር ታጥባለህን? አለው። መልሶ፦ እኔ የማደርገውን አንተ አሁን አታውቅም፥ በኋላ ግን ታስተውለዋለህ አለው። ጴጥሮስም፦ የእኔን እግር ለዘላለም አታጥብም አለው። ኢየሱስም፦ ካላጠብሁህ፥ ከእኔ ጋር ዕድል የለህም ብሎ መለሰለት። ስምዖን ጴጥሮስም፦ ጌታ ሆይ፥ እጄንና ራሴን ደግሞ እንጂ እግሬን ብቻ አይደለም አለው። ኢየሱስም፦ የታጠበ እግሩን ከመታጠብ በቀር ሌላ አያስፈልገውም፥ ሁለንተናው ግን ንጹሕ ነው፤ እናንተም ንጹሐን ናችሁ፥ ነገር ግን ሁላችሁ አይደላችሁም አለው። አሳልፎ የሚሰጠውን ያውቅ ነበርና፤ ስለዚህ፦ ሁላችሁ ንጹሐን አይደላችሁም አለው። እግራቸውንም አጥቦ ልብሱንም አንሥቶ ዳግመኛ ተቀመጠ፥ እንዲህም አላቸው፦ ያደረግሁላችሁን ታስተውላላችሁን? እናንተ መምህርና ጌታ ትሉኛላችሁ፤ እንዲሁ ነኝና መልካም ትላላችሁ። እንግዲህ እኔ ጌታና መምህር ስሆን እግራችሁን ካጠብሁ፥ እናንተ ደግሞ እርስ በርሳችሁ እግራችሁን ትተጣጠቡ ዘንድ ይገባችኋል። እኔ ለእናንተ እንዳደረግሁ እናንተ ደግሞ ታደርጉ ዘንድ ምሳሌ ሰጥቻችኋለሁና። እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ባሪያ ከጌታው አይበልጥም። መልእክተኛም ከላከው አይበልጥም። ይህን ብታውቁ፥ ብታደርጉትም ብፁዓን ናችሁ።" ዮሐ 13፡4-17
ሰሙነ ሕማማቱን አሳልፎ የትንሣኤውን ብርሃን ያሳየን!
የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
ሰሙነ ሕማማት ዕለተ ረቡዕ የምክር ቀን እና የመልካም መዓዛ ቀን
"ጌታ ኢየሱስም እነዚህን ቃሎች ሁሉ በፈጸመ ጊዜ፥ ለደቀ መዛሙርቱ፦ ከሁለት ቀን በኋላ ፋሲካ እንዲሆን ታውቃላችሁ፥ የሰው ልጅም ሊሰቀል አልፎ ይሰጣል አለ። በዚያን ጊዜ የካህናት አለቆች የሕዝብም ሽማግሎች ቀያፋ በሚባለው በሊቀ ካህናቱ ግቢ ተሰበሰቡ፥ ኢየሱስንም በተንኰል ሊያስይዙት ሊገድሉትም ተማከሩ፤ ነገር ግን፦ በሕዝቡ ዘንድ ሁከት እንዳይነሣ በበዓል አይሁን አሉ። ኢየሱስም በቢታንያ በለምጻሙ በስምዖን ቤት ሳለ፥ አንዲት ሴት ዋጋው እጅግ የበዛ ሽቱ የሞላው የአልባስጥሮስ ብልቃጥ ይዛ ወደ እርሱ ቀረበች በማዕድም ተቀምጦ ሳለ በራሱ ላይ አፈሰሰችው። ደቀ መዛሙርቱም ይህን አይተው ተቈጡና፦ ይህ ጥፋት ለምንድር ነው? ይህ በብዙ ዋጋ ተሽጦ ለድሆች ሊሰጥ ይቻል ነበርና አሉ። ኢየሱስም ይህን አውቆ እንዲህ አላቸው፦ መልካም ሥራ ሠርታልኛለችና ሴቲቱንስ ስለ ምን ታደክሙአታላችሁ ድሆች ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ይኖራሉና፥ እኔ ግን ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር አልኖርም፤ እርስዋ ይህን ሽቱ በሰውነቴ ላይ አፍስሳ ለመቃብሬ አደረገች። እውነት እላችኋለሁ፥ ይህ ወንጌል በዓለም ሁሉ በማናቸውም ስፍራ በሚሰበክበት እርስዋ ያደረገችው ደግሞ ለእርስዋ መታሰቢያ እንዲሆን ይነገራል። በዚያን ጊዜ የአስቆሮቱ ይሁዳ የሚባለው ከአሥራ ሁለቱ አንዱ ወደ ካህናት አለቆች ሄዶ።" ማቴ 26፡1-14
ሰሙነ ሕማማቱን አሳልፎ የትንሣኤውን ብርሃን ያሳየን!
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
ሰሙነ ሕማማት ማክሰኞ የትምህርትና የጥያቄ ቀን
"ወደ መቅደስም ገብቶ ሲያስተምር የካህናት አለቆችና የሕዝብ ሽማግሎች ወደ እርሱ ቀረቡና፦ በምን ሥልጣን እነዚህን ታደርጋለህ? ይህንስ ሥልጣን ማን ሰጠህ? አሉት። ኢየሱስም መልሶ፦ እኔ ደግሞ አንዲት ነገር እጠይቃችኋለሁ፤ እናንተም ያችን ብትነግሩኝ እኔ ደግሞ እነዚህን በምን ሥልጣን እንዳደርግ እነግራችኋለሁ፤ የዮሐንስ ጥምቀት ከወዴት ነበረች? ከሰማይን ወይስ ከሰው? አላቸው። እነርሱም እርስ በርሳቸው ሲነጋገሩ፦ ከሰማይ ብንል፦ እንኪያስ ስለ ምን አላመናችሁበትም? ይለናል፤ ከሰው ግን ብንል፥ ዮሐንስን ሁሉም እንደ ነቢይ ያዩታልና ሕዝቡን እንፈራለን አሉ። ለኢየሱስም መልሰው፦ አናውቅም አሉት። እርሱም ደግሞ፦ እኔም በምን ሥልጣን እነዚህን እንዳደርግ አልነግራችሁም አላቸው።" ማቴ 21፡23-27
ሰሙነ ሕማማቱን አሳልፎ የትንሣኤውን ብርሃን ያሳየን!
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
ሰሙነ ሕማማት ሰኞ መርገመ በለስ
"በማለዳም ወደ ከተማ ሲመለስ ተራበ። በመንገድም አጠገብ በለስ አይቶ ወደ እርስዋ መጣ፤ ከቅጠልም ብቻ በቀር ምንም አላገኘባትምና፦ ለዘላለሙ ፍሬ አይገኝብሽ አላት። በለሲቱም ያንጊዜውን ደረቀች። ደቀ መዛሙርቱም ይህን አይተው፦ በለሲቱ ያንጊዜውን እንዴት ደረቀች? ብለው ተደነቁ። ኢየሱስም መልሶ፦ እውነት እላችኋለሁ፥ እምነት ቢኖራችሁ ባትጠራጠሩም፥ በበለሲቱ እንደ ሆነባት ብቻ አታደርጉም፤ ነገር ግን ይህን ተራራ እንኳ፦ ተነቅለህ ወደ ባሕር ተወርወር ብትሉት ይሆናል፤" ማቴ 21፡18-21
ሰሙነ ሕማማቱን አሳልፎ የትንሣኤውን ብርሃን ያሳየን!
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
+8
የ2017 ዓ.ም ሆሣዕናን ከሕፃናት ጋር መርሐ ግብር የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ት/ት ክፍል ሐላፊ በተገኙበት በጽ/ጽ/ሐዋርያት እና ጎላ ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት በድምቀት ተከብሯል።
ሚያዝያ 5/2017 ዓ.ም (የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት)
የ2017 ዓ.ም ሆሣዕናን ከሕጻናት ጋር መርሐ ግብር የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ት/ት ክፍል ሐላፊ መጋቤ ሃይማኖት ቀሲስ ይታገሱ ደሴ በተገኙበት በጽ/ጽ/ሐዋርያት እና ጎላ ቅ/ሚካኤል ቤ/ክ ፍኖተ ብርሃን ሰንበት ት/ቤት አዘጋጅነት በድምቀት ተከብሯል።
በመርሐ ግብሩም ላይ ከ60 በላይ ሰንበት ት/ቤቶች እንዲሁም ከ2500 በላይ ሕፃናት ተሳታፊ ሆነዋል። በበዓሉ ላይ መጋቤ ሃይማኖት ቀሲስ ይታገሱ ደሴ ''ከሚጠቡና ከሕፃናት አንደበት ምስጋና ለራስህ አዘፋጀህ'' በሚለው የልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት መዝሙር መነሻ አድርገውበዕለተ ሆሣዕና በዘመኑ የነበሩ ሊቃነ ካህናትና ጸሓፍት ሕጻናት እንዳይዘምሩ ዝምም እንዲያሰኛቸው ጌታን ጠይቀውት ነበር እርሱ ግን የዝማሬው ባለቤት መሆናቸውን በመጥቀስ መልሶላቸዋል በዛሬው ዘመንም እንዲህ ዓይነቱ ክልከላ መልኩን ቀይሮ ቴክኖሎጂን ተደግፎ ተጽዕኖ በመፍጠር ላይ ስለሚገኝ ልጆቻችን በዚህ የተቀደሰ ሕይወት እንዲቀጥሉ ከተፈለገ በጸሎት ልናግዛቸው በርትተንም ልንሰራባቸው ይገባል በማለት መልእክት አስተላልፈዋል። በማለት መልዕክት አስተላልፈዋል።
በተለያዩ አጥቢያ ሰንበት ት/ቤቶች ለሕጻናቱ የተዘጋጁ በተለያየ ዓይነት ቋንቋየ ተዘጋጁ መዝሙሮች ፤ ኪነ ጥበባዊ ሥራዎች ፤ አውደ ርዕይና እና ትምህርት ቀርበዋል።
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
ከጥቂት ደቂቃ በኋላ ከ60 ደብራት በላይ የሚሳተፉበት ልዩ የሆሣዕና በዓል ሆሣዕናን ከሕፃናት ጋር በቀጥታ ይጠብቁን!
ኒቆዲሞስ ሰባተኛ ሳምንት
"እውነት እውነት እልሃለሁ፥ ሰው ከውኃና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም።"
ዮሐ 3፡5
የዕለቱ ቅዱስ ወንጌል
ዮሐ 3፡1-21
የዕለቱ የቅዱስ ጳውሎስ መልእክት
ሮሜ 7፡1-12
የዕለቱ መልእክት
1ኛ ዮሐ 4፡18-21
የሐዋርያት ሥራ
ሐዋ 5፡34-42
የዕለቱ ምስባክ
መዝ 17፡3 -5
መልካም ዕለተ ሰንበት!
የበረከት ጾም ያድርግልን።
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
ጥንተ ስቅለት
"ሙሴም በምድረ በዳ እባብን እንደ ሰቀለ እንዲሁ በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ የሰው ልጅ ይሰቀል ይገባዋል።" ዮሐ 3፡14
መጋቢት 27 የክብር ባለቤት ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበትና ዓለምን ከመርገመ ሥጋ ከመርገመ ነፍስ ያዳነበት የጥንተ ስቅለት መታሰቢያ ነው።
መልካም በዓል!
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
የ8ኛ እና የ9ኛ ክፍል የሰንበት ት/ቤቶች መማሪያ መጸሐፍት የአርትዖ ሥራ መርሐ ግብር ተካሔደ።
(የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት) መጋቢት 23/07/2017 ዓ.ም
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክ መንበረ ፓትሪያሪክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ በሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የሚዘጋጀው የሰንበት ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት መማሪያ መጻሕፍት ከ1-7ኛ ክፍል በአማርኛ እንዲሁም 1ኛ እስከ 4ኛ ክፍል ደግሞ በኦሮምኛ ቋንቋ አዘጋጅቶ ለኅትመት እና ሥርጭት ማብቃቱ ይታወቃል። አሁን ደግሞ ከ8-12ኛ ክፍል ያሉትን የመማሪያ መጸሐፍት አዘጋጅቶ ለማጠናቀቅ ባሳለፍነው ሳምንት ከመጋቢት 19 እስከ 21 ለ3 ተከታታይ ቀናት በጌቴሰማኔ ቤተ ደናግል ጠባባት የሴቶች ገዳም የ8ኛ እና የ9ኛ ክፍል መጸሐፍትን የአርትኦት ሥራ ማካሔዱን በመንበረ ፓትሪያሪክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሓላፊ የሆኑት መጋቤ ሐዲስ ጸጋ ወ/ትንሣኤ ገልጸዋል። በዚህ የአርትኦት ሥራ የሊቃውንት ጉባኤ ምክትል ሐላፊ መጋቤ ምሥጢር ፍሬ ስብሐት ዱባለን ጨምሮ መምሪያው ሊቃውን ፣ የነገረ መለኮት ምሁራን ፣ የሰንበት ት/ቤቶች መምህራን እና የሥርዓተ ትምህርት ባለሞያዎች ተሳትፈዋል።
የመምሪያው ሐላፊ እንደገለጹት የአርትኦት ሥራውን አርታኢያኑ በ3 ምድብ ተከፋፍለው የሠሩት ሲሆን በእያንዳንዱ ምድብ ከ3-4 መጸሐፍት አርትኦት እንደተደረጉ እንዲሁም በአርትዖ ሥራው ላይ በየቡድኑ ቀርበው የነበሩ አሻሚ ጉዳዮች ላይ ሁሉም የአርትዖ ኮሚቴ ዓባላት ባሉበት በአንድነት ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸው መፍትሔ እንደተሰጣቸው ተናግረዋል።
በአርትኦት ሥራው ተሳታፊ የነበሩት ዓባላትም ቆይታቸው የተሳካ የአርትዖ ሥራውም ውጤታማ እንደነበር ገልጸዋል። በመጨረሻም በዚህ የአርትኦት ሥራ ላይ ጊዜያቸውን ሰጥተው ለተሳተፉ የአርትኦት ኮሚቴ አባላት በሙሉ የመምሪያ ሓላፊ መጋቤ ሐዲስ ጸጋ ወ/ትንሣኤ ምስጋናን አቅርበዋል።
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!
(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)
👉 Youtube
👉 Facebook
👉 Telegram
👉 Tiktok
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
