ch
Feedback
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU

前往频道在 Telegram

📈 Telegram 频道 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU 的分析概览

频道 የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት -EOTC GSSU (@eotcgssu21) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 14 309 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 6 161,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 365

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 14 309 名订阅者。

根据 21 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 502,过去 24 小时变化为 16,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 48.88%。内容发布后 24 小时内通常能获得 13.10% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 0 次浏览,首日通常累积 1 875 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 0

📝 描述与内容策略

尚未提供频道描述。

凭借高频更新(最新数据采集于 22 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。

14 309
订阅者
+1624 小时
+1117
+50230
帖子存档
"እርስ በርሱ የሚናበብ ትውልድን በተገቢው መንገድ በመቅረጽ ቤተ ክርስቲያንን ለመታደግ ሥርዓተ ትምህርቱን ማስተግበር የሁላችንም ድርሻ ነው።" (ብፁዕ አቡነ ኒቆዲሞስ የምሥራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት
+6
"እርስ በርሱ የሚናበብ ትውልድን በተገቢው መንገድ በመቅረጽ ቤተ ክርስቲያንን ለመታደግ ሥርዓተ ትምህርቱን ማስተግበር የሁላችንም ድርሻ ነው።" (ብፁዕ አቡነ ኒቆዲሞስ የምሥራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት ጳጳስ) (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) መጋቢት 22/07/2017 ዓ.ም በምሥራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት አዘጋጅነት በሀገረ ስብከቱ ስር ላሉ የሰንበት ትምህርት ቤቶች ተወካዮችና የአድባራት አስተዳዳሪዎች በቅዱስ ሲኖዶስ ጸድቆ በመላው ሀገሪቱ እየተተገበረ የሚገኘውን የሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ትግበራና መዋቅራዊ አደረጃጀትን በተመለከተ በማደራጃ መምሪያው ልዑክ መጋቤ ሃይማኖት ቀሲስ ይታገሱ ደሴ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ተሰጠ። ሥልጠናውን በትኩረት ሲከታተሉ የነበሩት የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ እስከ "ዛሬ የሥርዓተ ትምህርቱ መዘግየት ብዙ ያጎደለብን ሲሆን አሁንም ባለማስተግበር እንዳናዘገየው አደራ ፤ እንደ ምሥራቅ ሐረርጌ ከሥልጠናው እንደተረዳነው ሥርዓተ ትምህርቱን ለማስተግበር ሁሉም ባለድርሻ አካላት የሚመለከተው ስለሆነ ተባብረን ለማስተግበር እንጥራለን። እስከ ዛሬ እርስ በርሱ የማይናበብ ትውልድ ፈጥረን የምንቸገረው ሥርዓተ ትምህርት ባለመኖሩ ነው።" በማለት አባታዊ መልእክትና መመሪያ አስተላልፈዋል። በሥልጠናውም በቂ ግንዛቤ ማግኘታቸውን ተሳታፊዎች ገልጸው ሥርዓተ ትምህርቱን ለማስተግበር ያላቸውን ቁርጠኝነት በአቋም መግለጫ አረጋግጠዋል። የሀገረ ስብከቱ ሰንበት ት/ቤት ክፍል ሐላፊ የሆኑት መልአከ ሰላም ከበደ ይፍሩ የሥልጠናው መርሐ ግብር እስከ ወረዳ በማውረድ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት በመንበረ ጵጵስና ርዕሰ ከተማ (አዳማ) ወረዳ ቤተ ክህነት ስር በሚገኙ ሰ/ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርቱን እያስተማሩ ከሚገኙ መምህራን ጋር በትምህርት አተገባበሩ ዙርያ በቀን
+4
በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት በመንበረ ጵጵስና ርዕሰ ከተማ (አዳማ) ወረዳ ቤተ ክህነት ስር በሚገኙ ሰ/ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርቱን እያስተማሩ ከሚገኙ መምህራን ጋር በትምህርት አተገባበሩ ዙርያ በቀን 20/07/2017 ዓ.ም ውይይት እና ሥልጠና ተከናወነ። የመንበረ ጵጵስና ሰ/ት/ቤቶች አንድነት በ2014 ዓ.ም በ2 ሰ/ት/ቤቶች ብቻ የተጀመረውን የሥርዓተ ትምህርት ትግበራ በማጠናከር በአሁኑ ሰዓት በከተማው በሚገኙ 26 ሰ/ት/ቤቶች እየተገበረ የሚገኝ ሲሆን ፤ ባለፉት 3 ዓመታት ለሥርዓት ት/ቱ ባለ ድርሻ አካላት ብዙ ሥልጠናዎች ሰጥቷል። የትላንቱም ሥልጠና በዋናነት “የማስተማር ሥነ -ዘዴ” ላይ ያተኮረ ሲሆን ፤ ሥልጠናው የመንበረ ፓትርያርክ የጠቅላይ ቤተ ክህነት ሰ/ት/ቤቶች አንድነት የግንኙነት ክፍል ሐላፊ በመ/ር ያረጋል አስፋው ተሰጥቷል። በሥልጠናው የሰ/ት/ቤት አባላት ፣ሰባኪያነ ወንጌል እና የአብነት መምህራን የተሳተፉ ሲሆን ከሥልጠናው በተጨማሪ መምህራን በማስተማር ሒደቱ ላይ ያጋጠሟቸው ችግሮች ላይ ሰፊ ውይይት ተደረጓል። ለሥርዓተ ትምህርቱ ተጠናክሮ መተግበር የመንበረ ጵጵስና ወረዳ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ላደረገው ድጋፍና ክትትል የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ከፍተኛ ምሥጋና አቅርቧል። መረጃው የምሥራቅ ሸዋ ሀ/ስብከት ሰ/ት/ቤቶች አንድነት ነው። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

የመማርያ መጻሕፍት ሥርጭት በቅርብ ቀን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምርያ ዕድሜን መሠረት ያደረገ ወጥ የሆ
+1
የመማርያ መጻሕፍት ሥርጭት በቅርብ ቀን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምርያ ዕድሜን መሠረት ያደረገ ወጥ የሆነ ሥርዓተ ትምህርት አዘጋጅቶ በሀገር ውስጥ እና በውጭ ሀገራት በትግበራ ላይ ይገኛል። ለሥርዓተ ትምህርት ትግበራውም ለረጅም ጊዜያት በቤተክርስቲያን ሊቃውንትና መምህራን እንዲሁ በሥርዓተ ትምህርት ባለሙያዎች ሲደከምበት የኖረውን የሥርዓተ ትምህርት መማርያ መጻሕፍት በባለፈው ዓመት ከ1ኛ-4ኛ ክፍል 23 የመማሪያ መጻሕፍት በማሳተም በሥርጭት ላይ ማዋሉ ይታወቃል። በዘንድሮውም ዓመት ደግሞ በአምላካችን ቅዱስ ፈቃድ 👉 ከ1-4ኛ ክፍል 23 የኦሮምኛ ትርጉም የመማርያ መጻሕፍት በአራት ጥራዝ 👉 ከ5ኛ እስከ 7ኛ ክፍል በ3 ጥራዝ የተዘጋጁ 18 መጻሕፍት በአጠቃላይ 41 መጻሕፍት  ተዘጋጅተው ለኅትመትና ለሥርጭት በቅተዋል።   ለሕዝበ ክርስቲያንም በሙሉ እንኳን ደስ አላችሁ እንላለን፡ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

ደብረ ዘይት (እኩለ ጾም) "ከክብሩ ውበት ከጽዮን እግዚአብሔር ግልጥ ሆኖ ይመጣል። አምላካችን ይመጣል ዝምም አይልም፤ እሳት በፊት ይነዳል።" መዝ 49(50)፡2-3 መልካም ዕለተ ሰንበት! የበረከት
ደብረ ዘይት (እኩለ ጾም) "ከክብሩ ውበት ከጽዮን እግዚአብሔር ግልጥ ሆኖ ይመጣል። አምላካችን ይመጣል ዝምም አይልም፤ እሳት በፊት ይነዳል።" መዝ 49(50)፡2-3 መልካም ዕለተ ሰንበት! የበረከት ጾም ያድርግልን። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

በድሬደዋ የአዲሱ መዋቅራዊ አደረጃጀት አፈፃፀም ዙሪያ ከአጥቢያ ሰ/ት/ቤቶች ሊቃነ መናብርት ጋር ሰፊ ውይይት ተደረገ። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በድሬደዋ ሀገረ ስብከት በ13ኛው
+3
በድሬደዋ የአዲሱ መዋቅራዊ አደረጃጀት አፈፃፀም ዙሪያ ከአጥቢያ ሰ/ት/ቤቶች ሊቃነ መናብርት ጋር ሰፊ ውይይት ተደረገ። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በድሬደዋ ሀገረ ስብከት በ13ኛው ሀገር አቀፍ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ ላይ ጸድቆ ወደ ትግበራ እየገባ ባለው የሰ/ት/ቤቶች ዝርዝር መዋቅራዊ አደረጃጀት ዙሪያ መጋቤ ሃይማኖት መምህር ዘላለም ፍቃዱ የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ ክፍል ሐላፊ ፣ የአንድነቱ አመራር እና የአጥቢያ ሰ/ት/ቤቶች ሊቃነ መናብርት በተገኙበት በትላንትናው ዕለት ሰፊ ውይይት ተደርገጓል። በውይይቱም  በመወቅራዊ አደረጃጀቱ ዙሪያ ሰፊ ማብራሪያ ለጉባኤው የተሰጠ ሲሆን በአፈፃፀሙ ዙሪያ ከጉባኤው ለተነሱ ጥያቄዎችም በቂ ምላሽ እንደተሰጠም ተገልጧል። በመጨረሻም የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ ክፋል ሐላፊ መጋቤ ሃይማኖት ዘላለም ፈቃዱ የአንድ ወር መዋቅሩን የማጥኛ ጊዜ በመስጠት እና ለተፈፃሚነቱ ሁሉም ባለድርሻ አካላት የበኩላቸውን እንዲወጡ በማሳሰብ ስብሰባውን በፀሎት ዘግተዋል። መረጃው የአንድነቱ መረጃና መዛግብት ክፍል ነው። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

በማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት የ2017 ዓ.ም 1ኛ መንፈቅ ዓመት የሥርዓተ ትምህርት ማጠቃለያ ፈተና በጎንደር ርዕስ ከተማ ውስጥ በሚገኙ በ24 ሰንበት ት/ቤቶች የካቲት 30 / 2017 ዓ.ም ተሰጥ
+5
በማዕከላዊ ጎንደር ሀገረ ስብከት የ2017 ዓ.ም 1ኛ መንፈቅ ዓመት የሥርዓተ ትምህርት ማጠቃለያ ፈተና በጎንደር ርዕስ ከተማ ውስጥ በሚገኙ በ24 ሰንበት ት/ቤቶች የካቲት 30 / 2017 ዓ.ም ተሰጥቷል። በሀገረ ስብከቱ በተለይም በዕርሰ ከተማ በሚገኙ ሰንበት ት/ቤቶች ከ2014 ዓ.ም ጀምሮ እየተተገበረ የሚገኘው የሰንበት ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ዘንድሮ ሦስተኛ የትግበራ ዓመታችው  ሲሆን ከ2200 በላይ ተማሪዎች  የ2017 ዓ.ም 1ኛ መንፈቅ ዓመት ማጠቃለያ ፈተና የካቲት 30/ 2017 ዓ.ም ከ፩ኛ -፬ኛ ክፍል ሥርዓተ ትምህርቱን የሚማሩ ተማሪዎች በ24 ሰንበት ት/ቤቶች ውስጥ ምዘናውን ወስደዋል። በሀገረ ስብከቱ የሥርዓተ ትምህርት ትግበራ በዕርስ ከተማው ከሚገኙ ሰንበት ት/ቤቶች በተጨማሪ በ5 ወረዳዎችም ሥርዓተ ትምህርቱ እየተተገበረ ይገኛል፡፡ በአዘዞ ወረዳም መጋቢት 08/2017 ዓ/ም ከ1400 ያላነሱ ተማሪዎች ተፈትነዋል፡፡ መረጃው የሀገረ ስብከቱ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ነው። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

ቅዱስ መስቀል "ነገር ግን ዓለም ለእኔ የተሰቀለበት እኔም ለዓለም የተሰቀልሁበት ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በቀር ሌላ ትምክህት ከእኔ ይራቅ።" ገላ 6:14 መጋቢት 10 የክብር ባለቤት ጌታ
ቅዱስ መስቀል "ነገር ግን ዓለም ለእኔ የተሰቀለበት እኔም ለዓለም የተሰቀልሁበት ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ መስቀል በቀር ሌላ ትምክህት ከእኔ ይራቅ።" ገላ 6:14 መጋቢት 10 የክብር ባለቤት ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተሰቀለበት የከበረ መስቀል የተገለጠበት እና የተገኘበት ቀን  ዓመታዊ መታሰቢያ ነው። ከዕፀ መስቀሉ በረከት ያሳትፈን የበረከት ጾም ያድርግልን። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

በባሌ ሀገረ ስብከት ለመጀመሪያ ጊዜ የተጀመረው አዲሱ የሰ/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ትግበራ የ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የመጀመሪያ መንፈቀ ዓመት የማጠቃለያ ፈተና በመሰጠት ላይ ይገኛል። እስካሁን
+7
በባሌ ሀገረ ስብከት ለመጀመሪያ ጊዜ የተጀመረው አዲሱ  የሰ/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ትግበራ የ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የመጀመሪያ መንፈቀ ዓመት የማጠቃለያ ፈተና በመሰጠት ላይ ይገኛል። እስካሁን በሦስት ወረዳወች በ10 አጥቢያ ሰ/ትቤቶች ከ1ኛ እስከ 7ኛ ክፍል 1271 ተማሪዎች የመንፈቀ ዓመት ማጠቃለያ ፈተና የወሰዱ ሲሆን ቅድመ መደበኛ ለ344 ህጻናት ምዘና ተሰጥቷል። ሌሎች በአጀማመር ወቅት በተለያየ ምክንያት ወደ ኋላ የቀሩ (ዘግይተው የጀመሩ አጥቢያወች) ከመጋቢት 13 እስከ 21 የሚሰጥ ይሆናል። እስካሁን በመንፈቅ ዓመቱ አፈጻጸም 402 ተማሪዎችን በማስፈተን የጎባ ደብረ መድኃኒት መድኃኔ ዓለም ፍሬ ሰላማ ሰ/ት/ቤት  ትልቁን ድርሻ ተወጥቷል። መረጃው የሀገረ ስብከቱ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ነው። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

በምሥራቅ ሸዋ ሀ/ስብከት በአዳማ/ናዝሬት የና/ደ/መ/መድኃኔዓለም ገዳምና ካቴድራል ፈለገ ጥበብ ሰ/ት/ቤት ከገዳሙና ከካቴድራሉ ሰበካ ጉባኤ ጋር በመተባባር ለገዳሙና ካቴድራሉ ማኅበረ ካህናት የሰ/ት/
+4
በምሥራቅ ሸዋ ሀ/ስብከት በአዳማ/ናዝሬት  የና/ደ/መ/መድኃኔዓለም ገዳምና ካቴድራል ፈለገ ጥበብ ሰ/ት/ቤት ከገዳሙና ከካቴድራሉ ሰበካ ጉባኤ ጋር በመተባባር ለገዳሙና ካቴድራሉ ማኅበረ ካህናት የሰ/ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫና የውይይት መርሐግብር አካሔድዋል፡፡ ሥልጠናው የተሰጠው ከጠቅላይ ቤተክህነት ሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ዓለም አቀፍ የሰ/ት/ቤቶች አንድንት አገልጋይ በየሆኑት ቀሲስ አለማየሁ ደበበ ሲሆን ከሥልጠናው በተጨማሪ ከማኅበራት ካህናት በተሰኑ ጥያቄዎች ላይ በቂ ማብራሪያና ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ መልአከ ጽዮን ቆሞስ አባ ጳውሎስ መርሐግብሩን በጸሎት በማስጀመር የሥልጠናውን ዓላማውን በመግለጸ መርሐግብሩን ያስጀመሩ ሲሆን ማኅበረ ካህናቱም በሥርዓተ ትምህርቱ ተግበራ ላይ ከማስተማረ ጀምሮ በንሰሐ ልጆቻቸው በኩል ሰፊ የቅስቃሳና ሥርዓተ ትምህርቱን የማስተዋወቅ ሥራ እንዲሰሩ  መመሪያ አስተላልፈዋል፡፡ በመጨረሻም መሰል ሥልጠናዎች ጠቀሜታቸው የጎላ በመሆኑ እንዲሚቀጥሉም አቅጣጫ አስቀምጠዋል፡፡ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

በጅማ ሀገረ ስብከት የ2017 ዓ.ም 1ኛ መንፈቅ ዓመት የሥርዓተ ትምህርት ማጠቃለያ ፈተና በሁሉም ሰንበት ት/ቤቶች መጋቢት 6 እና 7 ቀን 2017 ዓ.ም ተሰጠ። በጅማ ሀገረ ስብከት በተለይም በጅማ
+3
በጅማ ሀገረ ስብከት የ2017 ዓ.ም 1ኛ መንፈቅ ዓመት የሥርዓተ ትምህርት ማጠቃለያ ፈተና በሁሉም ሰንበት ት/ቤቶች መጋቢት 6 እና 7 ቀን 2017 ዓ.ም ተሰጠ። በጅማ ሀገረ ስብከት በተለይም በጅማ ከተማ በሚገኙ ሰንበት ት/ቤቶች ከ2016 ዓ.ም ጀምሮ እየተተገበረ የሚገኘው የሰንበት ት/ቤቶች ሥርዓት ትምህርት ዘንድሮ ሁለተኛ የትግበራ ዓመቱ ሲሆን የ2017 ዓ.ም 1ኛ መንፈቅ ዓመት ማጠቃለያ ፈተና መጋቢት 6 እና 7 ቀን 2017 ዓ.ም በሁሉም ሰንበት ት/ቤቶች ተሰጥቷል። በሀገረ ስብከቱ የሥርዓተ ትምህርት ትግበራ በከተማው ከሚገኙ ሰንበት ት/ቤቶች በተጨማሪ በተወሰኑ ወረዳዎችም መጀመሩን የጅማ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጽ/ቤት አስታውቋል። መረጃው የጅማ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ነው። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

መጻጉዕ 4ኛ ሳምንት "ጌታ ኢየሱስ :- ተነሣና አልጋህን ተሸክመህ ሂድ አለው። ወዲያውም ሰውዬወወ ዳነ። አልጋውንም ተሸክሞ ሄደ።" ዮሐ 5:8-9 መልካም ዕለተ ሰንበት! የበረከት ጾም ያድርግልን። የ
መጻጉዕ 4ኛ ሳምንት "ጌታ ኢየሱስ :- ተነሣና አልጋህን ተሸክመህ ሂድ አለው። ወዲያውም ሰውዬወወ ዳነ። አልጋውንም ተሸክሞ ሄደ።" ዮሐ 5:8-9 መልካም ዕለተ ሰንበት! የበረከት ጾም ያድርግልን። የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ሙሉ በሙሉ እንዲተገበር ክትትልና ድጋፍ እያደረገ መሆኑን የወልድያ ከተማ አስተዳደር የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት አስታወቀ፡፡ የወልድያ ከተማ አስተዳደር የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የሁሉም ሰንበት ትምህርት ቤቶች የትምህርት ክፍል ሐላፊዎች፣ የሥርዓተ ትምህርት ትግበራ አስተባባሪዎችና የአንድነቱ ሥራ አስፈጻሚዎች በተገኙበት በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት የመጀመሪያ ወሰነ ትምህርት አተገባበር ላይ ያተኮረ ግምገማ በዛሬው ዕለት አካሄዷል፡፡ የከተማ አስተዳደር ቤተ ክህነቱ የስብከተ ወንጌልና የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ ክፍል ሐላፊ መ/ር ቡሩክ ተስፋዬ “ዛሬ ላይ በሕፃናትና ወጣቶች ላይ የሚሠራ ሥራ የነገን ቤተክርስቲያን ቀጣይነት ያረጋግጣል” የሚል መሪ መልእክት መነሻ አድርገው ንግግር ያደረጉ ሲሆን አድባራት ከቁሳዊ ልማት ባሻገር ለሰው ኃይል ልማት ልዩ ትኩረት ሊሰጡ ይገባል ብለዋል፡፡ መ/ር ቡሩክ አክለውም በከተማ አስተዳደሩ አድባራት ከተመዘገቡት 13 ሰንበት ትምህርት ቤቶች መካከል በአሥሩ አዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ተግባራዊ መደረጉን ገልጸው የሰበካ ጉባኤያት ትኩረት አናሳ መሆን፣ የግንዛቤ ክፍተትና የሥርዓተ ትምህርት ትግበራ ወጥ አለመሆን ከገጠሟቸው ችግሮች መካከል ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል፡፡ ከሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በተገኘ መረጃና በአካል በተደረገ ክትትል የተሻለ አፈጻጸም ያላቸው ሰንበት ትምህርት ቤቶች ቢኖሩም በመረጃ ክፍተት ምክንያት በትግበራው ላይ ውስንነት ያለባቸው እንዲያሻሽሉ አጫጭር የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናዎች እየተሰጡ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የወልድያ ከተማ አስተዳደር ቤተ ክህነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት አመራሮችና የኹሉም አድባራት ሰንበት ትምህርት ቤቶች ሥራ አስፈጻሚ አባላት በተገኙበት መርሐ ግብሩ ተካሂዷል፡፡ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok

በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የመንብረ ጵጵስና ርዕሰ ከተማ ወረዳ ቤተ ክህነት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የ2017 ዓ.ም አንደኛ መንፈቅ ዓመት ማጠቃለያ ምዘና
+7
በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የመንብረ ጵጵስና ርዕሰ ከተማ ወረዳ ቤተ ክህነት ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የ2017 ዓ.ም አንደኛ መንፈቅ ዓመት ማጠቃለያ ምዘና አሰጠ፡፡ የመንበረ ጵጵስና ርዕሰ ከተማ ወረዳ ቤተክህነት ሰ/ት/ቤቶች አንድነት በወረዳው ስር ባሉ 26 አጥቢያ ሰ/ት/ቤቶች ላይ በሀገረ አቀፍ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በወጣ የጊዜ ሰሌዳ መሠረት በ23/06/2017 ከ1ኛ -5ኛ ክፍል እና በ30/06/2017 ዓ.ም ከ6ኛ - 9ኛ ክፍል ያሉ አዲሱን የሰ/ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት እየተገበሩ ባሉ አጥቢያ ሰንበት ትምህርት ቤቶች ላይ ምዘና አሰጥቷል፡፡ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ! (የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት) 👉 Youtube 👉 Facebook 👉 Telegram 👉 Tiktok