Pharo School - Assosa
前往频道在 Telegram
Dear all, Welcome to Pharo School - Assosa Telegram channel. We will be able to reach you through this telegram channel, and share messages and update you with important information. Thank you! The school.
显示更多2 329
订阅者
+124 小时
+87 天
+11830 天
帖子存档
ለፋሮ ቁ2 ት/ቤት ተማሪ ወላጆች
የአዲስ ተማሪዎች ለመግቢያ ፈተና ምዝገባ የሚከናወነው ነገ 06/11/2018 ዓ.ም 2:30-6:30 ጠዋት 10:00 ከሰዓት እና ማክሰኞ 07/11/2018 ዓ.ም ጠዋት ከ2:30-6:30 ብቻ መሆኑ አውቃችሁ በተባለው ጊዜና ሰዓት በአዲሱ ጊቢ በአካል በመገኘት ልጆን እንዲያስመዘግቡ እያልን
፨ ይህ ምዝገባ ተማሪወችን ለፈተና ለማስቀመጥ ብቻ ነው።
፨ የተመዝጋቢው ተማሪ ውጤት አማካኝ 60 መሆን አለበት።
፨ የመግቢያ ፈተናው የእንግሊዘኛ እና የሒሳብ ትምህርቶች ናቸው። የፈተናው ይዘትም በ2018 ዓ.ም የት/ት ዘመን የነበሩበትን የክፍል ደረጃ ይሆናል።
፨ ፈተና የሚካሄደው ሮብ 08/11/2018 ዓ.ም ከ3:00_5:00 ይሆናል።
፨ ውጤት ሮብ ከሰዓት ይገለፃል።
፨ ምዝገባ ሀሙስ ከ2:30-6:30 ጠዋትና 8:00-10:00 ከሰዓት ብቻ ይደረጋል።
ማሳሰቢያ
ማንኛውም ወላጅ ፈተና አልፎ ለምዝገባ ብቁ የሆነውን ልጁን በተጠቀሰው ቀን ተከታትሎ ማስመዝገብ ይኖርበታል። በምንም አይነት ጉዳይ ምዝገባ ያልፈፀመን የተማሪ ወላጅ የማናስተናግድ መሆኑን በአክብሮት እናሳውቃለን።
ት/ቤቱ
ሃምሌ 2 ቀን 2018 ዓ/ም
ለፋሮ ቁ2 ትምህርት ቤት ተማሪ ወላጆች!
ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ በገለጽነው መሰረት የ2019 ዓ/ም የነባር ተማሪዎች ምዝገባ ሀምሌ 3 2018 ዓ.ም የሚጠናቀቅ በመሆኑ አስቀድማችሁ ላስመዘገባችሁ ወላጆች ላቅ ያለ አክብሮትና ምስጋናችንን እያቀረብን እስካሁን ያልተመዘገቡ ጥቂት ተማሪዎች መኖራቸውን ከዝርዝሩ ላይ ስላገኘን ዛሬ ሀሙስ ሀምሌ 02 2018 2:30-10:00 እና ዓርብ ሀምሌ 03 2018 እለት እስከ 6:30 ሰአት ብቻ እንድትመዘገቡ የመጨረሻ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
ማሳሰቢያ ፤ በወቅቱ ባለመመዝገብ ምክንያት አዲስ ተማሪ ከተተካ በኋላ ለሚከተለው ችግር ሃላፊነቱን ት/ቤቱ አይወስድም!!
ሃምሌ 1 ቀን 2018 ዓ/ም
ለፋሮ ቁ1 ትምህርት ቤት ተማሪ ወላጆች!
ከዚህ በፊት በተደጋጋሚ በገለጽነው መሰረት የ2019 ዓ/ም የነባር ተማሪዎች ምዝገባ በዛሬው ዕለት የሚጠናቀቅ በመሆኑ አስቀድማችሁ ላስመዘገባችሁ ወላጆች ላቅ ያለ አክብሮትና ምስጋናችንን እያቀረብን እስካሁን ያልተመዘገቡ ጥቂት ተማሪዎች መኖራቸውን ከዝርዝሩ ላይ ስላገኘን በዛሬው እለት እስከ 10፡00 ሰአት ብቻ እንድትመዘገቡ የመጨረሻ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን።
ማሳሰቢያ ፤ በወቅቱ ባለመመዝገብ ምክንያት አዲስ ተማሪ ከተተካ በኋላ ለሚከተለው ችግር ሃላፊነቱን ት/ቤቱ አይወስድም!!
World's Best School Prizes 2026 https://share.google/AXLwD6e2pRNCovoVs
Click the link - Search Entries - Pharo - Vote Now - Fill the form - Vote
ውድ የፋሮ ት/ቤት ተማሪ ወላጆች
የፋሮ ት/ቤቶች አካል የሆነዉ የፋሮ ሆሞሻ የሴቶች አዳሪ ት/ቤት በዓለም አቀፍ የት/ቤቶች ዉድድር "አስቸጋሪ ሁኔታዎችን ተቋቁሞ ስኬታማ በሆኑ ት/ቤቶች" ዘርፍ ከአስር የዓለማችን ምርጥ ት/ቤቶች አንዱ ሆኖ በመመረጡ እንኳን ደስ አላችሁ እያልን ዉድድሩን በ1ኛነት እንዲያጠናቅቅ የርስዎ ድምፅ አስፈላጊ በመሆኑ ከታች ያለዉን ሊንክ/ማስፈንጠሪያ ተጭናችሁ በመግባት Pharo School - Homosha የሚለው ላይ Vote የሚለውን በመጫን የወደፊት የክልላችን ሴት ልጆች ተስፋ ለሆነው ትም/ቤት ድምፅዎን እንዲሰጡ እንጠይቃለን።
ውድ የፋሮ ት/ቤት ተማሪ ወላጆች
የፋሮ ት/ቤቶች አካል የሆነዉ የፋሮ ሆሞሻ የሴቶች አዳሪ ት/ቤት በዓለም አቀፍ የት/ቤቶች ዉድድር "አስቸጋሪ ሁኔታዎችን ተቋቁሞ ስኬታማ በሆኑ ት/ቤቶች" ዘርፍ ከአስር የዓለማችን ምርጥ ት/ቤቶች አንዱ ሆኖ በመመረጡ እንኳን ደስ አላችሁ እያልን ዉድድሩን በ1ኛነት እንዲያጠናቅቅ የርስዎ ድምፅ አስፈላጊ በመሆኑ ከታች ያለዉን ሊንክ/ማስፈንጠሪያ ተጭናችሁ በመግባት Pharo School - Homosha የሚለው ላይ Vote የሚለውን በመጫን የወደፊት የክልላችን ሴት ልጆች ተስፋ ለሆነው ትም/ቤት ድምፅዎን እንዲሰጡ እንጠይቃለን።
ውድ የካምፖስ 2 ተማሪ ወላጆች
ወርሀዊ መመዝገቢያ ድ.
1. ኬጂ -6ኛ 1500 300 1800
2. 7እና8 1750 300 2050
3. 9-12 1875 300 2175
ልጆን ለማስመዝገብ ሲመጡ ከላይ የተመለከተውን ክፍያ መሠረት በማድረግ እና ዝርዝር ብር በመያዝ ተዘጋጅተው እንዲመጡ እናሳውቃለን። ምዝገባው የነባር ተማሪዎች ሲሆ ከዛሬ ሰኞ እስከ ዓርብ ከ3:00-6:30 ጠዋት 8:00-10:00 ከሰዓት መሆኑን እየገለፅን ከተጠቀሰው ሰዓት ዉጭ የማናስተናግድ መሆኑን እናሳውቃለን።
አዲስ ተመዝጋቢ ተማሪዎች ቀጣይ ሰኞ ና ማክሰኞ ለመግቢያ ፈተና ዝግጅት ምዝገባ የሚደረግበት ሲሆን ሮብ ፈተና ይቀመጣሉ።ያለፉ ተማሪዎች ምዘገባ ሀሙስና ዓርብ ይካሄዳል።
ት/ቤቱ
«የዓለም ምርጥ ትምህርት ቤት» ሽልማት ከመጨረሻዎቹ 10 እጩዎች አንዱ ትምህርት ቤት ሆኖ መመረጡን አስታውቋል፡፡
******
የፋሮ ፋውንዴሽን ሆሞሻ አዳሪ ትምህርት ቤት ለ«የዓለም ምርጥ ትምህርት ቤት» ሽልማት ከመጨረሻዎቹ 10 እጩዎች አንዱ ትምህርት ቤት ሆኖ መመረጡን አስታውቋል፡፡
በዓለም ዙሪያ ከቀረቡ በሺዎች የሚቆጠሩ ማመልከቻዎች መካከል ፋሮ ትምህርት ቤት ሆሞሻ በ«ችግሮችን በማሸነፍ» (Overcoming Adversity) ዘርፍ ለመጨረሻዎቹ 10 ትምህርት ቤቶች አንዱ በመሆን ተመርጧል።
ይህ ሽልማት በT4 Education በየዓመቱ ከሚሰጡት አምስት ዓለም አቀፍ ሽልማቶች አንዱ ነው። ይህ እውቅና ፋሮ ትምህርት ቤት ሆሞሻ ከዓለም ዙሪያ ከሚገኙ እጅግ ፈታኝ ሁኔታዎችን የሚጋፈጡ ተማሪዎችን የትምህርት ዕድልና የሕይወት ተስፋ በአስደናቂ ሁኔታ በመቀየር ዓለም አቀፍ እውቅና ካገኙ ተመራጭ ትምህርት ቤቶች ተርታ እንዲሰለፍ አድርጎታል።
ትምህርት ቤቱ ለመጨረሻ ዙር ከተመረጡት ትምህርት ቤቶች መካከል ብቸኛው የኢትዮጵያ ትምህርት ቤት በመሆን ነው መመረጥ የቻለው።
ትምህርት ቤቱ ለሴት ተማሪዎች ሙሉ ስኮላርሽፕ፣ ደህንነቱ የተጠበቀ የመኖሪያ አገልግሎት እና በSTEM (ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ኢንጂነሪንግ እና ሂሳብ) ዘርፎች ላይ ያተኮረ ጥራት ያለው ትምህርት እየሰጠ ይገኛል።
ለመጨረሻ ውድድሩ የህዝብ ድምጽ ምርጫ ከሰኔ 18 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ኅዳር 10 ቀን 2019 ዓ.ም ድረስ የሚካሄድ ሲሆን፣ የፋሮ ፋውንዴሽን ደጋፊዎችን፣ አጋሮችን እና በዓለም ዙሪያ ያሉ ማህበረሰቦችን ፋሮ ስኩል ሆሞሻን በvote.worldsbestschool.org ገብተው እንዲመርጡም ጥሪ አቅርቧል። የዘገበው የክልሉ ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ነው።
ውድ የካምፓስ 1 ተማሪ ወላጅች
በቅድሚያ የማክበር ሰላምታችንን እያቀረብን ነገ እሁድ ሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ.ም በሚከበረው የመዝጊያ በአል ላይ የገበያ ቀን (Market Day) ስለሚኖር እንግሊዝኛ ተናግረው የሰበሰቡትን ኩፖን ይዘው እንዲመጡ እንጠይቃለን።
ት/ቤቱ
ውድ የካምፓስ 1 ተማሪ ወላጅች
በቅድሚያ የማክበር ሰላምታችንን እያቀረብን የፋሮ ት/ቤት ካምፓስ 1 በ 2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ካላንደር መሰረት እሁድ ሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ከ 2፡30 – 6:00 የት/ቤት መዝጊያ በዓል ላይ እንዲገኙልን እናሳዉቃለን።
ት/ቤቱ
ውድ የካምፓስ 2 ተማሪ ወላጅች
በቅድሚያ የማክበር ሰላምታችንን እያቀረብን የፋሮ ት/ቤት ካምፓስ 2 በ 2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን ካላንደር መሰረት እሁድ ሰኔ 28 ቀን 2018 ዓ.ም ከ 2፡30 – 6:00 የት/ቤት መዝጊያ በዓል ላይ እንዲገኙልን እናሳዉቃለን።
ት/ቤቱ
ውድ የተማሪ ወላጆች/አሳዳጊዎች
ሰላም ለእናንተ ይሁን
🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼🌼
የአራተኛ ሩብ አመት ማጠቃለያ ፈተና ከ1ኛ-5ኛ ክፍል ከሰኔ 15-17፣ 2018; ይሰጣል፡፡ ስለዚህ ከዚህ በታች በቀረበው የፈተና መርሀግብር መሠረት ለልጅዎ አስፈላጊውን ድጋፍ እና ክትትል ያድርጉ።
ት/ቤቱ
ቀን፦ ሰኔ 1/2018 ዓ/ም
ማስታወቂያ ለወላጆች!
ጉዳዩ፡ የፅሁፍ መጠይቅ ሞልተዉ እንዲልኩልን ስለማሳሰብ፤
ዉድ ወላጆች ፋሮ ት/ቤት አሶሳ፤ በሚሰጠዉ የትም/አገልግሎት ዙሪያ የእናንተን የተማሪዎቻችን ወላጆች የእርካታ መጠን በዳሰሳ ጥናት መረጃ ለመሰብሰብ የሚያስችል መጠይቅ በተማሪዎቻችን በኩል በዛሬዉ ዕለት የላክን በመሆኑ ከ10 ~15 ደቂቃ ጊዜ በመዉሰድ ሞልተዉ ነገ ጧት በተማሪዎች በኩል መልሰዉ እንዲልኩልን በአክብሮት እንጠይቃለን።
ስለ ትብብርዎ እናመሰግናለን!!
ፋሮ ት/ቤት አሶሳ (ገብርዔል ካምፓስ)
