Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር) 的分析概览
频道 Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር) (@ibnumunewor) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 109 358 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 327,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 261 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 109 358 名订阅者。
根据 30 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -20,过去 24 小时变化为 20,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 17.71%。内容发布后 24 小时内通常能获得 8.79% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 19 366 次浏览,首日通常累积 9 607 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 0。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“كناشة ابن منور”
凭借高频更新(最新数据采集于 01 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
109 358
订阅者
+2024 小时
+707 天
-2030 天
帖子存档
109 358
Repost from HUDA SOFT
«አህሉል አሠር» የሞባይል አፕልኬሽን
ይህ መተግበሪያ የተለያዩ ኢስላማዊ ደርሶችን በደረጃና በስርዓት ለመማር እጅግ አመቺ ተደርጎ የተዘጋጀ ሲሆን፣ የሚከተሉትን ጠቃሚ ይዘቶች በአንድ ላይ አካቶ ይዟል፦
ዘርፈ-ብዙ የኪታብ ደርሶች፦ የዐቂዳ፣ የመንሀጅ፣ የሲራ፣ የአደብ፣ የሐዲሥ፣ የፊቅህ፣ የነሕው እና የሶርፍ ትምህርቶች።
እያንዳንዱ የድምፅ ቅጂ (ኦዲዮ) ከኪታቡ ሶፍት ኮፒ (PDF) ጋር አብሮ የተያያዘ ነው።
አፑን ለአጠቃቀም ልዩ እና ምቹ የሚያደርጉት ባህሪያት፦
• ደርሶችን ከጀማሪ ጀምሮ ደረጃ በደረጃ በቅደም-ተከተል የሚያስተምር።
• ትምህርቱን ሲጨርሱ ራሶን የሚፈሹበት ፈተናዎች ያሉት።
• በትምህርቱ መሃል አስፈላጊ ነጥቦችን በቀላሉ መፃፍ የሚያስችል ጥሩ ማስታወሻ መያዣ ያለው።
• የደርሶች ማውጫ በየዘርፉ በጥራት የተከፋፈለበት።
• የፈለጉትን ደርስ በቀላሉ መልሰው ለማግኘት ምልክት ማድረግ የሚያስችል።
• ከቅጅዎቹ መካከል የመረጡትን ለሌሎች ማጋራት (Share) የሚያስችል አማራጭ።
• አፑን ለአጠቃቀም አመቺ የሚያደርጉት ማስተካከያዎች ያሉት።
• ደርሱን አቋርጠው በሌላ ጊዜ ማዳመጥ ቢፈልጉ በትክክል ካቆሙበት ሰከንድ የሚጀምር።
የአፕሊኬሽን አዘጋጅ፦ HUDASOFT
https://t.me/hudasoft
ይህ ስራችን የላቀው አላህን ፊት ብቻ ተፈልጎበት የተሰራ (የጠራ) ይሆን ዘንድ፤ በዚህ ስራ ላይ ለተባበሩትም ሆነ ይህንን ስራ ለሚያሰራጩት በሙሉ አላህ መልካም ስራችንን እንዲቀበለን እንማፀነዋለን።
አፑን አሁኑኑ አውርደው ይጠቀሙበት፦
🔗 የማውረጃ ሊንክ (Google Play Store)፦
https://play.google.com/store/apps/details?id=com.ahlulaser.hs.app
109 358
እውነት ለመናገር እንደ ህዝብ በውስጣችን ሰፊ ክፋት ነው ያለብን። ክፋታችን በጣም ስር የሰደደ ከመሆኑ የተነሳ እምነትም፣ ትምህርትም ብዙ አይቀይረንም። ግብይታችን በብዛት በሸፍጥ የተሞላ ነው። የአገልግሎት ቦታዎች ማጉላላትና ማንገለታታት የበዛባቸው ነው። ክፋቱን ሲፈፅም ሁሉም የዳቦ ስም ይፈልግለታል። በአለባበሳቸው ሁሌ አበሳቸውን የሚያዩት ሙስሊም ተማሪዎች የዚህ ክፋት ሰለባ ናቸው። የሚነሱ ነጥቦች ሁሉ ማመሀኛዎች ብቻ ናቸው። ዋናው ምክንያት ክፋት ነው፣ እድሜም፣ መማርም፣ እምነትም የማይቀይረው ምቀኝነት።
በየመንገዱ የምትጠየቁትን መታወቂያ ቀበሌ እንደዋዛ አታገኙትም። ማመሀኛ ሰበቡ ብዙ ነው። ሁላችንም ፖለቲካ እናወራለን። መንግስትን እንተቻለን። እርስ በርስ ያለን ክፋት ግን ተቆጥሮ የሚዘለቅ አይደለም። በየመን፣ በሊቢያ ከሚታገው ወገን ውስጥ አብዛኛው በኢትዮጵያውያን ነው ግፉ የሚደርሰው።
እንዲያውም መከራ እንኳ አያስተምረንም። ተገፋሁ ብሎ የሚያለቅሰው እንዳቅሙ ገፊ ወይም የገፊዎች ደጋፊ ነው። በብሄር፣ በእምነት ብንለያይም ብዙዎቻችንን አንድ የሚያደርገን ብሄራዊ ቅርሳችን ክፋት ነው፣ አንዱ ሌላውን ጠልፎ ለመጣል የሚደረግ ያላሰለሰ ጥረት።
=
የቴሌግራም ቻናል :-
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
109 358
ከማይፈቀዱ የቀልድ አይነቶች ውስጥ
~
የአላህ መልክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
لا يأخذُنَّ أحدُكم متاعَ أخيه لاعبًا ولا جادًّا
“ከናንተ ውስጥ ማናችሁም የወንድሙን ዕቃ በቀልድም ሆነ በምር አይውሰድ።”
አቡ ዳውድ (5003) እና ቲርሚዚይ (2160) ዘግበውታል። [ሶሒሑ ተርጊብ፡ 2808]
=
የቴሌግራም ቻናል :-
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
109 358
የኪታቡ ተውሒድ ደርስ
* በሑዘይፋ መስጂድ እየቀረበ ያለ
* ክፍል - 04
=
የቴሌግራም ቻናል :-
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
109 358
የአላህ መልክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
مَن قال في مؤمنٍ ما ليس فيهِ؛ أسكنَهُ اللهُ رَدغةَ الخَبالِ، حتى يخرُجَ ممَّا قالَ
"በሙዕሚን ላይ የሌለበትን የተናገረበት ሰው፤ ከተናገረው ነገር እስካልወጣ ድረስ አላህ ከጀሃነም ሰዎች አካል በሚወጣ የእዥና የመ^ግል አረንቋ ውስጥ ያኖረዋል።"
[ሶሒሑ ተርጊብ፡ 2845]
=
የቴሌግራም ቻናል :-
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
109 358
Repost from ABU MUSLIM A-DUROOS
📌 የጁሙዓ ኹጥባ (ምክር) - 11
🔶 የክረምት ዕረፍት በትርፍ እና በኪሳራ መካከል!!
https://t.me/AbumuslimAlarsi/14209
109 358
“የሱንና ሐቅ በኛ ላይ”፣
እንዲሁም ሱንናን ለሚያስተባብሉ ሰዎች የተሰጠ ምላሽ
ትላንት እሁድ ሰኔ 22/2018 በሑዘይፋህ መስጂድ የቀረበ
=
የቴሌግራም ቻናል :-
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
109 358
የኪታቡ ተውሒድ ደርስ
* በሑዘይፋ መስጂድ እየቀረበ ያለ
* ክፍል - 03
=
የቴሌግራም ቻናል :-
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
109 358
ዛሬ እሁድ ሰኔ 21/2018 የኪታቡ ተውሒድ ደርስ ይኖራል፣ ኢንሻአላህ።
* ቦታ፦ ሑዘይፋ መስጂድ (ከየሺ ደበሌ ከፍ ብሎ)
* ጊዜ፦ ዘወትር ቅዳሜና እሁድ ከመግሪብ እስከ ዒሻ
* ኪታቡ የሌላችሁ በዚህ ሊንክ pdf ፋይል ታገኛላችሁ:- https://t.me/IbnuMunewor/9564
109 358
Repost from የወረኢሉ ሙስሊም ወጣቶች ድምፅ
#የአፋልጉኝ ማስታወቂያ
👉ይህ ወንድማችን ጁሃር ሙሃመድ እንድሪስ ይባላል
የትውልድ ቦታው ጃማ ወረዳ 08 ቀበሌ ሲሆን
ኗሪነቱ ጃማ ከተማና ወረኢሉ እየኖረ እያለ ለስራ ብሎ 2017 ህዳር አካባቢ ከጃማ ተነስቶ ደቡብ ክልል ድማ ወደሚባል አካባቢ ለስራ እንደወጣ ስላልተመለሰ ስልክም ለመጨረሻ ጊዜ የደወለው የዛሬ አመት የካቲት አካባቢ ላይ ሲሆን ከዚያ ወድህ ስልኩም አይሰራም ድምፁም ስለጠፋብን እሱን ያያችሁና ስለሱ መረጃ ያላችሁ ወገኖቸ ይህን ወንድማችንን እንድታፈላልጉልን ስንል በትህትና እንጠይቃለን !
0914268902 ከረም ሙሃመድ ወንድም
0933519871 ጀማል እንድሮ ቤተሰብ
#ሼር በማድረግ ተባበሩን !
#አንዱባያየውሌላውሊያየው ይችላልና !
#በተለይ ደቡብ ቴፒ ወይም ድማ አካባቢ ያላችሁ ወንድምና እህቶች በቻላችሁት ተባበሩን !✍️
109 358
ሃገሪቱ በዲግሪ ማምረቻ "ፋብሪካዎቿ" በያመቱ ብዙ ሺ ባለ ማእረጎችን ታመርታለች። አሳዛኙ እውነት ግን ለበርካታ አስርት አመታት ዲግሪ እያመረቱ ያሉት እነዚህ ሁሉ "ፋብሪካዎች" የሃገሪቱን የህዝቡን ችግር በመቅረፍ ላይ ያላቸው ሚና የረባ አለመሆኑ ነው። ብዙ የግብርና ምርምር ተቋማት ቢኖሩም ገበሬውን ከዲግር አልገላገሉትም። የሃገራችን ገበሬ ዛሬም በሬ ላይ ጥገኛ ነው። የበሬ ዋጋ ደግሞ ጣራ ነክቷል። በዚህ የተነሳ በዶማ የሚቆፍረው ቀላል አይደለም። ሰብል ከመዝራት እስከ መሰብሰብ ያለው የሃገራችን የእርሻ ስራ እጅግ ኋላ ቀርና አድካሚ የሚታወቅ ነው።
ሃገሪቱ በከብት ሃብቷ ከአፍሪካ አንደኛ ናት። የስጋና የወተት ምርቱ ግን ለሀገር ውስጥ ገበያ እንኳ የሚሆን ባለመሆኑ ከውጭ ይገባል። መሬቱም ውሃውም ሳይጠፋ ፍራፍሬና ጥራጥሬ የኢትዮጵያን ውሃ ከሚጠቀሙት ከግብፅና ከሱዳን እናስገባለን።
ሀገሪቱ የውሃ ማማ ናት እያሉ ያስተምራሉ። አብዛኛው ህዝባችን ግን ንፁህ የመጠጥ ውሃ አያገኝም። የትምህርት ስርአታችን ህዝብ ተኮርና ችግር ፈቺ የሚሆነው መቼ ይሆን? ሌላው ቢቀር እርሱ በርሱ በዘር ተቧድኖ የሚናከስ፣ መርዝ የሚዘራ፣ ሃገር አፍራሽ ትውልድ ከማፍራት ቢወጡ ራሱ ቀላል ውለታ አልነበረም።
=
የቴሌግራም ቻናል :-
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
109 358
የደዕዋ ማስታወቂያ
~
ነገ እሁድ ሰኔ 21/2018 በሑዘይፋ መስጂድ የደዕዋ ፕሮግራም ስለሚኖር ሁላችሁም ተጋብዛችኋል።
ጊዜ፦ ከረፋዱ 3፡30 ጀምሮ
* ሳዳት ከማል
* አቡል 0ባስ፣
* ሙሐመድ ሱልጧን እና
* ኢብኑ ሙነወር
ቦታው ከየሺ ደበሌ ከፍ ብሎ
በሰዓት እንድትገኙ እናስታውሳለን።
109 358
ዛሬ ቅዳሜ ሰኔ 20/2018 የኪታቡ ተውሒድ ደርስ ይኖራል፣ ኢንሻአላህ።
* ቦታ፦ ሑዘይፋ መስጂድ (ከየሺ ደበሌ ከፍ ብሎ)
* ጊዜ፦ ዘወትር ቅዳሜና እሁድ ከመግሪብ እስከ ዒሻ
* ኪታቡ የሌላችሁ በዚህ ሊንክ pdf ፋይል ታገኛላችሁ:- https://t.me/IbnuMunewor/9564
109 358
ደርስ
~
• ሒልየቱ ጧሊቢል ዒልም
• ክፍል:- 24
• የኪታቡ ፋይል በpdf መልኩ በዚህ ሊንክ ይገኛል:- https://t.me/IbnuMunewor/9421
• የእለቱ ደርስ መነሻ፦ ገፅ፡ 62
109 358
አንዳንድ ሰዎች ላይ - ዱዓቶች ላይ ጭምር - የሚታይ መታረም ያለበት አነጋገር አለ።
~
"ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም" ለማለት "ሰላሰለም"፣ "ሳሰለም"፣ ... የሚሉ አሉ። መቼም ትኩረት አለመስጠት እንጂ "ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም" ማለት የሚያቅትም፣ ጊዜ የሚወስድም ሆኖ አይደለም። ስለዚህ ትኩረት በማድረግ አሟልተን በትክክል "ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም" በማለት አጉል ልማዳችንን እናስወግድ። ባረከላሁ ፊኩም።
=
የቴሌግራም ቻናል :-
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
109 358
ዛሬ ጁሙዐ ሰኔ 19/2018 የሒልየቱ ጧሊቢል ዒልም ኪታብ ደርስ ይኖራል፣ ኢንሻአላህ።
* የሚሰጥበት ቦታ:- አሸዋ ሜዳ መስጂደል ዋሊደይን
* ጊዜ:- ከመግሪብ እስከ ዒሻእ
* ኪታቡን በpdf መልኩ በዚህ ታገኙታላችሁ፦ https://t.me/IbnuMunewor/9421
* የዛሬ ደርስ መነሻ:- ገፅ፡ 62
* ቦታው ላይ መገኘት ለማትችሉ ደርሱ በዚህ የቴሌግራም ቻናል ይተላለፋል፡-
https://t.me/IbnuMunewor
109 358
قال الإمام البخاري رحمه الله تعالى في صحيحه
حَدَّثَنِي مُحَمَّدُ بْنُ بَشَّارٍ ، حَدَّثَنَا غُنْدَرٌ ، حَدَّثَنَا شُعْبَةُ ، عَنِ الْحَكَمِ ، سَمِعْتُ ابْنَ أَبِي لَيْلَى ، قَالَ : حَدَّثَنَا عَلِيٌّ ، أَنَّ فَاطِمَةَ عَلَيْهَا السَّلَامُ شَكَتْ مَا تَلْقَى مِنْ أَثَرِ الرَّحَا، فَأَتَى النَّبِيَّ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ سَبْيٌ، فَانْطَلَقَتْ فَلَمْ تَجِدْهُ، فَوَجَدَتْ عَائِشَةَ، فَأَخْبَرَتْهَا، فَلَمَّا جَاءَ النَّبِيُّ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ أَخْبَرَتْهُ عَائِشَةُ بِمَجِيءِ فَاطِمَةَ، فَجَاءَ النَّبِيُّ صَلَّى اللَّهُ عَلَيْهِ وَسَلَّمَ إِلَيْنَا وَقَدْ أَخَذْنَا مَضَاجِعَنَا، فَذَهَبْتُ لِأَقُومَ، فَقَالَ : " عَلَى مَكَانِكُمَا "، فَقَعَدَ بَيْنَنَا، حَتَّى وَجَدْتُ بَرْدَ قَدَمَيْهِ عَلَى صَدْرِي، وَقَالَ : " أَلَا أُعَلِّمُكُمَا خَيْرًا مِمَّا سَأَلْتُمَانِي ؟ إِذَا أَخَذْتُمَا مَضَاجِعَكُمَا ؛ تُكَبِّرَا أَرْبَعًا وَثَلَاثِينَ، وَتُسَبِّحَا ثَلَاثًا وَثَلَاثِينَ، وَتَحْمَدَا ثَلَاثًا وَثَلَاثِينَ، فَهُوَ خَيْرٌ لَكُمَا مِنْ خَادِمٍ ".
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
