ch
Feedback
HOP Ministry

HOP Ministry

前往频道在 Telegram

HOP Ministry — Hear. Obey. Practice. A discipleship platform sharing devotionals, revival histories, spiritual biographies, testimonies, and Amharic Christian literature to build Christ-like lives. Based on Luke 11:28.

显示更多
未指定国家未指定类别
563
订阅者
+324 小时
+217 天
+5530 天
帖子存档
“ግን እኔ የምሄድበትን መንገድ ያውቃል፤ ከፈተነኝም በኋላ እንደ ወርቅ እወጣለሁ።”   — ኢዮብ 23፥10 (አዲሱ መ.ት) “But He knows the way that I take (He has concern for it, appreciates, and pays attention to it). When He has tried me, I shall come forth as refined gold (pure and luminous).”   — Job 23፥10 (AMP) ያለ እግዚአብሔር ፈቃድ፣ ከእርሱ እውቅና ውጪ በሕይወታችን የሚሆን ምንም ነገር የለም። ለምሳሌ አካባቢውን እና የመሬቱን አቀማመጥ የማያውቀው ስፍራ ዓይኖቹን በጨርቅ ታስሮ መንገድ እንዲሄድ የተደረገን ሰው ብናይ ከመጀመሪያው እርምጃው አንስቶ ቀጣዩን እስከሚዘረጋ ድረስ በብዙ ጭንቀት፣ የውድቀት ፍርሃት፣ ግራ መጋባት ውስጥ ነው የሚሆነው። ምክንያቱም ቀጣዩ እርምጃው ጉዞውን የሚያስቀጥለው ይሁን ወይንም ለውድቀት የሚያበቃው እንደሆነ አያውቅም ፤ ከፊቱ ለጥ ያለ ሜዳ፣ ተራራ፣ ሸለቆ፣ ገደል...ምን እንዳለ ለእርሱ ግልጽ አይደለም። ከእግዚአብሔር ጋር ስንጓዝ የመንገዳችን እያንዳንዱ ዝርዝር በእኛ መታወቅ የለበትም። ምክንያቱም እኛ ሂደቱ ቢገባንም ባይገባንም ፣ መንገዱ ቀላል ወይም ከባድ ቢሆንም እግዚአብሔር የምንሄድበትን መንገድ ከማንም በላይ አጥርቶ ያውቀዋል። መልካም እረኛ ፣ ሁሉን አዋቂ አምላክ እንዳለው ሰው ቀጣዩን እርምጃችንን በእርሱ ታምነን፣ ድፍረታችን ስለ መንገዳችን ያለን እውቀት ሳይሆን አምላካችን መሆኑ ገብቶን እንቀጥል። ለወርቅ ያማረ፣ ውድ እና ተፈላጊ ሆኖ መውጣት ምክንያቱ ተፈትኖ ያለፈበት እሳት ነውና ከምንፈተንበት እሳት በላይ ስንወጣ ይዘን የምንወጣውን ማንነት እያሰብን እንታገስ። ✍️ መክሊት አየለ 📆 May 23, 2022 #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional

የምንሄድበትንመንገድእርሱያውቃል.mp34.46 MB

4_5832406532444135046.m4a5.35 MB

Ethiopia_Yosef_Alamrew_ልቤ_አንተን_አምኖ_ልቤ_new_worship_አስደናቂ_አምልኮ_2020.m4a7.99 MB

#Guide_the_Blind በስልጠና (Training) ወቅት አሰልጣኞች የተሳታፊዎችን፣ የሰልጣኞችን ተሳትፎ ለመጨመር፣ ስልጠናውን አሳታፊ ለማድረግ፣ እንዲሁም ቁልፍ የሆኑ ነጥቦችን በማይረሳ መልኩ ለማስጨበት የተለያየ ጨዋታዎችን፣ አሳታፊ የቡድን ስራዎች (Activities) ይጠቀማሉ። በአንድ ወቅት ታዳሚ ሆኜ በተገኘሁበት ስልጠና ላይ አሰልጣኙ የተጠቀመው #Guide_the_Blind (ማየት የተሳነውን ሰው መምራት) የተሰኘ የቡድን ስራ (group activity) ነበር። ጨዋታውን (ስራውን) ሁለት ሁለት ሆነን፣ የአንዱ ሰው አይን ምንም በማያሳይ ጨርቅ ታስሮ፣ አንዱ ሰው ደግሞ ልክ ማየት የተሳናቸውን ሰዎች በምንመራበት መንገድ የማያየውን ሰው እጅ ይዞ በመምራት ነበር የሚተገበረው። በአጋጣሚ እኔ አይናቸውን ከታሰሩት ሰዎች አንዷ ነበርኹ። በጊዜው ሥልጠናው ሲሰጥበት የነበረው አዳራሽ ደግሞ የሚገኘው ባለ ሶስት ወለል ሕንፃ ላይ፣ ሶስተኛው ወለል ላይ ነበር። ሕንጻው ሊፍት ስለሌለው መወጣጫችን ደረጃዎች ነበሩ። ለጨዋታው አሰልጣኙ የሰጠው መመሪያ፦ ከላይ ከስልጠና አዳራሹ ጀምሮ መሪው አይኑ የታሰረውን ሰው እየመራ፣ ደረጃውን ሁሉ በጥንቃቄ ወርዶ፣ ስልጠናው የተዘጋጀበት ጊቢ የውጪው በር ጋር ደርሶ፣ ተመልሶ ደግሞ የሕንጻውን ደረጃዎች በመውጣት፣ ከሌሎች ቡድኖች ቀድሞ ወደ ስልጠናው አዳራሽ መድረስ ነው። ለዚህ የቡድን ስራ መሳካት የሁለቱ ሰዎች መናበብ፣ መደማመጥ፣ የመሪው በሳል የመሪነት ክህሎት፣ የተመሪው ንቁ አድማጭነትና መሪውን መታመን ወሳኝ ነገሮች ናቸው። መሪው እግርህን ጣል ወዳለው አቅጣጫ ተመሪው እግሮቹን ይጥላል፣ አንሳ ወዳለው አቅጣጫ ደግሞ ያነሳል፤ እንዲህ እያሉ ደረጃውን በጋራ ይወርዳሉ፣ በጋራ ተመልሰው ይወጣሉ። አሰልጣኙ በጨዋታው ውስጥ ማስተላለፍ የፈለገው መልዕክት ስለ አመራር፣ ንቁ አድማጭነት፣ ቡድን መመስረት (Leadership, Active listening, Team Building) ነው። ጨዋታው ጨዋታ ተብሎ በወቅቱ ቢያዝናናንም በውስጡ ቁልፍ መልዕክቶች ነበሩት። ጨዋታውን ጨርሰን ከተመለስን በኋላ በሂደቱ ወቅት ምን እንደተሰማን አሳባችንን፣ ስሜታችንን እንድናጋራ አሰልጣኙ ለተወሰኑ ሰዎች እድል ሰጠ፤ እድል የደረሳቸው ሰዎችም ከራሳቸው እይታ አንጻር የተሰማቸውን ገለጹ። እኔ ግን ከስልጠናው ርዕስ ውጪ፣ አሰልጣኙ በጨዋታው ውስጥ ማስተላለፍ ከፈለገው መልዕክት ለየቀል የሆነ ነገር በውስጤ ተፈጠረ፣ ከእግዚአብሔር ጋር ስላለኝ ሕብረት፣ ስለ እምነት አንዳች ነገር እግዚአብሔር ሲናገረኝ፣ ያንን ምሳሌም ተጠቅሞ ሲያስተምረኝ ተሰማኝ፤ ደጋግሜ እያሰላሰልኹት ግን ለማንም ትንፍሽ አላልኹም፤ ወይ ጉድ! ብዬ መልዕክቴን ይዤ ቀኑ አለፈ። ነገሩ እንዲህ ነው፦ እኔ አይኔ ታስሮ፣ አሰልጣኙ አደራ የሰጠው አንድ ሰው እጄን ይዞ ጉዞ ጀመርን። መሪዬ እንዳልወድቅ ከመፍራቱ የተነሳ እጆቼን ግጥም አድርጎ ይዟል፤ እንዳልፈራና በእርሱ ላይ እንድታመን ደጋግሞ አይዞሽ፣ እኔ አለሁ፣ ደርሰናል ይለኛል። እኔ ግን ከሚናገረኝ ከእርሱ ድምጽ ይልቅ የውስጤ ፍርሃት ጮኽ ብሎ ይሰማኝ ነበር። ከዛ ሕንጻ ላይ ስገለበጥ፣ ወድቄ ስሰበር ይታየኛል፣ ከአሁን አሁን ለቀቀኝ፣ ተጋጨሁ፣ እግሬ የማይሆን ቦታ ረገጠ፣ አደናቀፈኝ እያልኹ ራሴን ለመጠበቅ፣ ለራሴ ለመጠንቀቅ ብዙ ጣርኹ፣ በአጠቃላይ በመሪዬ ላይ ራሴን መጣልና በመሪነቱ መታመን አልቻልኹም፤ ከእርሱ ይልቅ እኔ ለራሴ የማስብ፣ የምጠነቀቅ፣ የማውቅ መስሎ ታየኝ። እንዲሁ እንደፈራሁ፣ እንደ ጮኽሁ፣ እንደታገልኹት፣ እንዳስቸገርኹት ምንም ሳልሆን ጨዋታውን በሰላም ጨረስን። ለእኔ ግን አንድ ትምህርት ቀረልኝ። እግዚአብሔር ላይ ራሴን አለመጣሌ፣ በፍጹም ልቤ እርሱን አለመታመኔ፣ ተጠራጣሪነቴ፣ ከአንተ በላይ ለራሴ አውቃለሁ፣ እጠነቀቃለሁ ባይነቴ ፍንትው ብሎ ታየኝ፤ ልክ ጨዋታው ላይ መሪዬ የነበረውን ሰው አላምን ብዬ እንዳስቸገርኹት ሁሉ እግዜርንም ማስቸገሬ ታየኝ። በዚህ Guide the Blind በተሰኘ ጨዋታ ውስጥ ከተመሪው ኃላፊነት የመሪው ኃላፊነት ይከብዳል። የመሪው ኃላፊነት አንድን መንገዱን የማያውቅ፣ የማያይን ሰው፦ ኃላፊነት ወስዶ፣ ተጠንቅቆ፣ ተንከባክቦ፣ አይን ሆኖ፣ መንገድ እየመረጠ፣ አደጋ ሳያደርስበት ከግቡ ማድረስ ነው፤ ቢወድቅ፣ አንዳች ጉዳት ቢደርስበት ኃላፊነት የወሰደው፣ ተጠያቂው እርሱ ነውና ክፉ እንዳይነካው አብዝቶ ይጠነቀቅለታል። ተመሪው ግን ስለ እርሱ ኃላፊነት የወሰደ መሪ፣ የሚጠነቀቅለት መሪ አለውና እርሱን አምኖ፣ ታምኖ፣ ራሱን መሪው ላይ ጥሎ መሄድ፣ መንገዱን የሚመርጥለትን በሙሉ ልብ መከተል ነው። የዚያች ዕለት ስልጠናው እስኪያልቅ፣ ወደ ቤቴም ገብቼ ትኩረቴ በዚህ አሳብ፣ ጸሎት ተወስዶ ነበር፦ እግዚአብሔር ሆይ እንዳምንህ፣ አንተ ላይ ራሴን ጥዬ እንድከተልህ እርዳኝ!! ዛሬም እግዚአብሔርን ስለ ማመን፣ ስለ መታመን፣ ራስን እርሱ ላይ ጥሎ እርሱን ስለመከተል ሳስብ፣ ሳሰላስል፣ ስጸልይ ይህ ከዛሬ አራት ዓመት በፊት የተፈጠረ ምሳሌ ትዝ አለኝ፤ ትማሩበት እና ጸሎቴንም ትጋሩኝ ዘንድ ለእናንተም ላካፍላችሁ ወደድኹ። ዛሬም ጸሎቴን አልቀየርኹም ያው ነው፦ እግዚአብሔር ሆይ እንዳምንህ፣ አንተ ላይ ራሴን ጥዬ እንድከተልህ እርዳኝ!! ✍️ መክሊት አየለ 📆 July 5, 2026 #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional

ላውድልህ_መስፍን_ዱጉና_Devotional_Worship_Night_Lawedeleh_Mesfin_Duguna.m4a16.41 MB

ይድነቃቸው_ተካ_ቸኮለብኝ_ልቤ_Yidnekachew_Teka_chekolebgn_lbe_eliron_lyrics128k.m4a7.05 MB

#የዝናብ_ልብስ! #በመነካት_ከውስጥ_ሰውነት_የሆነ_ክርስትና! የዝናብ ልብስ ስሪቱ በላዩ ላይ የሚወርደውን ውኃ ወደ ውስጥ እንዳያሳልፍ ተደርጎ ነው። የውስጠኛው የሰውነታችን ክፍል በልብሱ ተሸፍኗልና ከዝናቡ ጋር የመነካካት እደሉ በጣም ጠባብ ነው። ከላይ የሚዘንበው ውኃ ኩልል እያለ ወደ መሬት ይወርዳል እንጂ ወደ ውስጥ አይዘልቅም። ይሄን ምሳሌ የተጠቀምኹት ስለ ዝናብ ልብስ ላወራ ፈልጌ ሳይሆን በዚህ ሂደት ውስጥ ከምናየው ነገር ለመንፈሳዊ ሕይወታችን የሚጠቅምን ትምህርት ለመቅሰም ነው። በክርስትናችን መነካት (የውስጥ ሰውታችን በእግዚአብሔር ቃል፣ በመንፈስ ቅዱስ መነካት) ቁልፍ ነገር ነው። የውስጥ ሰውነታችን በእግዚአብሔር ካልተነካ መንፈሳዊ የሆነውን ነገር ሁሉ ለምደን ከማድረግ አንቆጠብም፤ ነገር ግን ክርስትናችን የልማድ ነው። የቤተክርስቲያን መደበኛ ፕሮግራሞችን ያለማቋረጥ እንሳተፋለን፣ መዝሙር ስለምናውቅ እንዘምራለን፣ ትምህርቶች እንማራለን፣ ስብከት እንሰማለን፣ እድል ከቀናን ደግሞ እኛ ራሳችን ሰባኪዎችም ነን። ይሄ ሁሉ ሲሆን ግን መነካት የተባለውን ነገር ስለማናውቀው ሕይወታችን ፍሬ አልባ አዙሪት ይሆናል። በቤተክርስቲያን ስንሆን በተለምዶ የምናደርገውን ተግባር ሁሉ እናደርጋለን፤ ከዚያ ስንወጣም እንደማንኛውም ሰው የሆነውን መደበኛ ኑሮአችንን እንቀጥላለን። አንዳንዴ እኛን ከ ኢ-አማንያኑ የሚለይ ፍንጭ እንኳን ሕይወታችን ላይ አይታይም፤ ተመሳስለን እንኖራለን። ልክ እንደ ዝናብ ልብሱ ከሰማይ የሆነው ነገር በላያችን ይፈሳል እንጂ ወደ ውስጣችን አይዘልቅም ከእኛ ጋር በእምነት አይዋሃድምና አይጠቅመንም። ለራሴ፣ ለዘመናችን ቤተክርስቲያን እና አማኞች፣ ለትውልዴ ይሆን ዘንድ ለእግዚአብሔር የማቀርበው አንድ መሻት፣ ናፍቆት፣ ልመና አለኝ፤ ይህም ፦ የውስጥ ሰውነታችን በመንፈስ ቅዱስ እንዲነካ፣ የልቦና አይኖቻችን እንዲበሩ፣ ኢየሱስን እንድናይ፣ የመጥራቱ ተስፋ ምን እንደሆነ እንድናስተውል፣ በቅዱሳን ዘንድ ያለ የርስት ክብር ባለጠግነት እንዲገባም፣ ለምናምን ለእኛ ከሁሉ በላይ ታላቅ የሆነውን ኀይሉን እንድናውቅ ነው። አቤቱ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ሆይ በሕያው እጆችህ ዳሰን፤ ውስጠታችንን ንካው!! አሜን!! ኤፌሶን 1 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁷ የክብር አባት የሆነውን የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክ ይበልጥ እንድታውቁት፣ የጥበብና የመገለጥን መንፈስ እንዲሰጣችሁ ያለ ማቋረጥ እለምናለሁ። ¹⁸ እንዲሁም በእርሱ የተጠራችሁለት ተስፋ፣ ይህም በቅዱሳኑ ዘንድ ያለውን ክቡር የሆነውን የርስቱን ባለጠግነት ምን እንደሆነ ታውቁ ዘንድ የልባችሁ ዐይኖች እንዲበሩ ¹⁹ ለእኛ ለምናምነውም ከሁሉ በላይ ታላቅ የሆነውን ኀይሉን እንድታውቁ እጸልያለሁ። ይህም ኀይል እንደ እርሱ ታላቅ ብርታት አሠራር፣ ²⁰ ክርስቶስን ከሙታን ሲያስነሣውና በሰማያዊ ስፍራ በቀኙ ሲያስቀምጠው የታየው ነው። ✍️ መክሊት አየለ 📆 July 4, 2026 #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional

_ድሮ_ገና_Diro_Gena_lyrics_video_by_Dawit_Getachew_from_Volume_1128k.m4a5.34 MB

በእኛ ጊዜ፣ በእኛ ሁኔታ፣ በእኛ ዘመን፣ በእኛ ትውልድ....ከእግዚአብሔር ተሰጥቶን የእኛ በሆነው ነገር ሁሉ እግዚአብሔር መስራት፤ ፈቃዱን መፈጸም ይችላል። ነገር ግን እኛን ጨምሮ የሁሉ ነገር ባለቤት ለሆነው ለእግዚአብሔር ከእርሱ ተቀብለን የእኛ የሆነውን ነገር ሳንሰስት መስጠት፣ ለፈቃዱ ማዋል ካቃተን በምድር መቆየታችን ጥቅሙም ትርፉም ለእኛ እንጂ ለእግዚአብሔርና ለመንግሥቱ አይሆንም። እስትንፋሳችን ለምን ይቀጥላል? ለምን በምድር ያቆየናል? ለምን ሌላ ሰዓት፣ ሌላ ማለዳ፣ ሌላ ቀን፣ ሌላ ሳምንት፣ ሌላ ወር፣ ሌላ የምህረት ዓመት ይሰጠናል? ደግሞም ሌላ ብዙ አቅርቦት ለምን ያፈስልናል? የእግዚአብሔር የለጋስነት ዓላማው እኛን ማብላት፣ ማጠጣት፣ ማልበስ፣ ማስጌጥ.....እና ምንም ያልጎደለባቸው ቅምጥል የእግዚአብሔር ልጆች ማድረግ ነው? ኢየሱስስ የታረደው ስለ መብልና ስለ መጠጥ ጉዳይ ነው? የእግዚአብሔር መንግሥት አሳብስ የሚያጠነጥነው ስለዚህች ምድር አበይት ክስተቶች፣ የሰዎች የኑሮ ጉዳይ ላይ ነው? ይሄ ሁሉ ሲሆን የክርስቶስ የክብሩ ወንጌል ብርሃን በልባችን በርቶ፣ የድነትን ወንጌል ሰምተን፣ በእርሱም አምነን፣ ደህንነትን አግኝተን በእግዚአብሔር ቤት ካለን እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ያልጨረሰው ጉዳይ፣ በእኛ ሊሰራው ያሰበው ስራ አለ ማለት ነው። ስለዚህ ጠዋት በማለዳ ተነስቶ ለራስ ጉዳይ ሲሯሯጡ ማምሸቱ አያዛልቀንም! በእግዚአብሔርም አልታየልንምና ወደ ልቡ አሳብ በመመለስ፣ ሸክም በመቀየር፣ ትኩረታችንን የእግዚአብሔር መንግሥት ጉዳይ ላይ በማድረግ በምድር ያለ ቀሪ ጊዜያችንን በትጋት መኖር ይሁንልን!! “.... ብዙ ከተሰጠው ሁሉ ብዙ ይፈለግበታል፤ ብዙ ዐደራም ከተቀበለም ብዙ ይጠበቅበታል።”   — ሉቃስ 12፥48 (አዲሱ መ.ት) ✍️ መክሊት አየለ 📆 September 13, 2024 #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional

“.... ብዙ ከተሰጠው ሁሉ ብዙ ይፈለግበታል፤ ብዙ ዐደራም ከተቀበለም ብዙ ይጠበቅበታል።”   — ሉቃስ 12፥48 (አዲሱ መ.ት) #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional t.me/hopministry10

10,000 Reasons (Bless the Lord) Song by Matt Redman and Steve "Bless the Lord O my soul O my soul Worship his holy name Sing like never before O my soul I'll worship your holy name The sun comes up It's a new day dawning It's time to sing your song again Whatever may pass and whatever lies before me Let me be singing when the evening comes Bless the Lord O my soul O my soul Worship his holy name Sing like never before O my soul I'll worship your holy name You're rich in love and you're slow to anger Your name is great and your heart is kind For all your goodness I will keep on singing 10, 000 reasons for my heart to find Bless the Lord O my soul O my soul Worship his holy name Sing like never before O my soul I'll worship your holy name Sing like never before O my soul I'll worship your holy name And on that day when my strength is failing The end draws near and my time has come Still my soul will sing your praise unending 10, 000 years and then forever more Bless the Lord O my soul O my soul Worship his holy name Sing like never before O my soul I'll worship your holy name Bless the Lord O my soul O my soul Worship His holy name Sing like never before O my soul I'll worship your holy name O I'll worship your holy name I will worship your holy name Holy name"

Matt_Redman_-_10,000_Reasons__Bless_the_Lord_(128k).m4a4.03 MB

የሰው ልጅ ረሃብን ፈልጎ ሊራብ አይችልም፤ ነገር ግን በውስጡ የጎደለው ነገር ሲኖር እርሱ ቢፈልግም ባይፈልግም የረሃብ ስሜት ይሰማዋል። ረሃብ የአንድን ነገር ጉድለት ያሳያል፣ በሚያስፈልገው ነገር መገኘት የሚሞላ ጉድለትም ነው። ስለዚህ ረሃብ ከውስጥ ነው፣ ከጉድለቱ የተነሣ በውስጥ የሚፈጠር መሻት ነው። እግዚአብሔር እንደሚያስፈልገን ካላወቅን፣ በእርሱ ካልሆነ በቀር በሌላ በምንም የማይረካ ማንነት፣ የማይሞላ ውስጠት እንዳለን ካላወቅን እንዴት እግዚአብሔር ሊርበን ይችላል? ሁሉ ሞልቶ፣ የዕለት ተዕለት ክንውናችን ሳይቋረጥ፣ የምንበላውና የምንጠጣው ነገር ሳናጣ፣ መልበስ ማጌጥ ሳያቅተን፣ ቤታችን ሳይጎድል፣ አሉን በምንላቸውና በምንወዳቸው ሰዎች ተከበን....ሌላም፣ ሌላም ብዙ ነገር.....በአጠቃላይ እንደ ሰው ልማድ ለመኖር አንዳች ሳይጎድልብን ልባችን አላርፍ ካለ፣ ጉድለት ከተሰማን፣ ሁሉ ሞልቶን ሳለ ነገር ግን አንዱም አላረካ ካለን፤ ታዲያ ክፍተታችን የልባችን ሰሪ፣ የሕይወታችን ፈጣሪ ራሱ እግዚአብሔር አይደለም? በምንም የማይተካ #አንድ_ነገራችን፣ #ዋናችን፣ #አሳራፊያችን እግዚአብሔር!!! ሁሉ ጎድሎን በእርሱ ከእኛ ጋር መኖር፣ በእርሱ መገኘት እንረካለን፤ ሁሉን እየጣልን እርሱን ለመያዝ ልባችን ስፍስፍ ይላል፤ ከእርሱ ጋር ለመሆን የማንሰዋው ነገር አይኖርም፤ ለእናንተ ውዱ ነገር፣ ምርጡ ጊዜ የቱ ነው ተብለን ስንጠየቅ የእርሱ እግር ስር መሆን፣ በፊቱ መቆየት ቀዳሚ መልሳችን ይሆናል። ምንም ሳናጣ እግዚአብሔር ይራበን፤ ሁሉ እያለን እርሱ ጉድለታችን ሆኖ ወደ ፊቱ ያሩጠን፤ ሁሉን አጥተንም ፍለጋችን እርሱ ብቻ ይሁን፤ ወደ እርሱ በመገስገሳችን ውስጥ ሊነግሱብን የሚሹና የገዘፉብን ነገሮች ይረሱ፤ የእርሱ ፍቅር፣ የመገኘቱ ረሃብ ብቻ በፊቱ ያክርመን!! ✍️ መክሊት አየለ 📆 July 2, 2024. #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional

4_5931303518848689246.mp319.21 MB

YOHANNES_BELAY_Yednkwane_Tsehay_ዮሐንስ_በላይ_የድንኳኔ_ፀሐይ_New_Video”_2013.m4a4.77 MB

#ኢየሱስ፦ የእኔ ወገግታ፣ የእኔ ፀሐይ። አንተን ተጠግቼ አላፈርኹም፤ በቀረብኹህ ቁጥር በራኽልኝ። የተቀጠቀጠ ሸንበቆ ሳይሰበር፣ የሚጤስ የጧፍ ክርም ሳይጠፋ፣ ተስፋው በአንተ ታድሶ እንደገና በሕይወት ይኖራል። ቸርነትህን የቀመሱ ሁሉ ይወዱኻል፤ ማዳንህን ያዩ ሁሉ እግዚአብሔር ታላቅ ነው ይላሉ። ከአንተ ጋር መወዳጀት እንዴት መታደል ነው?! የማያልቅ፣ የማይደበዝዝ፣ ዘመን የማይሽረው ፍቅር ታስይዛለህ፤ በቀረቡህ ቁጥር ትበራለህ፣ ትብራራለህ፤ የቀመሱህ ሁሉ የአንተ ጥገኛ እንዲሆኑ ፍቅርህን በልባቸው ታፈስሳለህ፤ ኢየሱስ የምትወደድ አምላክ ነህ። አቤቱ በፍቅርህ አሰንብተን፤ ጥገኛህ ሆነን እንድንኖር ከአንተ ጋር አቆየን። ተግተን እንድናመልክህ፣ እንድንከተልህ፣ እንድንኖርልህ፣ እንድናገለግልህ ነፍሳችንን ዘወትር በፊትህ አፍስስልን። በፊትህ ስንቆይ እንበረክታለን፣ እንበዛለን፣ እናተርፋለንና በፊትህ አሰንብተን፤ የአንተ ጉልህ ድምፅ አድርገን። አሜን!! ✍️ መክሊት አየለ 📆 July 1, 2026 #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional

#ኢየሱሴ አቤቱ በፍቅርህ አሰንብተን፤ ጥገኛህ ሆነን እንድንኖር ከአንተ ጋር አቆየን። ተግተን እንድናመልክህ፣ እንድንከተልህ፣ እንድንኖርልህ፣ እንድናገለግልህ ነፍሳችንን ዘወትር በፊትህ አፍስስልን። #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional t.me/hopministry10

4_5922664346751604609.mp36.20 MB

" #We_are_God's_fellow_workers. " ብቻውን ያልተተወ፣ እግዚአብሔር በመስኩ፣ በእርሻው ውስጥ ያሰማራው፣ የእርሻው፣ የሕንጻው ሰራተኛ ያደረገው፣ ከእግዚአብሔር ጋር አብሮ የሚሰራ ሰው ምስጉን ነው። ሰራተኛ አምላክ ደካሞችን አብሮ ሰራተኛ ማድረጉ የእነርሱን ክፍተት ማጉላቱ ሳይሆን ኃይሉን በድካማቸው መግለጡ ነው። እርሱ እየሰራ ያሰራናል፣ እየሰራ እኛን ሰራተኞቹ ያስብለናል። ኃይሉን  በድካማችን እየገለጠ በእግዚአብሔር መንግሥት ውስጥ የሚተጉ ብርቱዎች ያስብለናል። በእግዚአብሔር ቤት ሥራ ላይ እንዳንቀልድ ከሚያደርገን፣ ልባችንንም ከጥፋት ከሚጠብቅ ነገር አንዱ፦ አገልግሎታችን የእኛ አለመሆኑን፤ ይልቁንም በእግዚአብሔር አገልግሎት፣ የሥራ ገበታ፣ መስክ ውስጥ እድል ደርሶን፤ ከእርሱ ጋር አብሮ-ሰራተኛ መሆናችንን ማወቃችን ነው። ይሄን እውነት ስንረዳ፦ መድረኩን፣ መንገዱን፣ ሥራውን፣ ፈቃዳችንን ሁሉ ለእርሱ ለባለቤቱ እየለቀቅን፣ እያስገዛን፣ የእኛ የምንለው አንዳች ሳይኖረን፣ እንደ እርሱ ልብ፣ እንደ አሳቡም ለመሥራት፣ ለማነጽ፣ ለማገልገል እንተጋለን። #ጸሎት፦ እግዚአብሔር ሆይ ዛሬ አንድ ልመና እለምንሃለሁ፦ ልክ እንደ አብሮ-ሰራተኛ፣ ከአንተ ጋር ስራህን እንደሚሰራ ሰው ልባችንን ወደ ፈቃድህ፣ ወደ አሳብህ አዘንብል። የእርሻህ፣ የሕንጻህ ጉዳይ ልክ እንዳንተ፣ አንተ የምታስበውን ያህል ያሳስበን። ለመንግሥትህ ጉዳይ፣ ለቤትህ ሥራ ቸልተኛ፣ ዝንጉ፣ ዳተኛ አንሁን። ልባችን በሸክም ከከበደ ሸክሙ የመንግሥትህ ጉዳይ ይሁንልን!! በሰማይ የታሰበ፣ የታቀደ ያንተ ውጥን በምድር በእኛ ይከወን፣ ፍጻሜውን ያግኝ። እየሰራህ አሰራን፤ በጸጋህ ለመንግሥትህ ስራ እግሮቻችንን አፍጥን፣ ክንዶቻችንንም አበርታ። ስናስብ በእግዚአብሔር ልብ እንዳለ እንደዛ ማሰብ ይሁንልን። አሜን!! “እኛ ከእግዚአብሔር ጋር አብረን የምንሠራ ነንና፤ እናንተም የእግዚአብሔር ዕርሻ ናችሁ፤ የእግዚአብሔር ሕንጻ ናችሁ።”   — 1ኛ ቆሮንቶስ 3፥9 (አዲሱ መ.ት) “For we are God's fellow workers. You are God's field, God's building.” —1 Corinthians 3: 9 (ESV) ✍️ መክሊት አየለ 📆 June 30, 2026 #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional