HOP Ministry
Открыть в Telegram
HOP Ministry — Hear. Obey. Practice. A discipleship platform sharing devotionals, revival histories, spiritual biographies, testimonies, and Amharic Christian literature to build Christ-like lives. Based on Luke 11:28.
БольшеСтрана не указанаКатегория не указана
445
Подписчики
+224 часа
+237 дней
+6630 день
Архив постов
447
ቤተክርስቲያን የፍጹማን፣ ተሰርተው ያለቁ ሰዎች ጉባኤ ብትሆን ኖሮ እግዚአብሔር አገልጋዮችን ባልሾመና ባላበዛ ነበር። የሚሰራ፣ የሚታነጽ ብዙ ሕይወት ይጠብቀናል።
447
#በድካማችን_የሚራራልን_ሊቀካህናት_ኢየሱስ።
የሰው ድካም ብርቱ ነኝ ባዩን ሰው ራሱን ከደካማው ሰው ጋር አነጻጽሮ በራሱ እንዲኮራ፣ እንዲመካ፣ ደካማውን እንዲንቀው ሲያደርገው፤ በራሱ፣ ጻድቅ በመሆኑ፣ ኃጢአትን ባለማድረጉ ሊመካ የተገባውን በሰማያት በግርማው ቀኝ የተቀመጠው ታላቁ ሊቀ ካህናት ኢየሱስ ግን ለደካማው በድካሙ ይራራለታል።
ሰው ሆኖ ከኃጢአት በቀር ሰው የሚያልፍበትን መንገድ፣ የሚደርስበትን ነገር ሁሉ ስላየው ይረዳዋል፣ ይረዳዋል ( ይረዳዋል፦ ሲጠብቅም፣ ሲላላም)።
የዚህን ሊቀ ካህናት ታላቅነት አስቤ በታላቅነቱ ስደነቅ ለደካማው የሚራራ ልቡ፣ የወደቁትን ለማንሳት ፈጥኖ የሚዘረጋው እጁ ደግሞ ሌላው ድንቅ የጥልቅና የፍጹም ፍቅሩ ማሳያ ሆነብኝ።
ክብር ለሊቀ ካህናችን ይሁን!!
#ይራራልናል!
ዕብራውያን 4 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁴ እንግዲህ ወደ ሰማያት ያረገ ታላቅ ሊቀ ካህናት የእግዚአብሔር ልጅ ኢየሱስ ስላለን፣ እምነታችንን አጥብቀን እንያዝ።
¹⁵ በድካማችን የማይራራልን ሊቀ ካህናት የለንምና፤ ነገር ግን እንደ እኛ በማንኛውም ነገር የተፈተነ ሊቀ ካህናት አለን፤ ይሁን እንጂ ምንም ኀጢአት አልሠራም።
¹⁶ እንግዲህ ምሕረትን እንድንቀበልና በሚያስፈልገንም ጊዜ የሚረዳንን ጸጋ እንድናገኝ፣ ወደ ጸጋው ዙፋን በእምነት እንቅረብ።
✍️ መክሊት አየለ
📆 March 23, 2025
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
447
“እንግዲህ እነዚህን የሚያህሉ ምስክሮች እንደ ደመና በዙሪያችን ካሉልን፥ እኛ ደግሞ ሸክምን ሁሉ ቶሎም የሚከበንን ኃጢአት አስወግደን፥ የእምነታችንንም ራስና ፈጻሚውን ኢየሱስን ተመልክተን፥ በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግሥት እንሩጥ፤ እርሱ ነውርን ንቆ በፊቱም ስላለው ደስታ በመስቀል ታግሦ በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ ተቀምጦአልና።”
— ዕብራውያን 12፥1-2
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
#LookingtoJesus
447
ብልኽ የኢየሱስ ተከታዮች፦ ተልከው የመጡበትን ዓላማ ሳይዘነጉ፣ አይናቸውን ጉዳያቸው ላይ እንደተከሉ፣ ትኩረታቸው በባዕዳን ሳይቀማና ሳይደበዝዝ ከግብ ይደርሳሉ።
447
#ጉዳዩ ኢየሱስ ብቻ የሆነ ሰው፤ ከእርሱ ሌላ ነገር ማየት፣ ማሰብ፣ መስማት፣ ማውራት ያቃተው እንዴት የታደለ ነው?!
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
t.me/hopministry10
447
" #አይኔን_ጉዳዬ_ላይ_ማድረግ! "
#ጉዳዩ ኢየሱስ ብቻ የሆነ ሰው፤ ከእርሱ ሌላ ነገር ማየት፣ ማሰብ፣ መስማት፣ ማውራት ያቃተው እንዴት የታደለ ነው?!
በዚህ ቢሉት በዚያ ልቡንና አሳቡን ከተከለበት ከአምላኩ ውልፍት የማይል፣ ብዙ ነገሮች አባብለው ከትኩረቱ ሊወስዱት ቢጥሩ እንኳን ዞሮ አይኑን ወደ ተከለበት መነሻው የሚመለስ፣ ከእግዚአብሔር ውጪ ርዕስ ያጣ ሰው እንዴት የታደለ ነው?!
ይሄንን እያሰላሰልኩ አንድ ነገር ትዝ አለኝ፦ ልጆች እያለን ወላጆቻችን ሱቅ አልያም ሌላ ቦታ ሲልኩን ለመሄድ ከመውጣታችን በፊት የሚሰጠን አንድ ማስጠንቀቂያ ነበር፤ "የላኩሽ ቦታ እስክትደርሺ ድረስ በየመንገዱ እንዳትቆሚ፣ ማንም ቢያናግርሽ መልስ እንዳትሰጪ፣ ቆመሽ ወሬ እንዳታዪ፣ እንዳትጫወቺ.....ወደ ተላክሽበት ቦታ ቀጥ ብለሽ ሄደሽ በፍጥነት ተመለሺ" እነዚህ እና እነዚህን የመሳሰሉት ዛቻ የተቀላቀለባቸው ጥብቅ ማስጠንቀቂያዎች ዓላማቸው ከተላክንበት ስፍራ፣ ተልከን ከወጣንበት ጉዳይ ላይ አይናችንን ሳንነቅል፣ በሌላ በምንም ነገር ትኩረታችን ሳይወሰድ፣ ከቤት የወጣንበትን ዓላማ ዘንግተን በመንገድ ላይ እንዳንባዝንና እንዳንባክን ነው።
በዚህ ምሳሌ ውስጥ እኛን እና በዚህ ዘመን ያለንበትን ሁኔታ አስገብቼ ስገመግም አንዳንዴ እንዲሁም አብዛኛውን ጊዜ፣ አብዛኞቻችን አተኩረን ልናይ የተገባንን ነገር፣ ተልከን የወጣንበትን ዓላማ ዝንግት አድርገን፦ በየፌርማታው እየቆምን ሕይወት የሌለበትን፣ የማያሰነብተንን፣ የማያሳድገንን፣ የማይጠቅመንን ወሬ ማየት፤ በጠፊ በአላፊው ነገር መደነቅና መወሰድ፤ ጠልፎ በሚጥለን፣ አንቆ እንዳናፈራ በሚያደርገን፣ በመንገድ በሚያስቀረን የማይመች አካሄድ መጠመድ፤ ከግብ ሳይደርሱ እንደወጡ ለመቅረት መጣደፍ ስራችን ሆኗል።
ብልሆቹ ግን ተልከው የመጡበትን ዓላማ ሳይዘነጉ አይናቸውን ጉዳያቸው ላይ እንደተከሉ፣ ትኩረታቸው በባዕዳን ሳይቀማና ሳይደበዝዝ ከግብ ይደርሳሉ።
ጌታ እግዚአብሔር የልቦና አይኖቻችንን ያብራልን፤ ማተኮር የተገባን ነገር ላይ አይኖቻችንን ተክለን ዘመናችን እንዲጠቀለል ይርዳን!!
✍️ መክሊት አየለ
📆 February 25, 2025
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
447
" #ከእግዚአብሔር_ጋር_ያለ_ሰው_ድፍረት"
በጨለማ አግኝተኸኝ ለጨለማው ስላልተውኸኝ፣ ታካች ነፍሴን ስላበረታኽ፣ በሕይወት መንገድ ስለመራኸኝ፣ እግዚአብሔር ብርሃኔና መድኃኒቴ ስለሆንኸኝ ከልቤ አመሰግናለሁ።
ከእግዚአብሔር ጋር ያለ ሰው ድፍረት ወደ ራሱ፣ ወደ ሰዎች፣ ወደ ቁስ አያመለክትም፤ ነገር ግን
ከእግዚአብሔር ጋር ያለ ሰው ድፍረት ይህ ነው፦
“እግዚአብሔር ብርሃኔና መድኅኔ ነው፤ የሚያስፈራኝ ማን ነው? እግዚአብሔር ለሕይወቴ ዐምባዋ ነው፤ ማንን እፈራለሁ?”
— መዝሙር 27፥1 (አዲሱ መ.ት)
ከእግዚአብሔር ጋር ያለ ሰው ድፍረት፦ በጨለማው ላይ ብርሃኑን እግዚአብሔርን እያበራ፣ የሕይወት ዐምባውን ታምኖ፣ በብርሃን፣ በሕይወት ይኖራል።
ቅዱሱ መጽሐፍ እንዴት ድንቅ ነው?! "ከእግዚአብሔር ጋር ያለ ሰው ድፍረት" ብሎ ወደ ሰው ልጆች ኃይል ወይም በሰው አይን መመኪያ ወደ ተባሉ ቁሶች አይጠቁምም፤ ይልቁንም የሁሉ ምንጭ፣ የሁሉ ፈጣሪ የሆነውን እግዚአብሔርን፦
“እግዚአብሔር ብርሃኔና መድኅኔ ነው፤ የሚያስፈራኝ ማን ነው? እግዚአብሔር ለሕይወቴ ዐምባዋ ነው፤ ማንን እፈራለሁ?”
— መዝሙር 27፥1 (አዲሱ መ.ት)
ሲል አድምቆ ያሳየናል።
ከእግዚአብሔር ጋር ያለ ሰው ድፍረት ልባችንን ይሙላው፣ ይክበበን፤ ሞገስ፣ ትምክህትም ይሁነን!!
✍️ መክሊት አየለ
📆 June 8, 2026
#HOPMinistry #DailyDevotional
#TheLORDismylight #TheLORDismysalvation
447
#ምድር_ትሞቃለች_ግን_የዘላለም_ቤት_አትሆንም!
ሰማይን የሰነቀ፣ መዝገቡን በዚያ የሰወረ ልብ ያለው ሰው ምን ፈዝዞ ከምድሩ ነገር ጋር ቢዛመድ አንድ ቀን ማብቂያ እንዳለው፣ የተሻለ ተስፋ እንዳለው ያውቃል፣ ያስባል።
እግዜሩ በዚህ ዘመን የዘላለም አጀንዳውን ለጠፋው የሰው ልጅ ለመግለጥ፣ ሹክ ለማለት አንደበት ሊሆኑት በብርሃን ያሉትን፣ የዳኑትን ልጆቹን ይጠቀማል፤ ይጠብቃል። መልዕክተኛ ብሎ፣ አድርጎም ሾሟቸዋልና አንደበታቸው የሰማዩን ዜና እንዲያበስር፣ ሕይወታቸውም እርሱን እንዲሰብክ፣ የክርስቶስ ግልጽ ደብዳቤ እንዲሆን ይጠብቃል።
ዛሬ በጌታ ፊት ሆኜ ስለፈቃዱ ለመጸለይ፣ የመንፈስ ቅዱስንም አሳብ ለማድመጥ ስሞክር ሕይወቴ ውስጥ ያለ ትልቅ ክፍተት ታየኝ። ራሴን ሳይ፦ ምድር የተመቸኝ፣ የሞቀኝም እንመስላለኹ። የእግዚአብሔር መንግሥት ጉዳይ፣ የነፍሳት መዳን ብዙም ልቤ ላይ ከብዶ ሲከነክነኝ አላይም።
በፊት በፊት በቀን ውሎዬ ድንገት ምን እንደነካኝ ሳላውቅ ኢየሱስ የሞተላቸው ብዙዎች ገና በጨለማ እንዳሉ አስብና ማልቀስ እፈልጋለሁ፤ አንዳንዴም እንደ ሰው ልማድ ወንጌል ለመመስከር "ይሄ ትክክለኛው ቦታ አይደለም" የሚባል ስፍራ እንኳ ቢሆን የእሳት ፍም የተጨመረበት ይመስል ልቤ ስለሚቃጠል፣ ተንፍሺ እያለ የሚተናነቀኝ አንዳች ነገር ስላለ፤ ጨከን ብዬ ኢየሱስ ይወድሃል/ ይወድሻል ለማለት ድፍረቱ ነበረኝ።
የስራ ሁኔታዬ የተለያዩ ሰዎችን፣ ከትንሽ እስከ ትልቅ፣ የተለያየ ሁኔታና ደረጃ ላይ ያሉ ሰዎችን አገናኝቶኝ ስለሚያውቅ ምነው እነዚህ ሁሉ ሰዎች ጌታ ኢየሱስን ቢያውቁት ብዬ አስባለሁ፤ ደግሞ የመናገር፣ የማስተማር፣ የማሰልጠን እድሉን ሳገኝ የዕለቱ አበይት ርዕሰ ጉዳይ ሌላ ቢሆን እንኳን በዚህም በዚያም ብዬ፣ ነገሩን ጠምዝዤ የሕይወትን ትርጉም እንዲያስቡ፣ ራሳቸውንና ያሉበትን ሁኔታ እንዲመረምሩ፣ ዓላማ እንዲኖራቸው ለማድረግና የእግዚአብሔር መንግሥት፣ የዘላለም ሕይወት የሚባል ነገር እንዳለ ጠቆም አድርጌ ለማለፍ ሞክራለሁ።
አሁን ግን የምገባ፣ የምወጣ፣ የምሰራ፣ የምማር፣ በስራ ገበታዬ፣ በቀን ውሎዬ ከተለያዩ ሰዎች ጋር የምገናኝ ብሆንም ያ የጠፉትን ለመፈለግ የተከፈተው አይኔ፣ የነፍሳት መዳን ጉዳይ ረሃቡ የሆነው ልቤ በእኔ ውስጥ ኮስሷል። ምድር ሞቃኝ ተደላድዬ ለመኖር ብዙ እቅድ አቅዳለሁ።
ከዚህ ሁሉ ብክነት እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ቆም! እንድል ስለረዳኝ አመሰግነዋለሁ። እኔማ በፊቱ መንበርከኬና ልሰማው መጠጋቴ ሕይወቴን ስራው፣ ቀይረኝ ከሚለው ራስ ተኮር ጸሎቴ እልፍ ያለ አልነበረም። እርሱ ከልብ ለሚሹት መገኘት፣ ለመሰራት ፈቅደው የተጠጉትን ማበጃጀት መች ተስኖት፤ ባልጠይቀውም ላይተወኝ፣ ሊሰራኝ የታመነ ነው።
ነገር ግን የኔን ነገር ገታ አደረገና፤ ስለ ዘመኑ ማለቅ፣ ስለ ብዙዎች አሁንም በጨለማና በእስራት ውስጥ መኖር እንዳስብ አደረገኝ። ሳላስብ ማልቀስ ጀመርኹ፤ ከልቤ የተወሰደው ስለ ሌሎች የነበረ ሸክሜ ትዝ አለኝ፤ በዙሪያዬ፣ ደግሞም በመላው ዓለም ብዙ ያልዳኑ ሰዎች እንዳሉ እንዳስብ አደረገኝ።
የእግዚአብሔር አምሳል የሆነውን የክርስቶስ፣ የክብሩን ወንጌል ብርሃን እንዳያዩ፣ የዚህ ዓለም አምላክ የማያምኑትን ሰዎች ልቡና እንዳሳወረ ሁሉ የእኛ ልቡናም በጠፊ በአላፊው ፍቅር ተነድፎ፣ ምድር ሞቅ ብላን፣ ሁሌ የምንኖርባት እስኪመስለን ድረስ ተደላድለን እንድንቀመጥ፣ ወንጌላችን የተከደነ እንዲሆን አዚም ያደረገብን ነገር እንዳለ አሰብኹ።
ይኼንን ጽሁፍ ስጽፍ፦ የሚያነቡትን ሰዎች ሁሉ እኔን ያነቃ መንፈስ ቅዱስ እንዲያነቃቸው፣ እኔን እንደሞገተ እና ቆም ብዬ እንዳስብ እንዳደረገኝ ሁሉ ልባቸውን እንዲሞግት በማሰብ ነው።
በመጨረሻም በርዕሱ ላይ እንዳልኹት ደግሜ፦ #ምድር_ትሞቃለች_ግን_የዘላለም_ቤት_አትሆንም! እላለሁ። በተለይ ለእኛ ለአማኞች ምድር የጥቂት ጊዜ የስራ ቦታ፣ የአገልግሎት መስካችን ነች። ለመከሩ ከሚያስፈልጉት ሰራተኞች መካከል አንዱ ነን።
በአንድ ወይም በሌላ መንገድ፣ በእኛ ሁኔታ የሚሰበክ ወንጌል፣ የሚገለጥና የሚታይ ኢየሱስ፣ የሚድኑ እልፍ ሰዎች አሉና ጌታ እግዚአብሔር እንደገና የመንግሥቱን አሳብ በልባችን ይሙላ፣ ለሥራው የታጠቁ ያድርገን፣ ልባችን፣ አንደበታችን፣ እጃችን ለመንግሥቱ ወንጌል ሁነኛ መሳሪያ ይሁን እላለሁ።
ጸጋ ይብዛልን፤ መንፈስ ቅዱስ ያግዘን!!
✍️ መክሊት አየለ
📆 June 8, 2026
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional #Gospel #JesusSaves
447
#የእናቴ_ምክር
ከዕለታት በአንዱ ቀን ከየዋህዋና የልብ ጓደኛዬ ከሆነችው እናቴ ጋር እንደተለመደው ስለማልፍበት መንገድ፣ ስለገጠሙኝ ነገሮች እየተጨዋወትን እውነት መስሎኝ እውነት ሳይሆን ስለቀረው፣ ሞኝ መስዬ ስለታየኋቸው ጥበብ ባልሆነ መንገድ ጠቢብ ለመሆን እየጣሩ ሊያታልሉኝ ስለሞከሩት ሞኞች፣ ስለ ሰው ልጅ የልብ ክፋት ዘረዘርኩና "ብቻ ይሁን! እግዜር ይጠብቀኝ!" ብዬ ነገሬን ለመቋጨት ስሞክር....ነገሩን ገና ከአፌ ሳልጨርሰው ከአፌ ቀበለ አድርጋ...."አረ ተይ አንቺ ልጅ አሁንስ አበዛሽው! ከስህተትሽ ተማሪ! ራስን ጠብቆ ነው እግዜር ይጠብቀኝ ማለት። እግዜር የስንቶቻችንን ሸክም ተሸክሞ፣ ስንቶቻችንን ጠብቆ ይችለዋል? የሁላችንም ሸክም እንደሆነ እርሱ ላይ ነው ያለው። ለእርሱም እዘኚለት፤ እራስሽን እርጂ እርሱም ይረዳሻል!" አለችኝ።
በወቅቱ ንግግሯ ከልብ ነው ያሳቀኝ😅 በተለይ ለእግዜር ያሳየችው ርህራሄና አዘኔታ ደግሞ ምስኪንነቷን አሳይቶኛል። ከእናቴ ጋር በምናሳልፈው ጊዜ ከቁም ነገሩና ከልብ ወጉ ባለፈ እንዲህ አይነት ሳቅን የሚያጭሩ ጨዋታዎች የተለመዱ ስለሆኑ እንደተለመደው የልቤን ተንፍሼ፣ ምክሯን ሰንቄ፣ ስቄ ቀኑ አለፈ።
ዛሬ ግን ጌታን ካወቅሁበት ቀን ጀምሮ እርሱ ተሸክሞ ያሳለፈኝን ልዩ ልዩ መንገዶች መለስ ብዬ እየቃኘኋቸው ሳለሁ ድንገት ያ የእናቴ ምክር ትዝ አለኝ። ጌታን መጠበቅ አቅቶኝ ከእቅፉ ለመውጣት እየተጣደፍኩ ስታገለው ሲታገሰኝ፣ እምነት ያለኝ መስሎኝ እየጠበቅሁት ነው ብዬ ስታበይ እርሱ ግን ከብዙ ጥፋት እየጠበቀኝ እንደሆነ ሲያስተምረኝ፤ ቆይ እስቲ እርሱ ይዘገያልና በራሴ ነገሬን አፈጣጥኜ ልጨርስ ብዬ ከገባሁበት ማጥ እቅፍ፣ ድግፍ አድርጎ ሲያወጣኝ፣ በመውጣትም ሆነ በመውረዴ ውስጥ ከትከሻው ላይ ሳያወርደኝ፣ የሚያስጨንቀኝንም ሁሉ በእርሱ ላይ ለመጣል በርትቼ ሳራግፍበት ሸክሜን ሁሉ ተሸክሞ፣ እጄን እንደያዘኝ ዛሬ ላይ መድረሴን አስተዋልኹ።
ታዲያ ይሄን ወረት የማያውቀውን፣ እስከ ሽበት፣ እስከ ሽምግልና የሚሸከመውን ደግ አባት እናቴ እንዳለችው #የሁላችንም_ሸክም_በዝቶ_ያደክመው_ይሆን?
አንዳንዶቻችንስ ከልክ በላይ አስቸጋሪና አልታዘዝ ባዮች ስለሆንን የእናንተ ነገርስ አቅቶኛል በሉ ከትከሻዬ ውረዱ! ይለን ይሆን? በእያንዳንዳችን ላይ ያለመታከት አይኖቹን ማሳረፉና እንደ አይኑ ብሌን ለእኛ መጠንቀቁስ ያሰለቸው ይሆን?
መልሱን ለእናንተ ልተወውና ዘማሪው እንዳለው፦
"ይሸከማል፣ ይሸከማል፣....ይሸከማል ወረት የለበት!" ብዬ ነገሬን ልቋጭ።
✍️ መክሊት አየለ
📆 December 9, 2025
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
447
የማርታ ችግር ኢየሱስን ወደ ቤቷ አለመቀበል፣ ቤቷ እንዳለም አለማወቅ አልነበረም። ነገር ግን በደስታ ተቀብላ ወደ ቤቷ አስገብታው ከእርሱ ጋር ከመቀመጥ ይልቅ እርሱን ደስ የሚያሰኘውን ነገር ፍለጋ ትታው ወጥታለች፤ እዚህ ጋር የእሷ ሀሳብና የእርሱ ሀሳብ ተላልፈዋል፤ እርሱ ቤቷ ለተገኘው ለእርሱ በሙሉ ማንነቷ፤ ራሷን፣ ትኩረቷን፣ ጊዜዋን ሰጥታ እንድትገኝ ፈልጓል፤ እርሷ ደግሞ እርሱን የሚያስደስት ሌላ ነገር ፍለጋ ወጥታለች። ማርታ ወዲህ ወዲያ ትላለች፣ አልተቀመጠችም፤ ነገር ግን ይህ ሁኔታዋ ለኢየሱስ ብክነት ሆኖ ታየው እንጂ ልቡን አላሳረፈም።
ከኢየሱስ ጋር መቀመጥ፣ መቆየት፣ ሊገኝልን ወዶ ሲገኝልን ለእርሱ መገኘትና በፊቱ ማረፍ ጥቂት ወይም አንድ ነገር ነው፤ ነገር ግን ከእልፍ አገልግሎት፣ ሩጫ ይበልጣል፤ ትርፉም እጅግ ብዙ ነው። የሚያስፈልገውን አንዱን በመያዝ ብዙ ማረፍ፣ ብዙ ማትረፍ፣ የማይወሰደውን መልካም ዕድል በመምረጥ ከከንቱ ድካምና ከብክነት መጠበቅ ይሁንልን!!
ሉቃስ 10
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
³⁸ ሲሄዱም እርሱ ወደ አንዲት መንደር ገባ፤ ማርታ የተባለች አንዲት ሴትም በቤትዋ ተቀበለችው።
³⁹ ለእርስዋም ማርያም የምትባል እኅት ነበረቻት፥ እርስዋም ደግሞ ቃሉን ልትሰማ በኢየሱስ እግር አጠገብ ተቀምጣ ነበረች።
⁴⁰ ማርታ ግን አገልግሎት ስለ በዛባት ባከነች፤ ቀርባም፦ ጌታ ሆይ፥ እኔ እንድሠራ እኅቴ ብቻዬን ስትተወኝ አይገድህምን? እንኪያስ እንድታግዘኝ ንገራት አለችው።
⁴¹ ኢየሱስም መልሶ፦ ማርታ፥ ማርታ፥ በብዙ ነገር ትጨነቂአለሽ ትታወኪማለሽ፥
⁴² የሚያስፈልገው ግን ጥቂት ወይም አንድ ነገር ነው፤ ማርያምም መልካም ዕድልን መርጣለች ከእርስዋም አይወሰድባትም አላት።
✍️ መክሊት አየለ
📆 January 10, 2024
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
📍 Telegram Channel: https://t.me/hopministry10
447
ፍለጋው ለጥቅሙ ሳይሆን ለጥቅማችን፤ ሊኖርበት ሳይሆን እኛ ልንኖርበት፤ ሕይወት ይሆንልን ዘንድ፣ በሕይወትም እንድንኖር እንደሆነ ገብቶን ቸሩን ጌታ እንከተለው፣ እንከታተለው። በፍለጋችን ውስጥ የቀመስነው ቸርነቱ እልፍ ረሃብ ወልዶ በፊቱ ያሰንብተን፤ ያለ እርሱ የማይኖሩ ጥገኞቹ ያድርገን።
✍️ መክሊት አየለ
📆 June 6, 2026
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
t.me/hopministry10
