HOP Ministry
前往频道在 Telegram
HOP Ministry — Hear. Obey. Practice. A discipleship platform sharing devotionals, revival histories, spiritual biographies, testimonies, and Amharic Christian literature to build Christ-like lives. Based on Luke 11:28.
显示更多未指定国家未指定类别
560
订阅者
+324 小时
+217 天
+5530 天
帖子存档
560
2ኛ ቆሮንቶስ 5 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁸ ይህ ሁሉ ከእግዚአብሔር ነው፤ እርሱ በክርስቶስ አማካይነት ከራሱ ጋር አስታረቀን፤ የማስታረቅንም አገልግሎት ሰጠን፤
¹⁹ እግዚአብሔር በክርስቶስ ዓለምን ከራሱ ጋር ሲያስታርቅ የሰዎችን በደል አይቈጥርባቸውም ነበር፤ ለእኛም ደግሞ የማስታረቅ ቃል ሰጠን።
²⁰ ስለዚህ እኛ የክርስቶስ እንደራሴዎች ነን፤ እግዚአብሔርም በእኛ አማካይነት ጥሪውን ያቀርባል፤ እኛም ከእግዚአብሔር ጋር ታረቁ ብለን በክርስቶስ እንለምናችኋለን።
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
560
#የክርስቶስ_ግልጽ_ደብዳቤ
2ኛ ቆሮንቶስ 3 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ እንደ ገና ራሳችንን ልናመሰግን እንጀምራለንን? ወይስ እንደ ሌሎቹ ለእናንተ ወይም ከእናንተ የተጻፈ የምስጋና ደብዳቤ ያስፈልገን ይሆንን?
² እናንተኮ ሰው ሁሉ የሚያውቃችሁና የሚያነባችሁ በልባችን ላይ የተጻፋችሁ ደብዳቤዎቻችን ናችሁ፤
³ እናንተ በቀለም ሳይሆን በሕያው እግዚአብሔር መንፈስ፣ በድንጋይ ጽላት ላይ ሳይሆን በሰው ልብ ጽላት ላይ የተጻፋችሁና በእኛ የተገለገላችሁ የክርስቶስ ግልጽ ደብዳቤ ናችሁ።
2 Corinthians 3: 3 (ESV)
"And you show that you are a letter from Christ delivered by us, written not with ink but with the Spirit of the living God, not on tablets of stone but on tablets of human hearts."
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
560
1ኛ ዮሐንስ 5 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹³ በእግዚአብሔር ልጅ ስም የምታምኑ እናንተ፣ የዘላለም ሕይወት እንዳላችሁ ታውቁ ዘንድ ይህን እጽፍላችኋለሁ፤
¹⁴ በእግዚአብሔር ፊት ለመቅረብ ያለን ድፍረት ይህ ነው፤ ማንኛውንም ነገር እንደ ፈቃዱ ብንለምን እርሱ ይሰማናል፤
¹⁵ የምንለምነውን ሁሉ እንደሚሰማን ካወቅን፣ የለመነውንም ነገር እንደ ተቀበልን እናውቃለን።
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
560
“በእግዚአብሔር ፊት ለመቅረብ ያለን ድፍረት ይህ ነው፤ ማንኛውንም ነገር እንደ ፈቃዱ ብንለምን እርሱ ይሰማናል፤”
— 1ኛ ዮሐንስ 5፥14 (አዲሱ መ.ት)
https://t.me/hopministry10
560
“በመንገድህ ሁሉ እርሱን ዕወቅ፤ እርሱም ጐዳናህን ቀና ያደርገዋል።”
— ምሳሌ 3፥6 (አዲሱ መ.ት)
"In all your ways acknowledge him, and he will make straight your paths."
— Proverbs 3: 6 (ESV)
560
ዘጸአት 13 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹⁷ ፈርዖን ሕዝቡን በለቀቀ ጊዜ አቋራጭ ቢሆንም እንኳ እግዚአብሔር (ኤሎሂም) በፍልስጥኤም ምድር በሚያልፈው መንገድ አልመራቸውም “ጦርነት ቢያጋጥማቸው ሐሳባቸውን ለውጠው ወደ ግብፅ ይመለሱ ይሆናል” ብሎአልና።
¹⁸ ስለዚህ እግዚአብሔር (ኤሎሂም) ሕዝቡን ዙሪያ በሆነው በምድረ በዳው መንገድ ወደ ቀይ ባሕር መራቸው፤ እስራኤላውያንም ለጦርነት ዝግጁ ሆነው ከግብፅ ወጡ።
¹⁹ ዮሴፍ፤ እግዚአብሔር (ኤሎሂም) በእርግጥ ይጐበኛችኋል፤ በዚያን ጊዜም ዐፅሜን ይዛችሁ ከዚች ምድር መውጣት አለባችሁ ብሎ የእስራኤልን ልጆች አስምሎአቸው ስለ ነበር ሙሴ የዮሴፍን ዐፅም ይዞ ወጣ። እግዚአብሔር (ኤሎሂም) ሕዝቡን ዙሪያ በሆነው በምድረ በዳው መንገድ ወደ ቀይ ባህር መራቸው፤ እስራኤላውያንም ለጦርነት ዝግጁ ሆነው ከግብፅ ወጡ።
²⁰ እነርሱም ከሱኮት ከተነሡ በኋላ ከምድረ በዳው ጥግ ባለው በኤታም ሰፈሩ።
²¹ ስለዚህ በቀንም ሆነ በሌሊት መጓዝ ይችሉ ዘንድ፣ እግዚአብሔር (ያህዌ) በቀን በመንገዳቸው ሊመራቸው በደመና ዓምድ፣ በሌሊት ደግሞ ብርሃን ሊሰጣቸው በእሳት ዓምድ በፊታቸው ይሄድ ነበር።
²² በቀንም ሆነ በሌሊት የደመናውና የእሳቱ ዓምድ ከሕዝቡ ፊት የተለየበት ጊዜ አልነበረም።
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
560
በፀሎት የሚፈለገው፣ የሚገኘውም ሕያው አምላክ እንደሆነ ሲገባን፦ ፍለጋችን፣ ናፍቆታችን፣ ወደ እርሱ መገስገሳችን፣ ረሃባችን ያለ ማቋረጥ ይሆናል።
https://t.me/hopministry10
560
#እግዚአብሔርን_መውደድ፤ #ፀሎትን_መውደድ
በምድር እስካለን ድረስ እግዚአብሔርን ከምናይባቸውና ከምናገኝባቸው መንገዶች አንዱ ፀሎት ነው።
ከእግዚአብሔር ከራሱ ፍቅር ሲይዘን ፀሎትን መውደድ እንችላለን። እግዚአብሔርን ለማግኘት ስንል በፊቱ እንሆናለን፤ እርሱ እንዲገኝልን አብዝተን እንሻዋለን።
በፀሎት እግዚአብሔር እንደሚገኝ፣ ፀሎት የእግዚአብሔር መገኛ እንደሆነ ሲገባን፦ ፀሎት ለእኛ መሰረታዊ ነገር ይሆናል።
ያስፈልገናል ስጠን ብለን እግዚአብሔር ፊት ከምንቀርበው ጥያቄ በላይ፤ ሰጪው፣ የጥያቄያችን መላሽ ራሱ እግዚአብሔር ተፈላጊ ይሆንልናል።
ፀሎት ራበኝ፣ ውስጤ መጸለይ ፈለገ፣ ፀሎት ናፈቀኝ ማለት መቻል፤ እንዳሉትም መሆን እንዴት መታደል ነው?! ይሄኮ በእግዚአብሔር ከተነካ ማንነት ውጪ በማንም ሊሆን አይችልም።
እግዚአብሔር ናፈቀኝ፣ ህልውናው ናፈቀኝ ብሎ ወደ ፀሎት ጥድፍ ማለት የእግዚአብሔር ረሃብ ከበዛለት ሰው ዘንድ እንጂ ከወዴት ይገኛል?!
ፀሎት የእግዚአብሔርን አብሮነት፣ መገኘት የምናጣጥምበት መነካካት፣ ስፍራ ካልሆነ፦ ስራ፣ ሸክም ይሆናል፤ ሥጋንም ያዝላል፤ ለነፍስም ጠብ የሚል ነገር አይገኝበትም።
ፀሎት በእግዚአብሔር ህልውና ሲሞላ፣ በመንፈስ ቅዱስ ሲሆን ግን ትቶ ለመውጣት የሚያሳሳ ስፍራ፣ ከራቁበትም እያጣደፈ የሚያመጣ ረሃብ ይሆናል።
በፀሎት የሚፈለገው፣ የሚገኘውም ሕያው አምላክ እንደሆነ ሲገባን፦ ፍለጋችን፣ ናፍቆታችን፣ ወደ እርሱ መገስገሳችን፣ ረሃባችን ያለ ማቋረጥ ይሆናል።
መዝሙር 42 (አዲሱ መ.ት)
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ ዋላ የምንጭ ውሃ እንደምትናፍቅ፣ አምላክ ሆይ፤ ነፍሴም እንዲሁ አንተን ትናፍቃለች።
² ነፍሴ አምላክን፣ ሕያው አምላክን ተጠማች፤ መቼ ደርሼ ነው የአምላክን ፊት የማየው?
✍️ መክሊት አየለ
📆 August 1, 2026
#HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional
560
🕯️📖 A hidden story. A timeless faith. A life-changing journey. ✨
Welcome to HOP Ministry’s HOP Reads 📚🌿
Begin reading “The Martyr of the Catacombs” and discover a powerful story of courage, sacrifice, and unwavering faith that still speaks today. 🔥
📚 Your reading journey starts here👇
🔗 https://t.me/hopministry10
✨ HOP Ministry
HOP Reads — Hear. Obey. Practice.
560
🎧📚 Something exciting is coming!
HOP Reads is about to begin! Join us as we start our first reading journey with The Martyr of the Catacombs. 🕯️✨
▶️ Listen to the invitation and join us!
📍 https://t.me/hopministry10
🌿 HOP Ministry | HOP Reads — Hear. Obey. Practice.
560
📚✨ HOP Reads is here! ✨📚
Our first reading journey begins with “The Martyr of the Catacombs” 🕯️📖
A powerful story of faith, courage, and sacrifice — reminding us that true devotion is revealed not only in comfort, but also in times of challenge and persecution.
Join us as we open this book together, reflect on its lessons, and discover how stories of faith can shape our lives today. ✨
📖 One book. One journey. One community growing together.
✨ HOP Reads — Hear. Obey. Practice.
Join our platforms and be part of the journey:
📍 Facebook Page: https://www.facebook.com/hopministry10
📍 Telegram Channel: https://t.me/hopministry10
📍 TikTok: @hopministry
#HOPReads #TheMartyrOfTheCatacombs #FaithJourney #ChristianReading #GrowingInFaith #HearObeyPractice
