ch
Feedback
HOP Ministry

HOP Ministry

前往频道在 Telegram

HOP Ministry — Hear. Obey. Practice. A discipleship platform sharing devotionals, revival histories, spiritual biographies, testimonies, and Amharic Christian literature to build Christ-like lives. Based on Luke 11:28.

显示更多
未指定国家未指定类别
445
订阅者
+224 小时
+237
+6630
帖子存档
#የዝናብ_ልብስ! #በመነካት_ከውስጥ_ሰውነት_የሆነ_ክርስትና! የዝናብ ልብስ ስሪቱ በላዩ ላይ የሚወርደውን ውኃ ወደ ውስጥ እንዳያሳልፍ ተደርጎ ነው። የውስጠኛው የሰውነታችን ክፍል በልብሱ ተሸፍኗልና ከዝናቡ ጋር የመነካካት እደሉ በጣም ጠባብ ነው። ከላይ የሚዘንበው ውኃ ኩልል እያለ ወደ መሬት ይወርዳል እንጂ ወደ ውስጥ አይዘልቅም። ይሄን ምሳሌ የተጠቀምኹት ስለ ዝናብ ልብስ ላወራ ፈልጌ ሳይሆን በዚህ ሂደት ውስጥ ከምናየው ነገር ለመንፈሳዊ ሕይወታችን የሚጠቅምን ትምህርት ለመቅሰም ነው። በክርስትናችን መነካት (የውስጥ ሰውታችን በእግዚአብሔር ቃል፣ በመንፈስ ቅዱስ መነካት) ቁልፍ ነገር ነው። የውስጥ ሰውነታችን በእግዚአብሔር ካልተነካ መንፈሳዊ የሆነውን ነገር ሁሉ ለምደን ከማድረግ አንቆጠብም፤ ነገር ግን ክርስትናችን የልማድ ነው። የቤተክርስቲያን መደበኛ ፕሮግራሞችን ያለማቋረጥ እንሳተፋለን፣ መዝሙር ስለምናውቅ እንዘምራለን፣ ትምህርቶች እንማራለን፣ ስብከት እንሰማለን፣ እድል ከቀናን ደግሞ እኛ ራሳችን ሰባኪዎችም ነን። ይሄ ሁሉ ሲሆን ግን መነካት የተባለውን ነገር ስለማናውቀው ሕይወታችን ፍሬ አልባ አዙሪት ይሆናል። በቤተክርስቲያን ስንሆን በተለምዶ የምናደርገውን ተግባር ሁሉ እናደርጋለን፤ ከዚያ ስንወጣም እንደማንኛውም ሰው የሆነውን መደበኛ ኑሮአችንን እንቀጥላለን። አንዳንዴ እኛን ከ ኢ-አማንያኑ የሚለይ ፍንጭ እንኳን ሕይወታችን ላይ አይታይም፤ ተመሳስለን እንኖራለን። ልክ እንደ ዝናብ ልብሱ ከሰማይ የሆነው ነገር በላያችን ይፈሳል እንጂ ወደ ውስጣችን አይዘልቅም ከእኛ ጋር በእምነት አይዋሃድምና አይጠቅመንም። ለራሴ፣ ለዘመናችን ቤተክርስቲያን እና አማኞች፣ ለትውልዴ ይሆን ዘንድ ለእግዚአብሔር የማቀርበው አንድ መሻት፣ ናፍቆት፣ ልመና አለኝ፤ ይህም ፦ የውስጥ ሰውነታችን በመንፈስ ቅዱስ እንዲነካ፣ የልቦና አይኖቻችን እንዲበሩ፣ ኢየሱስን እንድናይ፣ የመጥራቱ ተስፋ ምን እንደሆነ እንድናስተውል፣ በቅዱሳን ዘንድ ያለ የርስት ክብር ባለጠግነት እንዲገባም፣ ለምናምን ለእኛ ከሁሉ በላይ ታላቅ የሆነውን ኀይሉን እንድናውቅ ነው። አቤቱ ጌታችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ሆይ በሕያው እጆችህ ዳሰን፤ ውስጠታችንን ንካው!! አሜን!! ኤፌሶን 1 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁷ የክብር አባት የሆነውን የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክ ይበልጥ እንድታውቁት፣ የጥበብና የመገለጥን መንፈስ እንዲሰጣችሁ ያለ ማቋረጥ እለምናለሁ። ¹⁸ እንዲሁም በእርሱ የተጠራችሁለት ተስፋ፣ ይህም በቅዱሳኑ ዘንድ ያለውን ክቡር የሆነውን የርስቱን ባለጠግነት ምን እንደሆነ ታውቁ ዘንድ የልባችሁ ዐይኖች እንዲበሩ ¹⁹ ለእኛ ለምናምነውም ከሁሉ በላይ ታላቅ የሆነውን ኀይሉን እንድታውቁ እጸልያለሁ። ይህም ኀይል እንደ እርሱ ታላቅ ብርታት አሠራር፣ ²⁰ ክርስቶስን ከሙታን ሲያስነሣውና በሰማያዊ ስፍራ በቀኙ ሲያስቀምጠው የታየው ነው። ✍️ መክሊት አየለ 📆 July 4, 2026 #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional

_ድሮ_ገና_Diro_Gena_lyrics_video_by_Dawit_Getachew_from_Volume_1128k.m4a5.34 MB

በእኛ ጊዜ፣ በእኛ ሁኔታ፣ በእኛ ዘመን፣ በእኛ ትውልድ....ከእግዚአብሔር ተሰጥቶን የእኛ በሆነው ነገር ሁሉ እግዚአብሔር መስራት፤ ፈቃዱን መፈጸም ይችላል። ነገር ግን እኛን ጨምሮ የሁሉ ነገር ባለቤት ለሆነው ለእግዚአብሔር ከእርሱ ተቀብለን የእኛ የሆነውን ነገር ሳንሰስት መስጠት፣ ለፈቃዱ ማዋል ካቃተን በምድር መቆየታችን ጥቅሙም ትርፉም ለእኛ እንጂ ለእግዚአብሔርና ለመንግሥቱ አይሆንም። እስትንፋሳችን ለምን ይቀጥላል? ለምን በምድር ያቆየናል? ለምን ሌላ ሰዓት፣ ሌላ ማለዳ፣ ሌላ ቀን፣ ሌላ ሳምንት፣ ሌላ ወር፣ ሌላ የምህረት ዓመት ይሰጠናል? ደግሞም ሌላ ብዙ አቅርቦት ለምን ያፈስልናል? የእግዚአብሔር የለጋስነት ዓላማው እኛን ማብላት፣ ማጠጣት፣ ማልበስ፣ ማስጌጥ.....እና ምንም ያልጎደለባቸው ቅምጥል የእግዚአብሔር ልጆች ማድረግ ነው? ኢየሱስስ የታረደው ስለ መብልና ስለ መጠጥ ጉዳይ ነው? የእግዚአብሔር መንግሥት አሳብስ የሚያጠነጥነው ስለዚህች ምድር አበይት ክስተቶች፣ የሰዎች የኑሮ ጉዳይ ላይ ነው? ይሄ ሁሉ ሲሆን የክርስቶስ የክብሩ ወንጌል ብርሃን በልባችን በርቶ፣ የድነትን ወንጌል ሰምተን፣ በእርሱም አምነን፣ ደህንነትን አግኝተን በእግዚአብሔር ቤት ካለን እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ያልጨረሰው ጉዳይ፣ በእኛ ሊሰራው ያሰበው ስራ አለ ማለት ነው። ስለዚህ ጠዋት በማለዳ ተነስቶ ለራስ ጉዳይ ሲሯሯጡ ማምሸቱ አያዛልቀንም! በእግዚአብሔርም አልታየልንምና ወደ ልቡ አሳብ በመመለስ፣ ሸክም በመቀየር፣ ትኩረታችንን የእግዚአብሔር መንግሥት ጉዳይ ላይ በማድረግ በምድር ያለ ቀሪ ጊዜያችንን በትጋት መኖር ይሁንልን!! “.... ብዙ ከተሰጠው ሁሉ ብዙ ይፈለግበታል፤ ብዙ ዐደራም ከተቀበለም ብዙ ይጠበቅበታል።”   — ሉቃስ 12፥48 (አዲሱ መ.ት) ✍️ መክሊት አየለ 📆 September 13, 2024 #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional

“.... ብዙ ከተሰጠው ሁሉ ብዙ ይፈለግበታል፤ ብዙ ዐደራም ከተቀበለም ብዙ ይጠበቅበታል።”   — ሉቃስ 12፥48 (አዲሱ መ.ት) #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional t.me/hopministry10

10,000 Reasons (Bless the Lord) Song by Matt Redman and Steve "Bless the Lord O my soul O my soul Worship his holy name Sing like never before O my soul I'll worship your holy name The sun comes up It's a new day dawning It's time to sing your song again Whatever may pass and whatever lies before me Let me be singing when the evening comes Bless the Lord O my soul O my soul Worship his holy name Sing like never before O my soul I'll worship your holy name You're rich in love and you're slow to anger Your name is great and your heart is kind For all your goodness I will keep on singing 10, 000 reasons for my heart to find Bless the Lord O my soul O my soul Worship his holy name Sing like never before O my soul I'll worship your holy name Sing like never before O my soul I'll worship your holy name And on that day when my strength is failing The end draws near and my time has come Still my soul will sing your praise unending 10, 000 years and then forever more Bless the Lord O my soul O my soul Worship his holy name Sing like never before O my soul I'll worship your holy name Bless the Lord O my soul O my soul Worship His holy name Sing like never before O my soul I'll worship your holy name O I'll worship your holy name I will worship your holy name Holy name"

Matt_Redman_-_10,000_Reasons__Bless_the_Lord_(128k).m4a4.03 MB

የሰው ልጅ ረሃብን ፈልጎ ሊራብ አይችልም፤ ነገር ግን በውስጡ የጎደለው ነገር ሲኖር እርሱ ቢፈልግም ባይፈልግም የረሃብ ስሜት ይሰማዋል። ረሃብ የአንድን ነገር ጉድለት ያሳያል፣ በሚያስፈልገው ነገር መገኘት የሚሞላ ጉድለትም ነው። ስለዚህ ረሃብ ከውስጥ ነው፣ ከጉድለቱ የተነሣ በውስጥ የሚፈጠር መሻት ነው። እግዚአብሔር እንደሚያስፈልገን ካላወቅን፣ በእርሱ ካልሆነ በቀር በሌላ በምንም የማይረካ ማንነት፣ የማይሞላ ውስጠት እንዳለን ካላወቅን እንዴት እግዚአብሔር ሊርበን ይችላል? ሁሉ ሞልቶ፣ የዕለት ተዕለት ክንውናችን ሳይቋረጥ፣ የምንበላውና የምንጠጣው ነገር ሳናጣ፣ መልበስ ማጌጥ ሳያቅተን፣ ቤታችን ሳይጎድል፣ አሉን በምንላቸውና በምንወዳቸው ሰዎች ተከበን....ሌላም፣ ሌላም ብዙ ነገር.....በአጠቃላይ እንደ ሰው ልማድ ለመኖር አንዳች ሳይጎድልብን ልባችን አላርፍ ካለ፣ ጉድለት ከተሰማን፣ ሁሉ ሞልቶን ሳለ ነገር ግን አንዱም አላረካ ካለን፤ ታዲያ ክፍተታችን የልባችን ሰሪ፣ የሕይወታችን ፈጣሪ ራሱ እግዚአብሔር አይደለም? በምንም የማይተካ #አንድ_ነገራችን፣ #ዋናችን፣ #አሳራፊያችን እግዚአብሔር!!! ሁሉ ጎድሎን በእርሱ ከእኛ ጋር መኖር፣ በእርሱ መገኘት እንረካለን፤ ሁሉን እየጣልን እርሱን ለመያዝ ልባችን ስፍስፍ ይላል፤ ከእርሱ ጋር ለመሆን የማንሰዋው ነገር አይኖርም፤ ለእናንተ ውዱ ነገር፣ ምርጡ ጊዜ የቱ ነው ተብለን ስንጠየቅ የእርሱ እግር ስር መሆን፣ በፊቱ መቆየት ቀዳሚ መልሳችን ይሆናል። ምንም ሳናጣ እግዚአብሔር ይራበን፤ ሁሉ እያለን እርሱ ጉድለታችን ሆኖ ወደ ፊቱ ያሩጠን፤ ሁሉን አጥተንም ፍለጋችን እርሱ ብቻ ይሁን፤ ወደ እርሱ በመገስገሳችን ውስጥ ሊነግሱብን የሚሹና የገዘፉብን ነገሮች ይረሱ፤ የእርሱ ፍቅር፣ የመገኘቱ ረሃብ ብቻ በፊቱ ያክርመን!! ✍️ መክሊት አየለ 📆 July 2, 2024. #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional

4_5931303518848689246.mp319.21 MB

YOHANNES_BELAY_Yednkwane_Tsehay_ዮሐንስ_በላይ_የድንኳኔ_ፀሐይ_New_Video”_2013.m4a4.77 MB

#ኢየሱስ፦ የእኔ ወገግታ፣ የእኔ ፀሐይ። አንተን ተጠግቼ አላፈርኹም፤ በቀረብኹህ ቁጥር በራኽልኝ። የተቀጠቀጠ ሸንበቆ ሳይሰበር፣ የሚጤስ የጧፍ ክርም ሳይጠፋ፣ ተስፋው በአንተ ታድሶ እንደገና በሕይወት ይኖራል። ቸርነትህን የቀመሱ ሁሉ ይወዱኻል፤ ማዳንህን ያዩ ሁሉ እግዚአብሔር ታላቅ ነው ይላሉ። ከአንተ ጋር መወዳጀት እንዴት መታደል ነው?! የማያልቅ፣ የማይደበዝዝ፣ ዘመን የማይሽረው ፍቅር ታስይዛለህ፤ በቀረቡህ ቁጥር ትበራለህ፣ ትብራራለህ፤ የቀመሱህ ሁሉ የአንተ ጥገኛ እንዲሆኑ ፍቅርህን በልባቸው ታፈስሳለህ፤ ኢየሱስ የምትወደድ አምላክ ነህ። አቤቱ በፍቅርህ አሰንብተን፤ ጥገኛህ ሆነን እንድንኖር ከአንተ ጋር አቆየን። ተግተን እንድናመልክህ፣ እንድንከተልህ፣ እንድንኖርልህ፣ እንድናገለግልህ ነፍሳችንን ዘወትር በፊትህ አፍስስልን። በፊትህ ስንቆይ እንበረክታለን፣ እንበዛለን፣ እናተርፋለንና በፊትህ አሰንብተን፤ የአንተ ጉልህ ድምፅ አድርገን። አሜን!! ✍️ መክሊት አየለ 📆 July 1, 2026 #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional

#ኢየሱሴ አቤቱ በፍቅርህ አሰንብተን፤ ጥገኛህ ሆነን እንድንኖር ከአንተ ጋር አቆየን። ተግተን እንድናመልክህ፣ እንድንከተልህ፣ እንድንኖርልህ፣ እንድናገለግልህ ነፍሳችንን ዘወትር በፊትህ አፍስስልን። #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional t.me/hopministry10

4_5922664346751604609.mp36.20 MB

" #We_are_God's_fellow_workers. " ብቻውን ያልተተወ፣ እግዚአብሔር በመስኩ፣ በእርሻው ውስጥ ያሰማራው፣ የእርሻው፣ የሕንጻው ሰራተኛ ያደረገው፣ ከእግዚአብሔር ጋር አብሮ የሚሰራ ሰው ምስጉን ነው። ሰራተኛ አምላክ ደካሞችን አብሮ ሰራተኛ ማድረጉ የእነርሱን ክፍተት ማጉላቱ ሳይሆን ኃይሉን በድካማቸው መግለጡ ነው። እርሱ እየሰራ ያሰራናል፣ እየሰራ እኛን ሰራተኞቹ ያስብለናል። ኃይሉን  በድካማችን እየገለጠ በእግዚአብሔር መንግሥት ውስጥ የሚተጉ ብርቱዎች ያስብለናል። በእግዚአብሔር ቤት ሥራ ላይ እንዳንቀልድ ከሚያደርገን፣ ልባችንንም ከጥፋት ከሚጠብቅ ነገር አንዱ፦ አገልግሎታችን የእኛ አለመሆኑን፤ ይልቁንም በእግዚአብሔር አገልግሎት፣ የሥራ ገበታ፣ መስክ ውስጥ እድል ደርሶን፤ ከእርሱ ጋር አብሮ-ሰራተኛ መሆናችንን ማወቃችን ነው። ይሄን እውነት ስንረዳ፦ መድረኩን፣ መንገዱን፣ ሥራውን፣ ፈቃዳችንን ሁሉ ለእርሱ ለባለቤቱ እየለቀቅን፣ እያስገዛን፣ የእኛ የምንለው አንዳች ሳይኖረን፣ እንደ እርሱ ልብ፣ እንደ አሳቡም ለመሥራት፣ ለማነጽ፣ ለማገልገል እንተጋለን። #ጸሎት፦ እግዚአብሔር ሆይ ዛሬ አንድ ልመና እለምንሃለሁ፦ ልክ እንደ አብሮ-ሰራተኛ፣ ከአንተ ጋር ስራህን እንደሚሰራ ሰው ልባችንን ወደ ፈቃድህ፣ ወደ አሳብህ አዘንብል። የእርሻህ፣ የሕንጻህ ጉዳይ ልክ እንዳንተ፣ አንተ የምታስበውን ያህል ያሳስበን። ለመንግሥትህ ጉዳይ፣ ለቤትህ ሥራ ቸልተኛ፣ ዝንጉ፣ ዳተኛ አንሁን። ልባችን በሸክም ከከበደ ሸክሙ የመንግሥትህ ጉዳይ ይሁንልን!! በሰማይ የታሰበ፣ የታቀደ ያንተ ውጥን በምድር በእኛ ይከወን፣ ፍጻሜውን ያግኝ። እየሰራህ አሰራን፤ በጸጋህ ለመንግሥትህ ስራ እግሮቻችንን አፍጥን፣ ክንዶቻችንንም አበርታ። ስናስብ በእግዚአብሔር ልብ እንዳለ እንደዛ ማሰብ ይሁንልን። አሜን!! “እኛ ከእግዚአብሔር ጋር አብረን የምንሠራ ነንና፤ እናንተም የእግዚአብሔር ዕርሻ ናችሁ፤ የእግዚአብሔር ሕንጻ ናችሁ።”   — 1ኛ ቆሮንቶስ 3፥9 (አዲሱ መ.ት) “For we are God's fellow workers. You are God's field, God's building.” —1 Corinthians 3: 9 (ESV) ✍️ መክሊት አየለ 📆 June 30, 2026 #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional

በእግዚአብሔር ቤት ሥራ ላይ እንዳንቀልድ ከሚያደርገን፣ ልባችንንም ከጥፋት ከሚጠብቅ ነገር አንዱ፦ አገልግሎታችን የእኛ አለመሆኑን፤ ይልቁንም በእግዚአብሔር አገልግሎት፣ የሥራ ገበታ፣ መስክ ውስጥ እድል ደርሶን፤ ከእርሱ ጋር አብሮ-ሰራተኛ መሆናችንን ማወቃችን ነው። HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional t.me/hopministry10

#የጸሎት_ማስተካከያ_ጥሪ! እግዚአብሔር ሁሉን በአንድያ ልጁ በኢየሱስ ውስጥ ሰውሮታል። ተድላ፣ ደስታ፣ ሐሴት፣ ጥበብ፣ እውቀት በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ ውስጥ ነው ያለው። አንዴ የተገለጠ ብርሃን፣ እውቀት፣ እውነት፣ ሕይወት አለ፤ እርሱም በጌታ በኢየሱስ ክርስቶስ ውስጥ ነው። አሁን እግዚአብሔር እኛን ለማስደነቅ በየማለዳው የሚያመጣው፣ የሚገልጠው አዲስ መገለጥ የለም። እግዚአብሔር ጥበቡን፣ እውቀቱን፣ ሕይወቱን፣ እውነቱን በልጁ በክርስቶስ ኢየሱስ ገልጦ ጨርሷል። አሁን በእኛ የሚሰራው ስራ በልጁ በኢየሱስ የተገለጠውን እናይ ዘንድ የልቦና አይኖቻችንን ማብራት ነው። በዚህ ዘመን ከእግዚአብሔር ትኩረት (ከልጁ ከኢየሱስ) ላይ አይናችን እንዳይወሰድ፣ በአልባሌ ነገር ልባችን እንዳይያዝ፣ እግዚአብሔር በሚጠብቀን ስፍራ ላይ ሳይሆን ከምድሩ ነገር ጋር ተሰፍተን እንዳንገኝ ጸሎት መቀየር ይኖርብናል። ግለጥልኝ፣ አዲስ መገለጥ ስጠኝ ከሚለው አሳች መሻት ወጥተን በልጅህ የገለጥኸውን አሳየኝ፣ እንዳይ የልቦና አይኖቼን አብራ ማለት መቻል አለብን። እግዚአብሔር የልቦና አይኖቻችንን ሲያበራ፣ የጥበብና የመገለጥ መንፈስን ሲሰጠን፦ የተሰወረ የጥበብ እና የእውቀት ሀብት መገኛ የሆነውን ኢየሱስን ማየት፣ ማወቅ፣ እርሱ ላይ መተከል፣ ሳንታክት እርሱን መከታተል እንችላለን። የእግዚአብሔርን ጥበብ፦ ልጁን ክርስቶስ ኢየሱስን ማየት፣ በእርሱ ማረፍ፣ በእርሱ መርካት፣ በእርሱ መደሰት ይሁንልን!! ክርስቶስ ኢየሱስን ከማወቅ ታላቅነት ጋር ሲነጻጸር ሁሉ ነገር ጉድፍ ነውና ሁሉን እየናቅን፣ እያጣን እርሱን መከታተል ይሁንልን!! ኤፌሶን 1 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁷ የክብር አባት የሆነውን የጌታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን አምላክ ይበልጥ እንድታውቁት፣ የጥበብና የመገለጥን መንፈስ እንዲሰጣችሁ ያለ ማቋረጥ እለምናለሁ። ¹⁸ እንዲሁም በእርሱ የተጠራችሁለት ተስፋ፣ ይህም በቅዱሳኑ ዘንድ ያለውን ክቡር የሆነውን የርስቱን ባለጠግነት ምን እንደሆነ ታውቁ ዘንድ የልባችሁ ዐይኖች እንዲበሩ ¹⁹ ለእኛ ለምናምነውም ከሁሉ በላይ ታላቅ የሆነውን ኀይሉን እንድታውቁ እጸልያለሁ። ይህም ኀይል እንደ እርሱ ታላቅ ብርታት አሠራር፣ ²⁰ ክርስቶስን ከሙታን ሲያስነሣውና በሰማያዊ ስፍራ በቀኙ ሲያስቀምጠው የታየው ነው። ቆላስይስ 2 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ² ደግሞም ልባቸው እንዲጽናናና በፍቅር እንዲተሳሰሩ፣ ፍጹም የሆነውን የመረዳት ብልጥግና አግኝተው የእግዚአብሔር ምስጢር የሆነውን ክርስቶስን እንዲያውቁ እተጋለሁ፤ ³ የተሰወረ የጥበብና የዕውቀት ሀብት ሁሉ የሚገኘው በእርሱ ዘንድ ነውና። ✍️ መክሊት አየለ 📆 June 29, 2026 #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional

እግዚአብሔር የልቦና አይኖቻችንን ሲያበራ፣ የጥበብና የመገለጥ መንፈስን ሲሰጠን፦ የተሰወረ የጥበብ እና የእውቀት ሀብት መገኛ የሆነውን ኢየሱስን ማየት፣ ማወቅ፣ እርሱ ላይ መተከል፣ ሳንታክት እርሱን መከታተል እንችላለን። HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional t.me/hopministry10

4_5863842227012244782.mp35.72 MB

#ዐላማችን_እርሱን_ደስ_ማሰኘት_ነው። ለእግዚአብሔር መኖር፣ እርሱን ማገልገል እኛ ብቁ (Qualified) ስለሆንን የምናደርገው ነገር አይደለም። እንዲያው ከወደደን ከታላቅ ፍቅሩ የተነሣ እግዚአብሔር ለእኛ ባበዛው ምህረት እንጂ። በሰው መስፈርት አንድ ሰው ላዘጋጀው የክብር ስፍራ ታዳሚዎችን መጥራት ሲያስብ፦ በሰው አይን የሚገቡ፣ የማያሳፍሩ፣ ሰው አይቶ አንዳች የሚመኩበት ጥሪት እንዳላቸው በቀላሉ መገመት የሚያስችለው ሞገስ ያላቸውን ሰዎች ይመርጣል። እግዚአብሔር ግን በልጁ በክርስቶስ ኢየሱስ ወደ ፍቅሩ ልጅ መንግሥት ያፈለሳቸው፣ ለከበረው ስፍራ የጠራቸው፦ እዚህ ግቡ የማይባሉ ኃጢአተኞችን ነው። የዚህን ዓለም ጥበብ ሊያሳፍር፣ የራሱን ጥበብ ሊገልጥ የዓለምን ሞኝ ነገር መረጠ። ታዲያ እግዚአብሔር ወድዶ፣ በራሱ ዋጋ ከፍሎ የራሱ ካደረገን፣ ለእርሱ የምንኖርበትን ምክንያት ከሰጠን፣ ለኃጢአት ሞተን ለጽድቅ እንድንኖር ካደረገ፣ ሞታችንን ወስዶ ሕይወቱን በእኛ ሊገልጥ ከወደደ፣ የሕይወት ትርጉም፣ ዓላማ፣ ግብ ከሰጠን፣ የምንኖርበት ምክንያትም ከሆነን፦ በምድር ልንኖር በቀረልን ዘመን ለእርሱ ከመኖር፣ እርሱንም ከማገልገል ውጪ ምን ተድላ፣ ምን ደስታ፣ ምን ክብር፣ ምን ዕድል ፈንታ አለን?! የእግዚአብሔር መሰዊያ ላይ በቆየን ቁጥር፣ ሁሉን እያጣን እርሱን በተከተልን ቁጥር፣ የእርሱን መንግሥት ለማስፋት፣ እርሱንም ለማድመቅ ራሳችንን በደበቅን፣ የእኛ የምንለውን ነገርም እያጣን በሄድን ቁጥር፦ እየነደድን ለእግዚአብሔር የምናበራ መብራት እንሆናለን። ሕይወታችን እኛ ጋር ሰንብቶ አያለማንም፤ ለራሳችን፣ ለክብራችን ሸሽገንም ጥቂት እንኳን አናተርፍበትም፤ ለእግዚአብሔር ስንዘራው፣ ስንሰጠው፣ ስንሰዋው ግን እልፍ፣ ብዙ እጥፍ እናተርፍበታለን፣ በእግዚአብሔር መንግሥት እጅግ የከበረ ዋጋ ያለውን ፍሬም እናጭዳለንና ሳንሰስት፣ ሳንዝል፦ ለእግዚአብሔር፣ ለመንግሥቱ ሥራ መሰዋት፣ መሰጠት ይሁንልን። ብንኖር ወይም ብንሞት ዓላማችን እግዚአብሔርን ደስ ማሰኘት ይሁንልን!! ጥቂቷ ዘመናችን ከእኛ ተሰውራ በእግዚአብሔር ፊት፣ በአደባባዮቹም ትብዛልን!! ጸጋ ይብዛልን!! “ስለዚህ በሥጋ ብንኖርም ወይም ከሥጋ ብንለይም ዐላማችን እርሱን ደስ ማሰኘት ነው።”   — 2ኛ ቆሮንቶስ 5፥9 (አዲሱ መ.ት) ✍️ መክሊት አየለ 📆 June 28, 2026 #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional

ሰሪያችን እግዚአብሔር ሆይ እጅህ ውስጥ ገብቶ እንደነበረ ሆኖ የሚወጣ ምንም የለም። ለሸክላ የመታደስ፣የመሰራት፣ እንደገና ውብ ሆኖና ሰሪው የሚፈልገውን ሌላ ቅርፅ ይዞ የመውጣት ዋስትናው የሸክላው ማንነት፣ ብልሽት፣ ተሰባሪነት ሳይሆን የሸክላ ሰሪው እጅ ነው፤ ምክንያቱም ሸክላው ምንም አይነት ሁኔታ ላይ ይሁን ሸክላ ሰሪው ባለቤት ነውና እንደገና፣ እንደወደደ አድርጎ ይሰራዋል። ለዚህ ነው ሕይወታችንን፣ መንገዳችንን፣ ነገሮቻችንን የሰሪያችን እጅ ላይ አኑረን ማረፍ የሚገባን፤ ምክንያቱም እርሱ በእኛና በነገሮቻችን ሁሉ ላይ የወደደውን መስራት ይችላል። ስለዚህ እኛም ሁሉን ለእርሱ እያስገዛን፣ እኛንና የእኛ የሆነውን ሁሉ፦ ለሁሉን ቻይ እና ለታማኝ እጁ እየሰጠን በእረፍት እንኖራለን!! ኤርምያስ 18 (አዲሱ መ.ት) ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ ከእግዚአብሔር ወደ ኤርምያስ እንዲህ የሚል ቃል መጣ፦ ² “ተነሥተህ ወደ ሸክላ ሠሪው ቤት ውረድ፤ በዚያ መልእክቴን እሰጥሃለሁ።” ³ እኔም ወደ ሸክላ ሠሪው ቤት ወረድሁ፤ ሸክላውንም በመንኵ ራኩር ላይ ይሠራ ነበር። ⁴ ከጭቃ ይሠራው የነበረውም ሸክላ በእጁ ላይ ተበላሸ፤ ሸክላ ሠሪውም በሚፈልገው ሌላ ቅርጽ መልሶ አበጀው። ⁵ የእግዚአብሔርም ቃል ወደ እኔ እንዲህ ሲል መጣ፤ ⁶ “የእስራኤል ቤት ሆይ፤ ሸክላ ሠሪው እንደሚሠራው፣ እኔ በእናንተ ላይ መሥራት አይቻለኝምን?” ይላል እግዚአብሔር፤ “የእስራኤል ቤት ሆይ፤ ጭቃው በሸክላ ሠሪው እጅ እንዳለ፣ እናንተም እንዲሁ በእጄ ውስጥ ናችሁ። ✍️ መክሊት አየለ 📆 December 13, 2023 #HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional

HOPMinistry #HearObeyPractice #DailyDevotional t.me/hopministry10