Eotc Task Force
الذهاب إلى القناة على Telegram
7 367
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
+2117 أيام
+33630 أيام
أرشيف المشاركات
7 367
Repost from ፍኖተ አበው ዘኦርቶዶክስ (መ/ር ንዋይ ካሳሁን)
የመጀመሪያ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን
+ የመጀመሪያው ጳጳስ:- አባ ሰላማ
+የመጀመሪያው ኤጲስ ቆጶስ:- ሕዝበ ቀድስ (በኦሪት ስሙ እንበረም)
+ የመጀመሪያው ቄስ:- ቄስ ተክለ ሃይማኖት ( በኦሪት ስሙ ፊንሐስ)
+ የመጀመሪያ ምእመን:- ባኮስ (ጃንደረባው)
+ የመጀመሪያዋ ቤተ ክርስቲያን:- አክሱም ጽዮን
+ የመጀመሪያው ፓትርያርክ አቡነ ባስልዮስ
ንዋይ ካሳሁን
7 367
Repost from ፍኖተ አበው ዘኦርቶዶክስ (መ/ር ንዋይ ካሳሁን)
ዝኾኑን የመጣል ዘመቻ
አንድ የኮሌጅ ጓደኛችን ነበር። በጣም ጥሩ አመለ ሸጋ አስተዋይ ጓደኛ ነበረን። ኹላችንም ታናናሾቹ ብንኾንም በመቀለድም፣ በምንም የምንመታው የምንቀልድበት ወንድማችን ነው። አይናደድ አይበሳጭ እንደውም አንድ አባባል ጣል አድርጎ ይበልጥ ያበሳጨን ነበር።
ታድያ ኹላችንም አቅማችንን ስለማናሳይበት "በእኔና በጥምቀት የማይጨፍር የለም" ይል ነበር። እውነቱን ነው። አኹንም በኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን የማይጨፍር የለም።
አቡበከርም፣ አሕመዲንም፣ ኢዩጩፋም፣ አስቴር በዳኔም ይኽ ታዬ ቦጋለም ቤተ ክርስቲያን ላይ እየጨፈሩ ናቸው።ይኽ ኹሉ ርብርብ ዝኾኑን (ውርዝው ነጌ) ለመጣል ነው።
ታዬ ቦጋለ እንደምንም ብሎ እስልምናም ኦርቶዶክስም ከውጭ ነው የመጡት ለማለት የገባበት ገደል መውጭ የለውም።
ከመደበኛ እውቀት ማለትም በትምህርት ቤት ከመምህራን ከመጽሐፍት የሚገኝ እውቀት ስትወድቅ የምታርፈው የፕሮፓጋንዳ እውቀት ላይ ነው።
የፕሮፓጋንዳ እውቀት ምንጭ የለውም፣ ጫፍ ይዞ መሄድ ብቻ ነው። ግን አየሩን የሚሞላው እሱ ነው። ብዙዎቻችን የፕሮፓጋንዳ እውቀት ሰለባ ነን። ምንጩን መነሻውን ታሪኩንና የታሪኩን ምንነት አንድረዋው። ተንትነን አንገነዘብም። እንደ አብይ "አጼ ዮሐንስ በጎጃም ላይ ያደረጉትን አትረሱትም" ያለው ፕሮፓጋንዳ ነው። የኾነ ክስተት ተደርጓል። ግን ለውጦ ለሚፈልገው ማዋል ፈለገ። አደገኛ ነው።
ታዬ ኦርቶዶክስ በአምስተኛው ክፍለ ዘመን ወደ ኢትዮጵያ ከመጡ ዘጠኙ ቅዱሳን ጋር የኦርቶዶክስ ወደ ኢትዮጵያ መግባቱን ተናገረ። ይገርማል።
ጃንደረባው ባኮስ ከዲያቆኑ ፊሊጶስ ጋዛ ተጠምቆ መምጣቱን አያውቅም። ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ በበዓለ ሃምሳ ኢትዮጵያውያን መኖራቸውን መጻፉን አያውቅም። ሐዋ.8
የመጀመሪያዎቹ ነገሥታት ኢዛናና ሳይዛና በክርስትና ስማቸው አብርሃና አጽብሃ ስማቸው ክርስትናን መቀበላቸውን አያውቅም።
ተስዓቱ ቅዱሳን ወንጌል አስፋፉ፣ ምንኩስናን አስፋፉ እንጂ ክርስትና ይዘው አልመጡም። የመጡትኮ በኬልቄዶን ጉባኤ ስደት ሲደርስባቸው የምትመስለን ሰላማዊ ክርስቲያን ሃገር አለች እዚያ እንጠለል ብለው ነው።
ከነርሱ ቀድሞ እነ ቅዱስ ያሬድ ድርሰት ደርሰዋል። ክርስትና እየሰፋ መጥቷል ሰሜኑን አዳርሷል። ፍሬምናጦን የመጀመሪያው ጳጳስ እንጂ የመጀመሪያው ክርስቲያን አይደለም። በኢትዮጵያ የመጀመሪያው ክርስቲያን ባኮስ የመጀመሪያዋ ቤተክርስቲያን አክሱም ጽዮን፣ የመጀመሪያው ፣ ኤጲስ ቆጶስ ሕዝበ ቀድስ (እንበረም)፣ የመጀመርያው ጳጳስ ፍሬምናጦስ (ሰላማ) ነው። መቼ ከተባለ ከጰራቅሊጦስ በወረድ ማግሥት፣ በሠላሳ አራተኛው ዓመት።
ንዋይ ካሳሁን
7 367
+5
መዝግባችሁ ያዙ
በሀዲያ ዞን አመካ ወረዳ ጽንፈኛ ፕሮቴስታንቶችን አሰማርተው የቡታራ ኢስጢናፋኖስ ቤተ ክርስቲያንን ያስፈረሱና ኦርቶዶክሳውያንን ያስጨፈጨፉ የብልጽግና ወንጌል(የፕሮቴስታንት ) ባለሥልጣናት፦
፩ አቶ ደገፈ ሞላንጎ (የአመካ ወረዳ አስተዳዳሪ)
2)ኢ/ር እሸቱ አዳነ አሼቦ( የአመካ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ)
3)፶ አለቃ ጡምሲዶ ሞላጎ(የወረዳው ሰላምና ጸጥታ ሀላፊ)
የጊዜ ጉዳይ ነው ሁሉም የዘራውን ነው የሚያጭደው
አሁን ስልጣን ላይ ሆኖ ክርስቲያኖችን የሚያሳርደው
7 367
ወንድሜ ምን ማለት እንዳለብኝ አላውቅም ኋይለሚካኤል ብላችሁ በፀሎት አስቡት ድጋሜ ወንድሙን በሞት አቷል
አፅናኝ መንፈስ ቅዱስ ያበርታህ
7 367
+2
መዝግባችሁ ያዙ
በሀዲያ ዞን አመካ ወረዳ ጽንፈኛ ፕሮቴስታንቶችን አሰማርተው የቡታራ ኢስጢናፋኖስ ቤተ ክርስቲያንን ያስፈረሱና ኦርቶዶክሳውያንን ያስጨፈጨፉ የብልጽግና ወንጌል(የፕሮቴስታንት ) ባለሥልጣናት፦
፩ አቶ ደገፈ ሞላንጎ (የአመካ ወረዳ አስተዳዳሪ)
2)ኢ/ር እሸቱ አዳነ አሼቦ( የአመካ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ)
3)፶ አለቃ ጡምሲዶ ሞላጎ(የወረዳው ሰላምና ጸጥታ ሀላፊ)
የጊዜ ጉዳይ ነው ሁሉም የዘራውን ነው የሚያጭደው
7 367
+2
መዝግባችሁ ያዙ
በሀዲያ ዞን አመካ ወረዳ ጽንፈኛ ፕሮቴስታንቶችን አሰማርተው የቡታራ ኢስጢናፋኖስ ቤተ ክርስቲያንን ያስፈረሱና ኦርቶዶክሳውያንን ያስጨፈጨፉ የብልጽግና ወንጌል(የፕሮቴስታንት ) ባለሥልጣናት፦
፩ አቶ ደገፈ ሞላንጎ (የአመካ ወረዳ አስተዳዳሪ)
2)ኢ/ር እሸቱ አዳነ አሼቦ( የአመካ ወረዳ ፖሊስ አዛዥ)
3)፶ አለቃ ጡምሲዶ ሞላጎ(የወረዳው ሰላምና ጸጥታ ሀላፊ)
የጊዜ ጉዳይ ነው ሁሉም የዘራውን ነው የሚያጭደው
7 367
በጥቃቱ የአትሮንስ ማርያም ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ ቆሞስ አባ ሞገስ ፍስሃ፣ የቤተክርስቲያኗ አቃቢ እማሆይ ድንቄ ታከለን ጨምሮ ሌሎች ስድስት የቤተክርስቲያኗ አገልጋይ ቀሳውስትና ዲያቆናት ሲገደሉ ከ20 ፡ብላይ ንፁኋኖች ነቁሰላቸውን ነው በእለቱ ጣቢያችን ዘግቦ የነበረው።
መረብ ሚዲያ
7 367
ዳግም የድሮን ጥቃት ይፈፀምብናል በሚል የገዳሟ ተማሪዎች እየተሰደዱ መሆኑ ተነገረ!
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በደቡብ ወሎ ሐገረ ስብከት ከመካነሰላም ከተማ በቅርብ ርቀት ዓባይ ድልድይ አከባቢ በምትገኘው የዓባይ ቅድስት አርሴማ ገዳም በድሮን መደብደቧን ተከትሎ በገዳሟ ውስጥ ይማሩ የነበሩ የአብነት ተማሪዎች ገዳሟን ለቀው እየተሰደዱ መሆናቸው ታወቀ።
ፅረ ሕዝቡና ሃገር አውዳሚው የብልፅግና አገዛዝ ሐምሌ 15/2018 ዓ/ም ማርፈጃውን በገዳሟ ላይ የድሮን ድብደባ መፈፀሙ ይታወቃል።
ጥቃቱን ተከትሎ በገዳሟ ውስጥ መንፈሳዊ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩ የአብነት ተማሪዎችና አንዳንድ አበው መምህራን ልባቸው እጅጉን በመሰበሩ አካባቢውን እና ገዳሟን ጥለው ለመሰደድ መገደዳቸውን መረብ ሚዲያ ለማረጋገጥ ችሏል።
የብልፅግናው አገዛዝ ስለ ሀገር አንድነትና ሰላም በሚፀልዩ መናንያን መነኮሳትና ገዳማት እንዲሁም አብያተክርስቲያናት ላይ በሰው አልባ አውሮፕላንና በሜካናይዝድ መሣሪያዎች ታግዞ የሚፈፀመው እልቂትና ውድመት ተባብሶ ቀጥሏል።
ሀገር እያስተዳደርኩ ነው የሚለው ይሄው ኦህዴድ መሩ የብልፅግናው አገዛዝ፡ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በደቡብ ወሎ ሐገረ ስብከት ከመካነሰላም ከተማ በቅርብ ርቀት ዓባይ ድልድይ አከባቢ በምትገኘው ዓባይ ቅድስት አርሴማ ገዳም ውስጥ ታቅበው ስለ ነፍሳቸው መዳን፣ ስለ ሀገር አንድነትና ሰላም፣ ስለ ሰው ልጆች ሁሉ በሚፀልዩ መናንያን መነኮሳት ላይ ሐምሌ 15 /2018 ዓ/ም በፈፀመው ዘግናኝ የድሮን ጥቃት ሁለት መናንያን መነኮሳት ለሕይወተ ሕልፈት ሲዳረጉ በርካቶች ደግሞ ለከባድ የአካል ጉዳት መጋለጣቸውን መረብ ሚዲያ በእለቱ መዘገቡ አይዘነጋም።
በጥቃቱ በመነኮሳቱ ላይ ከደረሰው እልቂት በተጨማሪ፡ የገዳማውያኑ የዓመት ቀለብ እህልና ጥራጥሬ፣ ተግባር ቤት፣ ማብሰያ እቃዎች፣ የውሃ ማጠራቀሚያ ታንከር ሙሉ በሙሉ መውደማቸው ተረጋግጧል።
በዚህም መናኒያኑ የለት ቀለባቸውና በዛ በርሃ ውስጥ የመጠጥ ውሃ የሚያጠራቅሙበት የውሃ ታንከር በመውደሙ ምክኒያት ለረሃብና ለከባድ የውሃ ጥም ተጋልጠዋል።
በዚህ ምክኒያት እና ዳግም ጥቃት ይፈፀምብናል በሚል ስጋት በገዳሟ ውስጥ ይማሩ የነበሩ የአብነት ተማሪዎችና አንዳንድ አበው መምህራን ገዳሟን ለቀው እየተሰደዱ ስለመሆናቸው ነው መረብ ሚዲያ ለማረጋገጥ የቻለው።
በዚኸው ሃገረ ስብከት በመኃል ሳይንት ወረዳ በታሪካዊቷ ታዕካ ነገስት አትሮንስ ማርያም ቤተክርስቲያን ላይ የካቲት 28/2018 ዓ/ም ማርፈጃውን በተፈፀመ የከባድ መሣሪያ ጥቃት፡ ሁለት ካህናትና ሦስት ዲያቆናት እንዲሁም አንዲት የቤተክርስቲያኗ አቃቢ በድምሩ ስድስት ንፁኋኖች ሲገደሉ ከ20 በላይ ንፁኋኖች ደግሞ ለከባድ የአካል ጉዳት መጋለጣቸውን በእለቱ ጣቢያችን መረብ ሚዲያ የአይን እማኞችን ዋቢ አድርጎ መዘገቡ አይዘነጋም።
በአብርሃ አፅብሃ ዘመነ መንግስት እንደተመሠረተች የሚነገርላት ታሪካዊቷ ታዕካ ነገስት አትሮንሰ ቅድስተ ማርያም ቤተክርስቲያን፡ በርካታ ነገስታት ንግስናቸውን የተቀበሉባትና ከበርካታ ነገስታት በስጦታ መልክ የተሰጠችውን ልዩ ልዩ ታሪካዊ ቅርሶችን በውስጧ የያዘች ከሐይማኖታዊ ስፍራነቷ ባሻገር በአከባቢው እንደሙዝየም የምታገለግል ደብር ናት።
በዚች ታሪካዊትና እድሜ ጠገብ ቅድስት ቤተክርስቲያን ላይ የካቲት 28/2018 ዓ/ም ማርፈጃውን በጄነራል ዘውዱ ሰጣርጌ የሚመራው የብልፅግና መከላከያ ሰራዊት ተከታታይ የመድፍ ድብደባ ተፈፅሟል።
በጥቃቱ የአትሮንስ ማርያም ቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ ቆሞስ አባ ሞገስ ፍስሃ፣ የቤተክርስቲያኗ አቃቢ እማሆይ ድንቄ ታከለን ጨምሮ ሌሎች ስድስት የቤተክርስቲያኗ አገልጋይ ቀሳውስትና ዲያቆናት ሲገደሉ ከ20 ፡ብላይ ንፁኋኖች ነቁሰላቸውን ነው በእለቱ ጣቢያችን ዘግቦ የነበረው።
መረብ ሚዲያዳግም የድሮን ጥቃት ይፈፀምብናል በሚል የገዳሟ ተማሪዎች እየተሰደዱ መሆኑ ተነገረ!
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በደቡብ ወሎ ሐገረ ስብከት ከመካነሰላም ከተማ በቅርብ ርቀት ዓባይ ድልድይ አከባቢ በምትገኘው የዓባይ ቅድስት አርሴማ ገዳም በድሮን መደብደቧን ተከትሎ በገዳሟ ውስጥ ይማሩ የነበሩ የአብነት ተማሪዎች ገዳሟን ለቀው እየተሰደዱ መሆናቸው ታወቀ።
ፅረ ሕዝቡና ሃገር አውዳሚው የብልፅግና አገዛዝ ሐምሌ 15/2018 ዓ/ም ማርፈጃውን በገዳሟ ላይ የድሮን ድብደባ መፈፀሙ ይታወቃል።
ጥቃቱን ተከትሎ በገዳሟ ውስጥ መንፈሳዊ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩ የአብነት ተማሪዎችና አንዳንድ አበው መምህራን ልባቸው እጅጉን በመሰበሩ አካባቢውን እና ገዳሟን ጥለው ለመሰደድ መገደዳቸውን መረብ ሚዲያ ለማረጋገጥ ችሏል።
የብልፅግናው አገዛዝ ስለ ሀገር አንድነትና ሰላም በሚፀልዩ መናንያን መነኮሳትና ገዳማት እንዲሁም አብያተክርስቲያናት ላይ በሰው አልባ አውሮፕላንና በሜካናይዝድ መሣሪያዎች ታግዞ የሚፈፀመው እልቂትና ውድመት ተባብሶ ቀጥሏል።
ሀገር እያስተዳደርኩ ነው የሚለው ይሄው ኦህዴድ መሩ የብልፅግናው አገዛዝ፡ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን በደቡብ ወሎ ሐገረ ስብከት ከመካነሰላም ከተማ በቅርብ ርቀት ዓባይ ድልድይ አከባቢ በምትገኘው ዓባይ ቅድስት አርሴማ ገዳም ውስጥ ታቅበው ስለ ነፍሳቸው መዳን፣ ስለ ሀገር አንድነትና ሰላም፣ ስለ ሰው ልጆች ሁሉ በሚፀልዩ መናንያን መነኮሳት ላይ ሐምሌ 15 /2018 ዓ/ም በፈፀመው ዘግናኝ የድሮን ጥቃት ሁለት መናንያን መነኮሳት ለሕይወተ ሕልፈት ሲዳረጉ በርካቶች ደግሞ ለከባድ የአካል ጉዳት መጋለጣቸውን መረብ ሚዲያ በእለቱ መዘገቡ አይዘነጋም።
በጥቃቱ በመነኮሳቱ ላይ ከደረሰው እልቂት በተጨማሪ፡ የገዳማውያኑ የዓመት ቀለብ እህልና ጥራጥሬ፣ ተግባር ቤት፣ ማብሰያ እቃዎች፣ የውሃ ማጠራቀሚያ ታንከር ሙሉ በሙሉ መውደማቸው ተረጋግጧል።
በዚህም መናኒያኑ የለት ቀለባቸውና በዛ በርሃ ውስጥ የመጠጥ ውሃ የሚያጠራቅሙበት የውሃ ታንከር በመውደሙ ምክኒያት ለረሃብና ለከባድ የውሃ ጥም ተጋልጠዋል።
በዚህ ምክኒያት እና ዳግም ጥቃት ይፈፀምብናል በሚል ስጋት በገዳሟ ውስጥ ይማሩ የነበሩ የአብነት ተማሪዎችና አንዳንድ አበው መምህራን ገዳሟን ለቀው እየተሰደዱ ስለመሆናቸው ነው መረብ ሚዲያ ለማረጋገጥ የቻለው።
በዚኸው ሃገረ ስብከት በመኃል ሳይንት ወረዳ በታሪካዊቷ ታዕካ ነገስት አትሮንስ ማርያም ቤተክርስቲያን ላይ የካቲት 28/2018 ዓ/ም ማርፈጃውን በተፈፀመ የከባድ መሣሪያ ጥቃት፡ ሁለት ካህናትና ሦስት ዲያቆናት እንዲሁም አንዲት የቤተክርስቲያኗ አቃቢ በድምሩ ስድስት ንፁኋኖች ሲገደሉ ከ20 በላይ ንፁኋኖች ደግሞ ለከባድ የአካል ጉዳት መጋለጣቸውን በእለቱ ጣቢያችን መረብ ሚዲያ የአይን እማኞችን ዋቢ አድርጎ መዘገቡ አይዘነጋም።
በአብርሃ አፅብሃ ዘመነ መንግስት እንደተመሠረተች የሚነገርላት ታሪካዊቷ ታዕካ ነገስት አትሮንሰ ቅድስተ ማርያም ቤተክርስቲያን፡ በርካታ ነገስታት ንግስናቸውን የተቀበሉባትና ከበርካታ ነገስታት በስጦታ መልክ የተሰጠችውን ልዩ ልዩ ታሪካዊ ቅርሶችን በውስጧ የያዘች ከሐይማኖታዊ ስፍራነቷ ባሻገር በአከባቢው እንደሙዝየም የምታገለግል ደብር ናት።
በዚች ታሪካዊትና እድሜ ጠገብ ቅድስት ቤተክርስቲያን ላይ የካቲት 28/2018 ዓ/ም ማርፈጃውን በጄነራል ዘውዱ ሰጣርጌ የሚመራው የብልፅግና መከላከያ ሰራዊት ተከታታይ የመድፍ ድብደባ ተፈፅሟል።
