es
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

Ir al canal en Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

Mostrar más
2 936
Suscriptores
-324 horas
+3667 días
+38130 días
Archivo de publicaciones
ከጠላት ዕቅድ በተቃራኒ አጸፋዊ ምላሽ የሰጠው 206ኛ ኮር 34ኛ ክ/ጦር የባሶሊበን ወረዳ ኮርክ ከተማን በመቆጣጠር ወታደራዊ ድል አስመዝግቧል። ሐምሌ13/2018 ዓ.ም ~~~~~~~ የ206ኛ ኮር 34ኛ ክ/ጦር ከሌሊቱ 11:00 ኮርክ ከተማ በመሸገውን የአገዛዙን ኃይል ላይ እርምጃ በመውሰድ ከ35 በላይ አድማ ብተና ፣15 ሚኒሻ ፣አንድ ሻለቃ አዛዥ፣ሁለት ሻምበል መሪዎችን በመደምሰስ ከተማውን ሙሉ ለሙሉ ተቆጣጥሯል። በፈጣን ማጥቃት የጠላትን ምሽግ የሰበረው 34ኛ ክ/ጦር 5 ክላሽ፣ ጥይት፣ ወታደራዊ ቦርሳና ልዩ ልዩ ቁሳቁስ የማረከ ሲሆን ከየጁቤ ከተማ ተነስቶ ድጋፍ ለመስጠት በሁለት FSR መኪና ተጭኖ በተንቀሳቀው የመከላከያ ኃይል ላይ በተደረገ ተጨማሪ ጥቃት ሻምበል አዛጆችን ጨምሮ የሰራዊት አባላት ሙሉ  ተደምስሰው ተሽከርካሪው ከጥቅም ውጭ ሁኗል። የጁቤ ሆስፒታል በቁስለኞች ተሞልቶ መደበኛ አገልግሎት አቁሟል። ከጠላት እቅድ በተቃራኒ አጸፋዊ ምላሽ የሰጠው 206ኛ ኮር 34ኛ ክ/ጦር የታቀደ አንጸባራቂ ድል በማስመዝገብ የጠላትን ወታደራዊ ኃይል አርግፎታል። በተመሳሳይ 24ኛ ክ/ጦር ስናን አባጅሜ ሻለቃ ከደጋሰኝን፣ ደብረ ማርቆስ እና ረቡዕ ገበያ ተሰባስቦ  ሜካናይዝድ ድጋፍ ካለው የጠላት ኃይል ጋር ትንቅንቅ እያደረገ ሲሆን በጠላት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል ። ውጊያው እጅ በእጅ እንደቀጠለ ነው። አዲስ ትውልድ! አዲስ አስተሳሰብ ! አዲስ ተስፋ! የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት

የነፃነት ንድፍ፦ የጉዞው እሳትና የፅናት ዋጋ!! ​የአማራ ልጅ ፋኖ በአራቱም ማዕዘን ተነስቷል። ያንን አማራ ጠል የሆነ አረመኔያዊ ሥርዓት ከምድር ገፅ ለማጥፋትና የህዝቡን ክብር ለመመለስ ሌት ተቀን የሚከፍለው መስዋዕትነት የጀግንነት ጥግ፣ የታሪክም አሻራ ነው። በዚህ የታሪክ አጋጣሚ ውስጥ ተገኝቼ የዚህ ትውልድ አካል መሆኔ ሁልጊዜም ኩራት ይሰማኛል። ​ነገር ግን ታሪክ ሁሌም ቀና አይደለም፤ አማራ በመሆኔ ብቻ በገዛ ወገኖቼ፣ በሆዳም አማራዎች መገፋቴ እጅጉን ያመኛል። ዛሬም ድረስ በነዚሁ ጥቅመኞች እየተሳደድኩ ብኖርም፣ ተስፋ ግን አልቆረጥኩም። ምክንያቱም ዛሬ በሸዋ ጠቅላይ ግዛት በአሳምነው ዕዝ ውስጥ የህዝብ አስተዳደር አርበኛ የሆነውን የወንድሜን የኤፍሬም ባዬን እና የጓዶቹ የትግል ጉዞ ስመለከት፣ የነፃነት ፈር ቀዳጅነቱን ሳስተውል፣ የቆሰለው ልቤ እንደ እሳት ይሞቃል፤ ብርታትም ይሰማኛል። ​የፋኖ ትልቁ ፈተናው ጠላትን መጋፈጥ ብቻ አይደለም፤ ያንን አቀበትና ቁልቁለት፣ ያንን ተራራና ገደል እየወጡ መውረዱም ጭምር ነው። እንዲህ ባለው መከራ ውስጥ አልፎ፣ በዱር በገደሉ እየተዋደቀ ነው ፋኖ የአማራን ህዝብ ነፃ ለማውጣት እየታገለ ያለው። የምወድህና የማክብርህ አርበኛ ኤፍሬም ባዬ ወንድሜ ሆይ፣ እጅጉን ክበርልኝ! ​በዚሁ አጋጣሚ፣ በየጎጡ ተሸሽጋችሁ ጎንደርን ከጎጃም፣ ጎጃምን ከወሎ፣ ወሎን ከሸዋ ለመነጣጠልና ህዝቡን ለመከፋፈል የምትሞክሩ ሆዳም አስመሳዮች ሆይ ይህ መልእክት (ቪዲዮ) ለእናንተ ይድረሳችሁ። አንዳንዴ በሆዳችሁ ያደራችሁ እውነተኛ ጀግኖችን በመሳደብና ስም በማጥፋት ለተሰማራችሁ ሁሉ ይህ የታሪክ ትዝብት ነው። እውነታው ግን አንዱና ግልጽ ነው፦ የአማራ ልጅ ፋኖ እናንተንም እኛንም፣ መላውን ህዝብ ነፃ ለማውጣት ነው ዛሬ በየጫካው ውድ ህይወቱን እየገበረ ያለው! #Dave #Amhara

በዙ_23 የተመታው የ3ዓመት ታዳጊ የዐምሐራ ሕዝብ እንዲጠፋ ከተፈረደበት ዓመታትን አስቆጥሯል። ዐምሐራ ሆኖ መወለድ ወንጀል ከሆነ እና ስርዓት ከተዘረጋ ፣ሕገመንግሥት ከተቀረፀ መቶ አመታትን አስቆጥሯ
በዙ_23 የተመታው የ3ዓመት ታዳጊ    የዐምሐራ ሕዝብ እንዲጠፋ ከተፈረደበት ዓመታትን አስቆጥሯል።  ዐምሐራ ሆኖ መወለድ ወንጀል ከሆነ እና ስርዓት ከተዘረጋ ፣ሕገመንግሥት ከተቀረፀ መቶ አመታትን አስቆጥሯል። በተለይ የአብይ አህመድ ስርዓት የዐምሐራን ሕዝብ እሳት እያዘነበበት ነው። ይህ የሚታየው ሕፃን የሶስት አመት ህፃን ነው ። በምስራቅ ጎጃም ዞን ማቻከል ወረዳ    ቅዳምን(ድንጋይ በር )  ላይ ከዋዳን በተተኮሰ ዙ_23  የተመታ ህፃን ነው።    የዐምሐራ ሆኖ ስለተገኘ ብቻ ከቤቱ ደጅ ሳጫዎች በአብይ አህመድ ጨፍ*ፊ ሰራዊት  የተመታ ሕፃን ነው። የዐምሐራ ሕዝብ አገሩ ወዴት ነው? አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስሳሰብ፣አዲስ ተስፋ! የቴዎድሮስ ዕዝ  ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ      ሐምሌ 13/2018ዓ.ም

የምረቃት ዜና!! የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ  ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ 102ኛ ኮር የህግና ስነ-ስርዓት  ሰልጣኞችን በደማቅ ሁኔታ አስመረቀ። ሀምሌ 12/2018 ዓ/ም የ102ኛ ኮር አመራር በተገኘበት  ለተከታታይ  ሁለት ወር በወንጀልና በፍትሀ ብሔር ህግ የሰለጠኑ የህግና ስነ-ስርዓት ባለሙያዎችን ለመጀመሪያ ጊዜ በብቃት አስመረቀ። የ102ኛ ኮር  ከዚህ በፊት በሁሉም ክፍለጦሮች ብቁ የሆኑ የህግና ስነ-ስርዓት ባለሙያዎችን በመመደብ በሰራዊታችንና በህዝባችን ያሉ የፍትህ ጥያቄዎችን በመፍታትና የጀርባ አጥንት በመሆን ተስፋ የተጣለበት መሆኑ ይታወቃል። በአገዛዙ የብልፅግና ካድሬዎች አማካኝነት የአማራን ህዝብ የህግና ስነ-ስርዓት አገልግሎት እንዳያገኝ በማድረግ የተለያየ የፖለቲካ ስያሜ በመስጠትና የአለማቀፍ መርህ በመጣስ ህግና ስነ-ስርዓትን ለፖለቲካ ፍጆታ በማዋል በተለያዩ አካባቢዎች የፍትህ እጦት እዲፈጠር ተደርጓል ። በመሆኑም የ102ኛ ኮር የህግና ስነ-ስርዓት አገልግሎት  ከወታደራዊ ግዳጅ ጎን ለጎን በተቆጣጠራቸው አካባቢዎች ከሰራዊታችን አልፎ ለአማራ ህዝብ የፍትህ አገልግሎት  አቅም በፈቀደ መልኩ እየሰጠ ይገኛል ሲል የ102ኛ ኮር የህግ መምሪያ ሀላፊ አርበኛ አበበ በላይ ገልጿል። ችግሩን በበዘላቂነት ለመቅረፍ ተከታታይ የህግና ስነ-ስርዓት ስልሰጠናዎች እንደሚቀጥሉ የመምሪያ ሀላፊው  ገልፀዋል ። አርበኛ አበበ  አያይዘው እንደገለፁት ከሆነ ከማንም ጋር ሰላም መፍጠር የማይፈልገው አገዛዙ በመላው ሀገሪቱ የተራዘመ  የጦርነት አዙሪት በመለኮስ በአማራ፣ በትግራይ፣ በኦሮሚያ፣በቤንሻንጉልና በአፋር ክልል ህግና ስነ-ስርዓት እንዳይከበር በማድረግ በዜጎች ላይ ከፍተኛ በደል ተፈፅሟል በማለት ተናግረዋል። በመጨረሻም የ102ኛ ኮር የህግና ስነ-ስርዓት ሰልጣኞች በታማኝነትና በልበ ሙሉነት  በየትኛዉም አስቸጋሪ የግዜና የቦታ ሁኔታ ቢሆን ከራሳችን በፊት ለወጣንለት አላማና  የሙያ መስክ ቅድሚያ እንሰጥአለን ሲሉ የዕለቱ ተመራቂዎች ቃለ-ምህላ ፈፅመዋል ። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል! "ክብር ለትግሉ ሰማዕታት" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ወሎ(ቤተ-አማራ) ምኒልክ ዕዝ የ102ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ሐምሌ 13/2018 ዓ.ም

ሰበር ዜና❗❗ በአቶ ተስፋዬ ጌታቸው ላይ ነጓድጓድ ክ/ጦር እርምጃ መወሰዱን ገለጸ !! ​ሀምሌ 13 ቀን 2018 ዓ.ም. ደብረብርሃን ​አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ ዘረያዕቆብ ኮር ነጎድጓድ ክ/ጦር ታላቅ ጀብድ መፈፀሙ ተሰማ። ቅዱስ የሆነውን የፋኖን ትግል ከድቶ በተለያዬ ቦታ ፋኖን በማስከበብ እንቅስቃሴዎች ውስጥ ተሳታፊ በመሆን በህብረተሰቡ ሰላምና ደህንነት ላይ ስጋት ለነበረው ለአቶ ተስፋዬ ጌታቸው አገዛዙ የባሶናወረና ሰላም እና ደህንነት ሀላፊ አድርጎ የሾመው ቢሆንም ፣ በነጓድጓድ ክ/ጦር የውስጥ ስፔሻሊስቶቹ በደ/ብረብርሃን ከተማ እርምጃ ተወስዶበታል ። ​ በግለሰቡ ላይ በተደረገው የቅርብ ክትትል እና በተሰበሰበው የደህንነት መረጃ መሰረት፣ እርምጃው የተወሰደው ዛሬ ጠዋት በተካሄደ ልዩ ኦፕሬሽን ነው። አቶ ተስፋዬ ጌታቸው ከፋኖ ተቋም በመክዳት የአገዛዙን ሹመት ተቀብሎ በአማራ ህዝብና ፋኖ ላይ የዘመተ እና ያስገደለ ከሀዲ መሆኑ ይታወቃል።ቀደም ሲል ከሌሎች ከሀድዎች ጋር በመሆን በአገዛዙ ሚዲያ ድርጅታችን አፋብንን እና የአማራን ህዝብ ሲዘልፍ የነበረው ተስፋዬ በአማራ ህዝብ ትግል ላይ ሻጥር መስራት እና ደም መርገጥ የማይቻል መሆኑን መቀጣጫ በማድረግ የአገዛዙን ሁሉ የከተማ ዙሪያ ምሽግ ዘልቀው በመግባት በምሀል ደ/ብርሃን አደባባይ እርምጃ ተወስዶበታል። የተወሰደውን እርምጃ ተከተሎ በደ/ብርሃን ከተማ በአመራሮችና ከሀድዎች ቤት ውጥረቱ ነግሷል። "የአማራን ህዝብ ህልውና ለማስከበርና ለማረጋገጥ የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል" ሲሉ አልሞ ገዳይ ጀግኖች ገልጸዋል። ክብር ለትግሉ ሰማዕታት ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ

201ኛ ኮር 54ክፍለጦር የመዝገቡ ዋለልኝ ሻለቃ እና109ኛ ኮር 99ኛ ክፍለጦር ኢንጅነር ክበር ተመስገን ሻለቃ ጮቄው ላይ ጠላትን በልኩ እያናገሩት ነው። ከስናን ወረዳ ወደ ጮቄው የሚንቀሳቀሰውን ጠላት206ኛ ኮር 24ኛ ክፍለጦር ስናን አባጅሜ ሻለቃ እጅ በእጅ በቦብ እያጨማለቁት ነው። በርካታ ጀኔራሎች እና ኮረኔሎችን አሰልፍ ከደንበጫ ወደ ገሊላ እና ከድጎ ፅዮን ወደ አልማ የሚንቀሳቀሰው ሀይል እና ከስናን ወረዳ ወደ መስታይት የሚንቀሳቀሰው ጠላት ሰባዊና ቁሳዊ ኪሳራን እያስተናገደ ነው ። ከዙ-23 እሰከ መድፍ እና ድሮን ቢያሰልፍም ጠላት ሬሳውን በየጫካው እያጠባጠበ ነው። በእውር ድብር የሚተኩሰው ከባድ መሳሪያም ንፁሃንን እየጨፈጨፈ ቀጥሏል። የዐምሓራ ሕዝብ በዚህ አረመኔ* ስርዓት ዋጋ እየቀፈለ ነው። የአለም አቀፍ ማህበረሰብ እየጠፋ ላለውን ሕዝብ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል። ውጊያዎች በሁሉም ቀጠና እንደቀጠሉ ናቸው። አዲስ ትውልድ፣አዲስ አስተሳሰብ ፣አዲስ ተስፋ! ቴዎድሮስ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ሐምሌ13/2018ዓ.ም

የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ በደረፎ ክላስተር የመጀመሪያውን ጠቅላላ ጉባኤ በታላቅ ድምቀት አካሄደ!!              ሐምሌ 13/2018 ዓ.ም በአማራ ህዝብ የህልውና ትግል ታሪክ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት የክላስተር ጠቅላላ ጉባኤ ተካሄደ። በአፋብን  የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ተጉለት አውራጃ፣ አንኮበር ቀጠና በደረፎ ክላስተር ያሰናዳው ይህ ጉባኤ፤ የዕዙ ከፍተኛ አመራሮች እና የክላስተሩ ስራ አስፈፃሚዎች በተገኙበት በታላቅ ወታደራዊና ድርጅታዊ ስነ-ስርዓት ተካሂዷል። ጉባኤው የወደፊት የትግል አቅጣጫዎችንና የህዝቡን ህልውና የሚያረጋግጡ ቁልፍ አጀንዳዎችን በጥልቀት የመከረ ሲሆን፣ በዋናነትም በሚከተሉት አራት አበይት ነጥቦች ላይ ትኩረቱን አድርጓል፡- 1ኛ.የአፈጻጸም ሪፖርት ማቅረብ፡ የአጠቃላይ የክላስተሩንና የቀበሌዎችን የስራ እንቅስቃሴ የሚያሳይ ዝርዝር ሪፖርት ቀርቦ አጠቃላይ ዳሰሳ ተደርጎበታል። 2ኛ.ጥልቅ ግምገማ፡ ያለፉትን ወታደራዊ፣ ድርጅታዊና ህዝባዊ ስራዎችን ጥንካሬንና ክፍተትን በመለየት አጠቃላይ ግምገማ ተካሂዷል። 3ኛ.ወቅታዊ ሁኔታዎችና የአደረጃጀት ማሻሻያ፡ አሁን ባለው የትግል እንቅስቃሴ፣ ወቅታዊ ሀገራዊ ሁኔታዎች እና ድርጅታዊ አደረጃጀቶችን የበለጠ ለማጠናከር በሚያስችሉ ማሻሻያዎች ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል። 3ኛ.ቀጣይ አቅጣጫዎች፡ የትግሉን መንፈስ ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግሩና የህዝቡን ደህንነት የሚያረጋግጡ የወደፊት ስትራቴጂካዊ አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል። በጉባኤው ማጠቃለያ ላይ የተገኙት ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት፤ የትግሉን ፈጣን ዕድገትና ጥንካሬ አጉልተው አሳይተዋል። ትግሉ በሶስት ዓመታት አጭር ጊዜ ውስጥ ከሰፈርና ከቀበሌ አደረጃጀት ተሻግሮ፣ መላውን ህዝብ ያስተባበረ ታላቅ የአማራ ድርጅት መፍጠር መቻሉን ገልጸዋል። ህዝብን እንደ ህዝብ፣ ጦርን ደግሞ እንደ ጦር አደራጅቶ ዓመታዊ የክንውን ሒደትን በምክር ቤት ደረጃ መገምገም መቻሉ የትግሉን ብስለትና የደረሰበትን ከፍተኛ የለውጥ ደረጃ የሚያሳይ ህያው ማረጋገጫ መሆኑን አስምረውበታል። " ክብር ለትግሉ ሰማዕታት"! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን"! የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!!

የምስራቅ ዕዝ ምኞትን አክሽፈናል።   የአማራ ፋኖ በጠላት እቅድ ሰተት ብሎ የሚገባ የመሀይሞች ስብስብ አይደለም። ፋኖ ውትድርናን  ከማወቅም በላይ የህልውና ትግል እንዴት እንደሚመራ ጠንቅቀው የሚያውቁ ጦር መሪዎችን የያዘ ሀይል ነው። ፋኖ ፖለቲካ በምን መልኩ እንደሚሰራ እና ሕዝብን ከጦር ጋር እንዴት አዋህዶ  ለዓላማ መሰለፍ እንደሚቻል  የሚያውቁ ፖለቲከኞች የያዘ ተቋም ነው። ከሶስት ጀኔራሎች እና ከ7 በላይ ኮረኔሎች   እና የሀገሪትን መከላከያ ይዞ ጎጃምን ለመውረር ቢሞክርም በፍፁም ያሰበውን ሊያሳካ አልቻለም።      ከአማኑኤል የነጭ ፣ ከስናን የጠድ፣ ከደጋዳሞት ፈረስቤት ፣ ከቢቡኝ ድጎ ፅዮን ፣ ከደጀን የትኖራ ፣ ከሞጣ ከተማ በመሆን በርካታ መድፍ በማሰለፍ  ማህበረሰብን እየጨፈጨፈ ነው። በዚህም በርካታ ንፁሀን ከነቤታቸው አጠናል። መሀመድ ተሰማ የሚለው ፍፁም ከእውነት የራቀ ደረቅ ፕሮፖጋንዳ ነው። ፋኖ የሽምቅ ተዋጊ ነው  ቦታዎችን ሊይዝም ሊለቅም የሚችለው በራሱ ቀመር ነው። የቦታወች በፈለገው ስዓት መያዝ የሚያስችል አቅም አለው። በዛሬው ዕለትም ፋኖ በሚፈልገው ቦታ ወደ  ከቢቡኝ ወረዳ ሰንሰላታማ የጮቄ ተራራ በመሳብ እያናገሩት ይገኛሉ። በረካታ የጠላት ሀይል እየተደመሰሰ ይገኛል ። ውጊያዎች  የጠላትን ቅስም በሚሰብር መልኩ እየተደረጉ ነው። በራሳችን ስልተ ምት ወደ ምንፈልገው ቀለበቀት እያስገባነው እንጅ የተደመሰሰ ፋኖ የለም። የት ቦታ ማነን ደመሰሱ? ይህን በስም ሊመልሱልህ አይችሉም ።ተራራር ቧጭሮ ከመመለስ ውጪ ሌላ አማራጭ የለውም ። የፋኖ አቅም ገና እየተገለ ይገኛል ። አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ ፣አዲስ ተስፋ!   ቴዎድሮስ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ       ሐምሌ 12/2018ዓ.ም

ጉና ክፍለ ጦር ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ ውይይት አካሄደ ​ጎንደር – በሜጀር ጄነራል ውብአንተ አባተ ኮር ስር የሚገኘው የጉና ክፍለ ጦር፣ የሃገረ ቢዘን ብርጌድ ከፍተኛ አመራሮችና ታጋዮች በተገኙ
+3
ጉና ክፍለ ጦር ወቅታዊ ጉዳዮችን አስመልክቶ ውይይት አካሄደጎንደር – በሜጀር ጄነራል ውብአንተ አባተ ኮር ስር የሚገኘው የጉና ክፍለ ጦር፣ የሃገረ ቢዘን ብርጌድ ከፍተኛ አመራሮችና ታጋዮች በተገኙበት በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ የሁለት ቀናት ስኬታማ ውይይት አካሄደ። ​በውይይት መድረኩ የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብ) ወታደራዊ ስልጠና መምሪያ ምክትል ኃላፊ ኮሎኔል ሙላቴ ሲሳይ፣ የሜጀር ጄነራል ውብአንተ አባተ ኮር ዘመቻ መሪ አርበኛ ቢራራ ደምሴ፣ የጉና ክፍለ ጦር ዋና ወታደራዊ አዛዥ አርበኛ ደሳለኝን ጨምሮ ሌሎች ከፍተኛ የጦር መሪዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። ​በውይይቱ ላይ የትግሉ መነሻ፣ የደረሰበት ደረጃ እና የወደፊት የትግል አቅጣጫዎች ላይ ጥልቅ ትንታኔዎች ቀርበዋል። በተጨማሪም ታጋዮች የአማራዊ ብሔርተኝነት ግንዛቤን እንዲያጎለብቱ የሚያስችል ስልጠና የተሰጠ ሲሆን፣ የትግሉን አሁናዊ ቁመና በሚያጠናክር መልኩ ሰፊ የሃሳብ ልውውጥ ተደርጓል። ​የጉና ክፍለ ጦር የህዝብ ግንኙነት ክፍል እንደገለጸው፣ መድረኩ ወንድማዊ እና ጓዳዊ መንፈስ በተሞላበት መልኩ በስኬት መጠናቀቁን አስታውቋል።

የአማራ ልጅ ፋኖ የጀግንነት የፅናት ተምሳሌት!! ​በነፃነት የመኖር ማንነቱና የታሪክ አደራው የተቀበለው ​የአማራ ልጅ ፋኖ ማለት የጥንካሬ፣ የኩራትና የታሪክ ምስክር ነው። ከቀደሙት አባቶች የተረከበውን የነፃነትና የክብር አደራ አንግቦ፣ የነገውን ብሩህ ተስፋ ለመቅረጽ የሚተጋ የቁርጥ ቀን ልጅ ነው። ስሙ የነፃነት ጥሪ፣ መገኘቱ ደግሞ የፍትህና የጽናት ጋሻ የሚገርመው የጀግንነት መገለጫ ​በፈተናዎች ውስጥ የማይናወጥ፣ በግርማ ሞገሱ ፈተናዎችን የሚያስደነግጥ ኃይል አለው። ​እንደ አለት የጠነከረ ጽናት ማዕበልና አውሎ ንፋስ የማይበግረው፣ ለእውነትና ለወገኑ እምነት የቆመ የቁርጥ ቀን ጀግና። ​የማይፈራ ልብ ለማንነቱና ለህዝቡ ክብር ሲል ማንኛውንም መስዋዕትነት ለመክፈል ወደኋላ የማይል።​የኩራት መገለጫ በአካሄዱ ግርማ ሞገስ፣ በንግግሩ ደግሞ እምነትና ተስፋ የሚታይበት እውነተኛ የክብር ምልክት። የሚያስደምመው ታላቅ ዓላማ ​የፋኖ ዓላማ ግልጽና መሠረተ-ጽኑ ነው፤ እሱም ፍትህ፣ እኩልነት፣ ማንነትና ዘላቂ ሰላም ማስፈን ነው። ዓላማችን የግፍ ቀንበርን ሰብሮ፣ በእኩልነትና በነፃነት የሚኖሩ፣ በአለማችን የተከበሩ ማህበረሰብ መገንባት ነው። ​ይህ ጉዞ ለራስ ብቻ ሳይሆን፣ ለትውልድ የሚተርፍ የፍትህና የክብር አሻራ ለመተው የሚደረግ የታሪክ ጉዞ ነው። የአማራ ልጅ ፋኖ የትላንት ታሪክ ኩራት፣ የዛሬ የጽናት መሠረት፣ የነገ የሰላምና የነፃነት ዋስትና የሆነው የአማራ ልጅ ፋኖ ብቻ ነው!! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው እዝ ወታደራዊ እቅድና እስትራቴጂ ዋና መምሪያ መቶ አለቃ ልመነው ሻወል ደመቀ

የታሪክ አዲስ ምዕራፍ በደጋ ዳሞት፦ የቴዎድሮስ ዕዝ አናብስቶችና የፈርስቤት የጨበጣ ውጊያ!! በአራቱም ማዕዘናት አስደማሚ የድል ታሪኮችን እየቀረጸ የሚገኘው የአማራ ልጅ ፋኖ በደጋ ዳሞት ምድር ሌላ
የታሪክ አዲስ ምዕራፍ በደጋ ዳሞት፦ የቴዎድሮስ ዕዝ አናብስቶችና የፈርስቤት የጨበጣ ውጊያ!! በአራቱም ማዕዘናት አስደማሚ የድል ታሪኮችን እየቀረጸ የሚገኘው የአማራ ልጅ ፋኖ በደጋ ዳሞት ምድር ሌላ አዲስ ታሪክ እየጻፈ ይገኛል። የብርሃን መፍለቂያና የጀግኖች ማፍሪያ በሆነችው በደጋ ዳሞት ፈርስቤት፣ በታሪክ ታይቶ የማይታወቅ እጅግ አስገራሚና ታላቅ ፍልሚያ እየተካሄደ ነው። ይህ ፍልሚያ ታሪካዊውን የአፋብን የጦር ሜዳ ምዕራፍ በሚያስነቅፍ መልኩ በጀግንነት እየተመራ ይገኛል። የቀድሞ መሪዎችን የጀግንነት ስም የሰነቀው የምዕራብ አማራ ቴዎድሮስ ዕዝ" አናብስቶች፣ የንፅህና እና የፅናት ምልክት በሆነው የደጋ ዳሞት ተራራማ ምድር ላይ የአብይ አህመድ አርመኔያውያን ሰራዊት በፅናት በመመከት አልፎም በሰዓቱ በደጋ ዳሞት እየተካሄደ ያለው የጨበጣ ውጊያ በከፍተኛ ሁኔታ ተጠናክሮ የቀጠለ ቤሆንም የጦርነቱ ግለትና የጀግኖቹ መጋደል የኢትዮጵያን የነፃነት ታሪክ በደማቅ ቀለም የሚያድስ ሆኗል። ይህ ውጊያ ተራ የመከላከል ጦርነት አይደለም፤ የህልውና እና የክብር ማረጋገጫ እንጂ! እኒህ ቆራጥ የፋኖ ታጋዮች ከጠላት ጋር ፊት ለፊት እየተያዩ፣ አንገት ለአንገት ተያይዘው፣ በመሃላቸው ላለው ህዝብ እና ለተቀደሰው አላማቸው ሲሉ በክብር እየተዋደቁ ይገኛሉ። እያንዳንዱ ሰከንድ፣ እያንዳንዱ ፍልሚያ የጀግንነት መዝገብ እየሆነ ነው። በደጋ ዳሞት ፈርስቤት እየተቀጣጠለ ያለው ይሄው ፍልሚያ፣ የፋኖን የማይበገሬነት እና የአማራን ህዝብ የነፃነት ጥማት ለዓለም ያሳየበት አጋጣሚ ሆኗል። ታሪክ እያዩ መሸሽ የሌለባቸው እኒህ አናብስቶች፣ ዛሬም በደማቸው አዲስ የታሪክ ምዕራፍ እየጻፉ፣ የድል ብርሃንን እያበሰሩ ይገኛሉ! ​#ደጋ_ዳሞት #ፋኖ #አማራ_ቴዎድሮስ_ዕዝ #የአማራ_ተጋድሎ #ፈርስቤት Dave Amhara

በቅርቡ በአሜሪካ ኒውዮርክ ከተማ ጎዳናዎች ላይ አንድ ታዋቂ ዩቲዩበር (YouTuber) ሰዎችን እያስቆመ በሚያደርገው ተንቀሳቃሽ ቃለመጠይቅ ላይ፣ አቀራረቧ ፈረንጅ የሚመስል ነገር ግን በዜግነቷ ኢትዮጵያዊት የሆነች ወጣት የሰጠችው ምላሽ ማህበራዊ ሚዲያውን በከፍተኛ ሁኔታ እያነጋገረ ይገኛል። "ቪኪ" (Viki) በሚል ስም ራሷን ያስተዋወቀችውና ወደ አሜሪካ ከመጣች ገና ሁለት ዓመታት ብቻ እንደሆናት የገለጸችው ይህች ወጣት፣ ጋዜጠኛው በኒውዮርክ ከተማ ለመኖር በወር ምን ያህል ወጪ እንደምታወጣ ላቀረበላት ጥያቄ የሰጠችው ምላሽ እጅግ አስደንጋጭ ነበር። በየወሩ ከ35 ሺህ እስከ 40 ሺህ ዶላር ወጪ እንደምታደርግ የተናገረች ሲሆን፣ ይህንን ያህል ከፍተኛ የገንዘብ መጠን የምታገኝበትን የስራ መስክ ስትጠየቅ ግን "ምንም አይነት ስራ የለኝም" ስትል ምላሽ ሰጥታለች። ይህ በየወሩ የምታወጣው 40 ሺህ ዶላር አሁን ባለው የኢኮኖሚ እውነታ ወደ ኢትዮጵያ ብር ሲቀየር ከ6.4 ሚሊዮን ብር በላይ የሚገመት በመሆኑ፣ ያለምንም የስራ ገቢ ይህንን ያህል የቅንጦት ሕይወት እንዴት ልትኖር እንደቻለች በጠያቂውም ሆነ በተመልካቹ ዘንድ ትልቅ ጥያቄና መደናገጥን ፈጥሯል። ይሁን እንጂ ከጉዳዩ በስተጀርባ ያለው እውነት ሲመረመር፣ ይህች ወጣት በኢትዮጵያ ገቢዎች ሚኒስቴር ውስጥ ከፍተኛ ባለስልጣን የነበሩት የባለስልጣኑ የአቶ ዘሱ ወልደጊዮርጊስ ልጅ መሆኗ ተነግሯል። ይህ መረጃ ይፋ መሆኑን ተከትሎ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ የሚገኙ በርካታ ኢትዮጵያውያን ከፍተኛ ድምፅ እያሰሙ ይገኛሉ። የኢትዮጵያ ህዝብ የእለት ጉርሱን ለመሸፈንና የኑሮ ውድነቱን ለመቋቋም ሌሊት ከቀን እየደከመ፣ በግዴታም ይሁን በፈቃደኝነት የሚከፍለው ግብርና ታክስ ለሀገር ልማትና ለህዝብ አገልግሎት መዋል ሲገባው፣ የከፍተኛ ባለስልጣናት ልጆች በውጭ ሀገር ያለ ምንም ስራ በንጹሃን ዜጎች ገንዘብ እንዲህ ባለ የቅንጦትና የአምሮት ሕይወት እንዲኖሩበት መደረጉ እጅግ አሳዛኝና አሳሳቢ ክስተት ነው። እንዲህ አይነቶቹ ምናልባትም በሙስና እና በህዝብ ሀብት ያለአግባብ መበልጸግ ላይ የሚነሱ ጥርጣሬዎች በተቋማት ላይ ያለውን የህዝብ እምነት ሙሉ በሙሉ የሚሸረሽሩ በመሆናቸው፣ የሚመለከታቸው የህግ አካላት በባለስልጣናቱና በቤተሰቦቻቸው የሀብት ምንጭ ላይ ጥብቅና ግልጽ የሆነ ማጣራት ሊያደርጉ እንደሚገባ የብዙዎች ድምጽ እየሆነ ነው።

አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ የሰገነት ብርጌድ አባት አርበኛ የግምገማ መርሃ-ግብር አካሄደ። አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሰገነት ብርጌድ ሐምሌ 12 /2018 ዓ.ም አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ በተጉለትና ቡልጋ አውራጃ በተጉለት ቀጠና ሳሲት ክላስተር የሚገኘው የሰገነት ብርጌድ አባት አርበኛ ዓመታዊ የስራ አፈፃጸም ግምገማ መድረክ አካሄደ።መድረኩን የመሩት የዕዝ የፖለቲካ አመራሮች አርበኛ መስፍን ተስፋዬና አርበኛ ግዛቸው ሳህለ ሲሆኑ ተጉለት ያለውን የትላንት የታሪክ ዕርሾ በእኛ ትውልድ አጠናክሮ በመቀጠል የአባቶቹን የአርበኝነት ቃልኪዳን በመፈጸም ትውልዳዊ ሀላፊነቱን በመወጣት የአማራ ህልውና ለማረጋገጥ ታሪካዊ ሚናውን እየተወጣ ይገኛል ያሉ ሲሆን አርበኝነትና ተጉለት የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታ እንደሆኑም ከፍተኛ አመራሮቹ አንስተዋል።ይህ በእንድህ እንዳለ የሰገነት ብርጌ አመራሮችና አባላት ራሳችንን ከምንግዜውም በላይ በማጠናከር ከኋላ ደጀንነት በዘለለ እንደ ህዝብ ለመጣብን የህልውና አደጋ ለመቀልበስ ለሚደረገው ዘርፈ ብዙ ትግል በግንባር ጭምር ከመደበኛ ሰራዊቱ ጋር በመሰለፍ እንደሚፋለሙ ቃል የገቡ ሲሆን አገዛዙ ፀረ-አማራ ብቻ ሳይሆን ፀረ-ሰው መሆኑንም አንስተዋል።ሌላው ዓመታዊ የአባት አርበኛው የስራ ክንውንና የግዳጅ አፈጻጸም በጥንካሬና በድክመት የተገመገመ ሲሆን በአመራር ሽግሽግ ምክንያት ተጓድሎ የነበረውን ክፍት የአመራር ቦታ ሟሟላት የተቻለ ሲሆን በመጨረሻም ወቅቱን የሚመጥን ልዩ ልዩ የክላስተር፣የቀጠና፣የዕዝና የድርጅት ተልዕኮዎችን በመስጠት የቀጣይ የስራ አቅጣጫ በማስቀመጥ መርሃ ግብሩ ተጠናቋል። "ክብር ለትግሉ ሰማዕታት"! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ