ar
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

الذهاب إلى القناة على Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

إظهار المزيد
2 936
المشتركون
-124 ساعات
+3307 أيام
+38330 أيام
أرشيف المشاركات
ሰበር ባሕርዳር አሁን በዚህ ሰአት  ባህርዳር  ፈለገህይወት ሆስፒታል የአንድ ፖሊስ አመራር አስክሬን ገብቶ  ፖሊሶቹ የሆስፒታሉን ግቢ በጥይት እየበጠብጡት እንደሚገኙ ምንጮች በውስጥ ልከውልናል

#_3_የፓራ_ኮማንዶ አባላት ፋኖን ተቀላቀሉ የብልጽግና ካምፕ ባዶ ራቁቱን ቀርቷል !! ~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~ ....... ዛሬ ሰኔ 30/2018 ዓ.ም ብልሆቹ የምረት ጥሪውን ተቀብለው
+4
#_3_የፓራ_ኮማንዶ አባላት ፋኖን ተቀላቀሉ የብልጽግና ካምፕ ባዶ ራቁቱን ቀርቷል !! ~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~~ ....... ዛሬ ሰኔ 30/2018 ዓ.ም ብልሆቹ የምረት ጥሪውን ተቀብለው ህይወታቸውን በማትረፍ ላይ ናቸው የፓራ ኮማንዶ አባላቱ በዛሬው እለት ከግንደ ወይን እና ከደብረ ወርቅ ከተማ በመውጣት 201ኛ ኮር 74ኛ ክፍለ ጦርን የተቀላቀሉ ሲሆን፦ 1.ይልቃል አባየሁ....ፓራኮማንዶ 2.ጥጋቡ የሺ......ፓራ ኮማንዶ 3.ሐብቴ ቁሜ.....ፓራ ኮማንዶ በዛሬው እለት የተቀላቀሉ ሲሆን በክፍለ ጦር አመራሮች አቀባበል ተደርጎላቸዋል። ሁሉም እንደተናገሩት ከሆነ ማንም እዛ ውስጥ መቆየት አይፈልግም የትጥቅ ችግር ስለነበረብን ፍላጎታችን አሳክተን ወደ ወንድሞቻችን ተመልሰናል በማለት ተናግረዋል። ጊዜው አልረፈደም አሁንም ቢሆን ወደ ማንነታቹህ ተመለሱ ኑ እንቀበላቹሀለን እንደማንኛውም ሰው መደበኛ ህይወታቹሁ መኖር የምትችሉ መሆኑን ድርጅታችን ጥሪ አቅርቦላቹሀል። የአፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት

አስቴጎማ ተራራ ክፍለጦር በመኮይ ከተማ በአገዛዙ ጦር ላይ መብረቃዊ ጥቃት በመሰዘር ታላቅ ገድል ፈፅሟል!! ቀን 30/10/2018 ዓ.ም ከሰኔ 29 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ በትጥቅ ትግሉ መስመር አዲስ አንጸባራቂ ድል ተመዝግቧል። በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ይፋትና ጥሙጋ አውራጃ አንፆኪያ ገምዛ ክላስተር መኮይ ከተማ «44ቱ» ተብሎ በሚጠራው ልዩ ቦታ ላይ ሰፍሮ በነበረው የአገዛዙ ጥምር ጦር ላይ የተቀናጀና ስልታዊ ድንገተኛ ጥቃት ተፈጽሟል። በአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ስር የሚገኘው የሙሀመድ ቢሆነኝ ኮር «አስቴጎማ ተራራ ክፍለጦር» ይህንን የላቀ ወታደራዊ ኦፕሬሽን አስደማሚ ገድል ፈፅሟል። የክፍለጦሩ የቁርጥ ቀን ታጋዮች በከፈቱት ፈጣን ማጥቃት የአገዛዙን ዙፋን አስጠባቂ ሠራዊትና ተባባሪ ጥምር ኃይሎች ከጥቅም ውጪ ተደርገዋል። በጠላት ላይ የደረሰው ወታደራዊ ኪሳራ፦ . 10 የመከላከያ ሠራዊት አባላት የተደመሰሰ . ከ13 በላይ የቆሰሉ ሲሆን በርካቶቹ የጠላት ኃይል ተበታትኗል። የክፍለ ጦሩ አባላት የተሰጣቸውን ግዳጅ በአስተማማኝ ሁኔታ ከፈጸሙ በኋላ፣ ያለምንም የሰውና የማተርያል ጉዳት ሳይደርስባቸው በሰላም ወደ ምሽጋቸው ተመልሰዋል። ሽንፈት የገጠመው ጠላት የበቀል በትሩን በንጹኃን ዜጎች መኖሪያ መንደሮች ላይ የ«ዙ-23» ፀረ-አውሮፕላን መሣሪያን በዘፈቀደ ሲተኩስ በነበረው አሸባሪ ኃይል ላይ የተወሰደው እርምጃ፣ የትጥቅ ትግሉን የህልውናና የነጻነት ጉዞ ይበልጥ ያፋጠነ ሆኗል። የሙሀመድ ቢሆነኝ ኮር ሚዲያና ኮሚኒኬሽን ክፍል እንደገለጸው፣ የሕዝብን ሙሉ ነጻነትና ደህንነት እስኪረጋገጥ ድረስ የተባበረው የፋኖ ክንድ በአገዛዙ ላይ ማረፉን ይቀጥላል ሲል ገልጿል። " ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

በጊዜያዊ ማስታገሻዎች ሀገርን ረጅም መንገድ መውሰድ አይቻልም - ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) መንግሥት በጦርነትና በድርቅ ምክንያት የዕለት ደራሽ እርዳታ ያጡ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች እያሉ፣ የሰብዓዊ ድጋፍ ፈላጊዎችን ቁጥር ከ20 ሚሊዮን በላይ ወደ 2 ነጥብ 3 ሚሊዮን ዝቅ አድርጎ ማቅረቡ “ፖለቲካዊ ቁጥር ማሳመር እንጂ ከእውነት የራቀ ነው” ሲሉ የምክር ቤት አባል ደሳለኝ ጫኔ(ዶ/ር) ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ባቀረቡት ጥያቄ ተናገሩ። በምክር ቤቱ መደበኛ ስብሰባ ላይ ጥያቄ ያነሱት ደሳለኝ ጫኔ፤ መንግሥት የመረጃ ማጥራት ሥራ ሠርቻለሁ በሚል ሰብዓዊ ድጋፍ የሚፈልጉ ዜጎችን ቁጥር እጅግ አሳንሶ ማቅረቡን ተቃውመዋል። በተለያዩ አካባቢዎች ለቤተሰቦቻቸው የሚሆን በቂ ምርት የማያመርቱና ለከፋ ችግር የተጋለጡ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ዜጎች መኖራቸውን በመጠቆም፣ “ይህንን ቁጥር ወደ 2 ነጥብ 3 ሚሊዮን ዝቅ አድርጎ ማቅረብ ፖለቲካዊ ቁጥር ማሳመር እንጂ የዜጎችን ሕይወት በተጨባጭ የሚያሳይ አይደለም” ሲሉ ወቅሰዋል። ከተለያዩ ዓለም አቀፍ የእርዳታ ተቋማት የሚወጡ መረጃዎችን የጠቀሱት የምክር ቤት አባሉ፤ ተቋማቱ የሚያስቀምጡት ዝቅተኛ ግምት እንኳ ኢትዮጵያ ውስጥ ከ15 ነጥብ 8 እስከ 21 ነጥብ 4 ሚሊዮን የሚሆኑ ዜጎች በከፍተኛ የምግብ እጥረት ውስጥ እንደሚገኙ የሚያሳይ መሆኑን አብራርተዋል። ዶ/ር ደሳለኝ አክለውም መንግሥታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች የእርዳታ እህል እንዳያከፋፍሉ በመንግሥት መከልከላቸውንና ድጋፋቸውን ወደ ጥሬ ገንዘብ እንዲቀይሩ መገደዳቸውን ገልጸዋል። ይህ አሠራር አሁን ካለው የገበያ የዋጋ ግሽበት አንጻር “በርካታ ቤተሰቦችን ለከፋ የምግብ ዋስትና እጥረት የሚዳርግ ነው” ሲሉ ስጋታቸውን ገልጸዋል።

ወደ ትግራይ ግንባር ትዘምታላቹህ የተባሉ 4 የአገዛዙ ቅጥረኛ የሚሊሻ ሰራዊት አባላት 64ኛ ክ/ጦር ተቀላቀሉ። 64ኛ ክ/ጦር ሰኔ 30/2018 ዓ.ም ~~~~ በሸበል በረንታ ወረዳ የዕድውሃ እና መረገጭ ከተማ የሚገኘው የአገዛዙ ቅጥረኛ ሰራዊት ጥምር ጦር አባል የነበሩ አገዛዙ በአማራ ህዝብ ላይ ሲፈፅም የነበረውን ግፍ እና በደል በመረዳት ዛሬም ከአማራ ህዝብ እና ከሌሎች ህዝቦች ጋር ወንድም የሆነው የትግራይን ህዝብ ትወጋላቹህ ተብለው ቢታዘዙም ይህ ስረዓት የህዝብ ፀር መሆኑን በመረዳት ወደ ትግራይ ግንባር አንሄድም፣ የትግራይ ህዝብ ጋር ጦርነት አንገጥምም፣ የትግራይ ህዝብ ወንድማችን ነው የትግራይን ህዝብ ለሁለተኛ ግዜ አንወጋም በማለት ሰኔ 30/2018 ዓ.ም አፋብን 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ከእነ ሙሉ ትጥቃቸው ተቀላቅለዋል። 1ኛ.አባተ አራጋው አንድ ክላሽ ከ34 ጥይት፣ የደረት ትጥቅ እና ከአንድ ካዝና ጋር 2ኛ.ዘገየ ጌትነት አንድ ኮሪያ ክላሽ ከ31 ጥይት እና ከአንድ ካዝና ጋር 3ኛ.ማስሬ ወንድሜነህ አብራራው መስሪያ ከ13 ጥይት ጋር 4ኛ.ዘሪሁን አቢ የተባሉ የአገዛዙ መንገድ መሪ ቅጥረኛ ሚሊሻ ጥምር ጦር አባል ወደ ፋኖ ተቀላቅለዋል። አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ!!                ሰኔ 30/2018 ዓ.ም አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ሕዝብ ግንኙነት

ትናንት ለዛሬ ሌሊት በምዕራብ ወሎ ግንባር ቢሊ ታዳጊ ከተማን ሙሉ በሙሉ ነጻ ማድረግ ተችሏል!! የአፋብን ወሎ ቤተ- አማራ ምኒልክ እዝ 105 ኛ ኮር 29ኛ ክፍለ ጦር በሰራው የሌሊት ኦፕሬሽን ቢሊ ታዳጊ ከተማን ነጻ ማውጣት የቻለ ሲሆን ከአመሻሽ 12 ሰዓት ጀምሮ እስከ እኩለ ሌሊት ድረስ ሞት አይፈሬዎቹ የመካነሰላም አናብስት ጠላትን መፈናፈኛ አሳጥተው የጦር ሰፈራቸውን አስለቅቀዋል:: ኦፕሬሽኑ ላይ የተሳተፉት የ29ኛ ክፍለ ጦር ቃኝ አባላት በተለመደው ፈጣን የውጊያ ስልታቸው ጠላትን አናብዘው ሙት እና ቁስለኛ አስታቅፈውታል:: በሌሊቱ ኦፕሬሽን የተደመሰሱ እና የቆሰሉ የጠላት ኃይል አባላትን ትክክለኛ ቁጥር ለማወቅ የሰአቱ ሁኔታ አስቻይ ባይሆንም የውስጥ ወታደራዊ ምንጮች እንደተናገሩት ጠላት ያላሰበው ሽንፈት ገጥሞት አባላቱን ተነጥቋል:: ከሞት ያድነው ይመስል 3 ዲሽቃና 2 ሞርተር ከበርካታ የቡድን መሳሪያዎች ጋር ይዞ የነበረው ጠላት የ29 ክፍለ ጦር ቃኝን ወደ ሌላ ቀጠና መንቀሳቀስ ተከትሎ ወደ ቢሊ ታዳጊ ከተማ ቢገባም ቃኝይቱ በብርሀን ፍጥነት ተመልሳ ከ3ተኛ ሻለቃ ጋር በመናበብ ስትለበልበው የተማመነበትን የሽፋን እና የቡድን መሳሪያ ሁሉ ነቅሎ እግሬ አውጭኝ ብሎ እንደ ልማዱ ወደመጣበት ሊፈረጥጥ ችሏል:: መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል!! ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን መምሪያ!! ሰኔ 30 ቀን 2018 ዓ.ም

በሁለት እጅ እነሴ ወረዳ ቆንተር ቀበሌ ላይ በወቅታዊ ጉዳዮች በወረዳው ጊዜያዊ መንግስት አመራሮች በመገኘት ውይይት ተካሄደ። ============================= ....ሰኔ30/2018 ዓ.ም የአፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 54ኛ ክ/ጦር በ2እጁ እነሴ ወረዳ ከውጊያው ጎን ለጎን ቆንተር ቀበሌ ህዝብ ጋር ውይይት ተደርጓል። ➺ በፍትህ አሰጣጥ ና የመልካም አስ/ር ➺በፀጥታ ዙሪያ ያሉ ችግሮችን በመለየት ➺የሐብት አሰባሰብን በተመለከተ ➺የወል መሬት አጠቃቀም በተመለከተ ➺የአፋብን ትግል ከየት ወደየት አሁን የደረሰበት ሁኔታ እና ህዝባዊ አስተዳደርን ጨምሮ በመገምገመ የወደፊት የስራ አቅጣጫ ማስቀመጥ የተቻለ ሲሆን ትግላችን አሁን ላይትግሉ የደረሰበትን ሁኔታ አጭር ማብራሪያ በኮሩ እና በጊዜያዊ መንግስት አመራሮች የማስረዳት ስራ ተሰርቷል። እንደራጃለን ! እንመክራለን እንፈፅማለን!! አዲስ ትውለድ፣ አዲስ አስተሳሰብ፣ አዲስ ተስፋ!! አፋብን ቴወድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት

በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ይፋትና ጥሙጋ አውራጃ ልዩ ቦታው በአርማንያ ቀበሌ በአገዛዙ ሀይሎች በተፈፀመ የጦር ወንጀል አቶ ወንዳፍራሽ ንጉሴ የተባሉ አርሶ አደር በግፍ መገደላቸውን ተሰማ! ሰኔ 29/2018ዓ.ም የጦር ወንጀለኛው የብልፅግናው አገዛዝ በአማራ ህዝብ ላይ ያነጣጠረ ስርዓት ወለድ ታሪክ ይቅር የማይላቸውን ግፎች በህዝባችን ላይ በየቀኑ እየፈፀመ ሲሆን ሰኔ 25 ቀን 2018ዓ.ም ከምሽቱ 4:00 ላይ ከመኖሪያ ቤታቸው በአገዛዙ ሀይሎች የተወሰደው የአርማኒያ ቀበሌ ነዋሪ የ48 ዓመቱ ጎልማሳ አርሶ አደር አቶ ወንዳፍራሽ ንጉሴ እጅግ አሰቃቂ በሆነ አገዳደል በአገዛዙ ሀይሎች ህይዎቱ ማለፉን የአካባቢው ነዋሪዎች ተናገሩ። በሸዋ ጠቅላይ ግዛት ይፋትና ጥሙጋ አውራጃ ስር የምትገኘው የአርማኒያ ቀበሌ ታዳጊ ከተማ ለበርካታ ወራት በአማራ ፋኖ ቁጥጥር ስር የቆየች ሲሆን በቅርቡ ወደ ቀጠናው የገባው የአገዛዙ ኮማንዶ ክፍለጦር በንፁሀን ወገኖች ላይ በየቀኑ እየፈፀመ ያለው የጦር ወንጀል ተጠናክሮ የቀጠለ ሲሆን የሁለት ልጆች አባት የሆነው አርሶ አደር አቶ ወንዳፍራሽ ንጉሴ በመኖሪያ ቤቱ በምሽት በተወሰደ ማግስት ሁለት ዓይኖቹን በማውለቅ የቀኝ እጁን በገጀራ በመቁረጥ ለአንድ ቀን ካሳደሩት በኋላ በሁለተኛው ቀን ሙሉ ሰውነቱን በገጀራና በጩቤ በመቆራረጥ እጅግ ዘግናኝ በሆነ አገዳደል ህይዎቱን ማጥፋታቸውን የዓይን እማኞች ተናግረዋል። በአሰቃቂ ሁኔታ የተገደለውን የአቶ ወንዳፍራሽ ንጉሴ አስክሬን ለመውሰድ ዛሬ ሰኔ 29 ቀን 2018ዓ.ም ወደ መከላከያ ካምፕ ያቀኑት በአማራነቱ ሰማዕት የሆነው የቅርብ ዘመዶችና ህፃናት ልጆቹ በአገዛዙ ሀይሎች ከፍተኛ ድብደባ ተፈፅሞባቸው አስክሬን ተከልክለው በተኩስ እንዲበተኑ መደረጋቸውን በስፍራው የነበሩ የዓይን እማኞች ተናግረዋል። አገዛዙ በአርማኒያ ቀበሌ እየፈፀመ ያለው የጦር ወንጀል ሞልቶ የፈሰሰ ሲሆን ዕድሚያቸው ያልደረሰ ልጃገረዶች የአስገድዶ መድፈር ጥቃት ሲፈፀምባቸው በርካታ ወጣቶች በአስገዳጅ ሁኔታ የሚሊሻ ስልጠና ወስደው እንዲጠረነፉ መደረጋቸውን ቤተሰቦቻቸው በከፍተኛ መሬትና ሀዘን ውስጥ ሆነው ተናግረዋል። " ክብር ለትግሉ ሰማዕታት ! "ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ

በሌላ ዜና በቀን 29/10/2018 ዓ.ም የብልፅግናው ሠራዊት በንፁሀን ደም ከመጨማለቁ ባለፈ የሰውን ልጅ በአሰቃቂና ፍፁም አረመኔ በተሞላ ተግባር አማራን እየተበቀለ ይገኛል። ይሕ ድርጊት በይፋትና
+1
በሌላ ዜና በቀን 29/10/2018 ዓ.ም የብልፅግናው ሠራዊት በንፁሀን ደም ከመጨማለቁ ባለፈ የሰውን ልጅ በአሰቃቂና ፍፁም አረመኔ በተሞላ ተግባር አማራን እየተበቀለ ይገኛል። ይሕ ድርጊት በይፋትና ጥሙጋ አውራጃ አርማኒያ ቀበሌ የተፈፀመ ሲሆን የአርማኒያ ቀበሌ ነዋሪ የሆነውን " አቶ ወንዳፍራሽ ንጉሴን" በጨለማ አራት ሰዓት(4:00) ከቤቱ አውጥተው ወደ ካምፕ በመውሰድ ለአንድ ቀን አሳድረው በማግስቱ "አይኑን" በማውለቅ እጁን በመቆራረጥ የገደሉት ሲሆን፤ ከገደሉም በኋላ እሬሳውን ለቤተሠቡ እዳይሠጥ የከለከለ የአለማችን አረመኔ ሆኗል። አቶ ወንዳፍራሽ ንጉሴ የሁለት ልጆች አባት ሲሆን፡ ልጆቹን ያለ እናት በስስት ሲያሳድግ የኖረ፣ ሚስቱ ሞታበት በሀዘን የተጎዳ ትጉሕ ገበሬ ነበረ። ይሕንን አረመኔዊ ድርጊት የተመለከቱት ዘመድ ጎረቤቶቹ  ከሀዘን በላይ ሆኖባቸው ቤታቸውን ዘግተው በጫካ ይገኛሉ። ሌላኛው ደግሞ በቀን 28/10/2018 ዓ.ም በአንፆኪያ ገምዛ ክላስተር እዲሁ አንድ ንፁህ ገበሬ በአገዛዙ ተረሽኗል። አቶ መንገሽ ታዬ የተባሉ የ55 ዓመት ገበሬ ለህክምና ከአጋምሳ አምባ ቀበሌ ወደ መኮይ ከተማ ያቀኑ ሲሆን፡ ከሚታከሙበት ጤና ጣቢያ በማውጣት አስረው ከገረፉ በኋላ በግፍ  በአገዛዙ ተረሽነዋል።

በመንዝ አውራጃ ፤ ጥርጥራ ቀበሌ የደፈጣ ጥቃት፤ የአገዛዙ 104ኛ ኮማንዶ ክፍለ ጦር በፋኖ መብረቃዊ እርምጃ ጉዳት አስተናገደ!! ሰኔ 30/2018 ዓ.ም በትጥቅ ትግሉ ስትራቴጂካዊ የደፈጣ ውጊያ መርህ መሰረት፣ የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ አምደ ፅዮን ኮር ስር የሚንቀሳቀሰው የአፄ ምኒልክ ክፍለጦር (በአባተ ፩ኛ ሻለቃ) በመንዝ ላሎ ክላስተር ጥራጥር ቀበሌ ወታደራዊ የበላይነትን በማድረግ አንጸባራቂ ድል አስመዝግቧል። ከሰኔ 29 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 9:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽቱ 12:00 ድረስ በተካሄደው የሰዓታት ጠንካራ ውጊያ፣ ከመንዝ ላሎ ወገሬ ከተማ ተነስቶ ወደ ጥርጥራ ቀበሌ ለመንቀሳቀስ የሞከረው የብልፅግናው 104ኛ ኮማንዶ ክፍለ ጦር "ሀያደጋ" በተባለ ልዩ ቦታ ላይ በታቀደ ድንገተኛ የደፈጣ ጥቃት እቅዱ ከሽፏል። የኮሪ ሚዲያና ኮሙኒኬሽን ክፍል ለዕዙ ባስተላለፈው ግንባር መረጃ መሰረት፣ የፋኖ ስልታዊ ጥቃት የወታደራዊ ግዳጅ አፈጻጸሙን ሙሉ በሙሉ ያሳካ ነበር። በዚህም የአገዛዙ የጥምር ጦር አባላት የነበሩ አንድ የ፶ አለቃ ማዕረግ ያለው የሚሊሻ አመራርን ጨምሮ ከ10 በላይ ወታደሮች የተደመሰሱ ሲሆን፣ በርካቶች ቆስለው በአምቡላንስና በሕዝብ ትራንስፖርት ተሽከርካሪዎች ወደ ሞላሌ ከተማ ሆስፒታል እደላከ ተረጋግጧል። በሜዳው ፍልሚያ ከፍተኛ የሰው ኃይልና የሞራል ስብራት የገጠመው የአገዛዙ ሰራዊት፣ ሽንፈቱን ለመቀልበስ ከመንዝ ቀያ  ዘመሮ ከተማ የኃይል ማዛባት (ማጠናከሪያ ኃይል) ለማንቀሳቀስ ቢሞክርም በምኒልክ ልጆች ፅኑ መከላከል ወደ ኋላ እንዲያፈገፍግ ተገዷል። ሰራዊቱ ወታደራዊ ግዳጁን ማሳካት ሲያቅተው፣ የክፍለ ጦሩ አስተዳደር ኃላፊ የፋኖ ልዑል እሱባለውን ቤተሰቦች መኖሪያ ቤት በር በመስበርና ንብረት በመዝረፍ የተለመደውን የውንብድና ተግባሩን ፈፅሟል። ይህ በመንዝ ላሎ ቀጠና የተመዘገበው ድል፣ በትጥቅ ትግሉ ሂደት የፋኖን የደፈጣ ውጊያ ብቃት፣ የመረጃ የበላይነት እና የተደራጀ አቅም በተግባር ያሳየ ሲሆን፣ የአገዛዙ ኮማንዶ ክፍለ ጦር መራር ሽንፈት አከናንቦ ወደ መጣበት እንዲፈርጠጥ አድርጎታል። "ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! "ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን!" የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

በተጉለትና ቡልጋ አውራጃ ፡ ሳሲት ክላስተር የዓመታዊ ሥራ አፈፃጸምን ገምግሞ የዕውቅና መድረክ ሲያካሂድ፡ በይፋትና ጥሙጋ አውራጃ የብልፅግናው ሠራዊት ንፁሀንን በግፍ ረሸነ!! ሰኔ 30/2018 ዓ.ም የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ በቀን 29/10/2018 ዓ.ም በተጉለትና ቡልጋ አውራጃ፣ ተጉለት ቀጠና ሳሲት ክላስተር ዓመታዊ የሥራ አፈፃጸም ግምገማ መድረክ አካሄደ ። በዚሁ መድረክ ላይ የዕዙ ከፍተኛ የፖለቲካ አመራሮች፣ የክላስተርና የቀበሌ አመራሮች በተገኙበት ድርጅታዊ ተልዕኮዎች፣ የማኅበረሰብ አገልግሎት አሰጣጥና የመልካም አስተዳደር ጉዳዮች በስፋት ተገምግመዋል ። 📌 ዋና ዋና የውይይት ነጥቦች ~ ቀጥተኛ የድጋፍና አርአያነት: የዕዙ ከፍተኛ የፖለቲካ አመራሮች እስከ ቀበሌ ድረስ በመውረድ ያደረጉት ድጋፍ የሚበረታታ ጅምር በመሆኑ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ተጠይቋል ። ~ የተቋማት ነፃነት: ክላስተርና ቀበሌዎች ያለምንም ጣልቃ ገብነት የተሰጣቸውን ተቋማዊ ሥልጣን በነፃነትና በኃላፊነት እንዲተገብሩ የተፈጠረው ምቹ ሁኔታ ተጨማሪ አቅም መፍጠሩ ተገልጿል ። ~ የተጣለባቸውን ሕዝባዊና ድርጅታዊ ኃላፊነት በተሻለ ሁኔታ ለተወጡ ቀበሌዎችና አመራሮች የምስጋናና የዕውቅና ሽልማት ተበርክቷል ። ይህ ሽልማት ጠንካራዎችን ለማበረታታትና ደካማ አፈፃጸም ያሳዩትን ደግሞ ለቀጣይ ሥራ ለማነቃቃት ያለመ ነው ። ✊ ለቀጣይ ትግል የቀረበ ጥሪ:- ~ የዕዙ ከፍተኛ አመራሮች "ተጉለት በታሪክ የነበረውን ብሔራዊ ሚና በአማራ የሕልውና ትግል በድጋሚ በተግባር አሳይቶናል" በማለት ለአመራሩና ለማኅበረሰቡ ምስጋና አቅርበዋል ። ~ በመጨረሻም፣ በቀጣይ የሚሰጡ ድርጅታዊ ተልዕኮዎችንና ግዳጆችን በአግባቡ ለመወጣት እንዲሁም የተደቀነውን የሕልውና አደጋ ለመቀልበስ አመራሩና ሕዝቡ በተለመደው የጋራ አንድነትና ትውልዳዊ ኃላፊነት እንዲቆሙ ጥሪ ቀርቧል ። በሌላ ዜና በቀን 29/10/2018 ዓ.ም የብልፅግናው ሠራዊት በንፁሀን ደም ከመጨማለቁ ባለፈ የሰውን ልጅ በአሰቃቂና ፍፁም አረመኔ በተሞላ ተግባር አማራን እየተበቀለ ይገኛል። ይሕ ድርጊት በይፋትና ጥሙጋ አውራጃ አርማኒያ ቀበሌ የተፈፀመ ሲሆን የአርማኒያ ቀበሌ ነዋሪ የሆነውን " አቶ ወንዳፍራሽ ንጉሴን" በጨለማ አራት ሰዓት(4:00) ከቤቱ አውጥተው ወደ ካምፕ በመውሰድ ለአንድ ቀን አሳድረው በማግስቱ "አይኑን" በማውለቅ እጁን በመቆራረጥ የገደሉት ሲሆን፤ ከገደሉም በኋላ እሬሳውን ለቤተሠቡ እዳይሠጥ የከለከለ የአለማችን አረመኔ ሆኗል። አቶ ወንዳፍራሽ ንጉሴ የሁለት ልጆች አባት ሲሆን፡ ልጆቹን ያለ እናት በስስት ሲያሳድግ የኖረ፣ ሚስቱ ሞታበት በሀዘን የተጎዳ ትጉሕ ገበሬ ነበረ። ይሕንን አረመኔዊ ድርጊት የተመለከቱት ዘመድ ጎረቤቶቹ ከሀዘን በላይ ሆኖባቸው ቤታቸውን ዘግተው በጫካ ይገኛሉ። ሌላኛው ደግሞ በቀን 28/10/2018 ዓ.ም በአንፆኪያ ገምዛ ክላስተር እዲሁ አንድ ንፁህ ገበሬ በአገዛዙ ተረሽኗል። አቶ መንገሽ ታዬ የተባሉ የ55 ዓመት ገበሬ ለህክምና ከአጋምሳ አምባ ቀበሌ ወደ መኮይ ከተማ ያቀኑ ሲሆን፡ ከሚታከሙበት ጤና ጣቢያ በማውጣት አስረው ከገረፉ በኋላ በግፍ በአገዛዙ ተረሽነዋል። " ክብር ለትግሉ ሠማዕታት! "ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ

ከእንግዲህ አንገት አይደፋም፣ ዙፋኑ ተዘጋጅቷል፤ የብርሃን ሰይፉን የመዘዘው የአማራ ልጅ ፋኖ በአሸናፊነትና በግርማዊነቱ ወደ ፊት እየገሰገሰ የመኖራችን ዋስትና ሆኗል። ራስ አርበኛ ዘመነ ካሴ
ከእንግዲህ አንገት አይደፋም፣ ዙፋኑ ተዘጋጅቷል፤ የብርሃን ሰይፉን የመዘዘው የአማራ ልጅ ፋኖ በአሸናፊነትና በግርማዊነቱ ወደ ፊት እየገሰገሰ የመኖራችን ዋስትና ሆኗል። ራስ አርበኛ ዘመነ ካሴ