Tabor Bible Study (ሐዋሳ ታቦር መካነ ኢየሱስ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት)
الذهاب إلى القناة على Telegram
ሐዋሳ ታቦር መካነ ኢየሱስ ማህበረ ምዕመናን መጽሐፍ ቅዱስ የሚጠናበት የቴሌግራም ቻናል
إظهار المزيد1 079
المشتركون
+424 ساعات
+117 أيام
+3930 أيام
أرشيف المشاركات
. ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የዕለቱ ጥቅስ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
“በልቅሶ ወጡ እኔም በማጽናናት አመጣቸዋለሁ፤ በወንዝ ዳር በቅን መንገድ አስኬዳቸዋለሁ፥ በእርሱም አይሰናከሉም፤ እኔ ለእስራኤል አባት ነኝና፥ ኤፍሬምም በኵሬ ነውና።”
ኤርምያስ 31፥9
በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የዓመቱ የቀን መቁጠሪያ 🗓 አጀንዳ መሠረት #ነሐሴ_26 የዕለቱ ንባብ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል👉 @TME_bible_study
Repost from ቅዱሳት መጻሕፍት
#አዲስ_ዓመት
#New_Year
👉ርዕስ፦ መጽሐፍ ቅዱስን በሚገባ ለመረዳት
✍ጸሐፊ፦ ቲ. ኖርተን ስቴሬት
🗣ትርጉም፦ ተክሉ መንገሻ
ይህ መጽሐፍ፣ መጽሐፍ ቅዱስን በሚገባ ለመረዳት በጣም ጠቃሚ መጽሐፍ ስለሆነ በአዲስ ዓመት ቅዱሳት መጻሕፍትን በአዲስ መልኩ ለማጥናት ሁነኛ መጽሐፍ እንደሆነ አምነን እነሆ ብለናችኋል። በውስጡም የሚከተሉትን ጉዳዮች አካቷል፦
መሠረታዊ አሳቦች
👉መጽሐፍ ቅዱስን ማን ሊረዳው ይችላል?
👉ለማጥናት ትክክለኛውን መሣሪያ እንዴት መጠቀም እችላለሁ?
👉ለማጥናት እንዴት መጀመር እችላለሁ?
አጠቃላይ መመሪያዎች
👉አገባቡን፣ ቃላትን፣ ሰዋሰውን እና የደራሲውን ዓላማ እንዴት ልረዳው እችላለሁ?
👉ቅድመ ሁኔታውን ማጥናት
👉ቅዱስ ቃሉን በራሱ መተርጎም
ልዩ መመሪያዎች
👉ዘይቤያዊ አነጋገር፣ ተምሳሌቶች(Symbols), አምሳያዎች (Types), ምሳሌዎችና ምሳሌያዊ ገለጣዎች
👉የዕብራይስጥ ቋንቋ ፈሊጦች፣ ሥነ-ግጥም መረዳት
👉ትንቢት እና ትምህርተ-ሃይማኖት መረዳት
👉የብሉይና የአዲስ ኪዳናት ግንኙነትን መረዳት
በስተመጨረሻም ያጠናነውን ለግል ጥቅም ሥራ ላይ ማዋል እንዴት እንደሚቻል የሚያብራራ ድንቅ መጽሐፍ ነው።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
. ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የዕለቱ ጥቅስ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
“እግዚአብሔር . . . ስለ ያዕቆብ ደስ ይበላችሁ ስለ አሕዛብም አለቆች እልል በሉ፤ አውሩ፥ አመስግኑ፦ እግዚአብሔር ሕዝቡን የእስራኤልን ቅሬታ አድኖአል በሉ።”
ኤርምያስ 31፥7
በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የዓመቱ የቀን መቁጠሪያ 🗓 አጀንዳ መሠረት #ነሐሴ_25 የዕለቱ ንባብ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል👉 @TME_bible_study
የእለቱ የመልእክትና የወንጌል ክፍል
#የመልእክት_ክፍል
ኤርምያስ 31
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁷ እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና፦ ስለ ያዕቆብ ደስ ይበላችሁ ስለ አሕዛብም አለቆች እልል በሉ፤ አውሩ፥ አመስግኑ፦ እግዚአብሔር ሕዝቡን የእስራኤልን ቅሬታ አድኖአል በሉ።
⁸ እነሆ፥ ከሰሜን አገር አመጣቸዋለሁ፥ ከምድርም ዳርቻ እሰበስባቸዋለሁ፥ በመካከላቸውም ዕውሩና አንካሳው ያረገዘችና የወለደችም በአንድነት ታላቅ ጉባኤ ሆነው ወደዚህ ይመለሳሉ።
⁹ በልቅሶ ወጡ እኔም በማጽናናት አመጣቸዋለሁ፤ በወንዝ ዳር በቅን መንገድ አስኬዳቸዋለሁ፥ በእርሱም አይሰናከሉም፤ እኔ ለእስራኤል አባት ነኝና፥ ኤፍሬምም በኵሬ ነውና።
ሮሜ 5
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹² ስለዚህ ምክንያት ኃጢአት በአንድ ሰው ወደ ዓለም ገባ በኃጢአትም ሞት፥ እንደዚሁም ሁሉ ኃጢአትን ስላደረጉ ሞት ለሰው ሁሉ ደረሰ፤
¹³ ሕግ እስከ መጣ ድረስ ኃጢአት በዓለም ነበረና ነገር ግን ሕግ በሌለበት ጊዜ ኃጢአት አይቈጠርም፤
¹⁴ ነገር ግን በአዳም መተላለፍ ምሳሌ ኃጢአትን ባልሠሩት ላይ እንኳ፥ ከአዳም ጀምሮ እስከ ሙሴ ድረስ ሞት ነገሠ፤ አዳም ይመጣ ዘንድ ላለው ለእርሱ አምሳሉ ነውና።
¹⁵ ነገር ግን ስጦታው እንደ በደሉ መጠን እንደዚያው አይደለም፤ በአንድ ሰው በደል ብዙዎቹ ሞተዋልና፥ ነገር ግን የእግዚአብሔር ጸጋና በአንድ ሰው በኢየሱስ ክርስቶስ ጸጋ የሆነው ስጦታ ከዚያ ይልቅ ለብዙዎች በዛ።
¹⁶ አንድ ሰውም ኃጢአትን በማድረጉ እንደ ሆነው መጠን እንደዚያው ስጦታው አይደለም፤ ፍርድ ከአንድ ሰው ለኵነኔ መጥቶአልና፥ ስጦታው ግን በብዙ በደል ለማጽደቅ መጣ።
¹⁷ በአንዱም በደል ሞት በአንዱ በኩል ከነገሠ፥ ይልቁን የጸጋን ብዛትና የጽድቅን ስጦታ ብዛት የሚቀበሉ በአንዱ በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል በሕይወት ይነግሣሉ።
¹⁸ እንግዲህ በአንድ በደል ምክንያት ፍርድ ለኵነኔ ወደ ሰው ሁሉ እንደ መጣ፥ እንዲሁም በአንድ ጽድቅ ምክንያት ስጦታው ሕይወትን ለማጽደቅ ወደ ሰው ሁሉ መጣ።
¹⁹ በአንዱ ሰው አለመታዘዝ ብዙዎች ኃጢአተኞች እንደ ሆኑ፥ እንዲሁ ደግሞ በአንዱ መታዘዝ ብዙዎች ጻድቃን ይሆናሉ።
²⁰-²¹ በደልም እንዲበዛ ሕግ ጭምር ገባ፤ ዳሩ ግን ኃጢአት በበዛበት፥ ኃጢአት በሞት እንደ ነገሠ፥ እንዲሁ ደግሞ ጸጋ ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ የተነሣ በጽድቅ ምክንያት ለዘላለም ሕይወት ይነግሥ ዘንድ፥ ጸጋ ከመጠን ይልቅ በለጠ።
#የወንጌል_ክፍል
ማቴዎስ 23
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹ በዚያን ጊዜ ኢየሱስ ለሕዝቡና ለደቀ መዛሙርቱ እንዲህ ብሎ ነገራቸው፦
² ጻፎችና ፈሪሳውያን በሙሴ ወንበር ተቀምጠዋል።
³ ስለዚህ ያዘዙአችሁን ሁሉ አድርጉ ጠብቁትም፥ ነገር ግን እየተናገሩ አያደርጉትምና እንደ ሥራቸው አታድርጉ።
⁴ ከባድና አስቸጋሪ ሸክም ተብትበው በሰው ትከሻ ይጭናሉ፥ እነርሱ ግን በጣታቸው ስንኳ ሊነኩት አይወዱም።
⁵ ለሰውም እንዲታዩ ሥራቸውን ሁሉ ያደርጋሉ፤ ስለዚህ አሽንክታባቸውን ያሰፋሉ ዘርፉንም ያስረዝማሉ፥
⁶ በምሳም የከበሬታ ስፍራ፥ በምኵራብም የከበሬታ ወንበር፥
⁷ በገበያም ሰላምታና፦ መምህር ሆይ መምህር ሆይ ተብለው እንዲጠሩ ይወዳሉ።
⁸ እናንተ ግን፦ መምህር ተብላችሁ አትጠሩ፤ መምህራችሁ አንድ ስለ ሆነ እናንተም ሁላችሁ ወንድማማች ናችሁ።
⁹ አባታችሁ አንዱ እርሱም የሰማዩ ነውና በምድር ላይ ማንንም፦ አባት ብላችሁ አትጥሩ።
¹⁰ ሊቃችሁ አንድ እርሱም ክርስቶስ ነውና፦ ሊቃውንት ተብላችሁ አትጠሩ።
¹¹ ከእናንተም የሚበልጠው አገልጋያችሁ ይሆናል።
¹² ራሱን ከፍ የሚያደርግ ሁሉ ይዋረዳል፥ ራሱንም የሚያዋርድ ሁሉ ከፍ ይላል።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል👉 @TME_bible_study
ከሥላሴ በኋላ 10ኛ እሑድ
እውነተኛና ሐሰተኛ ጽድቅ
👉ኤር. 31፥7-9
👉ሮሜ 5፥12-21
👉ማቴ. 23፥1-12
በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የዓመቱ የቀን መቁጠሪያ 🗓 አጀንዳ መሠረት #ነሐሴ_24 የዕለቱ ንባብ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል👉 @TME_bible_study
. ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የዕለቱ ጥቅስ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
“እንዲህም አለ፦ እውነት እላችኋለሁ፥ ነቢይ በገዛ አገሩ ከቶ አይወደድም።”
ሉቃስ 4፥24
በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የዓመቱ የቀን መቁጠሪያ 🗓 አጀንዳ መሠረት #ነሐሴ_23 የዕለቱ ንባብ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል👉 @TME_bible_study
Repost from ቅዱሳት መጻሕፍት
ነገረ ፍጻሜ (Eschatology)
ክፍል-4
ድህረ ሚሊኒየማዊነት (Postmillennialism)
የዚህ አስተምህሮ ማዕከላዊው ሀሳብ፣ በወንጌል ኃይል እና በመንፈስ ቅዱስ ሥራ የእግዚአብሔር መንግሥት ክርስቶስ ከመመለሱ በፊት በሰው ልጅ ታሪክ ውስጥ ጉልህ የሆነ ድልን ያገኛል የሚል ነው። ቤተክርስቲያን ወንጌልን በታማኝነት ትሰብካለች፤ ሰዎች ወደ ክርስቶስ ዘወር እያሉ ይሄዳሉ እና የክርስቲያን መርሆዎች በማኅብረሰቡ እና ባህሎች ላይ ከፍተኛ ተጽዕኖ ያሳድራሉ። ይህ የወንጌል ወርቃማ ዘመን በተለምዶ የሺህ ዓመቱ ዘመን ይባላል። በዚህ ዘመን መጨረሻ ላይ ክርስቶስ በግልጽ እና በአካል ይመለሳል፤ ሙታንን ያስነሳል፤ ሰይጣንን እና ክፋትን ሁሉ ያሸንፋል እና ዘላለማዊውን መንግስት ማለትም አዲስ ሰማይ እና አዲስ ምድርን ያቋቁማል።
በጣም አስፈላጊው ነጥብ ድህረ ሚሊኒየማዊነት ክርስቲያኖች ኢየሱስ ከመመለሱ በፊት ዓለም ሙሉ በሙሉ ፍጹም እንደምትሆን ያምናሉ ማለት አይደለም። ይልቁንም ኃጢአት እና ሞት እስከ ክርስቶስ የመጨረሻ መምጣት ድረስ ሊኖሩ የሚችሉ ሲሆን፣ እነዚህ ሁነቶች የወንጌልን አስደናቂ እና ሰፊ ድል ይጠብቃሉ።
በድህረ ሚሊኒየም እምነት "ሚሊኒየም" ማለት ምን ማለት ነው?
ሚሊኒየም የሚለው ቃል የመጣው ከራዕይ 20፥1-6 ሲሆን ዮሐንስ ሰይጣን የሚታሰርበትንና ቅዱሳን ከክርስቶስ ጋር የሚገዙበትን የአንድ ሺህ ዓመት ጊዜ የሚገልጽ ነው። የድህረ ሚሊኒየም እምነት ተከታዮች "ሺህ ዓመታት" የሚለው ቃል እንደሚከተለው ሊተረጎም እንደሚገባ እርስ በእርሳቸው ይከራከራሉ፦
👉ቃል በቃል የሺህ ዓመት ጊዜ ወይም
👉ያልተለመደ የወንጌል በረከት ዘመንን የሚወክል ምሳሌያዊ/የተራዘመ የጊዜ ዘመን።
ስለዚህ፣ የድህረ ሚሊኒየም እምነት የሚገለጸው እያንዳንዱ የድህረ ሚሊኒየም እምነት ተከታዮች 1,000 ቁጥር ቃል በቃል መሆኑን በማመን ሳይሆን የሁነቶች ቅደም ተከተል ነው።
መሠረታዊው ቅደም ተከተል፦
አሁን ያለው የቤተክርስቲያን ዘመን → እየጨመረ የመጣ የወንጌል ስኬት → ሚሊኒየም → የክርስቶስ ሁለተኛ መምጣት → ትንሣኤ → የመጨረሻው ፍርድ → ዘላለማዊ ግዛት
ይህ ክርስቶስ ከሺህ ዓመቱ በፊት የሚመለስበት የpremillennialism (ቅድመ ሚሊኒየም) አስተምህሮ ተቃራኒ ነው።
ማዕከላዊው ሀሳብ፦ የክርስቶስ መንግሥት በታሪክ ድል ያደርጋል
ከድህረ ሚሊኒየም እምነት ጠንካራ ባህሪያት አንዱ የወንጌልን ኃይል በተመለከተ ያለው ብሩህ አመለካከት ነው። ድህረ ሚሊኒየም አማኞች ክርስቶስ ቤተክርስቲያንን ጉልህ ውጤቶችን ሳይጠብቅ አሕዛብን እንድትሰብክ እንዳላዘዛት ያምናሉ።
ኢየሱስ እንዲህ ብሏል፡- “ሥልጣን ሁሉ በሰማይና በምድር ተሰጠኝ። እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸው፥ ያዘዝኋችሁንም ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው፤ እነሆም እኔ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ።"
ማቴዎስ 28፥18-20
የድህረ ሚሊኒየም መከራከሪያ ነጥብ ክርስቶስ ሁሉንም ሥልጣን እንዳለው ስለዚህ ቤተክርስቲያን ወንጌል በመጨረሻ በአሕዛብ መካከል ሰፊ ለውጥ እንደሚያመጣ መጠበቅ እንዳለባት ነው። ይህ ማለት እያንዳንዱ ግለሰብ ክርስቲያን ይሆናል ማለት አይደለም። ይልቁንም የድህረ ሚሊኒየም አማኞች ክርስትና ከጊዜ ወደ ጊዜ ተጽዕኖ እያሳደረ እና የሰው ልጅ ብዙ ክፍሎች እንደሚለወጡ ይጠብቃሉ።
ይቀጥላል . . .
ምንጭ፦
Gentry, K. L., Jr. (1992). He shall have dominion: A postmillennial eschatology. Institute for Christian Economics.
Hodge, C. (1871–1873). Systematic theology (Vols. 1–3). Scribner, Armstrong, and Co.
Hoekema, A. A. (1979). The Bible and the future. Eerdmans.
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል፦ @Holy_scriptures
. ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የዕለቱ ጥቅስ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
“እኛ ፍጥረቱ ነንና፤ እንመላለስበት ዘንድ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን።”
ኤፌሶን 2፥10
በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የዓመቱ የቀን መቁጠሪያ 🗓 አጀንዳ መሠረት #ነሐሴ_22 የዕለቱ ንባብ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል👉 @TME_bible_study
📔ርዕስ፦ የወንጌላት ስምምነትና ንጽጽር
👤ጸሐፊ፦ ሮበርት ኤል ቶማስ እና ስታንሊ ኤን ጉንድሪ
📑የገጽ ብዛት፦ 303
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል👉 @TME_bible_study
. ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የዕለቱ ጥቅስ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
“ጸጋው በእምነት አድኖአችኋልና፤ ይህም የእግዚአብሔር ስጦታ ነው እንጂ ከእናንተ አይደለም፤”
ኤፌሶን 2፥8
በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የዓመቱ የቀን መቁጠሪያ 🗓 አጀንዳ መሠረት #ነሐሴ_21 የዕለቱ ንባብ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል👉 @TME_bible_study
. ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የዕለቱ ጥቅስ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
“ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነሣ በበደላችን ሙታን እንኳ በሆንን ጊዜ ከክርስቶስ ጋር ሕይወት ሰጠን፥ በጸጋ ድናችኋልና፥”
ኤፌሶን 2፥5
በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የዓመቱ የቀን መቁጠሪያ 🗓 አጀንዳ መሠረት #ነሐሴ_20 የዕለቱ ንባብ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል👉 @TME_bible_study
📔ርዕስ፦የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት መግቢያ
👤ጸሐፊ፦ የኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማህበር
💾መጠን፦ 2.1MB
📑የገጽ ብዛት፦ 364
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል👉 @TME_bible_study
. ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የዕለቱ ጥቅስ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
“. . . በምድር ላይ እግዚአብሔር ዝናብ እስከሚሰጥበት ቀን ድረስ፥ ዱቄቱ ከማድጋ አይጨረስም፥ ዘይቱም ከማሰሮው አይጎድልም።”
1ኛ ነገሥት 17፥14
በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የዓመቱ የቀን መቁጠሪያ 🗓 አጀንዳ መሠረት #ነሐሴ_19 የዕለቱ ንባብ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል👉 @TME_bible_study
የጌታ ጸሎት፣ ከትንሹ የሉተር ካታኪዝም
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል👉 @TME_bible_study
. ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የዕለቱ ጥቅስ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
“እነሆም፥ ትመግብህ ዘንድ አንዲት ባልቴት አዝዣለሁ የሚል የእግዚአብሔር ቃል መጣለት።”
1ኛ ነገሥት 17፥9
በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የዓመቱ የቀን መቁጠሪያ 🗓 አጀንዳ መሠረት #ነሐሴ_18 የዕለቱ ንባብ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል👉 @TME_bible_study
የእለቱ የመልእክትና የወንጌል ክፍል
#የመልእክት_ክፍል
1ኛ ነገሥት 17
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
⁸ ተነሥተህም በሲዶና አጠገብ ወዳለችው ወደ ሰራፕታ ሂድ፥ በዚያም ተቀመጥ፤
⁹ እነሆም፥ ትመግብህ ዘንድ አንዲት ባልቴት አዝዣለሁ የሚል የእግዚአብሔር ቃል መጣለት።
¹⁰ ተነሥቶም ወደ ሰራፕታ ሄደ፤ ወደ ከተማይቱም በር በደረሰ ጊዜ አንዲት ባልቴት በዚያ እንጨት ትለቅም ነበር፤ እርሱም ጠርቶ፦ የምጠጣው ጥቂት ውኃ በጽዋ ታመጭልኝ ዘንድ እለምንሻለሁ አላት።
¹¹ ውኃም ልታመጣለት በሄደች ጊዜ ወደ እርስዋ ጠርቶ፥ ቁራሽ እንጀራ በእጅሽ ይዘሽ ትመጭ ዘንድ እለምንሻለሁ አላት።
¹² እርስዋም፦ አምላክህ ሕያው እግዚአብሔርን! በማድጋ ካለው ከእፍኝ ዱቄት፥ በማሰሮም ካለው ከጥቂት ዘይት በቀር እንጀራ የለኝም፤ እነሆም፥ ገብቼ ለእኔና ለልጄ እጋግረው ዘንድ በልተነውም እንሞት ዘንድ ጥቂት እንጨት እሰበስባለሁ አለች።
¹³ ኤልያስም አላት፦ አትፍሪ ይልቅስ ሄደሽ እንዳልሺው አድርጊ፤ አስቀድመሽ ግን ከዱቄቱ ለእኔ ታናሽ እንጎቻ አድርገሽ አምጭልኝ፥ ከዚያም በኋላ ለአንቺና ለልጅሽ አድርጊ፤
¹⁴ የእስራኤል አምላክ እግዚአብሔር እንዲህ ይላልና፦ በምድር ላይ እግዚአብሔር ዝናብ እስከሚሰጥበት ቀን ድረስ፥ ዱቄቱ ከማድጋ አይጨረስም፥ ዘይቱም ከማሰሮው አይጎድልም።
¹⁵ እርስዋም ሄዳ እንደ ኤልያስ ቃል አደረገች፤ እርስዋና እርሱ ቤትዋም ብዙ ቀን በሉ።
¹⁶ በኤልያስም እጅ እንደ ተናገረው እንደ እግዚአብሔር ቃል ዱቄቱ ከማድጋው አልተጨረሰም፥ ዘይቱም ከማሰሮው አልጎደለም።
ኤፌሶን 2
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
¹-² በበደላችሁና በኃጢአታችሁ ሙታን ነበራችሁ፤ በእነርሱም፥ በዚህ ዓለም እንዳለው ኑሮ፥ በማይታዘዙትም ልጆች ላይ አሁን ለሚሠራው መንፈስ አለቃ እንደ ሆነው በአየር ላይ ሥልጣን እንዳለው አለቃ ፈቃድ፥ በፊት ተመላለሳችሁባቸው።
³ በእነዚህም ልጆች መካከል እኛ ሁላችን ደግሞ፥ የሥጋችንንና የልቡናችንን ፈቃድ እያደረግን፥ በሥጋችን ምኞት በፊት እንኖር ነበርን እንደ ሌሎቹም ደግሞ ከፍጥረታችን የቁጣ ልጆች ነበርን።
⁴ ነገር ግን እግዚአብሔር በምሕረቱ ባለ ጠጋ ስለ ሆነ፥
⁵ ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነሣ በበደላችን ሙታን እንኳ በሆንን ጊዜ ከክርስቶስ ጋር ሕይወት ሰጠን፥ በጸጋ ድናችኋልና፥
⁶-⁷ በሚመጡ ዘመናትም በክርስቶስ ኢየሱስ ለእኛ ባለው ቸርነት ከሁሉ የሚበልጠውን የጸጋውን ባለ ጠግነት ያሳይ ዘንድ፥ ከእርሱ ጋር አስነሣን በክርስቶስ ኢየሱስም በሰማያዊ ስፍራ ከእርሱ ጋር አስቀመጠን።
⁸ ጸጋው በእምነት አድኖአችኋልና፤ ይህም የእግዚአብሔር ስጦታ ነው እንጂ ከእናንተ አይደለም፤
⁹ ማንም እንዳይመካ ከሥራ አይደለም።
¹⁰ እኛ ፍጥረቱ ነንና፤ እንመላለስበት ዘንድ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን።
#የወንጌል_ክፍል
ሉቃስ 4
¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯
²³ እርሱም፦ ያለ ጥርጥር ይህን ምሳሌ፦ ባለ መድኃኒት ሆይ፥ ራስህን ፈውስ፤ በቅፍርናሆም እንዳደረግኸው የሰማነውን ሁሉ በዚህ በገዛ አገርህ ደግሞ አድርግ ትሉኛላችሁ አላቸው።
²⁴ እንዲህም አለ፦ እውነት እላችኋለሁ፥ ነቢይ በገዛ አገሩ ከቶ አይወደድም።
²⁵@⁶ ²⁵ ነገር ግን እውነት እላችኋለሁ፥ በኤልያስ ዘመን ሦስት ዓመት ከስድስት ወር ሰማይ ተዘግቶ ሳለ በምድር ሁሉ ብርቱ ራብ በነበረ ጊዜ፥ በእስራኤል ብዙ መበለቶች ነበሩ፤
²⁶ ኤልያስም በሲዶና አገር ወዳለች ወደ ሰራፕታ ወደ አንዲት መበለት እንጂ ከእነርሱ ወደ አንዲቱ አልተላከም።
²⁷ በነቢዩ በኤልሳዕ ዘመንም በእስራኤል ብዙ ለምጻሞች ነበሩ፥ ከሶርያዊው ከንዕማን በቀር ከእነርሱ አንድ ስንኳ አልነጻም።
²⁸ በምኵራብም የነበሩ ሁሉ ይህን ሰምተው ቍጣ ሞላባቸው፥ ተነሥተውም ከከተማ ወደ ውጭ አወጡት፥
²⁹ ይጥሉትም ዘንድ ከተማቸው ተሠርታባት ወደ ነበረች ወደ ተራራው አፋፍ ወሰዱት፤
³⁰ እርሱ ግን በመካከላቸው አልፎ ሄደ።
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል👉 @TME_bible_study
ከሥላሴ በኋላ 9ኛ እሑድ
ጊዜን በከንቱ አለማሳለፍ
👉1 ነገ. 17፥8-16
👉ኤፌ. 2፥1-10
👉ሉቃ. 4፥23-30
በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የዓመቱ የቀን መቁጠሪያ 🗓 አጀንዳ መሠረት #ነሐሴ_17 የዕለቱ ንባብ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል👉 @TME_bible_study
. ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የዕለቱ ጥቅስ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
“ድንገት መጥቶ ተኝታችሁ እንዳያገኛችሁ ስለዚህ ትጉ።”
ማርቆስ 13፥36
በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የዓመቱ የቀን መቁጠሪያ 🗓 አጀንዳ መሠረት #ነሐሴ_16 የዕለቱ ንባብ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል👉 @TME_bible_study
. ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የዕለቱ ጥቅስ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
“ጊዜው መቼ እንዲሆን አታውቁምና ተጠንቀቁ፤ ትጉ፤ ጸልዩም።”
ማርቆስ 13፥33
በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የዓመቱ የቀን መቁጠሪያ 🗓 አጀንዳ መሠረት #ነሐሴ_15 የዕለቱ ንባብ
ወደ ቻናሉ ለመ🀄️ላ🀄️ል👉 @TME_bible_study
