ar
Feedback
Ethio con Tender

Ethio con Tender

الذهاب إلى القناة على Telegram

የግንባታ ጨረታዎችን የምታገኙበት ቻናል ነው። የቻናሉ ቤተሰብ ይሁኑ!

إظهار المزيد
4 730
المشتركون
+2224 ساعات
+717 أيام
+11530 أيام
أرشيف المشاركات
👉 ማስታወቂያ፡ ለአርሶ አደር የይዞታ ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት እግድ ተነሳ! ​የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ከቀን 14/12/18 ዓ.ም ጀምሮ በአርሶ አደር ይዞታዎ
👉 ማስታወቂያ፡ ለአርሶ አደር የይዞታ ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት እግድ ተነሳ! ​የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ከቀን 14/12/18 ዓ.ም ጀምሮ በአርሶ አደር ይዞታዎች ላይ ተጥሎ የነበረውን የዝውውር እና የሶስተኛ ወገን ማስተላለፍ እግድ ሙሉ በሙሉ ማንሳቱን አሳወቀ። ​📌 ቁልፍ ነጥቦች፡ ​የተነሳበት ምክንያት፡ በእግዱ ምክንያት በጽ/ቤቶች እየተከሰቱ ያሉ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት። ​አቅጣጫ፡ ሂደቱ በመመሪያ ቁጥር 20/2013 መሰረት በከፍተኛ ጥንቃቄ እና በጥብቅ ዲስፕሊን መፈጸም እንዳለበት ተገልጿል፤ ​የሚመለከተው አካል፡ ለ11ዱም ክ/ከተማ መሬት ልማትና አስተዳደር ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች እና ለሚመለከታቸው ዘርፎች የተላለፈ ነው። ​ኢትዮ ኮን - ትክክለኛ የመረጃ ምንጭ

✅ የአዲስ አበባ መሬት አስተዳደር ቢሮ እግድ ተነስቶል።
✅ የአዲስ አበባ መሬት አስተዳደር ቢሮ እግድ ተነስቶል።

🫵 ለኢትዮጵያ የኮንስትራክሽን ስራ ተቋራጮች ማህበር አባላት በሙሉ፣ ​የውይይት መድረክ ጥሪ ማሳሰቢያ ​የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ግንባታ ፈቃድና ቁጥጥር ባለሥልጣን ከዋና ሥራ አስኪያጅ ጽ/ቤት
🫵 ለኢትዮጵያ የኮንስትራክሽን ስራ ተቋራጮች ማህበር አባላት በሙሉ፣ ​የውይይት መድረክ ጥሪ ማሳሰቢያ ​የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ግንባታ ፈቃድና ቁጥጥር ባለሥልጣን ከዋና ሥራ አስኪያጅ ጽ/ቤት ጋር በመሆን፣ በከተማው እየተገነቡ ያሉ ግንባታዎችን አስመልክቶ ከባለቤቶች፣ ኮንትራክተሮች እና አማካሪዎች ጋር የውይይት መድረክ አዘጋጅቷል። ​በመሆኑም በዕለቱ ከግንባታው ኮንትራክተር እና አማካሪ ጋር በመሆን እንዲገኙ ተጠርተዋል፡- ​ቀን፡ 21/12/2018 ዓ.ም ​ሰዓት፡ ከጠዋቱ 2፡30 ጀምሮ ​ቦታ፡ አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ጽ/ቤት ባህል አዳራሽ ​በውይይት መድረኩ ላይ ለመሳተፍ ፍላጎት ያላቸው አባላት ስማቸውን እና ስልክ ቁጥራችሁን 0984777722 ላይ እንዲያስቀምጡ ስንል በአክብሮት እንጠይቃለን። 🔷የኢትዮጵያ የኮንስትራክሽን ስራ ተቋራጮች ማህበር

✴️ጨረታ አዲስ ዘመን ነሀሴ 20 ቀን 2018 ዓ. ም ዕትም ላይ የተወሰደ https://t.me/ethioconbid
✴️ጨረታ አዲስ ዘመን  ነሀሴ 20 ቀን 2018 ዓ. ም ዕትም ላይ የተወሰደ https://t.me/ethioconbid

✴️ጨረታ አዲስ ዘመን ነሀሴ 19 ቀን 2018 ዓ. ም ዕትም ላይ የተወሰደ https://t.me/ethioconbid
✴️ጨረታ አዲስ ዘመን ነሀሴ 19 ቀን 2018 ዓ. ም ዕትም ላይ የተወሰደ https://t.me/ethioconbid

✴️ጨረታ አዲስ ዘመን ነሀሴ 14 ቀን 2018 ዓ. ም ዕትም ላይ የተወሰደ https://t.me/ethioconbid
✴️ጨረታ አዲስ ዘመን ነሀሴ 14 ቀን 2018 ዓ. ም ዕትም ላይ የተወሰደ https://t.me/ethioconbid

✴️ጨረታ አዲስ ዘመን ነሀሴ 14 ቀን 2018 ዓ. ም ዕትም ላይ የተወሰደ https://t.me/ethioconbid
✴️ጨረታ አዲስ ዘመን ነሀሴ 14 ቀን 2018 ዓ. ም ዕትም ላይ የተወሰደ https://t.me/ethioconbid

✴️ጨረታ አዲስ ዘመን ነሀሴ 15 ቀን 2018 ዓ. ም ዕትም ላይ የተወሰደ https://t.me/ethioconbid
✴️ጨረታ አዲስ ዘመን ነሀሴ 15 ቀን 2018 ዓ. ም ዕትም ላይ የተወሰደ https://t.me/ethioconbid

✴️ጨረታ አዲስ ዘመን ነሀሴ 15 ቀን 2018 ዓ. ም ዕትም ላይ የተወሰደ https://t.me/ethioconbid
✴️ጨረታ አዲስ ዘመን ነሀሴ 15 ቀን 2018 ዓ. ም ዕትም ላይ የተወሰደ https://t.me/ethioconbid

✴️ጨረታ አዲስ ዘመን ነሀሴ 15 ቀን 2018 ዓ. ም ዕትም ላይ የተወሰደ https://t.me/ethioconbid
✴️ጨረታ አዲስ ዘመን ነሀሴ 15 ቀን 2018 ዓ. ም ዕትም ላይ የተወሰደ https://t.me/ethioconbid

የደረጃ 1 ጨረታ ምዝገባ ቅድመ ምዘና ዉጤት ማሳወቅን ይመለከታል:: አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የከተማዋን ነዋሪዎች የቤት ፍላጎት ለማሟላትና የከተማዋን እድገት ለማፋጠን በልዩ ትኩረት እየተገበረ
+3
የደረጃ 1 ጨረታ ምዝገባ ቅድመ ምዘና ዉጤት ማሳወቅን ይመለከታል:: አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የከተማዋን ነዋሪዎች የቤት ፍላጎት ለማሟላትና የከተማዋን እድገት ለማፋጠን በልዩ ትኩረት እየተገበረ ለሚገኘው መጠነ ሰፊ የቤት ልማት ፕሮግራም በግንባታው ዘርፍ የተሰማሩ እና አስፈላጊውን መስፈርት የሚያሟሉ በደንብ ቁጥር 199/2018 መሰረት ሥራ ተቋራጮችን ለመመዝገብ ከቅዳሜ 09/12/2018 ዓ.ም እስከ ሐሙስ 14/12/2018 ዓ.ም ድረስ ጥሪ ማድረጉና የምዝገባ ሂደቱ በስኬት መጠናቀቁ ይታወቃል። በዚሁ መሠረት የቀረቡትን ሰነዶች የማጣራት ሥራ ተከናውኖ የመጀመሪያ ደረጃ የምዝገባ ሂደቱን ሙሉ በሙሉ ላሟላችሁ እና ስማችሁ ከዚህ በታች ለተዘረዘራችሁ ሥራ ተቋራጮች በሙሉ የቴክኒክ ሰነዳችሁን (Technical Proposal) በቴክኒክ ሰነዱ ላይ በተገለፀው የጊዜ ገደብ እና መስፈርት መሠረት እንድታስገቡ እናሳዉቃለን፡፡ ነሀሴ 15 ቀን 2018 ዓ/ም የቤቶች ልማት ኮርፖሬሽን ኮሙኒኬሽን ዳይሬክቶሬት

​📢 የዛሬ ምሽት ነሀሴ 18 ቀን 2018 ዓ.ም የ«ኢትዮ ኮን» ልዩ የሬዲዮ ፕሮግራም! 🧱🇪🇹 ​በሀገራችን የኮንስትራክሽን ዘርፍ ውስጥ ታይቶ የማይታወቅ ትልቅ ለውጥ ያመጣል ተብሎ የሚጠበቀውን አዲስ  ዲጂታል ፕላትፎርም ሊያወቁ ዝግጁ ኖት? ​በዓመት እስከ 300 ቢሊዮን ብር ማዳን የሚያስችለውን እና በዓፍሪካ ደረጃ የመጀመሪያ የሆነውን የተቀናጀ ሥነ-ምህዳር (Ecosystem) ፈጥሮ ወደ ሥራ የገባውን 'ኤቫኮኔት' (Evaconect) ፕላትፎርም ባለቤትና የሲቪል መሐንዲስ የሆነውን እንግዳችንን አቤሴሎምን ዛሬ ምሽት በቀጥታ ስርጭት ጋብዘናል! ​በዘርፉ ላይ ያላችሁን ማንኛውንም ጥያቄ፣ ሃሳብ እና አስተያየት በሚከተሉት አድራሻዎች ማድረስ ትችላላችሁ። ​💬 ጥያቄዎን 💡 ሃሳብዎን 🗣 አስተያየትዎን 0974466655 📩 በአጭር የጽሁፍ መልዕክት ላኩልን! ​⏰ ዛሬ ምሽት  ከ2:00-3:30 በአሀዱ ሬድዮ 94.3 በቀጥታ ስርጭት ይጠብቁን! ​🏗 “የነገውን ግንባታ በጋራ እንገንባ!” ኢትዮ ኮን - ትክክለኛ የመረጃ ምንጭ 📻

የግንባታ ስራ ጨረታ ማስታወቂያ፡ የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን "ከ ኮካ -ገዳመ እየሱስ መሳለሚያ የአስፋልት መንገድ ግንባታ የግንባታ ሥራዎች " በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል።
+9
የግንባታ ስራ ጨረታ ማስታወቂያ፡ የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለስልጣን "ከ ኮካ -ገዳመ እየሱስ መሳለሚያ የአስፋልት መንገድ ግንባታ የግንባታ ሥራዎች " በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል። ፍላጎት ያላቸው ተቋራጮች በሙሉ ከታች ባለው የeGP system ሊንክ በመግባትና አስፈላጊውን መረጃ በመሙላት መሳተፍ ይችላሉ። Construction Works Tender Notice: The Addis Ababa City Roads Authority invites eligible contractors through an Open Tender for the Construction Works of Coca - Gedame Eyesus - Mesalemia Asphalt Road Project. Qualified firms can participate by registering and submitting all required information through the official eGP System link below. Procurement Reference No.: AACRA-ICB-W-0007-2019-BID-Open eGP System Link: https://production.egp.gov.et/egp/bids/report/tendering/fea30a5e-b8f7-4e3a-8bff-a88fac1684fb/open

👉 ከዛሬ ጀምሮ ከአያት 49 ወደ ፊጋ የሚወስደው መንገድ በከፊል ይዘጋል ተባለ። የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን ከአያት 49 ወደ ፊጋ በሚወስደው መንገድ 72 ድልድይ አካባቢ የመንገድ ጥገ
👉 ከዛሬ ጀምሮ ከአያት 49 ወደ ፊጋ የሚወስደው መንገድ በከፊል ይዘጋል ተባለ። የአዲስ አበባ ከተማ መንገዶች ባለሥልጣን ከአያት 49 ወደ ፊጋ በሚወስደው መንገድ  72 ድልድይ አካባቢ የመንገድ ጥገና ሥራ ሊካሄድ በመሆኑ መንገዱ ከዛሬ ሰኞ ነሐሴ 18 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ በከፊል ለትራፊክ ዝግ እንደሚደረግ አስታውቋል ። ከአያት 49 ወደ ፊጋ በሚወስደው መንገድ ላይ 72 ድልድይ አካባቢ የሚካሄደው የመንገድ ጥገና ሥራ በፍጥነት እንዲጠናቀቅ መንገዱን በከፊል ለትራፊክ መዝጋት እንዳስፈለገ ገልጸዋል። የጥገና ሥራው በሚካሄድበት ወቅት በአካባቢው የትራፊክ መጨናነቅ ሊፈጠር እንደሚችል የተጠበቀ ሲሆን ለመንገድ ተጠቃሚዎች እንቅስቃሴ ችግር እንዳይፈጠር አሽከርካሪዎች ቀድመው የጉዞ እቅዳቸውን እንዲያስተካክሉ ባለሥልጣኑ አሳስቧል። በመሆኑም አሽከርካሪዎች በ72 ድልድይ አካባቢ ሲያልፉ ተጨማሪ ጥንቃቄ እንዲያደርጉ  የትራፊክ መመሪያዎችን እንዲከተሉና በተቻለ መጠን አማራጭ መንገዶችን እንዲጠቀሙ ባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ ጥሪ አቅርቧል።

​📌 አዲስ መሬት የያዘው የብሔራዊ ባንክ ስትራቴጂ፡ ከወለድ ነፃ የባንክ ገበያ ​የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በፍጥነት እያደገ ላለው ከወለድ ነፃ የፋይናንስ ዘርፍ አጠቃላይ ስትራቴጂያዊ መመሪያ ማዘጋጀቱ ተሰማ። ​📊 የዘርፉ ወቅታዊ ሁኔታ፡ ​31 የንግድ ባንኮች በአገሪቱ ውስጥ ይገኛሉ። ​ከነዚህም ውስጥ 23ቱ ከወለድ ነፃ የባንክ አገልግሎት በመስጠት ላይ ናቸው። ​በ26 ሚሊዮን የባንክ ሂሳቦች ውስጥ ከ331 ቢሊዮን ብር በላይ ቁጠባ ተከማችቷል። ​✨ በአዲሱ ስትራቴጂ የሚተገበሩ ዋና ዋና ነጥቦች፡ ​ግብር፡ ከወለድ ነፃ ፋይናንስን ከመደበኛው ብድር ጋር እኩል የግብር ተተኳሪነት እንዲኖረው ማድረግ። ​አዳዲስ ምርቶች፡ የሱኩክ ቦንድ ማስተዋወቅ። ​ቁጥጥር፡ ብሔራዊ የሸሪዓ ቁጥጥር ቦርድ ማቋቋም። ​ማስፋፋት፡ አገልግሎቱን ወደ አነስተኛ ፋይናንስ እና ዲጂታል ቴክኖሎጂ ማድረስ። ​ይህ እርምጃ የኢትዮጵያን የፋይናንስ ሥርዓት አካታችና ይበልጥ አዋጪ በማድረግ ረገድ ትልቅ ሚና ይጫወታል ተብሎ ይጠበቃል። ​ኢትዮ ኮን — ትክክለኛ የመረጃ ምንጭ

▶️ ሳምንታዊ ዓለም አቀፍ የኮንስትራክሽን እና ኢንጂነሪንግ ዳሰሳ ዓለም አቀፍ የኮንስትራክሽን፣ የኢንጂነሪንግ እና የቴክኖሎጂ ዜና ምንጮች ​🌍 የሳምንቱ ዓለም አቀፍ የኮንስትራክሽን ገበታ እና ዋና ዋና ዜናዎች ​1. የሜጋ ፕሮጀክቶች አፈፃፀም እና የትኩረት ማዕቀፍ በዓለም አቀፍ ደረጃ የኮንስትራክሽን ገበያው ከሰፊው የዕድገት ትንበያ ይልቅ አሁን ላይ "በአስፈላጊ ፍላጎት (Essential Demand)" ላይ የተመሰረተ ምርጫ እያደረገ ይገኛል። እንደ የትራንስፖርት መሠረተ ልማቶች፣ የታደሰ ኃይል ማመንጫዎች እና የዲጂታል ዳታ ማዕከላት ያሉ ወሳኝ ፕሮጀክቶች ቀዳሚውን የፋይናንስ ድልድል እያገኙ ሲሆን፣ በግል ባለሀብቶች የሚመሩ የቅንጦት እና የቢሮ ግንባታዎች ጥብቅ የኢኮኖሚ ምዘና እየተደረገባቸው ይገኛል። ​2. የሳውዲ አረቢያው የኒዮም (NEOM) እና የሜጋ ፕሮጀክቶች ምዕራፍ የሳውዲ አረቢያው የትራንስፎርሜሽን ፕሮጀክት የሆነው NEOM በዓለም ትኩረት ማዕከልነቱን ቀጥሏል። በተለይም በኦክሳጎን (Oxagon) የኢንዱስትሪ ማዕከል እና በሲንዳላህ (Sindalah) የቱሪዝም መዳረሻዎች ላይ እየተከናወኑ ያሉ የዲጂታል ቴክኖሎጂዎችና የታደሰ ኃይል (Green Hydrogen) ዝርጋታዎች ለቀጣዩ ትውልድ ስማርት ከተሞች ግንባታ አርአያ እየሆኑ ይገኛሉ። ​3. የሆቴል እና ቱሪዝም ኢንፍራስትራክሽን ዕድገት በዓለም አቀፍ ደረጃ የሆቴል ግንባታ ማዕቀፍ (Global Hotel Construction Pipeline) አዲስ ክብረ ወሰን አስመዝግቦ እጅግ ከፍ ባለ ደረጃ ላይ ይገኛል። በተለይም አሜሪካ እና እስያ (ቻይናን ጨምሮ) ግንባር ቀደም ተጠቃሽ ሲሆኑ፣ የቅንጦት (Luxury) እና የምርት ስም ማሻሻያ (Brand Conversion) ፕሮጀክቶች የገበያውን ሰፊ ድርሻ ይዘዋል። ​4. በግንባታ ቴክኖሎጂ እና አረንጓዴ ዕድገት (ConTech & BIM) የህንፃ መረጃ ሞዴሊንግ (BIM)፣ አርቴፊሻል ኢንተለጀንስ (AI) በዕቅድ አስተዳደር ውስጥ ያለው ሚና፣ እንዲሁም የካርቦን ልቀትን የሚቀንሱ አረንጓዴ የኮንስትራክሽን ግብዓቶች አጠቃቀም በዓለም አቀፍ ተቋራጮች ዘንድ የውድድር መመዘኛ እየሆኑ መጥተዋል። ​ኢትዮ ኮን - ትክክለኛ የመረጃ ምንጭ

👉 የተሻሻለዉ የፌዴራል ታክስ አስተዳደር አዋጅ በነጋሪት ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ሐምሌ 23 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ስራ ላይ ውሏል።