ar
Feedback
የገ/ጉ/ወ/ወ/የመ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት

የገ/ጉ/ወ/ወ/የመ/ኮ/ጉ/ጽ/ቤት

الذهاب إلى القناة على Telegram
913
المشتركون
-124 ساعات
+27 أيام
-730 أيام
أرشيف المشاركات
ሰኔ 26/2018 ዓ/ም ሀሚሊን ፌስቱላ ኢትዮጵያ ግብረ ሰናይ ድርጅት በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ፕሮጀክት ዜሮ ወረዳ በወረዳ ከኢትዮጵያ የማጥፋት ፍኖተ ካርታ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር በወልቂጤ ከተማ በዛሬው እለት ተካሄደ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ ሀሚሊን ፌስቱላ ኢትዮጵያ የተሰኘ ግብረ ሰናይ ድርጅት በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ለሚገኙ 6 ጤና ጣቢያዎችና በሁሉም ቀበሌዎች ፕሮጀክት ዜሮ ወረዳ በወረዳ ከኢትዮጵያ የማጥፋት ፍኖተ ካርታ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር በወልቂጤ ከተማ በዛሬው እለት ተካሄዷል። የሀሚሊን ፌስቱላ ኢትዮጵያ ኮርዲኔተር ወ/ሮ ሚስጥር አለባቸው በመርሃ ግብሩ ተገኝተው እንዳሉት ከ63 ዓመታት በፊት በአውስትራሊያዊቷ ፋና ወጊ የቀዶ ጥገና ሐኪም ዶክተር ካትሪን ሃምሊን እና ባለቤቷ ዶ/ር ሬግ ሃምሊን የተመሠረተው ሃምሊን ፊስቱላ ኢትዮጵያ እጅግ አሰቃቂ የሆነው የወሊድ ጉዳት ወይም የማሕፀን ፊስቱላ የደረሰባቸውን ኢትዮጵያውያን ሴቶች ለማከም መሆኑን ገልጸዋል። ወ/ሮ ሚስጥር አለባቸው አክለውም ሀምሊን ፊስቱላ ኢትዮጵያ ባለፉት 63 አመታት ከ70,000 በላይ የሚሆኑ ለማሕፀን ፊስቱላ የተጋለጡ ኢትዮጵያውያን ሴቶችን ጤና እና ክብር መመለሱን ጠቅሰው ዶ/ር ካትሪን ሃምሊን የፊስቱላ ታካሚን ማከም በፊኛ ላይ ያለውን ቀዳዳ ማከም ብቻ ሳይሆን ሴትን በሙሉ በፍቅር እና በጥንቃቄ ማከም እንደሆነ ሁልጊዜ ያምኑ ስለነበር በሃምሊን ፊስቱላ ኢትዮጵያ ከፊስቱላ ጉዳት የሚያገግሙ ሴቶችን የበለጠ ለመደገፍ የማገገሚያ እና የመልሶ ማቋቋም ፕሮግራም በማዘጋጀት የሃምሊን የሕክምና ሞዴል ያቀፈ እና ሴቶች በነጻነት እና በክብር ሕይወታቸውን እንዲመሩ የሚያስችል እንደሆነ ተናግረዋል። ሀሚሊን ፌስቱላ ኢትዮጵያ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ለሚገኙ 6 ጤና ጣቢያዎች ፕሮጀክት ዜሮ ወረዳ በወረዳ ከኢትዮጵያ የማጥፋት ፍኖተ ካርታ በይፋ መጀመሩን አስታውቀዋል። ወ/ሮ ሀና ተስፋዬ ፕሮጀክት ዜሮ ኮርዲኔተር ስለ ፕሮጀክቱ አጠቃላይ አላማና ግብ እንዲሁም እስካሁን በወረዳው የተሰሩ የአሰስመንት ስራዎች ለታዳሚዎች በማቅረብ አጠር ያለ ውይይት የተደረገ ሲሆን ለተነሱ ጥያቄና አስተያየቶች ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶል። በፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን የብልጽግና መንግስት በሽታ መከላከልንና አክሞ የማዳን ፖሊሲ በመቅረጽ ወደ ተግባር በመግባት የህዝቡን የጤና ችግር ለመቅረፍ ከመቼውም ጊዜ በላይ የበጎ አድራጎት ድርጅቶችን የአካባቢ ተወላጅ ባለሀብቶችና ህዝቡን በማቀናጀት በወረዳ ደረጃ በርካታ ተግባር እያከናወነ እንደሚገኝ ገልጸው የሀሚሊን ፌስቱላ ኢትዮጵያ ግብረ ሰናይ ድርጅት ወረዳችን ተማራጭ አድርጎ እንዲሰራ አስተዋጾ ላደረጉ በየደረጃው ለሚገኙ አካላት በወረዳው መንግስትና ህዝብ ስም ላቅ ያለ ምስጋናቸውን በማቅረብ ለበጎ አድራጊ ድርጅቱ አሰፈላጊውን ድጋፍ እንደሚያደርጉ አስገንዝበዋል። በመርሃ ግብሩ ላይ ወ/ሮ ሚስጥር አለባቸው የሀሚሊን ፌስቱላ ኢትዮጵያ ኮርዲኔተር፣ ወ/ሮ ሀና ተስፋዬ  ፕሮጀክት ዜሮ ኮርዲኔተር፣አቶ ዱጉማ ጋሮምሳ ፌስቱላ ኢትዮጵያ ፋይናንስ፣የጉራጌ ዞን ጤና መምሪያ ኃላፊ አቶ አየለ ፈቀደ፣የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፋታ ሁሴን ፣የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል እና የጉራጌ ዞን ባለሙያዎች ፣ የወረዳው ሴቶች ህጻናት ጉዳይ ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ ፈትያ መህዲ፣የወረዳው ጤና ጥበቃ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ኢብራሂም አብራር፣የጤና ጣቢያ ኃላፊዎችና የሃይማኖት አባቶችና ባለድርሽ አካላት ተገኝተዋል።

ሰኔ 23/2018 ዓ.ም የአየር ብክለትን በመቀነስ ለዜጎች ምቹና ማራኪ አከባቢ መፍጠር እንደሚገባ የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ደንና አከባቢ ጥበቃ ልማት ፅ/ቤት አስታወቀ ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ ይህ የተገለፀው የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ደንና አከባቢ ጥበቃ  ልማት ፅህፈት ቤት "ብክለትን እንቀንስ እንቆጣጠር"በሚል መሪ ቃል ከባለድርሻ አካላት የውይይት መድረክ በተካሄደበት ወቅት ነው ። የዕለቱ የመወያያ ዕቅድ ሰነድ በጽ/ቤቱ ኃላፊ በአቶ አብዲ አ/ሀፊዝ ቀርቦ ሰፋ ያለ ውይይት ተደርጓል። ከተሳታፊዎች ከተነሱ ሀሳብ አስተያየቶች መካከል  ለተግባሩ መሳካት አዋጅና መመሪያ ተግባራዊ መደረግ እንዳለበት ፣ምግብ ቤቶች ፣ሻይ ቡና ቤቶች ሽንት ቤት ማዘጋጀት እንደሚገባቸው አዲስ እየተሰራ ያለው መንገድ ላይ ቆሻሻ እየተጣለ መሆኑና የፈሳሽ ቆሻሻ ማስወገጃ ዲች በቆሻሻ እየተዘጋ መሆኑ ፣ባለድርሻ ተቋማት ተጠያቂ ማድረግ እንደሚገባ፣ የግንዛቤ ስራዎች በቅንጅት መስራት እንደሚያስፈልግ በጎ ፍቃደኛ ወጣቶችን በማቀናጀት የከተማ ንፅህና መጠበቅ የጋራ ዕቅድ መታቀድ እንዳለበት የሚሉት ናቸው ። የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ደንና አከባቢ ጥበቃ  ልማት ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አብዲ አ/ሀፊዝ እንደተናገሩት  የአካባቢያችን ውበትና ንፅህና ለመጠበቅ ተቋማት ተግባሮቻቸውን ማከናወን መቻል እንዳለባቸው ገልፀው አካባቢ ብክለትን ለመግታትና ህብረተሰቡን ያሳተፈ የአካባቢ ጥበቃ ስራን ለማጠናከር “ብክለት ይብቃ፣ ውበት ይንቃ!” በሚል መሪ ቃል የተፈጠረው የንቅናቄ መርሃ-ግብር ውጤታማ እንዲሆን አካባቢ ጥበቃ ስራ በልዩ ትኩት መስራት እንደሚገባ አስታውሰዋል። በከተሞች አካባቢ የሚታየውን የደረቅ፣ የፈሳሽ፣ የውሃ እና የድምፅ ብክለትን ለመቆጣጠር ቅንጅታዊ ስራ ማጠናከርና ባለድርሻ ተቋማት በጋራ በመስራት እንደ ተቋም ያሉብን ተግባራት ወስደን በመስራት ምቹና ማራኪ አከባቢ ለመፍጠር እንሰራለን ሲሉ ተናግረዋል። መድረኩን የመሩት የወረዳው መንግስት ረዳት ተጠሪ አቶ ሚፍታ አረቦ በበኩላቸው በመንገዶችና በተከለከሉ ቦታዎች የሚጣሉ የቆሻሻዎች ምንጭ በመለየት መመሪያ ለሚተላለፉ አካላት ተገቢው እርማት ማድረግ እንዳለባቸው የንግድ ድርጅቶች የሚሰሩበት ዘርፍ በመለየት ስራ መስራት እንደሚገባና ህግ መተግበር እንደሚገባ ተናግረዋል። የአካባቢ ብክለትን ለመቀነስ እና ለመከላከል ዋናው መፍትሔ የቆሻሻ አወጋገድ ስርዓትን ማሻሻል መሆኑ አስታውሰው የአረንጓዴ አሻራ ስራን በማጠናከር የአካባቢያችንን ጤና ለመጠበቅ የየዕለት ተግባሮቻችንን ማስተካከል እንደሚገባ ገልጸዋል።

ሰኔ 22/2018 ዓ.ም በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ 8.5 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል የቅድመ ዝግጅት ስራዎች መጠናቀቃቸውን  የወረዳው ደንና አካባቢ ጥበቃ ጽ/ቤት ገለፀ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ በ2018/19 የአረንጓዴ አሻራ መርሀ ግብር 8.5 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል እቅድ መያዙንና እስካሁን ከ6.5 ሚሊዮን በላይ ጉድጓድ መዘጋጀቱን ጽ/ቤት አክሎ ገልጿል። የወረዳው ደንና አካባቢ ጥበቃ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አብዲ አ/ሃፊዝ ባለፉት ዓመታት በተከናወኑት የአፈርና ውሃ ጥበቃ ስራዎች ተጨባጭ ውጤት መገኙቱን አስታውቀዋል። አቶ አብዲ አያይዘውም በችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ ላይ፤ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ነባርና ሀገር በቀል ችግኞ እንደሚተከሉ ጠቅሰው ለችግኝ ተከላ መርሃ ግብሩ፤ ከችግኝ ማፍላት ጀምሮ ሌሎች አስፈላጊ የቅድመ ዝግጅት ስራ መጠናቀቁንም አንስተዋል። በተለይም የአፈር ለምነትን የሚያሻሽሉ፣ ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ያላቸው፣ አግሮ ኢኮሎጂው ላይ ለውጥ የሚያመጡ ችግኞችን ለመትከል ስለመታቀዱ ተናግረዋል የዘንድሮው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያለቸው 8.5 ሚሊዮን ችግኞች የተዘጋጁ ሲሆን ከነዚሁ የተዘሩት ችግኞች መካከልም ለአካባቢ ጥበቃ፣ ለግንባታ እና ለማገዶ ዓላማ የሚውል ችግኞች ለመትከል መዘጋጀታቸውን አስታውቀዋል። በመንግስት ችግኝ ጣቢያ፤ በተቋማት፣ በአርሶ አደር ጓሮ፣ በግል፣ በማህበረሰብና በሌሎችም ችግኞቹ መዘጋጀታቸውን አቶ አብዲ አብራርተዋል። ከጉድጓድ ዝግጅት አፈፃፀም ጋር በተያያዘ ኃላፊው 8.5 ሚሊዮን በላይ ጉድጓድ ለማዘጋጀት በተያዘው ዕቅድ መሠረት እስካሁን ባለው ጊዜ ውስጥ 6.5 ሚሊየን በላይ ጉድጓድ የተዘጋጀ ሲሆን ቀሪው በቁፋሮ ሂደት ላይ እንደሚገኝ አስረድተዋል። በመጨረሻም አቶ አብዲ አ/ሃፊዝ ባስተላለፉት መልዕክት የዘንድሮውን የአረንጓዴ አሻራ መርሃ-ግብር ለማሳካት የሚደረገውን ርብርብ  በየደረጃው የሚገኙ አካላት እገዛቸውን አጠናክረው ማስቀጠል እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።

ሰኔ 21/2018 ዓ.ም በጉራጌ ዞን በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ በደነብ ቀበሌ በወዶ ጫንጮ መንደር የሙዝ ልማት በክላስተር ተካላ  ተጀመረ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ የ30-40-30 የፍራፍሬ ልማት ኢንሼቲቭ አካል የሆነው የሙዝ ልማት ክላስተር በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ በደነብ ቀበሌ በወዶ ጫንጮ መንደር ተመሰረተ። የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፋታ ሁሴን በተከላ ወቅት ተገኝተው በወረዳው ያሉ እምቅ ሀብቶችን በመጠቀም እንዲሁም ያሉ አቅሞችን ወደ ውጤት በመቀየርና የአርሶ አደሩን የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ እንደሚገባ አስገንዝበዋል። ሁሉም እርሶ አደር ሰይሰላችና በእንክብካቤ በማልማት አሁን የተተከለውን ችግኝ ፍሬ አፍርቶ ለማየት ሁሉም አካላት በርብርብ ሊሰሩ ይገባል ሲሉም ተናግረዋል። የወረዳው ም/አስተዳደርና ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ከድር መርጋ በበኩላቸው አርሶአደሩን በክላስተር በማደራጀት ፣ የክህሎት ስልጠና በመስጠት ከመሬት ዝግጅት ጀምሮ እስከ ተከላ ድረስ በባለሙያ ድጋፋዊ ክትትል ከተቋም ጀምሮ ጠንካራ ስራ መሰራቱን ጠቅሠው ቀጣይም ተጠናክሮ የሚቀጥል መሆኑን ገልጸዋል። ክላስተሩ እንዲመሰረትና የተሻሻለ የሙዝ ዝርያ G-ካቪዴሽን የተባለ ዝርያ በማቅረብ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ግብርና ቢሮ ከ4500 ሺህ በላይ ችግኝ ሙሉ ድጋፍ ማድረጉን ገልጸው በተቋማቸው ስም ላቅ ያለ ምስጋናቸውን አቶ ከድር መርጋ አቅርበዋል። የሙዝ ልማት ክላስተር ምስረታና ተከላ ፕሮግራም ላይ የወረዳው ዋናአስተዳዳሪ አቶ ሚፍታ ሁሴን፣ የወረዳው ብልጽግና ፓርቲ ጽ/ቤት ኃላፊና የመንግስት ዋና ተጠሪ አቶ አ/ረሂም ርዳ፣ የወረዳው ረዳት የመንግስት ተጠሪ አቶ ጠይብ አስፍር፣የወረዳው ግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ከድር መርጋ እና የጽ/ቤት ባለሙያዎች ተገኝተዋል።

የሳምንቱ ዓብይት ዜናዎች ሰኔ 21/2018 ዓ.ም 🎤  የሴቶችን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ይበልጥ ለማረጋገጥ የሴቶች ልማት ህብረት ስትሪንግ ኮሚቴዎች በተጠናከረና በተቀናጀ አግባብ ትኩረት ሰጥተው ሊሰሩ ይገባል ተባለ፡፡ ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤  የማር ምርት ጥራትን ለማሳደግና ምርትና ምርታማነትን ለማረጋገጥ ትኩረት ሰጥቶ እየተሰራ መሆኑን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ግብርና ጽ/ቤት ገለፀ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤  በወረዳው ያለውን የሰላም እሴት ለማፅናት የፀጥታው መዋቅር እያከናወነ ያለውን ተግባራት ይበልጥ ማጠናከር እንዳለበት ተገለጸ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤  የገደባኖ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ላለፉት ለሶስት አመታት ያስተማራቸው 64 የቅድመ አንደኛ ደረጃ ተማሪዎች ለ3ኛ ዙር በታላቅ ድምቀት አስመረቀ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤  በ2018/19 ምርት ዘመን 20 ሺህ 518 ሄክታ በላይ መሬት በዘር ለመሸፈን አቅዶ እየሰራ እንደሚገኝ የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ግብርና ፅ/ቤት አስታወቀ። ፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨ 🎤 "ኢትዮጵያ መርጣለች! አሸንፋለች! ኑ አገር በጋራ እንገንባ"በሚል መሪ ቃል በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የህዝብ የውይይት መድረክ ተካሄደ። ‎፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨