ar
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

الذهاب إلى القناة على Telegram

إظهار المزيد
1 077
المشتركون
+524 ساعات
+107 أيام
+530 أيام
أرشيف المشاركات
photo content
+7

በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር የአሰሪና ሰራተኛ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ዳንኤል ተሬሳ የሚመራ የሱፐርቪዥን ቡድን በድሬደዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የተሰሩ ስራዎችን እየጎበኙ እንደሚገኝ ተገለጸ። በሚኒስትር ዴኤታው የተመራው ቡድን በዛሬው ዕለት በዋናነት በአሰሪና ሰራተኛው ዘርፍ በኢንደስትሪዎች እና በኤጀንሲዎች ያለውን አጠቃላይ የስራ ሁኔታ እና የሙያ ደህንነትና ጤንነት ያለበትን ደረጃ ምልከታ ያደረገ ሲሆን በስራ ዕድል ፈጠራ እና ከኢንተርፕራይዝ ልማት አኳያ በወረዳ 08 እና 09 የተተገበሩና የስራ ዕድል ፈጠራ ተግባራት ያስገኛቸው ውጤቶችና ተጠቃሚ የሆኑ የማህበረሰብ ክፍሎችን ተመልክቷል። የሱፐርቪዥን ቡድኑ ድሬዳዋ የተገኘበት ዋና አላማ እንደ ሀገር በሥራና ክህሎት በኩል የሚሰሩ ስራዎች በህብረተሰቡ ተጠቃሚነት ረገድ የታሰበላቸውን ውጤት እንዲያስገኙ ድጋፍና ክትትል ለማድረግ መሆኑን ገልፀው በጉብኝታቸውም በከተማዋ በሥራና ክህሎት በኩል የህብረተሰቡ  ተጠቃሚነት ምን ደረጃ ላይ እንዳለ ለመመልከት ነዉ ብለዋል። ዛሬን ጨምሮ በቀጣይ በአስተዳደሩ በሚኖራቸው ቆይታም እንደ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በተቀመጡ አራት ዋና ዋና ጉዳዮች መሠረት ማለትም የተቋማት ግንባታ፣ የክህሎት ልማት፣ የሥራ ዕድል ፈጠራ፣ የአሰሪና ሠራተኛ ጉዳይና የኢንዱስትሪ ሰላም በአስተዳደሩ በምን አይነት ሁኔታ እየተጓዘ እንዳለ ምልከታ በማድረግ ላይ እንደሚገኙ ሚኒስቴር ዴኤታው ገልጸዋል። አቶ ዳንኤል አክለውም በድሬደዋ የተመለከቷቸውን የሥራ ዕድል ፈጠራ እንደ ሀገር ሚናቸው የላቀ እንዲሆን የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከአስተዳደሩ ጋር በቅንጅት እንደሚሰራና ብሎም አስፈላጊውን ድጋፍና ክትትል እንደሚያደርግ ነው ያረጋገጡት። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 23/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+9

በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ከፍተኛ አመራሮች የሚመራ የድጋፍና ክትትል ቡድን ድሬዳዋ ገባ። በሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ ሚኒስትር ድኤታ ክቡር አቶ ዳንኤል ቴሬሳ የተመራው ቡድኑ አስተዳደሩ የሥራና ክህሎት ቢሮ በበጀት አመቱ የተሰሩ ስራዎች ላይ የመስክ ምልከታ የሚያደርግ ይሆናል። በዛሬው ውሎም በመስክ ምልከታው ከክህሎት ልማት፣ ሥራ ዕድል ፈጠራ፣ አሠሪና ሠራተኛ ግንኙት እና ከተቋማት ግንባታ አኳያ የተሰሩ ሥራዎች ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተካሂዶባቸዋል። በዚህም ቡድኑ የተመረጡ የግልና የመንግስት የቴክኒክና ሙያ ማሰልጠኛ ተቋማትን፣ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫ ማዕከላትን፣ ኢንተርፕራይዞችን፣ የገጠር ሥራ ዕድል ፈጠራ ሥራንና ኢንዱስትሪዎችን ተዘዋውሮ የሚመለከት ይሆናል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 21/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+9

የግል ኮሌጆች  ከመንግስት  ኮሌጆች  ጋር  በቅንጅት  እና በመተባበር  ለጥቃቅን፣ አነስተኛና መካከለኛ  ኢንተርፕራይዞች የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ቴክኖሎጂ ሽግግር አገልግሎት  ድጋፍ ለማድረግ  የመግባቢያ  ሰነድ  ተፈራረሙ ። ከሥራና ክህሎት ቢሮ ጋር የመግባቢያ ሰነድ የተፈራረሙ የግል ኮሌጆች የሚከተሉት ናቸው፦ ✍️ አዲስ አበባ ቢዝነስና  ሜዲካል  ኮሌጅ ✍️ ኦልብራይት ኢንተርናሽናል  ኮሌጅ ✍️ ሉሲ ኮሌጅ ✍️ ሪፍት ቫሊ ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ✍️ ሲቲ ጤናና  ቢዝነስ ኮሌጅ   ✍️ ሻሎም ኢንጅነሪንግ ኮሌጅ በዚህም በአስተዳደሩ የሚገኙ ከላይ የተዘረዘሩት ኮሌጆች ከሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች ማለትም የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ እና የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች ጋር በክላስተር የተደለደሉ ሲሆን በአጭር ጊዜ የጋራ ግንዛቤ በመፍጠር ወደ ስራ የሚገቡ መሆኑን የቢሮው ም/ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ገልጸዋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 21/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content

ችግር ፈቺ በሆነ የተግባራዊ ጥናትና ምርምር አዘገጃጀት ላይ ያተኮረ ስልጠና ለቢሮ ባለሙያዎች እና ለኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራን ተሰጠ፤ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የኢንዱሰትሪ ኤክስቴንሽንና የቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት ችግር ፈቺ የሆኑ ጥናትና ምርምሮችን በዘርፉ የሚገኙ አሰልጣኝ መምህራን እና ባለሙያዎች እንዲሰሩ ምቹ ሁኔታ በመፍጠር ድጋፍ ያደርጋል። በዚህም ከቢሮው ለተወጣጡ ባለሙያዎች እና ከሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች ለተወጣጡ የአሰልጣኝ መምህራን በተግባራዊ ጥናትና ምርምር ላይ ያተኮረ ስልጠና በማዘጋጀት አቅም የሚገነቡበትን ዕድል ፈጥሯል፤ ይህም ስልጠና መሰረታዊ ጥናትና ምርምር ከተግባራዊ ጥናትና ምርምር ያለው ልዩነት፤ የአጠናን ስነ-ዘዴን በማወቅ የተቋማዊ ችግሮች ልየታ፤ ምልከታ በማድረግ ለተግባራዊ ጥናትና ምርምር ማድረግ በሚያስችሉ ጽንሰ ሃሳባዊና ተግባራዊ ዝግጅት ማድረግ የሚያስችል ይሆናል። ስልጠናውም ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ በመጡ አሰልጣኝ የተሰጠ ሲሆን  የስልጠናውም ዋና ዓላማ ባለሙያዎችና አሰልጣኝ መምህራኑ በስራ ቦታቸው ላይ  ያሉ ችግሮችን ተግባራዊ ልየታ በማድረግ በጥናትና ምርምር ላይ ተመስርቶ እንዲፈቱ በሚያስችል አቅም ለመገንባት ታሳቢ ያደረገ ነው። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 21/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+6

“ሰብአዊ መብትን ያከበረ የኤች አይ ቪ አገልግሎት ለሁሉም!” በሚል መሪ ቃል የአለም የኤች አይ ቪ ኤድስ ቀን በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በፓናል ውይይት እና የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በመስጠት ተከብሮ ዋለ፡፡ በአለም ለ37ኛ ግዜ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ36ኛ ግዜ “ሰብአዊ መብትን ያከበረ የኤች አይ ቪ አገልግሎት ለሁሉም!” በሚል መሪ ቃል የአለም የኤች አይ ቪ ኤድስ ቀን በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በፓናል ውይይት ተከብሮ የዋለ ሲሆን በእለቱም በመገኘት መድረኩን በንግግር የከፈቱት የኮሌጁ የኢ/ኤ/ቴ/ሽ ም/ዲን የሆኑት ወ/ሮ ትግስት በዙ ሲሆኑ በንግግራቸውም ጤናማ ትውልድ ለማፍራት ጤናውን የጠበቀ መምህርና የአስተዳደር ሰራተኛ ያስፈልጋል ስለሆነም ሁሉም የኮሌጁ ማህበረሰብ ራሱን እና ቤተሰቡን ከHIV AIDS ሊጠብቅ ይገባል ብለዋል፡፡ HIV AIDS ሀገር ወደ ፊት ለመሄድ ስትል ወጣቱን እና ለስራ ዝግጁ የሆነውን ትውልድ እያጠፋ እንዳትሄድ የሚያደርግና ለድህነት ምንጭ የሆነ አስከፊ በሽታ ነው ይህን በሽታ አመራሩና የኮሌጁ ሰራተኞች በጋራ በመሆን ማህበረሰቡ ንቃተ ህሊናው እንዲዳብር የተለያዩ ስራዎችን በጋራ መስራት እንደሚገባ አያይዘው ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪ ዘገባ “ሀገራዊ መግባባት ለህብረ ብሔራዊ አንድነት” በሚል መሪ ቃል 19ኛው የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በኮሌጁ አዳራሽ ተከብሮ ውሏል፡፡ በግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እና የኢትዮጵያ ብሔሮች፣ብሔረሰቦች እና ህዝቦች ቀን ክብረ በዓል ላይ የኮሌጁ ምክትል ዲኖችና አመራሮች እንዲሁም አጠቃላይ የኮሌጁ ማህበረሰቦች ተገኝተዋል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ህዳር 20/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

የቴክኖሎጂ እሴት ሰንሰለት ትንተና እና ሰነድ ዝግጅት ላይ ያኮረ ስልጠና ከየዘርፍ መስሪያ ቤቶች ለተወጣጡ ባለሙያዎች ስልጠና ተሰጠ፡፡ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና የቴክኖለጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት ከትኩረት ዘርፍ መ/ቤት ለተውጣጡ ባለሞያዎች፤ ለኮሌጅ አሰልጣኝ መምህራንና ከድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ ለተውጣጡ መምህራኖች የእሴት ሰንሰለት ትንተና ስልጠና ተሰጠ፡፡ ከቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ሥልጠና ዘርፍ ተልዕኮዎች ውስጥ አንዱ ተወዳዳሪነትን የሚያረጋግጥ አዋጭ ቴክኖሎጂ ለኢንተርፕራይዞች ማሸጋገር መሆኑን ጠቅሰው የምርት ወይም የአገልግሎት የአመራት ሂደት በመተንተን ክፍተቶችን በመለየት እና ለክፍተቶቹም የቴክኖሎጂዎችን መፍትሄ ለማስቀመጥ የእሴት ሰንሰለት ትንተና ማከናወን አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የዚህ ስልጠና ዋና አላማ ከትኩረት መ/ቤት የተውጣጡ የተለያዩ ባለሞያዎች የዘርፋቸውን እሴት ሰንሰለት መስራት እንዲችሉና ዘርፉን ተወዳዳሪ በማድረግ የስራ ዕድል እንዲፈጥር ለማድረግ ታሳቢ ያደረገ ሲሆን በሚለዩት ቴክኖሎጂዎች የኢንተርፕራይዞችን፣ የተቋማትን እና የኢንዱስትሪዎችን ምርታማነትና ተወዳዳሪነት በመጨመር ለበርካታ ዜጎች የሥራ-ዕድል ለመፍጠርና እና የገቢ መጠን ለመጨመር እንደሚያስችል ተናግረዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 19/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+7

በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ የአሰሪና ሰራተኛ ዳይሬክቶሬት በተለያዩ አዋጆች ዙሪያ ለአስተዳደሩ ነዋሪዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄደ። በመድረኩም ከሁሉም የወረዳ አስተዳደር ስር የተወጣጡ ነዋሪዎች ተሳታፊ የሆኑ ሲሆን በሰዎች መነገድ፣ ሰዎችን በህገወጥ መንገድ ድንበር ማሻገር እና ለስራ ወደ ውጭ ሀገር መላክ ወንጀል አዋጅ ቁጥር 1178/2012 እና ህጋዊ የውጭ ሀገር የስራ ስምሪት አዋጅ ቁጥር 1246/2013 ላይ ግንዛቤ ተፈጥሮላቸዋል። በዚህም አዋጆቹን በመረዳት በሰዎች የመነገድ፣ በህገወጥ መንገድ ድንበር ማሻገር እና በህገወጥ መንገድ ለስራ ወደውጭ ሀገር መላክ ወንጀልን በመከላከል ረገድ የህብረተሰቡን ግንዛቤ ማሳደግ ዓላማው አድርጎ ከዚህ በተያያዘ ህጋዊው የውጭ ሀገር የስራ ስምሪት አካሄድ ላይ ገለፃ ተደርጎላቸዋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 18/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+6

የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ2017 ዓ.ም የመጀመሪያ ሩብ ዓመት በዝግጅት ምዕራፍ የተከናወኑ ጉዳዮች ላይና በእቅድ አፈፃፀሙ ላይ ከአሰልጣኝ መምህራን ጋር የውይይት እና የግምገማ መድረክ አካሂዷል
+7
የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ2017 ዓ.ም የመጀመሪያ ሩብ ዓመት በዝግጅት ምዕራፍ የተከናወኑ ጉዳዮች ላይና በእቅድ አፈፃፀሙ ላይ ከአሰልጣኝ መምህራን ጋር የውይይት እና የግምገማ መድረክ አካሂዷል ። በ2017 ዓ.ም በጀት አመት የመጀመሪያ ሩብ ዓመት የእቅድ ክንውን ከትምህርትና ስልጠና፣በኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር አገልግሎት፣ ለኮሌጁ ተጨማሪ ገቢን ከማስገኘት አንጻር አንዲሁም በአጫጭር ስልጠና እና ከኢንዱስትሪዎች ጋር መልካም ትስስርን ከመፍጠር አንጻር በዝግጅት ምእራፍ ውስጥ በርካታ ስራዎች መሰራታቸውን እንዲሁም በቀጣይ ሩብ አመት የተሸለ አፈጻጸም ለማስመዝገብ እንደሚሰራ የተገለጸ ሲሆን ከኢንዱስትሪዎች ጋር መልካም ትስስርን በመፍጠር የኢንዱስትሪዎችን ችግር ለመፍታት የተሰራው ስራ ለሌሎች ኮሌጆጅ ጭምር አርአያ የሆነና የኢንዱስትሪዎችን ችግር ከመፍታት በዘለለ ለኮሌጁም ተጨማሪ ገቢ ማስገኛ መንገድ መሆን እንደ ቻለ በእለቱ ተገልጿል ። በእለቱም በዝግጅት ምእራፉ የተሰሩ እንዲሁም በአዲሱ ዕሳቤ መሠረት የተጀመሩ ስራዎችን በተመለከተና አፈፃፀማቸውን በዘየደ ተክሌ የቀረበ ሲሆን በአፈጻጸሙ ላይና በአዲሱ እሳቤ ላይ ሰፊ ውይይትም ተደርጓል ። የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ህዳር 18/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

ለነፃ የንግድ ቀጠናው ስኬታማነት ባለድርሻ አካላት በተቀናጀ ሁኔታ ስራዎችን መስራት እንደሚገባቸው ተገለፀ። የድሬዳዋ ነፃ የንግድ ቀጠና ስኬታማ ለማድረግ ቁልፍ ባለድርሻ አካላት ኃላፊነታቸውን  በተቀናጀ አግባብ መወጣት  እንዳለባቸው ተገልጿል ። የነፃ የንግድ ቀጠና ምንነትና የባለድርሻ አካላት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በድሬዳዋ ነፃ የንግድ ቀጠና በአንድ ማዕከል አገልግሎት ስር ውስጥ ያሉ ባለድርሻ አካላት እና ለነፃ የንግድ ቀጠናው አመራሮች ተሰጥቷል። በስልጠናው መክፈቻ ላይ ንግግር ያደረጉት  የኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ስራ አስፈፃሚ አማካሪ አቶ ፍፁም ከተማ  የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናው የነፃ የንግድ ቀጠናውን በሙሉ አቅሙ ወደ ስራ በመግባቱ ለስኬታማነቱ ሁሉም ባለድርሻ አካላት የሚሰጡትን አገልግሎቶች በቅንጅት እንዲሰጡ ለማስቻል  ያለመ መሆኑን ገልፀዋል። አቶ ፍፁም በተጨማሪም ስልጠናው የነፃ የንግድ ቀጠናው ቀልጣፋና ፈጣን አገልግሎት ለመስጠት ሁሉም ባለድርሻ አካላት የራሳቸውን የቤት ስራ ወስደው ከመስራት ባለፈ  ስራዎችን ተቀናጅቶ መስራት በሚችሉበት ሁኔታ ላይ ሰፊ ግንዛቤ ወስደው እንዲሰሩና  በነፃ የንግድ ቀጠናው የሚሰጡ አገልግሎቶችን በፍጥነትና በጥራት ለመስጠት ያስችላል  ብለዋል። የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊና የከተማ አስተዳደሩ ተወካይ አቶ ሮቤል ጌታቸው በበኩላቸው የነፃ የንግድ ቀጠናው ከመሰረቱ ጀምሮ ለስኬታማነቱ ከፍተኛ ትኩረት ሰጥቶ ከኮርፖሬሽኑ ጋር ሲሰራ መቆየቱን ገልፀው አሁን ላይም በተሟላ ሁኔታ አገልግሎት እንዲሰጥ በሚያስፈልገው ድጋፍ ሁሉ ከተማ አስተዳደሩ ለመስራት ዝግጁ ነው ብለዋል። የነፃ የንግድ ቀጠና ምንነትና የባለድርሻ አካላት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ ትኩረት አድርጎ በተሰጠው የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ላይ የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን፤ጉምሩክ ኮሚሽን ፤ ኢትዮ ቴሌኮም፤የኢትዮ ኤሌክትሪክ አገልግሎት፤የባህር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ ፤ የተስማሚነት ምዘና፤ካይዘን፤ የከተማ አስተዳደሩ ተወካዮች ፤የፌዴራል የፀጥታ አካላት እና የተለያዩ የፋይናንስ ተቋማት ኃላፊዎችና ተወካዮች  ተሳትፈውበታል። #ምንጭ IPDC

photo content
+8

ለገቢራ - ድሬዳዋ!! በዛሬው እለት ክቡር ከንቲባ ከድር ጁሀር በተገኙበት በለገቢራ ገጠር ቀበሌ የደረሰ የማሽላ ማሳ ሰብሎች መሰብሰብ እና በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የተመረቱ 26 ዘመናዊ የንብ ቀፎዎችን ለአካባቢው ማህበረሰብ አስረክበናል። አቶ ሮቤል ጌታቸው የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ