ar
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

الذهاب إلى القناة على Telegram

إظهار المزيد
1 064
المشتركون
-224 ساعات
-77 أيام
+130 أيام
أرشيف المشاركات
photo content
+5

photo content

#ዜና|የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከተለያየ የትምህርት ክፍል ለተውጣጡ ሰልጣኝ ተማሪዎች ቻይና ከሚገኝ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በAI tools and Modeling ላይ ትኩረቱን ያደረገ ስልጠና በ
+4
#ዜና|የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከተለያየ የትምህርት ክፍል ለተውጣጡ ሰልጣኝ ተማሪዎች ቻይና ከሚገኝ   ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በAI tools and Modeling ላይ ትኩረቱን ያደረገ ስልጠና በዛሬው እለት መስጠት ጀመረ፡፡ በስልጠናው ማስጀመሪያ እለት በመገኘት ስልጠናውን በንግግር የከፈቱት የኮሌጁ ኢ/ኤ/ቴ/ሽ ም/ዲን ወ/ሮ ትግስት በዙ ሲሆኑ በንግግራቸውም ጊዜው የAI ነው ስልዚህ የምንሰራቸውን ስራዎች በ AI የታገዙ እንዲሆኑ እንዲሁም የምናሰለጥናቸው ሰልጣኞች መጪውን ዘመን እንዲረዱ እንዲህ አይነት መሰል ስልጠናዎችን በመስጠት የሰልጣኞችን አቅም ማጎልበት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ ም/ዲኗ አያይዘውም በኮሌጁ የሚሰለጥኑ ሰልጣኝ ተማሪዎች በቀጣይም ሀገር ውስጥ እንዲሁም ውጪ ሀገር ከሚገኙ ከተለያዩ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር በጋራ በመሆን የተለያዩ ስልጠናዎችን እንዲያገኙና ለስራው አለም ብቁ እና ዝግጁ ሆነው እንዲገኙ ኮሌጁ በትጋት የሚሰራ ይሆናል ብለዋል፡፡ በዛሬው እለት ቻይና ከሚገኝ ዩኒቨርሲቲ ጋር በጋራ በመሆን የተጀመረው ስልጠና በኮሌጁ በተቋቋመው የICT ስልጠና ማእከል ውስጥ ሲሆን የመጀመሪያ ዙሩ ስልጠና ለ2 ቀን የሚቆይ ይሆናል እንዲሁም ሁለተኛ ዙሩ በቀጣይቀናት ለ 5 ቀናት የሚሰጥ እንደሆነ ስልጠናውን ከሚያስተባብሩት አካላት ለማወቅ ተችሏል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ህዳር 10/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

በአስተዳደሩ 600 ያህል ሰዎችን የማስተናገድ አቅም ያለው ዘመናዊ የመሰብሰቢያ አዳራሽ በድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ከድር ጁሃር ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆነ። ዘመናዊ የመሠብሰቢያ አዳራሹ ዲዛይኑ ሙሉ በመሉ በውስጥ አቅም ባለሞያዎች መሰራቱ በወቅቱ ተገልጿል። የኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ አዳራሹ ከ37 ሚለዮን ብር በላይ ወጪ ተደርጎበት ሙሉ በመሉ የመልሶ ግንባታ ሥራው የተከናወነ መሆኑን ገልፀው በመልሶ ግንባታው ስራ ፣ ዘመናዊ የድምፅ ማጉያዎች፣ ምቹ ወንበሮች ፣ የሙቀት መቆጣጠሪያ፣ መፀዳጃ ቤቶች ግንባታ ፣ መኪና ማቆሚያ ፣ የውጭ እግርኛ መንገድና አረንጓዴ ስፍራዎች ፣ ዘመናዊ መድረክ ግንባታ፣ አጠቃላይ የጣሪያና ዘመናዊ የብርሃን መቆጣጠሪያ እና ሌሎችንም ዘርፈ ብዙ ስራዎች መሰራታቸውን ገልፀዋል። ሃላፊው አክለውም ልዩ የእንግዳ ማረፊያው እና በልዩ ሁኔታ የተሰራ አካል ጉዳተኞችን ያማከለ ዘመናዊ መፀዳጃ ቤትና መንገዶችን ያካተተ መሆኑን ጠቁመዋል። አዳራሹ ድሬዳዋን የኮንፈረንስ ማዕከል ለማድረግ ለሚደረገው ጥረት የራሱን ሚና ይጫወታል ብለዋል። ©️ DireTvአማርኛ | ህዳር 10 ፥2018 ዓ.ም | ድሬዳዋ

photo content
+9

photo content

‹‹የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በmobile tvet እንቅስቀሴ የተለያዩ ወጣቶችን የሙያ ባለቤት ለማድረግ እየተጋ ያለ ኮሌጅ›› የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በወረዳ 8 የሚገኙ ወጣቶችን በተለያዩ ሙያ
+6
‹‹የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በmobile tvet እንቅስቀሴ የተለያዩ ወጣቶችን የሙያ ባለቤት ለማድረግ እየተጋ ያለ ኮሌጅ›› የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በወረዳ 8 የሚገኙ ወጣቶችን በተለያዩ ሙያዎች በmobile tvet እንቅስቀሴ በአካባቢያቸው የስልጠና ጣቢያ በማቋቋም ስልጠናዎችን እየሰጠ ይገኛል፡፡ ኮሌጆች የስልጠና ቦታ ሳይገድባቸው ወጣቶችን በሚመቻቸው ቦታ በመንቀሳቀስ ስልጠናዎችን በመስጠት የስራ እድል ፈጠራውን እንዲሁም ዜጎች የሙያ ባለቤት እንዲሆኑ የማድረግ ስራዎችን ሊሰሩ ይገባል ያሉት የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ በዚህም የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ግንባር ቀደም በመሆን ስራዎችን እየሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡ የኮሌጁ ዲን አያይዘውም ኮሌጁ በወረዳ 8 የሚገኙ ወጣቶችን በኤሌክትሪክ ሙያ፣በ Finishing construction ሙያ እንዲሁም በህይወት ክህሎትና የኢንተርፕሩነርሺፕ ክህሎቶችን ወጣቶች በሚመቻቸው ቦታ ከወረዳው ጽ/ቤት ጋር በመተባበር ስልጠናዎችን እየሰጠ ይገኛል ብለዋል፡፡ በቀጣይም በሌሎች ወረዳዎች መሰል ስልጠናዎችን በተለያዩ ሙያዎች የማሰልጠኑ ተግባር የሚቀጥል ይሆናል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ህዳር 9/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ማኔጅመንት ከEDI ከመጡ ባለሙያዎች ጋር የውይይት መድረክ አካሄደ:: የውይይት መድረኩ ኮሌጁ ከEntrepreneurship Development Institute(EDI)
+1
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ማኔጅመንት ከEDI ከመጡ ባለሙያዎች ጋር የውይይት መድረክ አካሄደ:: የውይይት መድረኩ ኮሌጁ ከEntrepreneurship Development Institute(EDI) ጋር በመተባበር ለተቋሙ አመራርና ሰራተኞች ሲሰጥ በቆየው የኢንተርፕርነርሺፕ ስልጠና መሰረት በቀጣይ እንደ ተቋም ወደ ተግባር ለማስገባት ያለመ መሆኑም ተገልፇል:: በዚህም በማኔጅመት ደረጃ ሊሰሩ የሚገባቸውን ተግባራት አስመልክቶ የቀጣይ ትግበራ ዝርዝር እቅድ እዘገጃጀት ላይ ውይይቶች የተካሄዱ ሲሆን የጋራ አቅጣጫ ማስቀመጥም ተችሏል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ህዳር 08/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

ታላቅ ቅናሽ በእጀ ወርቆች የተመረተ ልዩ ልዩ ቦርሳዎችን፣ባህላዊና ዘመናዊ ልብሶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ታገኛላችሁ ምርቶቻችን 💼 በቆዳ ውጤቶች የተማሪ ቦርሳ፣የላፕቶፕ ቦርሳ፣
ታላቅ ቅናሽ በእጀ ወርቆች የተመረተ ልዩ ልዩ ቦርሳዎችን፣ባህላዊና ዘመናዊ ልብሶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ታገኛላችሁ ምርቶቻችን 💼 በቆዳ ውጤቶች የተማሪ ቦርሳ፣የላፕቶፕ ቦርሳ፣የሴቶች ቦርሳ፣ዋሌት፣ቀበቶ 👗 በአልባሳት የሠራተኞች የደንብ ልብስ፣ጋውን፣የ ሰራተኞች ቱታ፣የባህል አልባሳት፣የስፖርት ቁምጣ እና ቲሸርት፣የህትመት ቲሸርቶች፣ስካርፕ እንዲሁም ዘመናዊ አልባሳትን በትእዛዝ እናመርታለን በቡድን ለሚመጡ ደንበኞች ልዩ ቅናሽ እናደርጋልን፡፡ጥራትና ቅልጥፍና መለያች ነው ይምጡ ይዘዙን አድራሻችን ከድሬዳዋ ፖሊስ ጠቅላይ መምሪያ ወደ ኤርፖርት በሚወስደው መንገድ 150 ሜትር ላይ እንገኛለን

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት የቢሮውን ሰራተኞች በማስተባበር የኦፊስ ካይዘን ትግበራ አካሄደ። በዚህም ትግበራው ከአስተዳደሩ የካይዘን ኢንስቲትዩት በመጡ ባለሙያዎች ጋር በመሆን ከዚህ ቀደም በቢሮው የሚገኙ ዳይሬክቶሬቶችና ክፍሎች ግንዛቤ በተፈጠረላቸው መሠረት ውጤት ሊያስገኝ በሚችል መልኩ የተሰራ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ም/ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ተናግረዋል። ቢሮው ለሪፎርም ስራዎች ትኩረት ሰጥቶ ሲሰራ መቆየቱ የሚታወቅ መሆኑን አስታውሰው እነዚህም ስራዎች የሆነ ጊዜ ብቻ ተግባር አለመሆኑ በሚያሳይ መልኩ ኦፊስ ካይዘንን በሁሉም የቢሮው ዳይሬክቶሬቶችና ክፍሎች ላይ ተግባራዊ ማድረግ መቻሉን ገልጸው ዘወትር አርብ የካይዘን ቀን ተብሎ መሰየሙንና ቀጣይነቱንም የማረጋገጥ ስራ ትኩረት እንደተሰጠው በቢሮው የካይዘን ቡድን መሪ የሆኑት ወ/ሮ ሰላም ደሳለኝ አስረድተዋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 8/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት የቢሮውን ሰራተኞች በማስተባበር የኦፊስ ካይዘን ትግበራ አካሄደ። በዚህም ትግበራው ከአስተዳደሩ የካይዘን ኢንስቲትዩት በመጡ ባለሙያዎች ጋር በመሆን ከዚህ ቀደም  በቢሮው የሚገኙ ዳይሬክቶሬቶችና ክፍሎች ግንዛቤ በተፈጠረላቸው መሠረት ውጤት ሊያስገኝ በሚችል መልኩ የተሰራ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ም/ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ተናግረዋል። ቢሮው ለሪፎርም ስራዎች ትኩረት ሰጥቶ ሲሰራ መቆየቱ የሚታወቅ መሆኑን አስታውሰው እነዚህም ስራዎች የሆነ ጊዜ ብቻ ተግባር አለመሆኑ በሚያሳይ መልኩ ኦፊስ ካይዘንን በሁሉም የቢሮው ዳይሬክቶሬቶችና ክፍሎች ላይ ተግባራዊ ማድረግ መቻሉን ገልጸው ዘወትር አርብ የካይዘን ቀን ተብሎ መሰየሙንና ቀጣይነቱንም የማረጋገጥ ስራ ትኩረት እንደተሰጠው በቢሮው የካይዘን ቡድን መሪ የሆኑት ወ/ሮ ሰላም ደሳለኝ አስረድተዋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 8/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽንና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት የቢሮውን ሰራተኞች በማስተባበር የኦፊስ ካይዘን ትግበራ አካሄደ። በዚህም ትግበራው ከአስተዳደሩ የካይዘን ኢንስቲትዩት በመጡ ባለሙያዎች ጋር በመሆን ከዚህ ቀደም  በቢሮው የሚገኙ ዳይሬክቶሬቶችና ክፍሎች ግንዛቤ በተፈጠረላቸው መሠረት ውጤት ሊያስገኝ በሚችል መልኩ የተሰራ መሆኑን በቢሮው የካይዘን ቡድን መሪ ወ/ሮ ሰላም ደሳለኝ ተናግረዋል። ወ/ሮ ሰላም አክለው ቢሮው ለሪፎርም ስራዎች ትኩረት ሰጥቶ ሲሰራ መቆየቱ የሚታወቅ መሆኑን አስታውሰው እነዚህም ስራዎች የሆነ ጊዜ ብቻ ተግባር አለመሆኑ በሚያሳይ መልኩ የዚህ ትግበራ አካል የሆነው ኦፊስ ካይዘንን በሁሉም የቢሮው ዳይሬክቶሬቶችና ክፍሎች ላይ ተግባራዊ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 8/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+5

Beeksisa! Namoota barnootaa fi leenjii ogummaa leenji'uu barbaaddan hundaaf. Bulchiinsa Diree Dawaattii giddu-gala gahoomina Afrikaa baahaa ta'uun tajaajilaa kan jiru koolleejiin pooliteeknika diree dawaa bara barnoota waggaa kanaattii ogumaallee gara garraattin barsiisota muxannoo fi gahumasa gahaa qabniin issiin leenjisuuf qopha'ee issiin eggaa jira. Dammeeleen barnoottaa fi leenjii ittii kenniinuu:- 1. Railway Technology 2. Manufacturing Technology 3. Automotive Technology 4. Electrical Electronics Technology 5. Information Communication Technology 6. Construction Technology 7. Textile Garment Fashion and Leather Technology 8. Surveying and Drafting Technology 9. Wood Work Technology 10. Business and Finance 11. Hotel and Tourism 12. Theater Art 13. Bio medical and HIT

ኤስ ኤን ቪ ኢትዮጵያ ፕሮግራም ከድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ጋር በመተባበር በአስተዳደሩ ለሚገኙ ሞዴል ኢንተርፕራይዞች በኢ ኮሜርስና ዲጂታል ገበያ ላይ የአቅም ግንባታ ስልጠና ተሰጠ፤ የዛሬው መድረክ ዋና አላማ በድሬዳዋ አስተዳደር የሚገኙ ወጣቶችና ሴቶች የሚመሯቸው ሞዴል ኢንተርፕራይዞች የተሻለ የገበያ አማራጭ የሚያገኙበትን ግንዛቤ በማስጨበጥ በዚህም ዘመናዊ የሆነ በአሁኑ ወቅት በአለም ላይ የኢንተርኔት በይነ መረብን በመጠቀም የሚደረገውን ግብይት እንዲቀላቀሉ ምቹ ሁኔታ የሚፈጥርላቸው መሆኑን የፕሮግራሙ ተወካይ አቶ ታጠቅ ተስፋዬ ተናግረዋል፡፡ በአብዛኛው ፕሮጀክቱ አዲስ አበባ ላይ ሲተገበር ቆይቶ አሁን ላይ በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ዜጎች ተጠቃሚ የሚሆኑበትን ሁኔታ እያመቻቸ የሚገኝ ሲሆን በኢ ኮሜርስና በዲጂታል ገበያው ምን አይነት አማራጭ አለ? አሰራሩ ምን ይመስላል? እንዴትስ መጠቀም ይችላሉ? የሚሉትን ጉዳዮች ተደራራሽ አድርጓል፡፡ በኢ ኮሜርስና ዲጂታል ገበያው ላይ የሚንቀሳቀሱ አሸዋ፣ ሁድሁድ፣ አምራች እና ሉሲ ገበያ የተሰኙ በግል እና በመንግስት የለሙ ዲጂታል ስርዓቶች ኢንተርፕራይዞቹ ተጠቃሚ ሊሆኑ የሚችሉባቸውን አማራጮች በሰፊው ገለጻ ቀርቦ ውይይት የተካሄደባቸው ሲሆን ኢንተርፕራይዞቹ ባሉት አማራጮች እንዳመቻቸው ገብተው አገልግሎትና ምርታቸውን በማስተዋወቅና በመሸጥ ተጠቃሚ የሚሆኑበትን ምቹ ሁኔታ የፈጠረ የአቅም ግንባታ መድረክ እንደነበር በቢሮው የኢንተርፕራይዞች ልማት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሙሉጌታ ሀ/ማርያም ገልጸዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ህዳር 5/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+9

የኢትዮጵያ ብሄር፣ ብሄረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በአል መከበሩ በአገሪቱን ያለውን ህብረ ብሄራዊ አንድነት ለማጠናከር ወሳኝ መሆኑ ተገለፀ። የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ህብረ ብሄራዊ አንድነት ለአገር እድገት በሚል መሪ ቃል 20ኛውን የኢትዮጵያ ብሄር፣ ብሄረሰቦች እና ህዝቦች ቀን አክብሯል ኢትዮጵያዊ በርካታ ብሄር እና ብሄረሰቦች ለዘመናት በመቻቻል እና በአንድነት አብረው እየኖሩበት የምተገኝ አገር በመሆን ትታወቃለች። በ1987 የፌዴራል ህገመንግስት የፀደቀበትን ቀን መክንያት በማድረግ በየአመቱ የኢትዮጵያን ብሄሮች፣ብሄረሰቦች እና ህዘቦች ቀን በዓል እየተከበረ ይገኛል። ዘንድሮ በማዕከላዊ ኢትዮጵያዊ ክልል አዘጋጅነት የሚከበረውን 20 ኹነት በማስመልከት የድሬዳዋ ስራና ከህሎት ቢሮ ስራተኞች በኢትዮ ጣሊያን እና ድሬደዋ ፓሊ ቴክኒክ ኮልጅ አዳራሽ በዓሉን አከብረዋል። በዘግጀቱ ላይ የተገኙት የቢሮው ምክትል ሀላፊ ወይዘሮ ፈጡም ሙስጠፋ ሀገራችን በርካታ ብሄሮች፣ብሔረሰቦችና ህዝቦች ልዩነታቸውን የጥንካሬቸው ምንጭ በማድረግ በአንድነት የሚኖሩባት ሀገር በመሆኗ ልዩ ያደረጋታል ብለዋል። የበዓሉ መከበር በሀገሪቱ ያለውን ህብረ ብሄራዊ አንድነት ለማስቀጠል ወሳኝ ነው ያሉት ወይዘሮ ፈጡም አንዳችን የሌላውን ባህል"፣ቋንቋ እና ወግ ማወቅ ዘርፈ ብዙ ጥቅም አለው ሲሉ ገለፀዋል። የሀገር አንድነትን ለማረጋገጥ የፓለቲካ ልዩነት አያግድም ያሉት ሀላፊዋ የዘንድሮው በዓል የታላቁ ህዳሴ ግድብን ያሳካንበት እና የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ተገቢነት የሁሉም የሀገሪቱ ህዞቦች መሆኑ በተገለፀበት ወቅት መሆኑ የተለየ ያደረገዋል ሲሉ አስታውቀዋል ። በመድረኩ የኢትዮጵያ ብሄሮች እና የፌዴራል ሰርአትን የሚገልፅ ሰነድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል። ©️ DireTv

photo content
+9

የኢትዮጵያ ብሄር፣ ብሄረሰቦች እና ህዝቦች ቀን በአል መከበሩ በአገሪቱን ያለውን ህብረ ብሄራዊ አንድነት ለማጠናከር ወሳኝ መሆኑ ተገለፀ። የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ህብረ ብሄራዊ አንድነት ለአገር እድገት በሚል መሪ ቃል 20ኛውን የኢትዮጵያ ብሄር፣ ብሄረሰቦች እና ህዝቦች ቀን አክብሯል ኢትዮጵያዊ በርካታ ብሄር እና ብሄረሰቦች ለዘመናት በመቻቻል እና በአንድነት አብረው እየኖሩበት የምተገኝ አገር በመሆን ትታወቃለች። በ1987 የፌዴራል ህገመንግስት የፀደቀበትን ቀን መክንያት በማድረግ በየአመቱ የኢትዮጵያን ብሄሮች፣ብሄረሰቦች እና ህዘቦች ቀን በዓል እየተከበረ ይገኛል። ዘንድሮ በማዕከላዊ ኢትዮጵያዊ ክልል አዘጋጅነት የሚከበረውን 20 ኹነት በማስመልከት የድሬዳዋ ስራና ከህሎት ቢሮ ስራተኞች በኢትዮ ጣሊያን እና ድሬደዋ ፓሊ ቴክኒክ ኮልጅ አዳራሽ በዓሉን አከብረዋል። በዘግጀቱ ላይ የተገኙት የቢሮው ምክትል ሀላፊ ወይዘሮ ፈጡም ሙስጠፋ ሀገራችን በርካታ ብሄሮች፣ብሔረሰቦችና ህዝቦች ልዩነታቸውን የጥንካሬቸው ምንጭ በማድረግ በአንድነት የሚኖሩባት ሀገር በመሆኗ ልዩ ያደረጋታል ብለዋል። የበዓሉ መከበር በሀገሪቱ ያለውን ህብረ ብሄራዊ አንድነት ለማስቀጠል ወሳኝ ነው ያሉት ወይዘሮ ፈጡም አንዳችን የሌላውን ባህል"፣ቋንቋ እና ወግ ማወቅ ዘርፈ ብዙ ጥቅም አለው ሲሉ ገለፀዋል። የሀገር አንድነትን ለማረጋገጥ የፓለቲካ ልዩነት አያግድም ያሉት ሀላፊዋ የዘንድሮው በዓል የታላቁ ህዳሴ ግድብን ያሳካንበት እና የኢትዮጵያ የባህር በር ጥያቄ ተገቢነት የሁሉም የሀገሪቱ ህዞቦች መሆኑ በተገለፀበት ወቅት መሆኑ የተለየ ያደረገዋል ሲሉ አስታውቀዋል ። በመድረኩ የኢትዮጵያ ብሄሮች እና የፌዴራል ሰርአትን የሚገልፅ ሰነድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል። ©️ DireTv

ባለብዙ ተሰጥኦው የድሬው ወጣት ክፍል 2 https://youtube.com/watch?v=ACbHftthjpo&feature=shared