Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa
الذهاب إلى القناة على Telegram
إظهار المزيد
1 084
المشتركون
+524 ساعات
+107 أيام
+530 أيام
أرشيف المشاركات
"ሰንደቅ ዓላማችን ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ከፍታ!" በሚል መሪ ቃል የሰንደቅ ዓላማ ቀን ተከበረ፡፡
በዚህም 17ኛውን የብሔራዊ የሰንደቅ አላማ ቀን በዓል የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ እንዲሁም የኮሌጅ አመራሮችና ሰራተኞች ቃለ-መሃላ በመግባት አክብረዋል፡፡
በበዓሉ ማጠናቀቂያ በአንድነት ለሰንደቅ ዓላማ ክብር በሰጠና የብሔራዊ አንድነታችን መገለጫ እንዲሁም የሉአላዊነታችንና የኢትዮጵያ ከፍታ ምልክት መሆኑን በሚያሳይ በኢትዮጵያ ህዝብ መዝሙር የታጀበ የባንዲራ መስቀል ስነ-ሥርዓት ተካሂዷል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥቅምት 4/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
"ሰንደቅ ዓላማችን ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ከፍታ!" በሚል መሪ ቃል የሰንደቅ ዓላማ ቀን ተከበረ፡፡
በዚህም ለ17ኛውን የብሔራዊ የሰንደቅ አላማ ቀን በዓል የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ እንዲሁም የኮሌጅ አመራሮችና ሰራተኞች ቃለ-መሃላ በመግባት አክብረዋል፡፡
በበዓሉ ማጠናቀቂያ በአንድነት ለሰንደቅ ዓላማ ክብር በሰጠና የብሔራዊ አንድነታችን መገለጫ እንዲሁም የሉአላዊነታችንና የኢትዮጵያ ከፍታ ምልክት መሆኑን በሚያሳይ በኢትዮጵያ ህዝብ መዝሙር የታጀበ የባንዲራ መስቀል ስነ-ሥርዓት ተካሂዷል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥቅምት 4/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ "ብቃት" የወጣቶች ሥራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም ሁለተኛ ዙር ትግበራ አምስተኛው ዙር የአቻ ለአቻ ውይይት ተደረገ፤
ወጣቶቹ በየወሩ የአቻ ለአቻ ውይይት በማድረግ በየጊዜው ያገኙትን እውቀት የገጠማቸውን ችግሮች ለይተው የተወያዩበት መድረክ ሲሆን ይህ ለአምስተኛ ጊዜ የተዘጋጀ ውይይት የተደረገ ሲሆን የሥራ ላይ ልምምዱን ሲያጠናቅቁ በተቀጠሩበት ወይም በሚቀጠሩበት ድርጅቶች በሰለጠኑት ሞያ መሰረት ለማገልገል እራሳቸውን የሚያዘጋጁበትና እርስበርሳቸው የሚመካከሩበት ይሆናል፡፡
በተለይ ወጣቶቹ በተመሳሳይ ዕድሜ ላይ የሚገኙ እንደመሆናቸው በነጻነትና በግልጽ መወያየት የቻሉ ሲሆን ከሥራ ባህልና ባህሪ ጋር የተገናኙ ጉዳዮችና የገጠሟቸውን ገጠመኞች ያነሱበት ነበር ለቀጣይ ጉዟቸውም የተማማሩበትና ትኩረት ማድረግ የሚገባቸው ነገሮች ላይ እንዲያተኩሩ ከፕሮግራሙ አስተባባሪዎች የሚደረግላቸው ድጋፍና ክትትልም ይቀጥላል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥቅምት 2/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ "ብቃት" የወጣቶች ሥራ ላይ ልምምድ ፕሮግራም ሁለተኛ ዙር ትግበራ አምስተኛው ዙር የአቻ ለአቻ ውይይት ተደረገ፤
ወጣቶቹ በየወሩ የአቻ ለአቻ ውይይት በማድረግ በየጊዜው ያገኙትን እውቀት የገጠማቸውን ችግሮች ለይተው የተወያዩበት መድረክ ሲሆን ይህ ለአምስተኛ ጊዜ የተዘጋጀ ውይይት የተደረገ ሲሆን የሥራ ላይ ልምምዱን ሲያጠናቅቁ በተቀጠሩበት ወይም በሚቀጠሩበት ድርጅቶች በሰለጠኑት ሞያ መሰረት ለማገልገል እራሳቸውን የሚያዘጋጁበትና እርስበርሳቸው የሚመካከሩበት ይሆናል፡፡
በተለይ ወጣቶቹ በተመሳሳይ ዕድሜ ላይ የሚገኙ እንደመሆናቸው በነጻነትና በግልጽ መወያየት የቻሉ ሲሆን ከሥራ ባህልና ባህሪ ጋር የተገናኙ ጉዳዮችና የገጠሟቸውን ገጠመኞች ያነሱበት ነበር ለቀጣይ ጉዟቸውም የተማማሩበትና ትኩረት ማድረግ የሚገባቸው ነገሮች ላይ እንዲያተኩሩ ከፕሮግራሙ አስተባባሪዎች የሚደረግላቸው ድጋፍና ክትትልም ይቀጥላል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
ጥቅምት 2/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
በህገወጥ መንገድ ያለ ፈቃድ በግል ሥራና ሠራተኛ አገናኝነት ሥራ ላይ የተሰማሩ ህገወጥ ኤጀንሲዎች ላይ ከፀጥታ አካላት ጋር በመተባበር ወደ ሕጋዊነት እንዲመጡ እርምጃ እየተወሰደ እንደሚገኝ ተገለጸ፡፡
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ በህገወጥ መንገድ ያለ ፈቃድ በመንቀሳቀስ በግል ሥራና ሰራተኛ አገናኝነት ሥራ ላይ የተሰማሩ ህገወጦች በአስተዳደሩ እየተበራከቱ ስለመጡ በእነዚህ ኤጀንሲዎች በዜጎች ላይ የሚደርሰውን የመብት ጥሰት ለመከላከል አስፈላጊውን ቁጥጥርና ክትትል በማድረግ ፍቃድ ሳይኖራቸው ቢሮ ከፍተው የሚሰሩትን ወደ ሕጋዊነት እንዲመጡ ቢሮአቸው እንዲታሸግ በመደረግ ላይ ይገኛል፡፡
ቢሮው ወደዚህ እርምጃ ከመምጣቱ አስቀድሞ መንግስት በአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ አዋጅ ቁጥር 1156/2011 መሰረት በማድረግ ኤጀንሲዎች አገልግሎት የሚሰጡበትን መመሪያ ቁጥር 45/2013 አውጥቶ ሥራ ላይ እንዲውል አድርገጓል፤ ይህም መመሪያ ለተግባራዊነቱም ይረዳ ዘንድ በአስተዳደሩ የሥራና ክህሎት ቢሮ በአሠሪና ሠራተኛ ጉዳይ ዘርፍ በተለያዩ መድረኮች ግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች ተሰርቷል ፡፡
በቀጣይም ቢሮው በሀገር ውስጥ በግል ሥራና ሠራተኛ አገናኝ ኤጀንሲዎች የሚሰጠውን የሥራ ስምሪት አገልግሎት በብቃትና በተገቢው በመከታተል፣ በመቆጣጠርና በመደገፍ፣ በሥራ ላይ የሚሠማሩ ሠራተኞች መብት፣ ደህንነትና ጥቅም የሚጠበቅበትን ሁኔታ መፍጠር እና የኢንዱስትሪ ሠላምን ማስፈን ላይ ትኩረት አድርጎ የሚንቀሳቀስ ይሆናል፡፡
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መስከረም 30/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
Repost from Dire Dawa Polytechnic College
+6
የ EASTRIP ፕሮጀክት የልህቀት ማእከል የህንጻ ግንባታ የስራ አፈጻጸም ከስራና ክህሎት ሚንስቴር እና ከEASTRIP National Project Coordinator ቢሮ በተውጣጣ የSupervision team ግምገማ በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ተከናወነ፡፡
በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ስር መተግበር ላይ ያለው የEASTRIP ፕሮጀክት ከስራና ክህሎት ሚኒስቴር የተውጣጡ ኃላፊዎችና ባለሞያዎች የልህቀት ማዕከሉን የህንጻው ግንባታ አፈጻጸም ገመገሙ፡፡
ለግምገማው የመጣውን ልኡክ ቡድን የተቀበሉትና የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር እንዲሁም የኮሌጁን ሁኔታና የፕሮጀክቱን ሁኔታ ለልኡክ ቡድኑ ያብራሩት የኮሌጁ ዲን አቶ ሳሊም ኡስማን ሲሆኑ በንግግራቸውም በኮሌጁ እየተተገበረ ያለው ይህ የ EASTRIP ፕሮጀክት መሳካት በኮሌጁ ማኔጅመንት ትልቅ ድጋፍና ክትትል እየተደረገበት አሁን ላለበት ደረጃ ደርሷል ሆኖም ግን በሚፈለገው ፍጥነት ልክ ተሰርቶና በአግባቡ ተጠናቆ ለታለመለት አላማ እንዲውል የከተማ አስተዳደሩ በቅርበት እየተከታተለው እንዲሁም የተለያዩ ድጋፎችን እያደረገ ይገኛል ብለዋል፡፡
በመቀጠልም ስለ ልህቀት ማእከሉ የህንጻ ግንባታ እንዲሁም አሁን ያለበትን ሁኔታና በቀጣይ የሚሰሩ ስራዎች የአማካሪ ድርጅቱ መሐንዲስ ዮሃንስ እቁባይ አማካኝነት ቀርቧል፡፡
ከሪፖርቶና ከመስክ ጉብኝቱ በኋላ በቀረበው አፈጻጸም ላይ ልኡክ ቡድኑ የተለያዩ ገንቢ አስተያየቶችን የሰጡ ሲሆን በመጨረሻም በፕሮጀክቱ የስራ አፈጻጸም ላይ የSupervision ቡድኑ አቅጣጫ ሰጥተዋል፡፡
የኮሌጁ ኮምኒኬሽን
መስከረም 28/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ
የ2017 ዓ.ም የሥራ ፈላጊዎች ምዝገባ በሁሉም የአስተዳደራችን ወረዳ አንድ ማዕከላት እየተካሄደ ይገኛል።
በዚህም ሥራ ፈላጊ የአስተዳደራችን ነዋሪዎች አቅራቢያችሁ በሚገኙ አንድ ማዕከላት(ቀበሌ) በመሄድ እንድትመዘገቡ እናስታውቃለን።
የድሬዳዋ አስተዳደር
የሥራና ክህሎት ቢሮ
በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ሰሞኑን ይፋ ከተደረጉት ሁለት ተጨማሪ የኢትዮጵያ የሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት አካል የሆኑ አገልግሎቶች መካከል የሳይኮሜትሪክ ምዘና ለክህሎት ልማት (Psychometric for Skills Development) አንዱ ነው፡፡
....ለዘንድሮም እንዳለፉት ጊዜያት በወንድማማችነት በእህትማማችነት በፍቅር አንድነት አሸብርቀን፤ ከጨለማ_ወደ_ብርሃን ላሸጋገረን ፈጣሪ ምስጋና የሚቀርብበት የሀገራችን ድንቅ ውበትና የኦሮሞ ህዝብ ውብ ባህል ደምቆ ለሚታይበት ኢሬቻ (2017) በዓል እንኳን በሰላም አደረሳችሁ!
አቶ ሮቤል ጌታቸው
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ
....ለዘንድሮም እንዳለፉት ጊዜያት በወንድማማችነት በእህትማማችነት በፍቅር አንድነት አሸብርቀን፤ ከጨለማ_ወደ_ብርሃን ላሸጋገረን ፈጣሪ ምስጋና የሚቀርብበት የሀገራችን ድንቅ ውበትና የኦሮሞ ህዝብ ውብ ባህል ደምቆ ለሚታይበት ኢሬቻ (2017) በዓል እንኳን በሰላም አደረሳችሁ!
አቶ ሮቤል ጌታቸው
የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ
በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ የውጪ አገር ሥራ ስምሪትና የሰራተኞች ደህንነት ጥበቃ ዳይሬክቶሬት ለአሰሪና ሰራተኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አዘጋጀ።
የስልጠና መድረኩ የሥራ ቦታ ማህበራዊ ምክክር በአዋጅ ቁጥር 1156/2011 በሕብረት ድርድር ዙሪያ ሲሆን በይበልጥ ትኩረቱን በሥራ ቦታ ማህበራዊ ምክክር ያደረገና በአሰሪና ሠራተኛ መካከል የሚከሰቱ ግጭቶችን ለማስቀርትና ምርታማነት ለማሳደግ የሥራ ቦታ ማሕበራዊ ምክክር የሚጫወተውን ሚና ለማስገንዘብ ያለመ ነው።
በዚህም አዋጁን በመረዳት የአሰሪውንና ሰራተኛውን ግንዛቤ ማሳደግ ዓላማው አድርጎ ከዚህ ጎን ለጎን የኢንዱስትሪውን ሰላም በማረጋገጥ ምርታማነትን ለማሳደግ የሚኖሩ አለመግባባቶችን በመቀነስ የስራ ክርክሮችን በምክክር መፍታት የሚያስችላቸው እንደሚሆን የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ መሀመድ ኢብራሂም ተናግረዋል።
የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት
መስከረም 23/2017 ዓ.ም
ድሬዳዋ
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
