NABAWI TUBE [ነበዊ ቲዩብ]
الذهاب إلى القناة على Telegram
4 230
المشتركون
+324 ساعات
-37 أيام
-6830 أيام
أرشيف المشاركات
Repost from የቡኻሪና ሙስሊም ሐዲሶች በአማርኛ
✔️ከትንሳዔ መድረስ ምልክቶች ውስጥ!
ረሱል (📿) እንዲህ ብለዋል፦
﴿لَا تَقُومُ السَّاعَةُ حَتَّى يَكُونَ أَسْعَدَ النَّاسِ بِالدُّنْيَا لُكَعُ بْنُ لُكَعَ﴾
“ትንሳዔ (ቂያማ) አይቆምም፤ በዱንያ (በዚህች ዓለም) ከሰዎች ሁሉ ይበልጥ ደስተኛው (ተጠቃሚው) ስነ‐ምግባር የጎደለው (ወራዳ አላዋቂ የነበረ ሰው ወይም የአላዋቂ ልጅ) እስከሚሆን ድረስ።”
📚 ቲርሚዚ ዘግበውታል፡ 2209
🟧🟧🟧🟧🟧🟧
🔸 በነዚህ አድራሻዎች ይከታተሉን፦
📱 Telegeram 📱 Whatsup
📱 Facebook 📱 Instagram
📱 X 📱 Youtube 📱 Tik tok
↙️ የሀዲሱን ማብራሪያ ከኮመንት መስጫው ስር ያገኛሉ።
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
"ዛሬ ደርስ አይኖርም" ብዬ ስፅፍ ይጨንቀኛል። የሰዎች የመማር ፍላጎት ላይ ቀዝቃዛ ውሃ የምቸልስ ነው የሚመስለኝ። ግን ደግሞ አንዳንዴ ሁኔታዎች ያስገድዳሉ። በሑዘይፋ መስጂድ ከመግሪብ በኋላ የሚቀርበው የኪታቡ ተውሒድ ደርስ ላይ መገኘት እንደማልችል ለማስታወስ ፈልጌ ሲከብደኝ ነው ይህን ማለቴ። ዛሬም ነገም የኪታቡ ተውሒድ ደርስ አይኖርም። ከትልቅ ይቅርታ ጋር!
ከሩቅ የሚታደሙ ስለሚኖሩ በማሰራጨት አግዙኝ፣ ለምታውቋቸውም አድርሱልኝ። ባረከላሁ ፊኩም።
ተው ተረጋጉ አንዱን ከአንዱ አታደበላልቁ።ቢያንስ ሚዛናችንን እንወቅ ማን ምን እንደሚገባው ጠንቅቀን እንወቅ
አቡ ሁዘይፋ (ሰዒድ)
t.me/tubaliligurebae
ኡስታዝ ኢብኑ ሙነወር (አቡ ሁዘይፋ)
መኸር ሳይከፍል የሞተ ሰው
እዳ ሳይከፍል እንደሞተ ይቆጠራል!
t.me/NABAWITUBE
ኡስታዝ ኢብኑ ሙነወር (አቡ ሁዘይፋ)
ወንድ ከሴት ሴት ከወንድ
አኗኗራችን ምን መምሰል አለበት
t.me/NABAWITUBE
Repost from SadatKemal Abu Meryem
አሰላሙአለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱሁ።
ኢንሻ አላህ ዘውትር እሁድ ረፋድ ላይ በሑዘይፋ መስጂድ ከነገ ጀምሮ
ሚን ኡሱሊ አቂደቲ አህሊ ሱነቲ ወል ጀመዓ
የሸይኽ ፈውዛንን ኪታብ እንማማራለን።
አድራሻ ከየሺ ደበሌ ከፍ ብሎ፣ አዲሱ ሸገር ሲቲ።
ብዙ ያልተወራለት አስገድዶ እምነት የማስለወጥ ታሪክ በኢትዮጵያ
~
“ርኩስ፣ ዲዮቆሮስን ቅዱስ ይሉታል፡፡ የኬልቄዶን ጉባኤ በኢትዮጵያ የተነቀፈ ነው፡፡ ስለዚህ አፄ ዮሃንስ የኬልቄዶንን ጉባኤ ለማጥፋት ደብረ ሊባኖስንም ለማውደም የኢትዮጵያን መኳንንትና ሊቃውንት ሰብስበው በፍየል አምባ ጉባኤ አደረጉ፡፡ ከዚህ በኋላ አዋጅ አደረጉ፡፡ እስላምና አሮሞ / ፓጋን ክርስትና እንዲነሳ ያውም በግድ፡፡ ከአሮሞ ሁሉ አስቀድሞ እስላም የሆነ የበርቱማ ነገድ ኦሮሞ ነው፡፡ ኦሮሞ ሁሉ አስቀድሞ የተጠመቀ የወሎ ኦሮሞ ሆነ፡፡ የወሎ ባላባቶች ይማሙዎች ተጠመቁ፡፡ ይማሙ አባ ዋጠው አመዴን ንጉስ ምኒልክ አባት ሁነው አስጠመቁ፡፡ ደጃች ሃይለማርያም አሰኟቸው፡፡ ይማሙ መሐመድ አሊን አፄ ዮሃንስ አባት ሁነው አስጠምቀው ራስ ሚካኤል አሰኟቸው፡፡
ከዚህ ህዝቡን በግድ ያጠምቁትና በግድ ያቆርቡት ጀመሩ፡፡ ጉልበት ያለውና በሃይማኖቱ የቆመ ወደ መተማ ከደርቡሽ ሲሆን እኩሉ ወደ ቀቤናና ወደ ጅማ ወደ ሃረርጌም ተሰደደ፡፡ በየሄዱበት ሃገር ሁሉ ሽፍታ ብቻ ሆነ፡፡ የሃበሻ አውራጃዋ ሁሉ ጦርነት ብቻ ሆነ፡፡ በየዥረቷ ሁሉ የሰው ደም ሆነ፡፡ ንጉስ ምኒልክ ወደ አፄ ዮሃንስ ቀርበው ጃንሆይ እግዚኣብሄር ይወድልናልን፣ በግድ ቁረብ እያልን ህዝባችንን ብንፈጀው? ብለው ጠየቁ፡፡ ጃንሆይም (ዮሐንስ) ሲመልሱ የኢትዮጵያን ደም እበቀልላታለሁ፡፡ ግራኝም ኢትዮጵያን ሲያሰልማት በግድ በእሳትና በሰይፍ ነው፡፡ እኛስ የማርቆስን ሃይማኖት ካላቀናነውና ካልመሰረትነው ማን ያቀናዋል? አሉ ተብሎ በጊዜው ክብር ሁኖ ይወራ ይነገር ነበረ፡፡ ከዚህ በኋላ አፄ ዮሃንስ ወሎ ላይ ከረሙ፤ ሲያቆርቡ፣ ያልቆረበውን ሲፈጁ፡፡ ቦሩ ሜዳ ቤተ ክርስቲያን እያሰሩ፡፡ ራስ አዳልም ጎዣም ተሻገሩ፣ ቅብአት የሚባለውን ሲያጠፉ፣ እስላሙንም ሲያቆርቡ፡፡ ንጉስ ምኒልክ ወደ አንኮበር ገቡ። የይፋትን እስላም፣ የአርጎባንም፣ የአብቹንና የገላንን [ኦሮሞ] መላ ቱለማን በግድ ሲያጠምቁ፣ ሲያቆርቡ ከረሙ፡፡"
[የኢትዮጵያ ታሪክ፣ ተክለ ፃዲቅ መኩሪያ ፡ ገ. 686-688]
1. አስገድዶ ማጥመቁ ላይ በዮሐንስ ፊታውራሪነት ቢጀመርም፣ ራስ አዳል ተሰማ (በኋላ ንጉሥ ተክለ ሃይማኖት) እና ምኒልክ እንደተሳተፉበት እናያለን።
2. አስገድዶ ማጥመቁ በወሎ ብቻ ሳይሆን በጎጃምም፣ በሸዋም፣ ...፣ በአማራውም፣ በኦሮሞውም፣ በአርጎባውም ላይ እንደተፈፀመ እናያለን።
እነዚህ ነጥቦች ብዙ ሰው የሚዘነጋቸው ናቸው።
ሃይማኖታቸው በዚህ መልኩ በጉልበት እንደተስፋፋ ደጋግሞ ማስታወስ ያስፈልጋል። እውነታውን ሸምጥጠው አፋቸውን ሲከፍቱ ማጉረስ ይገባል።
* አንተ ዘንድ ስሜ "ወሃቢ" እንደሆነ አውቃለሁ። አዎ ነኝ! ሳልሸማቀቅ አስረግጬ እነግርሃለሁ። ትምክህተኝነህን፣ አስመሳይነትን አጋልጣለሁ።
=
የቴሌግራም ቻናል፦
https://t.me/IbnuMunewor
https://t.me/IbnuMunewor
ሙሉ ትምህርት➧ ማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም ምን መምሰል አለበት? ➧ እዉን ጊዜአችንን በአግባቡ ተጠቅመንበታልን? አዳምጡ🎧🎧 🎙 ኡስታዝ ኢብኑ ሙነወር https://t.me/tefekurchannel
Repost from Ibnu Munewor (ኢብኑ ሙነወር)
السلام عليكم ورحمة الله وبركاته
ተቋርጦ የነበረው ሳምንታዊ የደርስ ፕሮግራም ነገ እሁድ ይጀምራል፣ ኢንሻአላህ።
* ቦታ፦ ሑዘይፋ መስጂድ
* ጊዜ፦ እሁድ ከረፋዱ 4፡00 ጀምሮ
ኪታቦች
1. منھج السالكين
2. كن سفيا على الجادة
ሼር በማድረግ አግዙን ባረከላሁ ፊኩም።
Sadat Kemal is live!
https://youtube.com/live/D-QFAb9ZP5s?si=sv379XAbZoA1jq0P
