ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።
الذهاب إلى القناة على Telegram
📚ፍኖተ መጻሕፍት @finoteBooks1623 ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 t.me/FinoteBooks1623
إظهار المزيد3 309
المشتركون
-224 ساعات
-97 أيام
-3630 أيام
أرشيف المشاركات
✨ተወዳጆች.....
#ኢትዮጽያዊው ቄርሎስ መፍቀሬ ድንግል 'ቅዱስ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ'ያበረከቱልን
'መጽሐፈ ምስጢር' መደብራችን ይገኛል!ብቅ በሉ..!
#ብፅዕትን_የሚቀድም_ትውልድ
➮የሦስቱ ጥቅሶች ኅብር ውጤቱ ሲያምር
❝ጌታ እነኋት እናትህ - እንዲሁም እነሆ ልጅሽ አለ። ዮሐ ፲፱: ፳፮። ይኽ ቃል ልዩ ነው። ታላቅ እና ክቡር ሥርዓተ ልደት መንፈሳዊን የመሠረተ ቃል። ይኽ ዓይነት የእናትና የልጅ ዝምድና የሚገኘው እጅግ ልዩ በኾነ መንፈሳዊ ሥርዓተ ልደት ነው። እመቤታችን በዚህ መንፈሳዊ ሥርዓተ ልደት የብዙዎች እናት ናት።
❝ምክንያቱም እርሷ እመ ብዙኀን ናት። ቅዱስ ዳዊት ስለ እመቤታችን የብዙዎች እናትነት "ሰው ኹሉ እናታችን ጽዮን ይላል" ሲል ተናግሯላ። መዝ ፹፮: ፭።
❝ሰው ኹሉ ሲባል ከዚህ መንፈሳዊ ልደት ለተወለደ ብቻ መኾኑ አያጠራጥርም። ለእነርሱ እናት ናት። ቅዱስ ዮሐንስ ከእነዚህ መኻል ይመደባል። አባቷ
ቅዱስ ዳዊት በቃለ ትንቢት በበገና ዜማ የጀመረውን እመቤታችን በቃሏ የእነማን እናት እንደኾነች ነግራናለች።
❝"ከዛሬ ጀምሮ ትውልድ ኹሉ ብፅዕት ይሉኛል" በማለት። ሉቃ ፩: ፵፰። ቅዱስ ዳዊት "ሰው ኹሉ" ያለውን እመቤታችን "ትውልድ ኹሉ" ብላ ተረጎመችው። #የእመቤታችንን_እናትነት_ለማግኘት_ከዚህ_መንፈሳዊ_ሥርዓተ_ልደት_መወለድ_ግድ_ይላል።
📚@ግዮን_መጻሕፍት
📖#ሰፌልያ📖
.....#ቅዱስ ጳውሎስ የቤተ ክርስቲያን ብርሃን ፣ የክርስቶስ ምርጥ ዕቃ ፣ የመናንያን አርኣያ ፣ የሰባኪያን መምህር ፣ የአገልጋዮች ሁሉ አርማ ነው:: ከመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ ብዙ መጻሕፍትን የጻፈውን ይህንን ሐዋርያ ማወቅ ሐዲስ ኪዳንን ለማወቅ እጅግ ወሳኝ የሆነ ቅድመ ሁኔታ ነው::
#መልአከ ሰላም ቀሲስ ያሬድ ገብረ መድኅን ኆኅተ ሰማይና በመሳሰሉ መጻሕፍቶቻቸው የቤተ ክርስቲያኒቱ ዘመነኛ የአማርኛ ሥነ ጽሑፍ ታሪክ ላይ አሻራቸውን ከተዉ ቀደምት ጸሐፍት መካከል አንዱ ናቸው:: በትንታግ አንደበታቸው በሰበኳቸው ድንቅ ትምህርቶቻቸውና "ስምሽን ጠርቼ መቼ አፍራለሁ?"ን በመሳሰሉ ውብ የዝማሬ ግጥሞቻቸው ብዙ የተጠቀምንባቸው መልአከ ሰላም ያሬድ አሁን ደግሞ የቅዱስ ጳውሎስን ሕይወት የሚዳስስ እና ከመጠራቱ እስከ ዕረፍቱ ድረስ ያለውን ሐዋርያዊ ጉዞ የሚያስቃኝ በደንብ የተደከመበት ሥራ ይዘውልን ብቅ ብለዋል:: ቅዱስ ጳውሎስ ስለ ክርስቶስ ይናገር ዘንድ ምርጥ ዕቃ እንደነበረ ይህ ሰፌልያ የተሰኘ መጽሐፍም መጽሐፍ ቅዱስ ጥናታዊ ይዘት ያለው ስለ ጳውሎስ ይናገር ዘንድ የተዘጋጀ ምርጥ ዕቃ ነው::
#ዲያቆን_ሄኖክ_ኃይሌ
©መጽሐፏም እኛ ዘንድ ውስን ቅጂ አለች እንዳታልቅባችኹ......!
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?]
📱ይደውሉልን ፦0913083816
https://t.me/GhionBookStore1623
📖#ታኦዶኮስ📖
©በመምህረ መምህራን በጽሐ ዓለሙ
✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥
❝.....በጎንደር መንበረ መንግሥት መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን የዐራቱ ጉባኤያተ መጻሕፍት የትርጓሜ መምህር የሆኑት የሊቀ ሊቃውንት ዕዝራ ሐዲስ ደቀ መዝሙርና የጉባኤ ቤቱ ምክትል መምህር በሆኑት በመምህር በጽሐ ዐለሙ ታኦዶኮስ በሚል ርእስ የተዘጋጀው ይህ መጽሐፍ አማኞችን ሳይቀር ለሚያነታርከው እመቤታችን ጥንተ አብሶ አለባት የለባትም ለሚለው ጥያቄ ከቤተ ክርስቲያናችን ነባር ኣስተምህሮ አንጻር መልስ የሚሰጥ ግሩም መጽሐፍ ነው፡፡
✍️#ብርሃኑ አድማስ
[ዲያቆን፣ በሥነ ድርሳን ሁለተኛ ዲግሪ]
⩩እንደ እውነቱ የእናታችን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ነገር የማይሸነቁጠው አማኝ [ኦርቶዶክሳዊ ] አለ ለማለት ያስቸግራል ለዚህም የልብን የሚያደርስ መጽሐፍ እነሆ ያሉንን የኔታ በጽሐ አለሙን ያኑርልንንን እያልን መጽሐፏን ሁላችንም አንብበን እናተርፍበት ዘንድ መጽሐፉን #በግዮን መጻሕፍት ያገኙታል ።
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?]
📱ይደውሉልን ፦0913083816
https://t.me/GhionBookStore1623
💥✨እነኾ አዲስ_ምግብ📚
📖#ሐመረ_ነፍስ📖
...✍️በተለይም እንዲህ የሚሉት ጥያቄዎች ከብዙ ወጣቶች በተደጋጋሚ ይሰማሉ... ➮እውነት ያለዉ በኦርቶዶክስ ክርስትና ውስጥ መሆኑን እንዴት እርግጠኛ መሆን እንችላለን? ➮ሰው በተወለደበት ማኅበረሰብ ባገኘው እምነት ወደ እውነትና ዘለዓለማዊ ሕይወት መድረስ አይችልምን? ➮በሁሉም ሃይማኖት ውስጥ ያለ አስተምህሮና መዳረሻስ አንድ አይደለምን?➮ በሂንዱይዝም ውስጥ እሉ የሚባሉት ታላላቅ ሰዎች (ጉሩዎች) የሚያደርጓቸው አስገራሚ ነገሮች ከእግዚአብሔር ኃይል የተገኙ አይደሉም ማለት እንዴት ይቻላል?➮ ዮጋ የሚባለው የተመስጦ ልምምድስ ከሃይማኖት ጋር ይገናኛልን? ➮ክርስቲያን ሆኜ ዮጋን ብለማመድ ምን ችግር አለው?
#ለእነዚህና መሰል ጥያቄዎችም መልስ የዚህ መጽሐፍ ደራሲ ከግሪክ ተነሥቶ ወደ ህንድ አገር ሄዶ በዚያ ካለ የሂንዱይዝም ታላላቅ ጉሪዎች ጋር ተገናኝቶ ያየውንና በራሱ ላይ በተጨባጭ የደረሰበትን ነገር የጻፈው እንደ እርሱ ያለ ጥያቄ ያላቸው ሰዎች በእርሱ የደረሰው ችግር ይደርስባቸውና ራሳቸውን ለአደጋ ማጋለጥ ሳያስፈልጋቸው ከእርሱ የድካም ፍሬ ትምህርት መውሰድ ይችሉ ዘንድ ነው። ስስዚህ ከዚህ ዓይነቱ ተግባራዊ ሙከራና ውጤት መማር ጠቃሚም ተገቢም ነው። ወንድማችን ዲ/ን ሁነኛው ተሾመም ይህን መጽሐፍ ወደ አማርኛ ተርጉሞ ስላቀረበልን ከልብ አመሰግነዋለኹ።#እግዚአብሔር ለወንድማችን መልካም ዋጋ ይክፈልልን እኛንም አንብበን ለመጠቀም ይርዳን! በማለት በዚሕ መልኩ
#ዲ/ን_ያረጋል_አበጋዝ የጋበዙን ሲኾን #ግዮን ደግሞ በልዩ ቅናሽ እነኾ....!
📚#ግዮን_መጻሕፍት
[ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?]
📱ይደውሉልን ፦0913083816
Telegram
👇
https://t.me/GhionBookStore1623
እንኳን አደረሳችሁ!
ጣዕሟን በአንደበታችን፣
ፍቅሯን በልቡናችን ይሳልብን ያሳድርብን።
💐💐💐💐💐💐💐💐💐💐💐💐
.... ሐዋርያት ከነሐሴ አንድ ጀምሮ በጋራ ስለ እመቤታችን ከፊታቸው መሰወር ሱባዔ ገቡ፣ ካንዱ #ከዮሐንስ በስተቀር ያለችበትን የሚያውቅ አልነበረምና፡፡ ሁለት ሱባዔ እንደ ጾሙ በወርኀ ነሐሴ በ49 ዓ.ም ዕለቱ ዕለተ እሁድ ነበር የእግዚአብሔር መላክ አምጥቶ ሰጥቶአቸው እነሱም ደስ ብሎአቸው ተቀብለው ዕለቱን ቀብረዋታል የተነሳችውም እነሱ ቀብረዋት ከሄዱ በኋላ ነሐሴ በ49 ዓ.ም በዚሁ ዕለት በዕለተ እሁድ ነው አልዋለችም አላደረችም፡፡
#በእውነት ትንሳኤዋን እንዲሁም እርገቷን
እናምናለን!
✍️[ሊቀ ሊቃውንት ስምዐኮነ መልአክ]
🥀🥀🥀🥀🥀🥀🥀🥀🥀🥀🥀🥀🥀
❝ #የእግዚአብሔር መንግሥት🥀
🥀 ወደ መንግሥተ ሰማያት
ገባች❞ 🥀
[ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሳርያ]
✨✨✨✨✨✨
#እንኳን ለእናታችን ለእመቤታችን
በዓለ ትንሳኤ እንዲሁም እርገት አደረሰን።🙏🙏🙏
✨✨✨✨✨✨✨
📚ግዮን መጻሕፍት
[ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?]
https://t.me/GhionBookStore1623
#ወደ_ላይ_አያዳልጣችሁ#
/ከዲያቆን ያረጋል አበጋዝ በጣም በጥቂቱ የተቀነጨበ../
...ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቴዎፍሎስን አንድ ጨዋነት የራቀው ሰው ሰደባቸው አሉ። በኋላ ግን ጸጽቶት እግራቸው ላይ ወድቆ “ይማሩኝ፣ አጥፍቻለሁ፣ አድጦኝ ነው” ሲላቸው፣ እርሳቸውም “ታዲያ ወደ ታች ያድጣል እንጂ ወደ ላይ ያድጣል እንዴ?” አሉት ይባላል።
ወደ ላይ የሚያድጣቸውን ብዙ ሰዎች እያየን ነው። ሰሞኑን 👉ዘነበ ወላ የተባለ ግለሰብ፣ ሊነቅፈው ቀርቶ ሊረዳውና ሊያደንቀው እንኳ እጅግ የሚበዛበትን የምናኔ ሕይወት ለመንቀፍ ሲሞክር ሰምተናል (የተነገረው በሕንድኛ ወይም በታይ ቋንቋ አይደለም!)። ይህን የመሰሉ እናውቃለን ከሚሉ አላዋቂዎች ወይም ጭፍን ጥላቻ ካሳወራቸው ሰዎች በኦርቶዶክሳዊነት ላይ በተለያየ መንገድ የሚሰነዘሩ ጥቃቶች እየበዙ መምጣታቸው ጉዳዩን እንደ ቀላል ለማለፍ የማይቻል ያደርገዋል። ዛሬ ካለው የተከማቸ ኦርቶዶክስ-ጠልነት ያደረሱን ከ20ኛው መ/ዓ መጀመሪያ ጀምሮ ኦርቶዶክስ ጠል በነበሩ ግለሰቦችና ቡድኖች ይሰነዘሩ የነበሩ የጥላቻ ንግግሮችና ጽሑፎች መሆናቸውን ልብ ይሏል።
ምናኔያዊ ሕይወት፣ ከትንሣኤ በኋላ የምናገኘውን እንደ መላእክት የመሆንን ሕይወት፣ በዚህ ዐለም ገንዘብ የማድረግ ሕይወት ነው። “በትንሣኤስ እንደ እግዚአብሔር መላእክት በሰማይ ይሆናሉ? እንጂ አያገቡም አይጋቡምም” እንዳለ ጌታችን። ማቴ. 22፡30
ምናኔያዊ ሕይወት በክርስትና ውስጥ ያለውን እጅግ የገዘፈና ዘርፈ-ብዙ የሆነ ነገረ-ሃይማኖታዊና መንፈሳዊ ፋይዳ ለጊዜው ብናቆየው እንኳ፣ ክርስቲያናዊ ገዳማት ለሰው ልጆች ያበረከቷቸው ኢኮኖሚያዊ፣ እውቀታዊና ታሪካዊ ጠቀሜታዎች እጅግ በጣም ብዙ ናቸው። ጥቂቶቹን እንኳ ብናስታውስ፤ ዩኒቨርሲቲዎችና አዳሪ ት/ቤቶች በዋናነት የተቀዱት ከገዳማት ነው። የከፍተኛ ተቋማት ተማሪዎች ሲመረቁ የሚለብሱት ጋዋንና የሚደፉት ቆብ የገዳማትን ቀሚስና ሞጣህት እንዲሁም ቆብ የሚመስለው በአጋጣሚ አይደለም።
*ገዳማት ለድሆች፣ ለስደተኞች፣ ለወላጅ አልባ ልጆች፣ ለሕሙማንና ለችግረኞች መጠጊያዎች በመሆን አገለግልዋል። ለምሳሌ ያህል፣ በ4ኛው መ/ዓ የነበረው ቅዱስ ባስልዮስ የመሠረታቸው ገዳማት ሐኪም ቤቶች፣ የድሆች መመገቢያዎችና የችግረኞች መርጃ ማዕከሎችም ነበሩ። የዘመናዊ ሆስፒታል ጽንሰ-ሐሳብ መሠረቱ ክርስቲያናዊ ገዳማት ናቸው።
መናንያን በሥራ የሻከሩ እጆች ያሏቸው ብቻ ሳይሆኑ ከርኩሰትና ከነውር ንጹሕ የሆነች ነፍስ ትኖራቸው ዘንድ የሚጋደሉ እውነተኛ ጀግናዎችና ትክክለኛ ፈላስፋዎች ናቸው። ከመብላትና መጠጣት፣ ከማግባትና ከመጋባት ባሻገር ወዳለው ሰማያዊ ሕይወት የሚያመለክቱ አቅጣጫ ጠቋሚዎችና ዐዋጅ ነጋሪዎች ናቸው።
ስለሆነም ሰው ያልደረሰበትን ነገር በመሰላል ወጥቼ ልንቀፍ ማለት ተገቢ አይደለም! ሊታገሡት የሚገባም አይደለም! በዕድሜያቸውም ሆነ በእውቀታቸው ታዳጊ የነበሩት የ1950ዎቹና 60ዎቹ ትውልዶች በኦርቶዶክስ-ጠል መምህራን የተሞሉት ጥላቻ ዛሬ ያፈራውን መራራ ፍሬ እያየን፣ የእነዚያ የመንፈስ ልጆች የሆኑ በዕድሜ እንኳ ባይሆን በአእምሮ ሕፃናት የሆኑ ኦርቶዶክስ-ጠሎች ተገቢ ያልሆኑ ነገሮችን ሲናገሩና ሲጽፉ እያዩ ኦርቶዶክሳውያን ዝም ማለት አይችሉም።
ኦርቶዶክሳውያን፣ ገና ለገና ያሻንን ብንላቸው ለክፉ አይሰጡንም የሚሉ የፈሪዎችና የአጎብዳጆች የብዕር መፈተኛና የአፍ ማሟሻ መሆንን መቀበል ከማይችሉበት የመጨረሻ ደረጃ ላይ ደርሰዋል። #ስለዚህ ወደ ላይ አያዳልጣችሁ! የሚታየውን ብቻ ሳይሆን የማይታየውን መፍራትም ብልህነት ነው!
#ተወዳጆች....
➮የዕቅበተ እምነቷ ቅመም...
#መድሎተ ጽድቅ ቅጽ-፩
#እነኾ_ለ19ኛ_ጊዜ_ታተመች
''ለሰው ልጆች መዳኛ ትሆን ዘንድ ከእግዚአብሔር የተሰጠችው አንዲቷ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ክርስትና በሰዎች ግለሰባዊ አስተሳሰብና 'መሰለኝ' በሚል ግምትና መላ ምት የተገኘች ሳትሆን ከራሱ ከእግዚአብሔር የተሰጠች ናት፡፡''
[ከውስጥ ገጽ....]
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?]
📱ይደውሉልን ፦0913083816
https://t.me/GhionBookStore1623
Repost from ዲያቆን ያረጋል አበጋዝ
#ሳታቋርጡ_ጸልዩ
"ሥራ የሚሠራ ሰው ቀኑን ሙሉ በጸሎት ተጠምዶ መዋል አይችልም" አትበለኝ፤ ይችላል። በጸሎት የሚያስፈልገው ድምፅ ሳይሆን ሀሳብ ነው ፤ እጅ ሳይሆን እደ ልቦናን ማንሣት ነው፤ አፍአዊ ሳይሆን ውስጣዊ አኳኋን ነው ።ይህን ለማድረግ ደግሞ ቦታም ጊዜም አይገድብህም። በጉልበትህ ባትንበረከክ፤ ደረትህንም ባትደቃ እንኳ መንፈስህ ትጉ ከሆነ ጸሎትህ ሥልጡን ነው ።
#ቅዱስ_ዮሐንስ_አፈወርቅ
#የቤተ ክርስቲያን ታሪክ
#የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በራሷ ቋንቋ የምትመሰክረው ከራሷ ማንነት (Identity) ጋር የሚመሳሰል እምነት እያላት እንደ ሌላት በመቊጠር የገዛ ልጆቿን ከጉያዋ እየነጠቁ እየወሰዱ በእርሷ እንዲነሡባት የጥላቻን ትምህርት የሚያስተምሩ አያሌ ናቸው:: ታዲያ ይህ ተንኮል ያልገባው የእኔ አገር ልጅ እውነት የሚናገሩ እየመሰለው እንደ ጠፍ ከብት ወደ ነዱት ይሔዳል፡፡ እነርሱ ግን ዓላማቸው የእግዚአብሔር መንግሥት አይደለም፤ የላካቸውም እግዚአብሔር አይደለም፡፡
አምጣ የወለደቻቸው ልጆቿ በመጤ ሃይማኖትና ባህል ሲበከሉ ቤተ ክርስቲያናችን ዝም ብላ መመልከት አይገባትም፡፡ እነርሱ ዛሬ ብዙ የመስበኪያና የመሳቢያ ስልት እንዳላቸው የታወቀ ነው። የእኛም ቤተ ክርስቲያን “እሾህ በእሾህ ይነቀሳል” እንደሚባለው በተመሳሳይ ዘዴ ልጆቿን ከያሉበት መሰብሰብ ይገባታል፤ እነርሱም ቃሏን ሰምተው ነገ ዛሬ ሳይሉ ይመለሱ፤ የሰው ቤት የራስ አይሆንምና፡፡
[ከውስጥ ገጽ የተቆረሰ]
ስለመጽሐፉ አንድ ነገር ብቻ ምለው
'አንብቡት ታተርፉበታላችኹ' !
#ውድ_አፍቃያነ_ንባብ በሥራ ምክንያት #ከሰኞ -ቅዳሜ አንችልም እኹድ ቢመቻችልን ብላችኹ በጠየቃችኹን መሰረት #እኹድ ከቅዳሴ ስዓት 【ከ3-ሰዓት 】በኋላ የምንከፍት መኾኑን ልናሳውቃችኹ እንወዳለን !
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?]
📱ይደውሉልን ፦0913083816
https://t.me/GhionBookStore1623
📖#ጾመ ድጓ ዘቅዱስ ያሬድ📖
#የቅዱስ ያሬድ ዋና ሥራ አባቶቻችን በልዩ ትጋትና ጥንቃቄ ባደራጁበት ስልት ተተርጉሞ መቅረቡ ለብዙኃን ግልጋሎት እንዲሰጥ ስለሚያስችል የትርጉም ሥራው አስፈላጊነት አጠያያቂ አይደለም። ድንቅ ሥራ ነው። የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ሥርዐተ ማኅሌት ምን ያኽል ድንቅና ውስብስብ እንደኾነ ያሳያል። እያንዳንዱ የድጓ ዘር ከየትኛው የቅዱሳት መጻሕፍት እንደሚጣቀስ፣ ምን እንደሚጨምር፣ ለዝማሬ ስልት ሲባል ምን ቃላት መደበኛ ሥፍራቸውን እንደሚለውጡ፣ ኹነኛ ቃላትን በመደጋገም የዕለቱን ዋና ጭብጥ እንዴት እንደሚያጎሉ፣ በጥቅሉም ቅዱስ ወንጌል በጾም ሳምንታት እንደምን ባለ ክብርና ሞገስ እንደሚሰበክ ለመማር ለሚፈልጉ መጽሓፉ ራሱን ችሎ መማሪያ ይኾናል። የጥንታዊት ኢትዮጵያዊት ርትዕት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ነገረ መለኮትም ኾነ ያሬዳዊ ሥርዐተ አምልኮ የተቀረው ክርስቲያናዊ ዓለም ገና ወደፊት እየተሳበ የሚቀርብበት እንጂ የገቡት ሳይቀሩ የሚወጡበት እንዳይኾን በደገኛ ትውፊቶቻችን ላይ በትጋት የሚሠሩ የትርጉም ሥራዎች እጅግ አስፈላጊ ናቸው። ይኸው ሥራ አንዱ ነው።
መልካም ንባብ!
#ይኩኖ አምላክ መዝገቡ የኢትዮጵያ [ብሔራዊ ቤተመዛግብትና ቤተ መጻሕፍት ዋና ዳይሬክተር]
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?]
📱ይደውሉልን ፦0913083816
https://t.me/GhionBookStore1623
💧እንኳን ደስ አለን ድጋሚ ታተመልን .....
📖ወላዲተ አምላክ በነገረ ድኅነት
...✍️#በእውነት ከመጻሕፍት ተዋውቆ፡ መምህራንን ጠይቆ ምሥጢርን ከምሥጢር አራቆ፣ በብዕር አግዝፎ፡ በትዕግሥት ጽፎ ለትውልድ ማቅረብ ልዩ ዕድል /ስጦታ/ ነው:: ይህ መጽሐፍ ለአእምሮ ረቆ፣ ለአንደበት ርቆ ዕፁብ ለተነግሮ የሆነውን ነገረ ድንግል ማርያምን ከነገረ ድኅነት ጋር በማገናዘብ ከብሉያት፣ ከሐዲሳት፣ ከሊቃውንትና ከሌሎችም መጻሕፍት ለቅሞ በምሥጢር አጣጥሞ፣ በጥሩ አቀራረብ ቀምሞ እንደ ቅብዐ ዘይት ጨምቆ ይዞ ቀርባል፡፡ ስለሆነም በጥርጥር የጠወለገ ባለማወቅ የደረቀና ከጠለ ምሥጢር የራቀ ልብን ያለሰልሳል፤
መጋቤ ሐዲስ ደጉ ዓለም ካሣ
[በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩኒቨርስቲ የመጻሕፍተ ሐዲሳት ትርጓሜ መምህር]
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን !📞፦0913083816
https://t.me/GhionBookStore1623
✨ሐና አንቺን የጸነሰችባት የደስታ ቀን ምን ያኽል የተባረከች የተቀደሰች ናት፤ ሟች ኢያቄምም ለሕይወት አንቺን ያፈራባት ቀን ምን ያኽል የተባረከች የተቀደሰች ናት" (አባ ጽጌ ድንግል)
ቂምን በማያውቀው በንጹህ ልቡናሽ ምህረትን አሰጪን ለኃጣን ልጆችሽ ልጅሽ ድል አድራጊው ከጥፋት ያድነን ዘንድ ለምኚልን እድል ፈንታችንን ከአንቺ ጋር አድርጊው፡፡
#አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ
"ኦ ድንግል አኮ በፍትወተ ደነስ ዘተፀነስኪ አላ በሩካቤ ዘበሕግ እምሐና ወኢያቄም ተወለድኪ"
ድንግል ሆይ በኃጢአት ፍትወት የተፀነስሽ አይደለሽም። በሕግ በሆነ ሩካቤ፤ከሐና ከኢያቄም ተወለድሽ እንጂ።
#አባ ሕርያቆስ
#እንኳን_አደረሰን!
የድኅነታችን ምልክት፤ የሕይወታችን መገኛ፤ የሆነችው እመ አምላክ፤እናታችን ቅድስት ድንግል ማርያም፤ፍቅሯ በልባችን፤አማላጅነቷ ከሁላችን ጋር ይኑር!!!🙏
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን !📞፦0913083816
https://t.me/GhionBookStore1623
📖"ነገረ ማርያም"
[በሶርያ አባቶች እና ሌሎች ]
☞ መነሻው #የመንፈስ_ቅዱስ_ዋሽንት በኾነው በተወዳጁ #ቅዱስ_ኤፍሬም ስለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በጻፋቸው ድርሳናት ነው ፥ ከዚም መለስ ሲባል እያንዳንዱ ገጽ ሕይወት ያለው ነው!-መምህር ዲያቆን ሽመልስ መርጊያ በርካታ የትርጉም ሥራ አበርክተውልናል... ግን እመኑኝ ይኽኛው እጅግ ልዩ ነው ልዩ ስለኾነችዋ ስለ #ድንግሏ_እመቤት -ከጽንሰቷ እስከ እርገቷ ጥፍጥ ባለ መልኩ ስለጌታም አስተዳደግ በመጠኑ የሚያትት ስለሐዋርያቱና -እመቤታችን የጠበቀ ወዳጅነት በተለይ በሶርያ ቤተክርስቲያን እዴት እንደምትከበር ሲተነትን አንዳንድ የእመቤታችን ክብር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የፈጠረችው እንጂ በሌሎች ኦርቶዶክስ አብያተ-ክርስያናት የማትከበር ለሚመስላቸው መናፍቃን የማያዳግም ምላሽ የሚሰጥ የሚሉትም ኹሉ የእነርሱ ተረት እና እሳቤ እንደኾነ የሚያስረዳ..ነው። በጥቅሉ እጅግ ተወዳጅ መጽሐፍ ነው! -ስታነቡት እንደምትጋሩኝ አልጠራጠርም ...!
💧ሱባኤውን በንባብ ለማሳለጥ ደግሞ አይነተኛ ምርጫም ነው!
➮ መጽሐፉን ለማግኘት ደግሞ ምንም መጨነቅ አይጠበቅም #በግዮን_መጻሕፍት በተለመዱት የሥራ ቀናት እና እኹድ ደግሞ ከቅዳሴ ሰዓት በኋላ ተሰናድቶ ይቆያችኋል!
📚ግዮን መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ ዘመድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን !📞፦0913083816
https://t.me/GhionBookStore1623
📖📖📖
#የቅዱስ_ጳውሎስ_14ቱ_መልእክታት
..፲፱ወይትዐወቅ ምግባሩ ለሥጋ
የሥጋም ሥራው ይህ ነው፤
ዝሙት፡ዝሙት፤፳ርኲስ፡ኃጢአት ወምርዓት፡መዳራት፤አጣዕዎ፡በጣኦት ማምለክ ፤ሥራይ፡ሥራይ ማድረግ ፤ ጸልእ፡ፀብዕ፤ትዝኅርት፡ትዕቢት፤ትውዝፍት፡የምንዝር ጌጥ፤ቅንአት፡ቅንአት፤መዓት፡በቁሙቁጣ፤ኑፋቄ፡ጥርጥር፤ተቃሕዎ፡ፉክክር፤ተሓምሞ፡ምቀኝነት፤ተቃትሎ፡ነፍስመ መግደል፤ ስክረት፡ያለመጠን ጠጥቶ መስከር】
፳፪/ ወፍሬሁሰ ለመንፈስ ቅዱስ
የነፍስ የሠራ ግን
【#ተፋቅሮ፤ ፍቅር፤#ፍሥሓ፤ተስፋ ደስታ ልጅነት#ሰላም፤አንድነት #ትዕግሥት ፡በነገር በመከራ መታገሥ፤
#ምጽዋት፣ መስጠት፣#ኂሩት፤ ቸርነት #ሃይማኖት ሃይማኖት፤ #የውሃት ኃዲገ በቀል፤ #ኢዘምዎት፡ንጽሕና 】ነው፡፡
፳፫/ #አልቦ ዘይኄይስ እምዝ ሕግ፡፡
ከዚህ ሥራ የሚበልጥ የለም፤
፳፬/ ወእለሰ በኢየሱስ ክርስቶስ ስቀሉ ሥጋሆሙ ምስለ ፍትወት ወምስለ ኃጢአት፡፡
በኢየሱስ ክርስቶስ አምነው ከ፲፭ቱፈቃዳተ ሥጋ ጋር ከፍትወት ከኃጢአት ሰውነታቸውን የለዩ ሰዎች ይገብሩ ፱ኙን ፈቃዳተ ነፍስ ይሠራሉ፡፡
#አንድም በኢየሱስ ክርስቶስ አምነው ፱ኙን ፈቃደተ ነፍስ የሚሠሩ ሰዎች ከፍትወት ከኃጢአት ጋር ከ፲፭ቱ ፈቃዳተ ሥጋ ሰውነታቸውን ይለያሉ፡፡
፳፭/ ወይእዜሰ በመንፈስ ንሕየው
አሆንም በፈቃደ ነፍስ እንኑር፤
ወዘመንፈስ ንግበር፡፡
ፈቃደ ነፍሳችነን እንሥራ፡፡
፳፮/ ወኢንኩን ዝኁራነ፤
ትዕቢተኞች አንሁን፡፡
[ከገላትያ ምዕራፍ ፭ የተቀነጨበ ]
✨መሰል ብስል ተግሳጻትን ብሎም ህግጋትን ኸረ ምኑ......ያጨቀውን የምርጥ እቃው የጳውሎስን 14ቱን መልእክታት አንድምታ ብቻ ሳይኾን ማብራሪያም ጭምር የያዘው በሊቁ #መጋቤ ሐዲስ ቃለ ሕይወት በዛ የተዘጋጀልንን ይህን ግሩም ክታብ እነኾ።
📚ግዮን መጻሕፍት
📱ይደውሉልን ፦0913083816
Repost from ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል
የነሐሴ ወር ሐመር #መጽሔት #በውስጧ ምን ይዛለች ?
የነሐሴ ወር ፳፻፲፯ ዓ.ም መልእክት ዘማኅበረ ቅዱሳን "#ሁሉም ወገን ለቤተክርስቲያን ተገቢውን ክብር ይስጥ ! . ›› በሚል የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ለሀገር ሉዓላዊነት እንዲሁም ልማትና ዕድገት ከፍተኛ አስተዋጽኦ ነበራት ሲባል ለኦርቶዶክሳውያን ብቻ የሚጠቅም ማለት አይደለም፤ መላውን የሀገር ዜጋ በአንድም በሌላም መንገድ የሚጠቅም እንጂ በማለት በመልእክቱ ዐምድ ይዛለች።
.#ዐውደ ስብከት ሥር” ጾምና ፈተናዎቹ" የቅድስት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ምእመናን በልዩ መንፈሳዊ ዝግጅትና ሙቀተ መንፈስ ቅዱስ ባልተለየው መንፈሳዊነት እንዲፈጽሟቸው ከተሠሩት የመንፈሳዊ ተጋድሎ መንገዶች መካከል አንዱ ጾም እንደሆነ በስፋት በመጋቤ ምሥጢር ቀሲስ ስንታየሁ አባተ የቅዱሳት መጻሕፍትና የሊቃውንቱን አስተምህሮ መሠረት በማደረግ ትምህርት ይዛለች፡፡
አጠቃላይ ጾም ፈቃደ ሥጋን ለፈቃደ ነፍስ የምናስገዛበት፣ ጠላት ዲያብሎስን ድል የምናደርግበት፣ ከእግዚአብሔር በረከትን የምንቀበልበት መንፈሳዊ ተጋድሎ ጾም እንደሆነ ሐመር መጽሔት ታስነብባለች፡፡
#በትምህርተ ሃይማኖት ዐምድ ሥር” ነኪር ነገሩ በእንቲአኪ ሀገረ እግዚአብሔር "በሚል ርእስ ይህንን ቅዱስ ቃል ስለ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ የራቀውን አቅርቦለት የቀረበውንም አጉልቶለት በትንቢት መነጸር ከሩቅ ሆኖ አይቶ የተናገረው ልዑል እግዚአብሔር እንደ ልቤ ያለው ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳዊት የተናገረውን ግሩም ጹሑፍ በትምህርተ ሃይማኖት ይዛለች።
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
