ar
Feedback
5killo Jem'a official Channel

5killo Jem'a official Channel

الذهاب إلى القناة على Telegram

This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt 👉Jem'a Tutors 👉Trainings and Da'ewa programs 👉Weekly lunches and halaqas(circles) 👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs) 👉Weekly Q&A sessions Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0

إظهار المزيد
1 159
المشتركون
-124 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
-130 أيام
أرشيف المشاركات
የሰመራ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለውን የመብት ጥሰት በማውገዝ መግለጫ አውጥተዋል። በመግለጫቸውም የሚከተሉትን ነጥቦች አስቀምጠዋል
+1
የሰመራ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለውን የመብት ጥሰት በማውገዝ መግለጫ አውጥተዋል። በመግለጫቸውም የሚከተሉትን ነጥቦች አስቀምጠዋል። ፨​  የአካዳሚክ ነፃነትና መድልዎ፦ የትምህርት ተቋማት የሁሉንም እምነትና ማንነት በእኩልነት የሚያስተናግዱ መሆን ሲገባቸው፣ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ የሚደርሰው ስነ-ልቦናዊ ጫና እና የእምነት መገለጫ ክልከላዎች በአስቸኳይ እንዲቆሙ ፨​  የተቋማት ግዴታና ተጠያቂነት፦ የሚመለከታቸው የመንግሥት አካላትና የዩኒቨርሲቲ አመራሮች በሙስሊም ተማሪዎች ላይ የሚፈጸሙ የሃይማኖት ነፃነት ጥሰቶችን በዝምታ ከመመልከት ወጥተው፣ ተገቢውን ሕጋዊ ጥበቃ እንዲያደርጉና አድሎአዊ አሰራር በሚዘረጉ አካላት ላይ ተጠያቂነት እንዲሰፍን እናሳስባለን። ፨​  የጋራ ትግልና አጋርነት፦ በየትኛውም የሀገሪቱ ክፍል በሚገኙ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ የሚደርስ  ጉዳት የሁላችንም ጉዳት መሆኑን እንገልጻለን። ​ ጥያቄው የሕዝበ ሙስሊሙ ነው። ሐረማያ፣ መደወላቡ፣ ወራቤ፣ ጅማ፣ አርባምንጭ፣ ሰመራ፣ወልዲያ፣ ወሎ ዩኒቨርስቲ ጀመዓዎች አጋርነታቸውን አሳይተዋል። ይቀጥላል። ጥያቄያችን እስኪመለስ። ፍትሕ እስኪሰፍን። ©aaumsu @fivekjemaa

የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የቅሬታና ጥቆማ ሳጥን! "ጥያቄ አለን!" ከዲጂታል አለም ወርዶ በአካል ሲገለፅ... ከአላህ ጋር ወደ ነፃነት የምናደርገው ጉዞ እንደ ቀጠለ ነው::  "ቀጣዩ እርምጃችን ወዴት?" ያላችሁ እንደሆን "ወደ ቅሬታ ሳጥን" ብለናል። "ለምን?" ካላችሁ ደግሞ መልሳችን ፦     ሣጥኖች የተቀመጡት በዩኒቨርስቲው ውስጥ ቅሬታ ያለው ማንም አካል ቅሬታውን እንዲያቀርብና ማስተካከያ እንዲደረግ ነው:: በደላቸውን በደብዳቤ አሳየናቸው፣ በጆሮዎቻቸው አሰማናቸው፣ አሁን ደግሞ taste of their own medicine እንስጣቸው፣ ቅሬታ እንሰማበታለን ብለው ባስቀመጡት ሳጥን ቅሬታችንን እናስቀምጥ። ቅሬታችንን ሰምተው ምላሽ ከሰጡ ትልቁ ድል ይሆናል። ካልሆነም የተቀመጡት ለይስሙላ እንደሆነ ለሁሉም ይገለፃል። ብዕር(ቀለም) በዲናችን ሀቅን ለማስፈር የምንጠቀምበት መሳሪያችን ነው። አላህ በቁርአኑ ውስጥ በአል ቀለም የማለው፣ ፅሁፍ በማህበረሰብ ውስጥ ለውጥ ማግኛ የተከበረ መንገድ ስለሆነ ነው። ይህን ብዕር ተጠቅመን የፈፀሙትን ግፍ ኢስላማዊ አደብን በተላበሰ መልኩ ፅፈን እናስገባ። ግመሉን አስሮ በአላህ እንደተመካው ሁሉ፣ እኛም ፊታችን የቀረበውን ሰበብ ሁሉ አሟጠን አድርሰን ለውጥ፣ ውጤትና ድልን ከጌታችን አል ፈታህ፣ አልነሲር እንጠብቃለን። ሶሀቢዩ ኻሊድ "ሰይፉላህ" በሙታህ ጦርነት ወቅት ሰበቡን እስከ ጥግ በማድረስ ላይ እያለ ዘጠኝ ሰይፎችን ሰብሮ አንድ ስለት እስኪቀረው ድረስ ተዋግቷል። ይህ ምን ያሳየናል? ፊታችን ያሉትን መንገዶች በሙሉ  አሟጠን መጠቀም ሰበብን የማድረስ አካል መሆኑንና በአላህ መንገድ ላይ ስንታገል ያን ማድረግ እንደሚኖርብን ነው። ከአላህ በታች የፃፋችሁት እያንዳንዱ ኮመንት ጠቃሚ እና ተፅዕኖ ፈጣሪ እንደነበረው ሁሉ አሁንም የምትፅፉት አንድ ወረቀት ከአላህ ጋር የለውጥ ሰበብ ይሆናል። እርምጃዎቻችን ተደማምረው ወዳሰብንበት የነፃነት ማማ የሚያደርሱን ናቸውና። ጊዜያችን የጌታችን ነው። እርሱው ከሰጠን ትንሽ ብቻን ቀንሰን በርሱው መንገድ ላይ ለመታገል እናውለው፣ ምንዳው በኛ ላይ የተርባባ እንዲሆን። ያዙ እንግዲህ! የኻሊድ ተማሪዎች! የሱመያ ልጆች! ወረቀት ፈለግ ፈለግ፣ ብዕር ወጣ ወጣ እናድርግና በየግቢዎቻችን ወደሚገኙ ቅሬታ ሳጥኖች! ያስገባችሁትን ቅሬታ @Niqab_issueBot ላኩልን። @aaumsu

photo content

ሐዲሰል ቁድስ! ረሱል (ﷺ) እንዲህ ብለዋል፦ ﴿يَعْجَبُ ربُّكَ من راعِي غَنَمٍ، في رأسِ شَظِيَّةٍ بجبلٍ، يُؤَذِّنُ للصلاةِ، فيقولُ اللهُ عَزَّ وجَلَّ: انظروا إلى عَبْدِي هذا يُؤَذِّنُ ويُقِيمُ الصلاةَ يَخافُ مِنِّي، قد غَفَرْتُ لعَبْدِي، وأَدْخَلْتُهُ الجنةَ﴾ “ጌታህ በተራራ ጫፍ ላይ ሆኖ የሶላት ጥሪ (አዛን) በሚያሰማና ሶላት በሚሰግድ እረኛ ይገረማል። የላቀውም አላህ እንዲህ ይላል፦ ተመልከቱ ባሪያዬን የስግደት ጥሪ (አዛን) ያሰማል። ሶላቱንም ይሰግዳል። እኔንም ይፈራል። ወንጀሎቹን ይቅር ብየዋለሁ። ጀነት እንዲገባም አድርጌዋለሁ።” 📚ሶሂህ አልጃሚ፡ 8102

🔥1ቀን ቀረው🔥 በአላህ ፈቃድ ከነዚህ ውድ ወንድሞች ጋር ለመገናኘት ይሄው 1ቀን ብቻ ይቀረናር ዝግጁ ናችሁ? ✸የመፅሀፍ ሽልማቱ የሚመለከተው የተመዘገቡትን ነው ያልተመዘገባችሁ ተመዝገቡ የወንዶች
🔥1ቀን ቀረው🔥 በአላህ ፈቃድ ከነዚህ ውድ ወንድሞች ጋር ለመገናኘት ይሄው 1ቀን ብቻ ይቀረናር ዝግጁ ናችሁ? ✸የመፅሀፍ ሽልማቱ የሚመለከተው የተመዘገቡትን ነው ያልተመዘገባችሁ ተመዝገቡ የወንዶች መመዝገቢያ ∘₊✧──────✧₊∘ የእህቶች መመዝገቢያ ©Qireat6k

ጥያቄ አለን (ከኮሜንት ማህደር የተወሰደ) ! «ጥያቄ አለን!» ብለን ስንነሳ፥ ይህ ጥያቄ ለተተኪዎቻችን ጥያቄ እንዳይሆን በማሰብ ነው።... የሆነ ጊዜ ሙስሊም መሆን ኢትዮጵያ ውስጥ ጥያቄ ሆኖ ያውቃል፥ ዛሬ ላይ እኛ ራሳችንን በሙስሊም ኢትዮጵያዊነት ስንገልጽ በኩራት ነው። ይህ የቀደምቶቻችን የትግል ውጤት ነው። «ኢትዮጵያ ውስጥ የሚኖሩ ሙስሊሞች» የሚልን ስያሜ ባለመቀበል ታግለው፥ ኢትዮጵያዊ ያለመባልን ዕዳ ለኛ ባለማውረሳቸው ገና ሀገር ሲባል ልባቸው የሚመታ፣ ሰንደቋን ሲመለከቱ እንባ የሚቀድማቸው፣ ቀን ሌት ለእድገቷ የሚታትሩ፣ ከአንገታቸው ቀና ያሉ ኢትዮጵያውያን "እኛዎች" ተፈጥረናል። ዛሬም ተመሳሳይ ነው። መረገጥን፣ ባርነትን፣ ጎንበስ ማለትን ለልጆቻችን አናወርስም። ኒቃብ የቀጣዩ ትውልድ የቤት ሥራ አይሆንም። ተወደደም ተጠላ፥ ይህ ዕዳ የኛ ነው። ከጨቋኞች የተረፈውን እኛው ራሳችንም ቢሆን ከፍለነው ሂሳቡን መዝጋት የግድ ግድ ነው። ... ሌሎች የቀሩ ሥራዎቹን ከመስራት ይህ አጀንዳ የማያደናቅፈው «ነጻ» ትውልድ እንፈጥራለን። ©aaumsu @fivekjemaa

የአርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለውን የሰብዓዊ መብት ጥሰት በማውገዝ መግለጫ አውጥቷል። በመግለጫው፦ "በአዲስ አበባ ዩኒቨር
+1
የአርባምንጭ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ጀመዓ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ላይ እየደረሰ ያለውን የሰብዓዊ መብት ጥሰት በማውገዝ መግለጫ አውጥቷል። በመግለጫው፦ "በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የሚማሩ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ያለምንም መድልዎ፤ የበቀል እርምጃ፤ ፍራቻ ወይንም ጫና፤ እምነታቸውን በነፃነት እንዲከተሉ እና ሒጃብ የመልበስ መብታቸው በሙሉ እንዲከበርላቸው ፤ በዩኒቨርስቲው ውስጥ የተገኙ ማንኛውም የመድልዎ አይነቶች እና የመብት ጥሰቶች በአስቸኳይ እንዲቆሙ እና ተጠያቂዎች በሕግ መሰረት እንዲጠየቁ እንጠይቃለን።" - ብለዋል።   ጥያቄው የሁሉም ሙስሊም ተማሪ ጥያቄ ነው ስንል በምክንያት ነው። ከሀረማያ የጀመረው የአብሮነት ጉዞ ከአርባምንጭ ደርሷል። ይህ ሙስሊም ሲኮን የሚገኝ ፀጋ ነው። ጥያቄው የሕዝበ ሙስሊም ነው !! ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! ! ©aaumsu @fivekjemaa

💥 ደርስ ማስታወሻ ::::::::::::::::::::::: 🗣🗣አሰላሙአለይኩም ወራህመቱላሂ ወበረካቱሁ 👋👋👋 ✅ ኢንሻአላህ  ዛሬ ሙዳራቱ ናስ (በመልካም መኗኗር)የተሰኘው የአደብ ደርስ ይኖረናል :: 📌የቂርዐት ቦታ ፦ 4 ኪሎ የተማሪዎች መስጂድ ⏰የቂርዐት ሰዐት፦ ከመጝሪብ እስከ ዒሻ

🗣🗣اَلسَلامُ عَلَيْكُم وَرَحْمَةُ اَللهِ وَبَرَكاتُهُ‎👋👋 ✅ኢንሻአላህ ዛሬ (ሰኞ ) የሰሂህ አል-ቡኻሪ ሙኽተሰር የሆነውን التجريد الصريح لأحاديث الجامع الصحيح ደርስ ይኖረናል ።  6ኪሎ እና 5ኪሎ የምንገኝ ሙስሊም ተማሪዎች በጊዜ እንገኝ ሌሎችንም በማስከተል  ቡዙ እናተርፍለን። ⏰ሰዓት: ከመግሪብ - ኢሻ 🕌ቦታ፡ 6ኪሎ አቅሳ መስጅድ 📎ትምህርቱን በቋሚነት በዚህ የቴሌግራም ግሩፕ ላይ ስለሚለቀቅ መከታተል ትችላላችሁ። https://t.me/durus_at_aqsa ⎙በPDF መከታተል ለምትፈልጉ👇🏻 https://t.me/durus_at_aqsa/4306/4934 @fivekjemaa

🔹 Narrated Abu Umamah (رضي الله عنه): The Messenger of Allah (ﷺ) said: I guarantee a house in the surroundings of Paradise for a man who avoids quarrelling even if he were in the right, a house in the middle of Paradise for a man who avoids lying even if he were joking, and a house in the upper part of Paradise for a man who made his character good. « أَنَا زَعِيمٌ بِبَيْتٍ فِي رَبَضِ الْجَنَّةِ لِمَنْ تَرَكَ الْمِرَاءَ وَإِنْ كَانَ مُحِقًّا، وَبِبَيْتٍ فِي وَسَطِ الْجَنَّةِ لِمَنْ تَرَكَ الْكَذِبَ وَإِنْ كَانَ مَازِحًا، وَبِبَيْتٍ فِي أَعْلَى الْجَنَّةِ لِمَنْ حَسُنَ خُلُقُهُ » 📖 Reference: Sunan Abi Dawud 4800 Authenticity: Stated as Hasan

"ይግቡ የሚል ወረቀት ይሰጠን። አለዚያ መመለስ መብቴ ነው። መታዎቂያሽን አስወስደዋለሁ። እዚህ ተቋም ውስጥ ሐይማኖትም፣ ቋንቋም ብሔርም አይሰራም።"    ይህ ትላንት ምሽት በMain Campus የተፈጠረ ነው። ጥበቃዋ ይግቡ የሚል ወረቀት ስላልተሰጠን ልናስገባ አንችልም በማለት ተማሪዎችን ከመስጂድ መልስ ለክርክር ጋብዛ ነበር። በንግግሯም ይግቡ ለምን ይከለከላል የሚል ወንድምን ግቢ ውስጥ የሀይማኖት ቅስቃሳ የሚያደርግ በማለት በመዝለፍ አብሮ መቆም እንደማይችል ገልፃለች። ኦረንቴሽን ላይ ጉዳዩን እንደምታቀርብ የገለፀች ሲሆንም መታዎቂያቸውን እንደምትቀማ በመግለፅ አስፈራርታለች። ግቢው ውስጥ ሐይማኖት እንደማይሰራ በድፍረት በመግለፅም ኒቃቢስቶች ኒቃባቸውን አውልቀው ካልሆነ እንደማይገቡ አሳውቃለች።    ይህ እየሆነ ያለው የፌደራል መጅሊሱ ፕሬዚዳንት ከዶክተር ሳሙኤል ጋር ተነጋግረው ችግሮችን ለመፍታት እንደተስማሙ ከገለፁ ከአምስት ቀናት ቡሃላ ነው። ቀድመን ስንለው እንደነበረው መብቶቻችን በመመሪያ እስካልተከበሩ ድረስ ዋስትና የለንም። መብቶቻችንን የሚጥሱ አካላት ተጠያቂ እስካልሆኑ ድረስ ክብራችን ሊመለስ አይችልም። መጅሊስ ቃሉን ያክብርና ችግሩ በዘላቂነት ይፈታ ዘንድ ከተማሪዎቹ ጋር ስምምነት የደረሰባቸውን 4 ነጥቦች በቶሎ ተግባራዊ ያድርግ። መጅሊስ እንዳቋቋመ የገለፀው ኮሚቴ የሙስሊም ተማሪዎች መብት ይከበር ዘንድ በቶሎ እንቅስቃሴ ያድርግ። በየሰዓቱ መብቶቻችንን የሚጥሱ አካላት ተጠያቂ ይደረጉ። የዩኒቨርስቲው አመራሮችም መብቶቻችንን በመጣስ ኪሳራ እንጂ ትርፍ እንደማይመጣ አውቀው መመሪያውን መብቶቻችንን በሚያከብር መልኩ ያክብር። አጥፊዎችንም ተጠያቂ ያድርግ። ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! ! ©aaumsu @fivekjemaa

ማንኛውም ነገር ሲከሰት ጀርባው ኸይር እንዳለው ማሰብ ህይወትን ያቀላል ኢንሻአላህ አንዳች እኛ እማንወደው መጥፎ ነገር እንኳን ቢገጥመን አላህ ይህን ያደረገው ለመልካም ነው ብሎ መልካሙን ነገር እንዲያቀርብለት መማፀን ተገቢ ነው ... ምክንያቱም አላህ ለኛ እሚበጀውን ሁሉ ያውቃልና ምን አልባትም ለኛ መልካም የመሰለን ጉዳት ሊኖረው ይችላል ፤ እንዲሁም ጉዳት መስሎ የታየን መልካም ሊሆን ይችላል ይህችን አያ እናስታውሳት كُتِبَ عَلَيْكُمُ الْقِتَالُ وَهُوَ كُرْهٌ لَّكُمْ ۖ وَعَسَىٰ أَن تَكْرَهُوا شَيْئًا وَهُوَ خَيْرٌ لَّكُمْ ۖ وَعَسَىٰ أَن تُحِبُّوا شَيْئًا وَهُوَ شَرٌّ لَّكُمْ ۗ وَاللَّهُ يَعْلَمُ وَأَنتُمْ لَا تَعْلَمُونَ سورة البقرة ٢١٦ ©

📢 ልዩ የ3 ቀን የንፅፅር ኮርስ አስደሳች ዜና በማህበራዊ ሚዲያ በጣፋጭ የንጽጽር ዳዕዋዎቹ የምናውቀው እንዲሁም የ"ከሰማይ በታች" እና የ"ድብቅ ብዥታዎች" መጽሐፍት ፀሀፊ ኡስታዝ አቡበከር በአካል
📢 ልዩ የ3 ቀን የንፅፅር ኮርስ አስደሳች ዜና በማህበራዊ ሚዲያ በጣፋጭ የንጽጽር ዳዕዋዎቹ የምናውቀው እንዲሁም የ"ከሰማይ በታች" እና የ"ድብቅ ብዥታዎች" መጽሐፍት ፀሀፊ ኡስታዝ አቡበከር በአካል የንጽጽር ኮርስ ሊሰጠን ቀጠሮ ተይዟል🎉። በአዕምሯችን ለሚመላለሱ የንፅፅር እና የፍልስፍና ጥያቄዎች በመረጃ የተደገፈ ምላሽ የምናገኝበት፣ እምነታችንን በእውቀት የምናጠናክርበት ልዩ አጋጣሚ! ↬የኮርሱ ዋና ዋና ርዕሶች፡-Tawheed and Trinity: በአምላክ አንድነት እና በሥላሴ አስተምህሮ ዙሪያ ያሉ መሠረታዊ ልዩነቶች በመረጃ ማስቀመጥ። ❀ Christology: ስለ ነቢዩ ዒሳ (ዓለይሂ ሰላም) ማንነት ቁርዓናዊ እና መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትንታኔዎች። ❀ Atheism፦ የዘመኑን የ ኢ-አማኝነት ፍልስፍናን እና የጥርጣሬ ማዕበል የምንመክትበት ስልት። ከዚህም ባሸገር ኮርሱ ላይ ከኡስታዙ ጋር በቀጥታ የመወያየት እና የፈለግነውን ጥያቄ የመጠየቅ ዕድል ይኖረናል! 🎁ኮርሱን ተመዝግበው በተከታታይ ላጠናቀቁ ተማሪዎች በቅርብ "ከሰማይ በታች" በሚል ርዕስ ያሳተመውን ልዩ መጽሀፍ እንሸልማለን። 📅 መቼ እና የት? ቀናት፦ April 28, 29, and 30 (Tuesday, Wednesday, and Thursday) ሰዓት፦ ከዐስር ሰላት በኋላ ከ11፡00 ጀምሮ ቦታ፦ አል-አቅሳ መስጂድ (አጅሩምያ ክላስ) 📍 "እውቀት ጋሻ ነው፤ የታጠቀው አይፈራም፤አያፍርምም!" ሁላችሁም ተጋብዛችኋል! ለጓደኞቻችሁ Share በማድረግ የጥሪው አካል ይሁኑ። ይመዝገቡ የወንዶች መመዝገቢያ ∘₊✧──────✧₊∘ የእህቶች መመዝገቢያ 『ማሳሰቢያ፦ ማስታዎሻ እና እስክሪብቶ መያዝ እንዳይረሳ!』 የ6ኪሎ ጀመዓ ዳዕዋና ቂርዓት ሴክተር ለማንኛውም ጥያቄ @Valid_Qireat_bot ©AAU6kilojemea @fivekjemaa

አንድ ጠቢብ ሲናገሩ :- ነፍሱ ያሸነፈችው ፣ስሜቷን በመውደድ ለሷ ምርኮኛ ይሆናል ፤በፍላጎቷ እስር ቤት ውስጥ ተጨቁኖ ይኖራል ፤ሰንሰለቷ በእጇ ውስጥ ሆኖ ወዳሰኛት ትወስደዋለች ፤ቀልቡ መልካምን ነገር እንዳይጠቀም ታደርገዋለች ብለዋል። ነፍስያችንን በአላህ ፍራቻ እናንፅዓት!!

📢 ልዩ የ3 ቀን የንፅፅር ኮርስ አስደሳች ዜና በማህበራዊ ሚዲያ በጣፋጭ የንጽጽር ዳዕዋዎቹ የምናውቀው እንዲሁም የ"ከሰማይ በታች" እና የ"ድብቅ ብዥታዎች" መጽሐፍት ፀሀፊ ኡስታዝ አቡበከር በአካል የንጽጽር ኮርስ ሊሰጠን ቀጠሮ ተይዟል🎉። በአዕምሯችን ለሚመላለሱ የንፅፅር እና የፍልስፍና ጥያቄዎች በመረጃ የተደገፈ ምላሽ የምናገኝበት፣ እምነታችንን በእውቀት የምናጠናክርበት ልዩ አጋጣሚ! ↬የኮርሱ ዋና ዋና ርዕሶች፡- ❀ Tawheed and Trinity: በአምላክ አንድነት እና በሥላሴ አስተምህሮ ዙሪያ ያሉ መሠረታዊ ልዩነቶች በመረጃ ማስቀመጥ። ❀ Christology: ስለ ነቢዩ ዒሳ (ዓለይሂ ሰላም) ማንነት ቁርዓናዊ እና መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትንታኔዎች። ❀ Atheism፦ የዘመኑን የ ኢ-አማኝነት ፍልስፍናን እና የጥርጣሬ ማዕበል የምንመክትበት ስልት። ከዚህም ባሸገር ኮርሱ ላይ ከኡስታዙ ጋር በቀጥታ የመወያየት እና የፈለግነውን ጥያቄ የመጠየቅ ዕድል ይኖረናል! 🎁ኮርሱን ተመዝግበው በተከታታይ ላጠናቀቁ ተማሪዎች በቅርብ "ከሰማይ በታች" በሚል ርዕስ ያሳተመውን ልዩ መጽሀፍ እንሸልማለን። 📅 መቼ እና የት? ቀናት፦ April 28, 29, and 30 (Tuesday, Wednesday, and Thursday) ሰዓት፦ ከዐስር ሰላት በኋላ ከ11፡00 ጀምሮ ቦታ፦ አል-አቅሳ መስጂድ (አጅሩምያ ክላስ) 📍 "እውቀት ጋሻ ነው፤ የታጠቀው አይፈራም፤አያፍርምም!" ሁላችሁም ተጋብዛችኋል! ለጓደኞቻችሁ Share በማድረግ የጥሪው አካል ይሁኑ። ይመዝገቡ የወንዶች መመዝገቢያ ∘₊✧──────✧₊∘ የእህቶች መመዝገቢያ 『ማሳሰቢያ፦ ማስታዎሻ እና እስክሪብቶ መያዝ እንዳይረሳ!』 የ6ኪሎ ጀመዓ ዳዕዋና ቂርዓት ሴክተር ለማንኛውም ጥያቄ @Valid_Qireat_bot ©Qireat6k ©AAU6kilojemea @fivekjemaa

የጁምዓ ኹጥባ በኡስታዝ ካሚል ጣሃ "ችግር የፈጠረው ሂጃቡ ሳይሆን የእነርሱ አዕምሮ ነው። በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ልጆቻችንን ሒጃብ ከልክለው እያሰቃዩ ነው። እነዚህ የእስልምና ጥላቻ ያለባቸው የሀገር ጠላቶች ናቸው።" @aaumsu

አለምባንክ ኢማም አሕመድ መስጂድ ከተደረገ ኹጥባ፦ "ሰዎች አንድን ነገር የሆነ ሳጥን ውስጥ ስለከተቱት ተከትለህ አትገባም። የፈለግከውን ልብስ መልበስ ሰብዓዊ መብት ነው። የፈለግከውን ቋንቋ መናገር Human Right ነው። ይሄንን ቋንቋ አትናገር ተብለህ ልትከለከል አትችልም። ይሄንን አይነት ልብስ አትልበስ ተብለህ ልትገደድ አትችልም። በተለይ ደግሞ ዲሞክራሲን በሚሞግቱ ሀገሮች ማለት ነው። ትልቁ ችግር ያለው እኛ ዘንድ ነው። አንዱ ሌላውን አሳልፎ መስጠት የለበትም። በትክክለኛው መስመር ላይ ያሉ ልጆቻችንን መደገፍ አለብን። ማገዝ ባንችል እንኳ እንቅፋት መሆን የለብንም።" የዶክተርነት ማዕረግ ጭነው ሰብዓዊ መብቶቻችንን እየጣሱ ላሉት አድርሱላቸውና ሰብዓዊ መብት ምን ማለት እንደሆነ በሚንበሮች ላይ ካሉ ኸጢቦች ይስሙ። @aaumsu

ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ በምርጫ 2018 ብልፅግናን ወክለው በእጩነት የቀረቡ ቢሆንም ከእጩነት እንደተነሱ ተዘግቧል። ከዚህ በፊት እርሳቸው የሙስሊም ተማሪዎችን መብት የሚጥስን መመሪያ በማውጣት እያደረሱ
ዶክተር ሳሙኤል ክፍሌ በምርጫ 2018 ብልፅግናን ወክለው በእጩነት የቀረቡ ቢሆንም ከእጩነት እንደተነሱ ተዘግቧል። ከዚህ በፊት እርሳቸው የሙስሊም ተማሪዎችን መብት የሚጥስን መመሪያ በማውጣት እያደረሱት ያለው በደል የብልፅግና ፓርቲ መርሆዎችን እንደሚጥስ በመጥቀስ ከእጩነት ይነሱ ዘንድ በተደጋጋሚ ስንጠይቅ ነበር። ይህንን ውሳኔ ላሳለፉ አካላት ክብር አለን። አሁንም ቢሆን መንግስት የእርሳቸው አመራር ያወጣውን ጨቋኝ መመሪያ በማሻሻል እና ለፈፀሙት የመብት ጥሰት ተጠያቂ በማድረግ ፍትሕን ያሰፍን ዘንድ ጥያቄያችን ነው። ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! ! ©aaumsu @fivekjemaa

በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የጀመረው የሙስሊም ጠልነት ዘመቻ ወደ ግል ዩኒቨርስቲዎችም እየተዛመተ ነው። ሆፕ ኢንተርፕራይዝ ዩኒቨርስቲ ኮሌጅ የሚባል ተቋም እንደ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ኒቃብን የሚከለክ
በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የጀመረው የሙስሊም ጠልነት ዘመቻ ወደ ግል ዩኒቨርስቲዎችም እየተዛመተ ነው። ሆፕ ኢንተርፕራይዝ ዩኒቨርስቲ ኮሌጅ የሚባል ተቋም እንደ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ኒቃብን የሚከለክል መመሪያ አውጥቶ በቴሌግራም ቻናሉ ላይ ፖስት አድርጓል። የመመሪያው አንቀፅ 1.3 እና አንቀፅ 2.3 በተመሳሳይ ይዘት "ፊትን በሙሉ የሚሸፍን (ኒቃብ) መልበስ አይፈቀድም።" - በማለት ኒቃብን መማር ማስተማሩን ይረብሻል ከሚል መግቢያ ጋር በግልፅ ይከለክላል።   አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የጀመረው ከእርሱ የማይጠበቅን መጥፎ አርዓያነት ነው ስንል የነበረው ለዚህ ነበር። በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ እየደረሰ ያለው በደል በሌሎች ተቋማት ውስጥ የሚማሩ ተማሪዎችም በደል እንዲደርስባቸው በር ይከፍታል ስንል የነበረውም ለዚህ ነው።   አሁንም ቢሆን ይህ የሙስሊምጠልነት ወረርሽኝ ሳይዛመት በቃ ሊባል ይገባል። መጅሊስ አስቸኳይ እንቅስቃሴ አድርጎ ዘላቂ መፍትሔ ይመጣ ዘንድ ሊተጋ ይገባል። አለበለዚያ ለቅሶው የሁሉንም በር ያንኳኳል። ©aaumsu @fivekjemaa

በወሎ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች መስጂድ (አልቀለም) በጁምዓ ኹጥባ ላይ ከተላለፈ መልዕክት፦ "እንደሚታወቀው አዲስአበባ ዩኒቨርስቲ ላይ የተያዘው ነገር ትክክል ያልሆነ ተግባር ነው። ይህንን በሙሉ ልባችን እንቃወማለን። ትላንትም ተቃውመናል፣ ዛሬም እንቃወማለን፣ ነገም እንቃወማለን። አዲስአበባ ዩኒቨርስቲ የያዘው አካሄድ ትክክል አይደለም ብለን እናምናለን በግልጽ ማለት ነው። በግልፅ ኢስላማዊ ጥላቻ እንጂ ሌላ ምንም ምንም አይደለም።" እንደ አንድ አካል ለአንድ አላማ በተመሳሳይ መንፈስ ሲቆም እንዲህ ነው። ጥያቄው የሁሉም ኢትዮጵያዊ ሙስሊም ነው። ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! ! @aaumsu