ar
Feedback
5killo Jem'a official Channel

5killo Jem'a official Channel

الذهاب إلى القناة على Telegram

This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt 👉Jem'a Tutors 👉Trainings and Da'ewa programs 👉Weekly lunches and halaqas(circles) 👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs) 👉Weekly Q&A sessions Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0

إظهار المزيد
1 159
المشتركون
-124 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
-130 أيام
أرشيف المشاركات
🔹 Narrated Ka‘b bin Malik (رضي الله عنه): The Messenger of Allah (ﷺ) said: "Two hungry wolves sent in the midst of a flock of sheep are no more destructive to them than a man's greed for wealth and fame is to his Deen." « مَا ذِئْبَانِ جَائِعَانِ أُرْسِلَا فِي غَنَمٍ، بِأَفْسَدَ لَهَا مِنْ حِرْصِ الْمَرْءِ عَلَى الْمَالِ وَالشَّرَفِ لِدِينِهِ » Riyad as-Salihin 484

"ኒቃብ ለባሾችን እንዳታስገቢ ስለተባልኩኝ ልትገቢ አትችይም። አዎን ቅድም ነው ይህ የተባለው። ይህ መመሪያ ዛሬ ነው የመጣው።" - የጥበቃ ሰራተኞች    ይህ የዶክተር ሳሙኤል አመራር በኒቃቢስት ተማሪዎች ላይ እየፈፀሙት ካለው በደል አንዱ ማሳያ ነው። የሚከለክልን መመሪያ አውጥተው ሲያበቁ አይ ግቢ ውስጥ ሲንቀሳቀሱ እያየን በማለት ለማሾፍ ይሞክራሉ። ከመጅሊስ ጋር ሲያወሩ ከአሁን ቡሃላ አንከለክልም ይሉና ለጥበቆች ደግሞ አንገላቱ ብለው መመሪያ ያወርዳሉ።   ከዚህ በፊት እንደተናገርነው ኒቃብን ለመከልከል የወጣው ጨቋኝ መመሪያ እስኪሻሻል ድረስ ስለመብታችን ምንም አይነት ዋስትና የለንም። ኒቃብ መልበስ መብት ነው። አንዲት ተማሪ ኒቃብ ስለለበሰች ብቻ ከሌሎች ተማሪዎች ተለይታ በር ላይ ልትቆም ልትጠየቅ ልትንገላታ አይገባም። ይህ እስልምናን እና ሙስሊሞችን ከመናቅ ነው። ይህ ዜጎችን በሐይማኖት ለይቶ ማጥቃት ነው። በቃ ሊባል ይገባል። ዩኒቨርስቲውም ሊጠየቅ ይገባል። መጅሊስም ጉዳዩን የምር ወስዶ ዘላቂ መፍትሔ ሊያመጣ ይገባል። ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! ! @aaumsu

የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ኒቃቢስቷ መልዕክት ነው፦ "የት ሄጄ ላውራው? ማን ዘንድ አቤት ልበል? ከ2017 ጀምሮ ጮህኩኝ ግን ምላሽ አላገኘሁም። ምን ስሆን ነው ምላሽ የማገኘው? ዛሬ እኛ ካላስተካከልነው ማን ሊያስተካክለው ነው? ዛሬ ሁላችንም ለዚህ መሳካት ሰበብ ካልሆንን ነገ ሁላችንም እናለቅሳለን። እስከ መቼ?" @aaumsu

💎የውመል ጁሙአ(ተወዳጁ ቀን)💎 💎 { ۝ إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا
💎የውመል ጁሙአ(ተወዳጁ ቀን)💎 💎 { ۝ إِنَّ اللَّهَ وَمَلائِكَتَهُ يُصَلُّونَ عَلَى النَّبِيِّ يَا أَيُّهَا الَّذِينَ آمَنُوا صَلُّوا عَلَيْهِ وَسَلِّمُوا تَسْلِيمًا ۝ }    ✨✨   ﷺ,ﷺ,ﷺ,ﷺ,ﷺ,ﷺ  ✨✨ 🌸የአሏህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፡- " የውመል ጁሙአ ቀኑንም ማታውን እኔ ላይ ሰለዋት ማድረግን አብዙ፡ እኔ ላይ አንድን ሰለዋትን ያወረደ አሏህ በሱ ላይ አስር ሰለዋት ያወርድለታል........ 🌸"أكثروا الصلاة علي يوم الجمعة وليلة الجمعة فمن صلى علي صلاة صلى الله عليه عشراً" ሰለዋት ልብን ያረጋጋል፣ ሰለዋት  ጭንቀትን ይቀንሳል፣ ሰለዋት ከአላህ ዘንድ በረካ እና ምህረትን ያመጣል፣ ዛሬ ጁሙአ ነው በረሱል ﷺ ላይ ሰለዋት አውርደናል❓ اللهم صلِّ وسلم على نبينا محمد ﷺ

السلام عليكم ورحمة الله وبركاته 💫 አስደሳች ዜና✨✨ አልሃምዱሊላህ የአላህ ፍቃድ ሆኖ የጁምዓ ቀን የ "class schedule" 5:30 ድረስ እንዲሆን በሚል ከጊቢው የበላይ አካላት ጋር ውይይት በማድረግ ከትልቅ ትግል በኃላ፣  በስተመጨረሻ ሊስተካከል ተችሏል። ስለዚህ ከነገ ጀምሮ 👉ለሁሉም ደፓርትመንት ጁምዓ ቀን የጠዋት schedule 5:30 ድረስ ይሆናል። 📍የ Software coordinator ባጋጣሚ አስቸኳይ ጉዳይ ገጥሟት ስለሌለች ኢንሻአላህ እስከ ቀጣይ ሳምንት schedule ተስተካክሎ የሚላክ ይሆናል ለጊዜው ለአስተማሪዎች email ተልኳል።  👉ተማሪዎች በያሉበት ክፍል ይህንን ጉዳይ ለክላስ ተወካዮች ከበላይ አካል እንደመጣ እና ክላስ ማብቂያም እስከ 5:30 መሆኑን፣ ይህም ለሁሉም ዲፓርትመንት  እንደሆነ በማሳወቅ አስተማሪው/ዋ በschedule እንዲያስተምር ማድረግ ይጠበቅባችኃል ። 👉ይህ ሳይሆን ቢቀር መምህሩ/ሯ ከ5:30 አሳልፈው የሚቀጥሉ ከሆነ department head በመሄድ ቅሬታችሁን መናገር ፤ አልያም ለጀምዓው ማሳወቅ ትችላላችሁ፤  ለሚመለከተው አካል በማሳወቅ እንዲስተካከል ይደረጋል። ✅በዚህም ሂደት ላይ ብዙ ዉጣ ወረድ አልፏል ፤ በየዲፓርትመንቱ ተምሪዎች ተወክለው የየዲፓርትመንቱን ኃላፊ ሲያናግሯቸው ጊዜው መሄዱን እና ከዚህ በኃላ ማስተካከል የማይችሉ መሆናቸውን ፤ ከዚህም አልፎ የዲፓርትመንቱ coordinator ሆነው ሳለ  schedule እራሳቸው አውጥተው ጁምዓ ሰዓት የሚያስተምሩም ነበሩ፤ አልሃምዱሊላህ ብዙ ተግዳሮቶች ቢገጥሙም አሚሮች ሳይሰለቹ ኃላፊዎቹን በማናገር ቢኢዝኒላህ ሊስተካከል ተችሏል። 💪ይህ ለዲን ለሚደረግ ትግል ትልቅ ማሳያ ነው ፤ሳይሰለቹ ፣የሰው ምላሽ ሳይሰብራቸው፣ አላህ ላይ ሙሉ ተስፋን ሰንቆ መጓዝ ውጤቱ ያማረና ፍሬያማ መሆኑን ማሳያ ነው። ☪️በተመሳሳይ ኒቃብ ክልከላ ተከትሎ ለሚደረጉት ትግሎች ተስፋ ሰንቀን እንድንታገል ትልቅ ሞራል ሰጪ ውጤት ነው። በዩኒቨርሲቲ ግቢ ውስጥ ለሚደርሱ በደሎች ፅናት አንግበን መጓዝ  እንዳለብን ፤ በእምነታችን ላይ ለሚደርስብን መገፋት በትዕግስት ማለፍ ና በደልን በፍትህ መጋፈጥን ያስተምረናል ፤ ዛሬ የሚደርስብን ጫና ቢከብድም የአላህ ድል ቅርብ መሆኑን ያሳየናል። በዚህ ትግል ላይ ለተሳተፋችሁ አሚሮች እንዲሁም ግለሰቦች አላህ በጊዜያቹ በእያንዳንዱ ተግባሮቻቹ ላይ በረካን ይስጣችሁ፤ ለዲን ለምትከፍሉት መስዋትነት አላህ ጀነትን ማረፊያቹ ያድርግላቹ። ⛔ክላስ schedule ላይ ችግር ከገጠማችሁ በዚ bot ወይም በስልክ ማሳወቅ ትችላላችሁ👇👇 @fivekjemaa_bot +251953439949 5ኪሎ ጀምዓ አሚር መሐመድ ኢድሪስ

Sem II 2025-26AY Final UG Class Schedule (02.12.2026) (1).pdf7.92 KB

Biomed👇👇👇

New_UG_Program_Classs_Schedule_for_the_second_semeser_of_2018_EC.pdf0.71 KB

Civil 👇👇👇

Class Schedule BY Sections (1).pdf1.31 KB

Elec👇👇👇

Final_Class Schedule 2025-26_SemII_new_260423_141912.pdf5.45 KB

Chemical👇👇

Mechanical Department Sem II Schedule.pdf4.99 KB

Sem II 2025-26AY Final UG Class Schedule (02.12.2026).pdf7.92 KB

Biomed👇👇👇

Revised Class Schedule for Regular UG Program students,

Civil 👇👇👇

Please find attached the class schedule. Kindly note that all Friday morning classes are scheduled to end at 11:30 a.m.

Elec👇👇👇

5killo Jem'a official Channel - إحصائيات وتحليلات قناة تيليجرام @fivekjemaa