5killo Jem'a official Channel
الذهاب إلى القناة على Telegram
This is the official channel of AAiT jem'a where we provide info abt 👉Jem'a Tutors 👉Trainings and Da'ewa programs 👉Weekly lunches and halaqas(circles) 👉qira'ts (Qur'an and other Kitabs) 👉Weekly Q&A sessions Group: https://t.me/+cw97UaRUF1YzMTg0
إظهار المزيد1 161
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
+37 أيام
+730 أيام
أرشيف المشاركات
🔖በ4ኪሎ የቂርዐትና ደዕዋ ክፍል የተዘጋጀ አዲስ የክረምት ደርስ
📚 ሲራ (የረሱልﷺን የህይወት ታሪክ) የተመለከተ
══━━━።◈።━━━━══
📚اَلْفُصُولُ فِي سِيرَةِ الرَّسُولِ
📝የመልእክተኛው የሕይወት ታሪክ ምዕራፎች
📌የቂርዐት አይነት ፦ ኦንላይን(Online)
⏰ሰዐት፦ዘወትር ሰኞ እና ማክሰኞ ከኢሻ በኋላ(2:45)
⎙በPDF መከታተል ለምትፈልጉ👇🏻
https://t.me/Qirat4k/835
📎ትምህርቱን በቋሚነት በዚህ የቴሌግራም ግሩፕ ላይ ስለሚለቀቅ መከታተል ትችላላችሁ።
https://t.me/Qirat4k
✴️ይህንን ኪታብ ምን ለየት ያደርገዋል???
🔵 የኪታቡ አዘጋጅ ኢብኑ ከሲር ሙፈሲር ፣ ሙሀዲስ ናቸው እንደሌላው የሲራ ኪታብ ደካማና አስተማማኝ ያልሆኑ ዘገባዎችን የሌለበት ፣ በትክክለኛ ዘገባዎች ላይ የተመሠረተ ነው።
🔴 የኪታቡ አፃፃፍ ከሌላው ለየት የሚያደርገው የነቢዩን (ﷺ) የሕይወት ታሪክ ፣ባህሪቸውን ፣ ሀዲሶች እና አህካሞችን በአንድ የያዘ ኪታብ ነው።
⚫️ ረጅም ታሪኮችን ዋና ሀሳባቸውን ሳይተው በአጭርና ግልጽ በሆነ አቀራረብ ያቀረበ፤
ለጀማሪዎች እና ዕውቀትን በፍጥነት ለመገንባት ምቹ በሆነ ማጠቃለያ የተዘጋጀ ነው።
🔷በመጨረሻም በአጫጭርና በተደራጁ ምዕራፎች የተከፋፈለ በመሆኑ፤
ለማንበብ፣ ለመረዳትና መረጃን በቀላሉ ለመፈለግ እጅግ ቀላል ነው።
✳️ ኪታቡ(ደርስ) የሚጀመረው 23/10/2018 ማክሰኞ ማታ 2:45
@aau4kilomsj
"መመሪያው መማር ማስተማሩን የሚረብሹ እና ስነ-ምግባርን ያልተከተሉ ብሎ እንደሚያስቀጡ ከገለፀ ቡሃላ ከእነዚህ መካከል በአንቀፅ 1.3 እና 2.3 ላይ 'ፊትን በሙሉ የሚሸፍን (ኒቃብ) መልበስ አይፈቀድም ይላል።" - የሆፕ ኢንተርፕራይዝ ዩኒቨርስቲ ኮሌጅ ሙስሊም ተማሪዎች
የኮሌጁ ሙስሊም ተማሪዎች ይህ መመሪያ ኒቃብን ስነ-ምግባርን ያልተከተለ ብሎ ማስቀመጡ እምነትን እና ማንነትን የሚያንቋሽሽ ነው በማለት ገልፀዋል። ይህንንም ተከትሎ በኒቃቢስት ተማሪዎች ላይ የተለያዬ ክልከላ እና እንግልት እየደረሰባቸው እንደሆነ አስቀምጠዋል። መፍትሔ ይመጣ ዘንድም ለኮሌጁ፤ ለአዲስ አበባ እና ፌደራል መጅሊስ ደቤዳቤ ያስገቡ ቢሆንም እስካሁን ድረስ መፍትሔ እንዳልመጣ በመግለፅ መመሪያው የሙስሊም ተማሪዎችን መብት ባከበረ መልኩ ይስተካከል ዘንድ እና ይህንን ያደረጉ አካላት በሕግ አግባብ እንዲጠየቁ ይሰራ ዘንድ ጠይቀዋል።
@aaumsu
🔖በ4ኪሎ የቂርዐትና ደዕዋ ክፍል የተዘጋጀ አዲስ የክረምት ደርስ
📚 ሲራ (የረሱልﷺን የህይወት ታሪክ) የተመለከተ
══━━━።◈።━━━━══
📚اَلْفُصُولُ فِي سِيرَةِ الرَّسُولِ
📝የመልእክተኛው የሕይወት ታሪክ ምዕራፎች
📌የቂርዐት አይነት ፦ ኦንላይን(Online)
⏰ሰዐት፦ዘወትር ሰኞ እና ማክሰኞ ከኢሻ በኋላ(2:45)
⎙በPDF መከታተል ለምትፈልጉ👇🏻
https://t.me/Qirat4k/835
📎ትምህርቱን በቋሚነት በዚህ የቴሌግራም ግሩፕ ላይ ስለሚለቀቅ መከታተል ትችላላችሁ።
https://t.me/Qirat4k
✴️ይህንን ኪታብ ምን ለየት ያደርገዋል???
🔵 የኪታቡ አዘጋጅ ኢብኑ ከሲር ሙፈሲር ፣ ሙሀዲስ ናቸው እንደሌላው የሲራ ኪታብ ደካማና አስተማማኝ ያልሆኑ ዘገባዎችን የሌለበት ፣ በትክክለኛ ዘገባዎች ላይ የተመሠረተ ነው።
🔴 የኪታቡ አፃፃፍ ከሌላው ለየት የሚያደርገው የነቢዩን (ﷺ) የሕይወት ታሪክ ፣ባህሪቸውን ፣ ሀዲሶች እና አህካሞችን በአንድ የያዘ ኪታብ ነው።
⚫️ ረጅም ታሪኮችን ዋና ሀሳባቸውን ሳይተው በአጭርና ግልጽ በሆነ አቀራረብ ያቀረበ፤
ለጀማሪዎች እና ዕውቀትን በፍጥነት ለመገንባት ምቹ በሆነ ማጠቃለያ የተዘጋጀ ነው።
🔷በመጨረሻም በአጫጭርና በተደራጁ ምዕራፎች የተከፋፈለ በመሆኑ፤
ለማንበብ፣ ለመረዳትና መረጃን በቀላሉ ለመፈለግ እጅግ ቀላል ነው።
✳️ ኪታቡ(ደርስ) የሚጀመረው 23/10/2018 ማክሰኞ ማታ 2:45
@aau4kilomsj
ልዩነቱን ተመልከቱ
አንዱ ከቤተ- መንግስት ፊት ለፊት ሲሆን ሌላኛው ደግሞ በወራቤ ዩኒቨርስቲ ነው። ሁለቱም ለኢንትራንስ ተማሪዎችን እያስፈተኑ ሲሆን ከቤተ- መንግስት ፊት ለፊት ያለው በትምህርት ሚኒስቴሩ ብርሃኑ ነጋ ኒቃባቸውን ገፍፎ ከመሬት ሲጥል፤ በወራቤ ያለው ደግሞ ክብራቸውን ጠብቆ ስርዓቱን በተከተለ መልኩ ፈትሾ አስፈትኗቸዋል።
@aaumsu
ከአራት ቀን በፊት ነበር "ኒቃቧን እንደለበሰች ትማራለች!" - የሚል ፅሁፍ ያለበትን ሪቫን የለበሱ 12 የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተመራቂ ተማሪዎች በምርቃታቸው ቀን ከእስር ቤት እንዲውሉ የተደረገው። ዛሬ ደግሞ ኢንትራንስ የሚፈተኑ ተማሪዎች "ኒቃብ ስለለበሳችሁ ልትገቡ አትችሉም!" - ተብለው ጓደኞቻቸው እየተፈተኑ ባለበት ከውጪ እንዲቀመጡ ተደረገ።
What are we waiting for? ምን እስኪደርስ ነው የሚጠበቀው? የክብራችን ዋጋ ምን ያክል ነው? የእስልምናችን ዋጋ ምን ያክል ነው?
@aaumsu
ማስክም ኒቃብም ፊትን የሚሸፍኑ ሆነው ሳለ ኒቃባቸውን አስወልቀው በማስክ አስገቧቸው። እንዳሉት ለደህንነት ጉዳይ ቢሆን ኖሮ ማስኩም ፊትን ስለሚሸፍን መለበስ አልነበረበትም። ሆኖም ግን ምክንያታቸው ሙስሊም ጠልነት ስለሆነ ፍላጎታቸው ኒቃቡን በማስወለቅ ማዋረድ፣ መጨቆን፣ ከእምነቷ ማራቅ ነው፤ አደረጉትም።
መብቷን ማስጠበቅ የነበረበት መጅሊስም ከቦታው ተገኝቶ ማስክ ገዝቶ ሰጣት።
@aaumsu
ክብራችንን ነው የገፈፉት
መብታችንን ነው የጣሉት
ነፃነታችንን ነው በማስክ የቀየሩት
ጨርቅ ነው ብለው ከወሰዱ ስህተት ነው። ሱና ነው ብሎ ያብራራም ካለ ውርደት ነው። ይህ እንደ ሀገር፤ እንደ ኢትዮጵያዊ፤ እንደ ዜጋ መብታችን የሆነ ነገር ነው። የክብራችን መገለጫ፤ የሐይማኖት መብታችን ዋስትና ነው።
ሆኖም ግን ገፈፏቸው
ሆኖም ግን አስወለቋቸው
ሆኖም ግን ከመሬት ጣሉት
ይህ በእኔ እና በአንተ ዘመን እየሆነ ያለ ነው!
@aaumsu
+1
ኒቃባቸውን በዚህ መልኩ ሰብስበው ከመለሱ ቡሃላ ማስከ አስለብሰው ነው ያስገቧቸው። ይህ ነው ጊዜያዊ መፍትሔ? ይህ ነው መፍትሔው?! ይህ እኮ ውርደት ነው ወገን!!!
@aaumsu
መጅሊስ የሙስሊም ተማሪዎችን መብት ለማስከበር ቁርጠኝነት ካለው የሚከተሉትን ነገሮች ያድርግ፦
፨ የመብት ጥሰት እየፈፀሙ ያሉ አካላትን በሕግ አግባብ እንዲጠየቁ ያድርግ
፨ ለሙስሊም ተማሪዎች መብት እውቅና የሚሰጥ መመሪያ ይወጣ ዘንድ በቁርጠኝነት ይስራ
@aaumsu
መንግስት ከሙስሊሙ ማህበረሰብ የመብት ጥያቄ ጋር ችግር ከሌለበት እና ችግሩ የብርሃኑ ነጋ ብቻ ከሆነ የሚከተሉትን ያድርግ፦
1ኛ፦ በሙስሊም ተማሪዎች ላይ ተደጋጋሚ የመብት ጥሰት እንዲፈፀም እያደረገ ያለውን ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ከሀላፊነቱ ያንሳ፤ በሕግ አግባብም ተጠያቂ እንዲሆን ይስራ
2ኛ፦ ለሙስሊም ተማሪዎች ሕገ- መንግስታዊ መብቶች እውቅና የሚሰጥን መመሪያ ያውጣ
@aaumsu
የሙስሊም ተማሪዎች መብቶች ማስከበር ለእነሱ የሚደረግ ውለታ አይደሉም። ከአላህ ለሁላችንም በቦታችን ልክ የተሰጠ አደራ፣ ህጋዊ ኃላፊነት እና የማህበረሰብ ግዴታ ናቸው። ሙስሊም ተማሪዎችን መደገፍ በጎ አድራጎት (ሰደቃ) አይደለም፤ አማናን (አደራን) መወጣት ነው።
@aaumsu
የትምህርት ሚኒስቴርን በሚኒስትርነት እንዲመራ የተቀመጠው ሰው ገብቶ እየጎበኘ ካለበት የፈተና ማዕከል በር ላይ ነበር ኒቃቢስት ተማሪዎች አትገቡም ተብለው ለሶስት ሰዓታት ያክል ከበር የተቀመጡት። ይህንን ሰው ነው መንግስት በትምህርት ላይ ለውጥ እንዲያመጣ ያስቀመጠው? ተማሪዎቹ እንዲገቡ ቢደረግም እንዲገቡ የሆነው ኒቃባቸውን አውልቀው በማስክ ብቻ ነው። ጊዜያዊ መፍትሔ የሚባለው ይህ ነው? ኒቃብ ማውለቃቸው ለምን ተፈለገ? በማስክ መሆኑን ለምን ፈለጉት?! አሁንም ጥንቃቄ እና ዘላቂ መፍትሔ ያስፈልጋል።
@aaumsu
+1
ግንቦት 7 ወ ሰኔ 23
ከ46 ቀናት በፊት የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች በኒቃብ ምክንያት እየደረሰባቸው ስላለው መጠነሰፊ የመብት ጥሰት፣ እንግልት እና ጭቆና አቤት ለማለት ከዩኒቨርስቲው ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ፊት ለፊት ቆመው ነበር። ሆኖም የሚያወያያቸው አካል እንኳ ሳይኖር ከምሽቱ 4:30 ደረሰ። የዚያኔም ከሰላም ሚኒስቴር፤ ሀይማኖት ተቋማት ጉባዔ፤ አዲስ አበባ ፀጥታ ጽ/ቤት፤ መጅሊስ እና ከዩኒቨርስቲው የመጡ አካላት ዘላቂ መፍትሔ ለማምጣት ውይይት እንደሚካሄድ በተማሪው ፊት ቃል ገብተው ተማሪው ተበተነ።
ከ46 ቀናት ቡሃላ በሰኔ 23 / 2018 ዓ.ል የ12ተኛ ክፍል ተማሪዎች ኒቃባችሁን ካላወለቃችሁ አትፈተኑም ተብለው ከጧቱ 2:00 እስከ 5:00 ድረስ ቆሙ። ከሰላም ሚኒስቴር፤ መጅሊስ፤ አዲስ አበባ ፀጥታ ወዘተ ... የመጡ ሰዎችም እንዲገቡ አደረጓቸው።
አሁንም ግን ዘላቂ መፍትሔ አልመጣም። አሁንም ግን ተማሪዎች ላይ እንግልት የፈፀሙ አካላት ተጠያቂ አልተደረጉም። እስከ መች? ቀጣይስ የት ይሆን? የት ይሆን ችግር የሚፈጥሩት? መች ይሆን የሚያስጮሁን? መች ይሆን ጊዜያዊ መፍትሔ መጣ የሚል ዜና የሚሰራው?!
መሰል እሽክርክሪት መቀጠል የለበትም። ለጥያቄዎቻችን ዘላቂ መፍትሔ እንሻለን። መጅሊስም መንግስትም ዘላቂ መፍትሔ ይመጣ ዘንድ በቁርጠኝነት ይስሩ።
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ !!!
@aaumsu
ተማሪዎቹ እንዲገቡ ሆኗል
አሁንም ዘላቂ መፍትሔ እንሻለን። ይህንን ውንብድና የፈፀሙ የመንግስት አካላት ተጠያቂ ይሁን። መጅሊስ እና የሚመለከታቸው የመንግስት አካላት ዘላቂ መፍትሔ እንዲመጣ ይስሩ።
@aaumsu
This is not axum! ከቤተ- መንግስቱ ፊት ለፊት ከሚገኘው አብርሆት ቤተ- መፅሐፍት ነው። This is not Gunchire! ከፓርላማው ፊት ለፊት ከሚገኘው አብርሆት ነው። ራቁቷን መጥታ፤ ወይንም ደግሞ የሆነ ነገር ደብቃ ይዛ መጥታም አይደለም። የሙስሊምነቷ መገለጫ የሆነን ልብስ ስለለበሰች ነው። ሒጃብ ስለለበሰች ነው። ኒቃብ ስለለበሰች ነው። 12 አመት ሙሉ የለፋችበትን ትምህርት ሊያመክኑ ቆርጠው ተነሱ። ዩኒቨርስቲ እንዳትገባ ከበር ላይ ቆሙባት። መንግስትም መጅሊስም መፍትሔ አላመጡም። ዘላቂ መፍትሔ ይመጣ ዘንድ ስንናገር ነበር። ሙስሊም ተማሪዎች ላይ በሒጃባቸው ምክንያት እንግልት እንዳይደርስ ስንጠይቅ ነበር።
አሁንም አልረፈደም!
ተማሪዎች ሞራላቸው ተክሶ ከፈተና እንዲፈተኑ፤ አትገቡም ብለው ያገዳቸው ሰዎችም በሕግ አግባብ እንዲጠየቁ ይሰራ።
ስለእህቶቻችን ጥያቄ አለን፤ ፍትሐዊ መልስም እንሻለን!!!
@aaumsu
+2
ኢንትራንስ የሚወስዱ ኒቃቢስት ተማሪዎች አብርሆት ለመፈተን አትገቡም ተብለው ከበር ላይ ቆመዋል።
@aaumsu
ከትልቅ ይቅርታ ጋር፦ ከ3:00 ጀምሮ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት የቲክቶክ ገፅ ሊካሄድ የነበረው የውይይት መድረክ ባልተጠበቁ የቴክኒክ ችግሮች ምክንያት እስካሁን ሊካሄድ አልቻለም። ሰዓቱም ከመሄዱ ጋር እንግዶቻችንን እና አክብራችሁን የመጣችሁትን ታዳሚዎቻችንን ከዚህ በላይ ማቆየቱ አግባብነት ስለሌለው የዛሬው ፕሮግራም እንዲሰረዝ ሆኗል። በአላህ ስም ይቅርታ እንጠይቃለን። በአላህ ፈቃድ በተሻሉ ፕሮግራሞች ደጋግመን እንገናኛለን።
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ !!!
@aaumsu
ታሪካዊው የቲክቶክ መድረክ በመጀመር ላይ ነው። ጆይን በሉ።
https://www.tiktok.com/@aaumsu
ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
@aaumsu
